1 296
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
1 296
Repost from Tнє Cσmpαrαtσr¹
በአላህ ፍቃድ 28 ወይም 29 የረመዳን ቀናት ቀርተውናል በነዚህ ቀናት ውስጥ ለዲናችን ትኩረት በመስጠት ቁርአንን እናኸትማለን ኢንሻአላህ፤በነዚህ በተቀሩት ቀናት በኢትዮጵያ ማታ ከ3:00 በኋላ እንገናኛለን❤
...
ወሰላሙ አለይኩም ወራህመቱላሂ ወበረካቱ
T.me/TheComparator
1 296
እንኳን ለተከበረው የረመዳን ወር ሁላችንም አደረሰን፣ አላህ በትክክል ከሚጠቀሙበት ያድርገን።🌙
▣ አላህ የፍልስጤም ወንድሞቻችንን ከካሕዲያን ይጠብቃቸው፣ በምንችለው ከጎናቸው እንሁን።
® Sαlαh Responds 🖋
1 296
Repost from Tнє Cσmpαrαtσr¹
¦አሰላሙ አለይኩም ወራህመቱላሂ ወበረካቱሁ¦
⨳አህመድ ሙሀመድ(አነፃፃሪው)ነኝ በቀድሞው ወደ 670+ ተከታይ ያፈራው ቻናሌ የተከፈተበት አካውንት ለመዘጋት ስለተቃረበ በዚህ መጥቻለሁ፤እናንተም ይህን ፅሁፍ በምትችሉት መንገድ በማጋራት ሊንኩንም በማስፈንጠር ለብዙ ክርስቲያን ወገኖች የብርሀን አመላካች እንድንሆን በአላህ ስም እጠይቃለሁ።
T.me/TheComparator
1 296
Repost from Tнє Cσmpαrαtσr¹
ጀግናው ኡስታዛችን ሙሐመድ ኸድር!
-----------------------------------------------------
t.me/TheComparator
©አነፃፃሪው|Comparator
1 296
Repost from Tнє Cσmpαrαtσr¹
አብዛኞቻችን ሰዎችን በንፅፅራዊ እይታ ውይይት ለማድረግ በምንቀርብ ጊዜ ከያዝናቸው የተገደቡ ጥቅሶች በስተቀር ለሙግታችን አንጠቀምም የዚህም እንደ ችግር ሆኖ ሊነሳ የሚችለው በሁለቱ መፅሐፍት ላይ የተገለጸውን ሀሳብ ጠንቅቆ ተረድቶ በሚዛናዊነት ለማየት አለመቻል ነው!
...
ለዚህም ሲባል ሙስሊሞች መፅሐፍ ቅዱስን ከዘፍጥረት ጀምሮ ያለውን ጥቅስ በጥቅስ ያለውን ሀሳብ በሰፊ እይታ እና በሚዛናዊነት ለመመልከት ሲኖርባቸው፤ከዚሁ በተቃራኒው ክርሰቲያን ወገኖቻችን ቁርአንን ከአል-ፋቲሃ ጀምሮ መልዕክቱን ጠብቀው መረዳት አለባቸው!
...
መፅሐፍ ቅዱስን ለሚያነቡ:
- የአውደ ምንባብ(Contextual Passage)
- መሰረታዊ ቋንቋ (Strong's Concordance)
- የማብራሪያ(Commentary)
- የተለያዩ የመፅሐፍ ቅዱስ እትሞች(Version)
- የጥቅሱ ታሪካዊ ዳራ(Historical Background)
...
ቁርአንን ለሚያነቡ:
- የአውደ ምንባብ(Contextual Passage)
- የመሰረታዊ ቋንቋ(Classical Arabic)
- ሰዋስዋዊ አወቃቀር(Grammatical Structure)
- የማብራሪያ(Tafsir)
- የጥቅሱ ታሪካዊ ዳራ(Historical Background)
...
እነዚህን በመጠቀም ጥቅስን ቆርጦ ትከሻ የመለካካት ሙግት ከመጠቀም መቆጠብን በማሳሰብ ነው፤ይህንን ለማድረግ ግሩፕ የሚከፈት ሲሆን በ3 ቀን አንድ ጊዜ ጥያቄ እና መልስ ይኖረናል ሀሳቡ ከተመቻችሁ Like ማድረግዎን አይርሱ።
T.me/TheComparator
— ከወንድም አህመድ(አነፃፃሪው)
1 296
Repost from Tнє Cσmpαrαtσr¹
ገና
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ፥ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው❲بِسْمِ اللَّهِ الرَّحْمَٰنِ الرَّحِيم❳
ذَٰلِكَ قَوْلُهُم بِأَفْوَٰهِهِمْ ۖ يُضَٰهِـُٔونَ قَوْلَ ٱلَّذِينَ كَفَرُوا۟ مِن قَبْلُ
“ይህ በአፎቻቸው (የሚናገሩት) ቃላቸው ነው፡፡ የእነዚያን ከነሱ በፊት የካዱትን ሰዎች ቃል ያመሳስላሉ፡፡”❲Qūrān 9:30❳
...
