840
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Data loading in progress...
Similar Channels
No data
Any problems? Please refresh the page or contact our support manager.
Tags Cloud
No data
Any problems? Please refresh the page or contact our support manager.
Incoming and Outgoing Mentions
---
---
---
---
---
---
Attracting Subscribers
August '24
August '24
+840
in 0 channels
Channel Posts
+3
የማላዊ ምክትል ፕሬዚዳንትን ጨምሮ 9 ሰዎችን ያሳፈረ አውሮፕላን መከስከሱ ተረጋገጠ
የማላዊ ምክትል ፕሬዚዳንት ሳውሎስ ቺሊማን ጨምሮ ዘጠኝ ሰዎችን አሳፍሮ ትናንት ተሰውሯል የተባለው አውሮፕላን መከስከሱ ተረጋገጠ፡፡
በደረሰው የመከስከስ አደጋ ሁሉም ተሳፋሪዎች ሕይወታቸው ማለፉን የማላዊ ፕሬዚዳንት ላዛሩስ ቻክዌራ ማሳወቃቸውን ቢቢሲ ዘግቧል።
ንብረትነቱ የሀገሪቱ መከላከያ ሃይል የሆነ አውሮፕላን የማላዊ መዲና የሆነችውን ሊሎንግዌን እንደለቀቀ ከራዳር ውጭ መሆኑ ትናንት መገለጹ ይታወሳል።
የአቪዬሽን ባለስልጣናት ከራዳር ውጭ ከሆነችው አውሮፕላን ጋር መገናኘት አለመቻላቸውን ማሳወቃቸውን ተከትሎ ፕሬዚዳንት ላዛሩስ ቻክዌራ የአውሮፕላኗ ፍለጋና የነፍስ አድን ተግባር እንዲከናወን ትዕዛዝ አስተላልፈው ነበር።
በዚህም መሰረት ትናንት ምሽቱን እና ዛሬ ረፋድ ድረስ የመከላከያ ሰራዊት አባላት በቺንካንጋዋ ደን ውስጥ ፍለጋ ሲያደርጉ መቆየታቸው ተገልጿል።
በዚህም አውሮፕላኗ ተከስክሳ መገኘቷን ፕሬዚዳንቱ በሰጡት መግለጫ ጠቅሰው፤ በደረሰው አሰቃቂ አደጋ እጅግ ሀዘን ተሰምቶናል ብለዋል።
| 2 | ቡርኪናፋሶ ቢቢሲ እና ቪኦኤን ጨምሮ ከሰባት በላይ ዓለም አቀፍ ሚዲያዎችን አገደች።
ምዕራብ አፍሪካዊቷ ቡርኪናፋሶ ከሰባት በላይ ዓለም አቀፍ ሚዲያዎችን አግዳለች።
ዓለም አቀፉ የሰብዓዊ መብት ሂውማን ራይትስ ዋች የቡርኪና ፋሶ ጦር 50 ህጻናትን ጨምሮ 223 ንጹሀንን ገድሏል ሲል ሪፖርት አውጥቷል።
ይህንን ሪፖርት መነሻ በማድረግም በቡርኪና ፋሶ ያሉ ዓለም አቀፍ ሚዲያዎች ዋቢ አድርገው ዘገባ የሰሩ ሲሆን የሀገሪቱ መንግስትም እገዳ ጥሎባቸዋል፡፡
በቡርኪና ፋሶ መንግስት እገዳ ከተጣለባቸው ዓለም አቀፍ ሚዲያዎች መካከልም ቪኦኤ፣ ቢቢሲ፣ ለሞንዴ፣ ዘ ጋርዲያን፣ ዶቸቪሌ፣ ቲቭ5 ሞንዴ ኦስት ፍራንስ፣ ኤፒ እና ሌሎችም ተጠቃሽ ናቸው፡፡
በቡርኪና ወታደራዊ መንግስት እገዳ የተጣለባቸው ዓለም አቀፍ ሚዲያዎች እስካሁን በጉዳዩ ዙሪያ ያወጡት መግለጫ የለም፡፡
ማሊ፣ ኒጀር እና ቡርኪና ፋሶ የአጋርነት ስምምነት ተፈራረሙ
የቡርኪና ፋሶ መንግስት በሚዲያዎቹ ላይ እገዳ የጣለው የሀገሪቱን ጦር ስም አጠልሽታችኋል በሚል ሲሆን የሂዩማን ራይትስ ዋች ሪፖርትንም ውድቅ አድርጓል፡፡
በመፈንቅለ ስልጣን ስልጣን የተቆጣጠረው የወቅቱ የቡርኪናፋሶ ወታደራዊ መንግስት ከምዕራባዊን ሀገራት ጋር ያለውን ግንኙነት በየጊዜው በማቋረጥ ላይ ሲሆን እንደ ዓለም ባንክ እና አይኤምኤፍ ያሉ አበዳሪ ተቋማትም ግንኙነታቸውን አቋርጠዋል፡፡