የገና አከባበር እና የሚከበርበት ቀን በተለያዩ ቡድኖች እና ምሁራን መካከል ለብዙ አመታት ክርክር እና ውይይት ተደርጎበታል የኢየሱስ ትክክለኛ የልደት ቀን በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ አልተጠቀሰም፤እናም የታሪክ መዛግብት በዚህ ጉዳይ ላይ ትክክለኛ እሣቤ ላይ አልተስተዋሉም እስቲ አላህ ባሳወቀን ነገሩን እንቃኝ።
...
ገና"γέννα" የሚለው የግሪክ ቃል ገን"γεν-" ከሚለው ሥርወ ቃል የተገኘ ሲሆን ትርጉሙም"ወደ መኖር መምጣት" ማለት ነው፤ኢየሱስ ወደዚህ ምድር የመጣበትም ቀን ከዚሁ ተጠቃሎ ገና ብለው ይጠሩታል በእንግሊዘኛው"Christmas" የሚለው ቃል"Cristes mæsse" ከሚል የጥንት እንግሊዝኛ ቋንቋ የተወሰደ ሲሆን"የክርስቶስ ቅዳሴ" ማለት ነው ይህም የክርስቶስን የልደት ቀን ለማወደስ የሚጠቀሙበትን ቀን በዚህ ስም ሰይመውታል።
...
1.የኢየሱስ የትውልድ ወር:
“በይሁዳ ንጉሥ በሄሮድስ ዘመን *ከአብያ* ክፍል የሆነ *ዘካርያስ* የሚባል አንድ ካህን ነበረ፤ ሚስቱም ከአሮን ልጆች ነበረች፥ ስምዋም ኤልሳቤጥ ነበረ።”
— ሉቃስ 1፥5
...
በአይሁድ ያሉ ካህናት ዓመቱን ሙሉ በቤተመቅደስ ውስጥ በሚያገለግሉ በ24 ምድብ የተደራጁ ሲሆን ዘካርያስ በ10ኛው ሳምንት የዑደታቸው ጊዜ የሚያገለግሉት አብያ የሚባል ከሀያ አራቱ ስምንተኛው ምድብ ላይ ነበር፦
“ሰባተኛው ለአቆስ፥ ስምንተኛው *ለአብያ*፥”
— 1 ዜና 24፥10
“በይሁዳ ንጉሥ በሄሮድስ ዘመን *ከአብያ* ክፍል የሆነ *ዘካርያስ* የሚባል አንድ ካህን ነበረ፤...”
— ሉቃስ 1፥5
...
“እንደ *ካህናት ሥርዓት* ወደ ጌታ ቤተ መቅደስ ገብቶ ለማጠን ዕጣ ደረሰበት።”
— ሉቃስ 1፥9
“የጌታም መልአክ በዕጣኑ መሠዊያ ቀኝ ቆሞ ታየው።”
— ሉቃስ 1፥11
“መልአኩም እንዲህ አለው፦ ዘካርያስ ሆይ፥ ጸሎትህ ተሰምቶልሃልና አትፍራ ሚስትህ *ኤልሳቤጥም* ወንድ ልጅ ትወልድልሃለች፥ ስሙንም *ዮሐንስ* ትለዋለህ።”
— ሉቃስ 1፥13
ዘካርያስ ባለው ምድብ መሰረት ከቤተ መቅደሱ ለማገልገል በገባ ጊዜ መልአኩን እንዳገኘው አንባቢ ልብ ይሏል በየአመቱ በ1 ወር ሁለቴ ተከፍሎ 24 አገልጋይ በአመት ካገለገለ ይህም "አብያ" ስምንተኛው ምድብ ከሆነ አራተኛው የአይሁድ ወር ታሙዝ "תַּמּוּז" ላይ እንደነበር ያስገነዝበናል የአይሁድ የመጀመሪያው ወር ኒሳን "ניסן" በጎርጎሮሳዊያኑ አቆጣጠር "ሚያዝያ" ከዋለች አራተኛው ወር ታሙዝ "תַּמּוּז" "ሃምሌ" ይውላል ማለት ነው።
በዚህ መልክ እና ልክ ከሃምሌ የዘካርያስ ብስራት ከስድስት ወር በኋላ ማርያም ጋር መልአኩ ሲመጣ "ጥር" ላይ መሆኑን እናስተውላለን፦
“በስድስተኛውም ወር መልአኩ ገብርኤል ናዝሬት ወደምትባል ወደ ገሊላ ከተማ፥”
— ሉቃስ 1፥26
ከጥር ጀምሮ ባለው የ9 ወር የእርግዝና ቆጠራ ስሌት የኢየሱስ መወለድ በጥቅምት መሆኑን እንገነዘባለን ይህም የሀገራችን ኢትዮጵያ የታህሳስ 29/28፣የምዕራባውያን December 25፣የምስራቃውያን ኦርቶዶክስ ጥር 6 አከባበር በእንቶ ፈንቶ የተሞላ መሆኑን ያስይዘናል!
...
2.የኢየሱስ የትውልድ አመት:
የማቴዎስ አዘጋገብ እና ውዝግብ:
“ኢየሱስም በይሁዳ ቤተ ልሔም በንጉሡ በሄሮድስ ዘመን በተወለደ ጊዜ፥...”
— ማቴዎስ 2፥1
...
ማቴዎስ ምንም እንኳ የተወሰነ ቀን ባይናገርም ይህ ክፍል ግን ኢየሱስ የተወለደው በታላቁ ሄሮድስ የግዛት ዘመን እንደሆነ ያመለክታል ከታሪክ አኳያ ታላቁ ሄሮድስ ከ72-4BC የኖረ ሮማዊ የይሁዳ ገዢ እንደነበር ይናገራል።¹ከ37 እስከ 4BC እንደገዛም ይታመናል።በዚህ መረጃ ላይ በመመስረት በአጠቃላይ ኢየሱስ የተወለደው በ4-6BC አካባቢ እንደሆነ ይታመን የነበረው ታላቁ ሄሮድስ ከመሞቱ ቀደም ብሎ እንደተወለደ በማስረዳት ነው ሆኖም ክርስቶስ ከክርስቶስ ልደት በፊት በ4BC ተወለደ እያሉን ነው!
...
የሉቃስ አዘጋገብ እና ውዝግብ:
የሉቃስ ድርሰት የኢየሱስን ውልደት ዓለሙ ሁሉ እንዲጻፍ ከአውግስጦስ ቄሣር ትእዛዝ በወጣበት ጊዜ ጋር በማያያዝ የማርያምን እና የዮሴፍን ወደ ቤተልሔም መጓዝ ለማጣመር ሞክሯል፦
“በዚያም ወራት ዓለሙ ሁሉ እንዲጻፍ ከአውግስጦስ ቄሣር ትእዛዝ ወጣች።ቄሬኔዎስ በሶርያ አገር ገዥ በነበረ ጊዜ ይህ የመጀመሪያ ጽሕፈት ሆነ።”
— ሉቃስ 2፥1-2
ይሁን እንጂ ታሪክ አሁንም"Census Of Quirinius" ተብሎ የሚታወቀው ቆጠራ 6-7AD እንደሆነ ያስረዳል።²ይህም ክርስቶስ ከክርስቶስ ልደት በኋላ በ6AD ተወለደ የሚል ከማቴዎስ የባሰ ውዝግብን በመፍጠሩ በተጨማሪም የሉቃስ የታሪክ ብልሽቶች ምሁራን የሉቃስ ዘገባ ስህተት መሆኑን መስክረዋል!
...
እነዚህ የታሪክ ብልሽቶች በፈጣሪ ቃል በተባለው ወንጌል ላይ ለምን ለሚለው ጥያቄ 1904-1984 በ20ኛው ክፍለ ዘመን ከነበሩት ከፍተኛ ተጽዕኖ ካላቸው የካቶሊክ የሃይማኖት ሊቃውንት አንዱ የሆነው ጀርመናዊ የኢየሱሳውያን ቄስ እና የሃይማኖት ምሁር ብለው ካርል ራህነር "Encyclopedia Of Theology" በተሰኘ መፅሀፉ ላይ የወንጌል አዘጋጆች በአጠቃላይ ከታሪካዊ የጊዜ ቅደም ተከተሎች ይልቅ በሥነ-መለኮታዊ አካላት ላይ እንዳተኮሩ ይገልጻል።³
...
ዋቢ ይመልከቱ:
¹ Perowne, Stewart Henry (2003).The Life and Times of Herod the Great. Sutton.pp.92–93❳
² https://www.britannica.com/topic/biblical-literature/The-life-of-Jesus
³ Encyclopedia Of Theology:Sacramentum mundi By Karl Rahner(1975),p.731.
...
T.me/TheComparator
— ከወንድም አህመድ(አነፃፃሪው)