አፍሪካ ህብረት እና የምዕራብ አፍሪካ የኢኮኖሚ ማህበረሰብ ወይም ኢኮዋስ ቡርኪናፋሶን ጨምሮ መፈንቅለ መንግስት ያደረጉት ማሊ እና ኒጀርንም ከአባልነት ሲያግድ ሀገራቱ በምላሹ ከኢኮዋስ አባልነት መውጣታቸውን አስታውቀዋል፡፡
via Alain | 454 |
| 3 | አንጋፋው አትሌት ቀነኒሳ በቀለ አዲስ ሪከርድ አስመዘገበ
ከረጅም ጊዜ ጉዳት በኋላ በቫሌንሺያ ማራቶን የተወዳደረው ቀነኒሳ ውድድሩን በአራተኛነት ጨርሷል። ቀነኒሳ ዛሬም አዲስ ሪከርድ በስሙ ያስመዘገበ ሲሆን በዚህም የዓለም የአንጋፋዎችን የማራቶን ክብረወሰን መስበር ችሏል፡፡
ከዚህ በፊት ከ40 አመት በላይ ሆኖ ውድድሩን 2:04:19 በሆነ ሰዓት ያጠናቀቀ ሌላ አትሌት የለም፡፡ በዚህም አዲስ ክብረወሰን ተብሎ በአለም አቀፉ አትሌቲክስ ተመዝግቦለታል፡፡ | 1 035 |
| 4 | በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ምዕመናን ላይ የሚደርሰው ግፍ’ና መከራ ሃይማኖትን የሚያጠፋ የሃገር መሠረት የሆነውን እሴት የሚንድ ነው - አቡነ ማትያስ
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቤተክርስቲያኗ ለ42ኛ ጊዜ የምታካሂደውን አመታዊ ዓለማቀፍ ጉባኤ ተከትሎ ባደረጉት የመክፈቻ ንግግር በቤተክርስቲያኗ፣ ምዕመኗ እንዲሁም አገልጋይ ካህናቶቿ ላይ የሚደረው ግፍና መከራ ሄዶ ሄዶ ሃይማኖትን የሚያጠፋ ነው ሲሉ አስጠንቅቀዋል፡፡
በቤተክርስቲያኗ ምዕመናን እና አገልጋይ ካህናቶቿ ላይ የሚደርሰው ሞት፣ ስደት፣ መፈናቀል እና እንግልት ኢትዮጵያ አለኝ የምትለውን እሴት በማጥፋት ሃገሩን፣ ባህሉን፣ እሴቱን በጥቅሉ ማነንቱን የማያውቅ ትውልድ እንዲፈጠር ያደርጋል ሲሉም አክለዋል፡፡
ድርጊቱ ሃገሩን ባህሉን እሴቱን በጥቅሉ ኢትዮጵያዊ ማንነውቱን የማያውቅ ትውልድ እንደሚፈጠር የሚናገሩት አቡነ ማትያስ ይህ አይነቱ ትውልድ ከመፈጠሩ አስቀድሞ በጥንካሬ መስራት እንደሚያስፈልግም መክረዋል።
በምዕመናን ህልውና ላይ አብዝቶ መስራት እንደሚገባ የገለጹት ፓትርያርኩ ሁሉም የሚኖረው ምዕመናን እስካሉ ድረስ ብቻ መሆኑን አንክሮ ሰጥተው ተናግረዋል፡፡ የምዕመናን ህልውና ሁሉም የቤተክርስቲያኗ አገልጋይ በትኩረት ሊገነዘበው እንደሚገባ አሳስበው ሊታለፍ የማይገባ አብይ ነጥብ የቤተክርስቲያኗ አንድነት ጉዳይ መሆኑንም አስገንዝበዋል፡፡
በቤተክርስቲያኗ አንድነት እና ቀኖናዊ ይዘቷ ላይ ጥያቄ ያለው ይኖራል ብለን አንገምትም የሚሉት አቡነ ማትያስ በአስተዳደራዊ እና በዘመን ወለድ ቅሬታዎች የቤተክርስቲያኗ አንድነት እየተፈተነ ስለመሆኑ አብራርተው ተናግረዋል፡፡
አክለውም በአስተዳደራዊ እና በዘመን ወለድ ቅሬታዎች የተፈተነው የቤተክርስቲያኗ አንድነት በውስጣቸው የተፈጠረ እንቅፋት ስለመሆኑ ተናግረዋል፡፡
ቤተክርስቲያኗን እየፈተናት የሚገኘውን የአንድነት ፈተና በተለመደው መጽሃፍ ቅዱሳዊ አስተምህሮ በጥበብ እና በብልሃት ማረም ግድ እንደሚላቸው የገለፁት አቡነ ማትያስ ተላያይቶ መኖር ያሳፍራል፣ ያዳክማል እንጂ በየትኛውም መመዘኛ ትክክል እና ብርታት ሊሆን አይችልም ብለዋል፡፡
ስለሆነም ቅሬታን በድርድር እና በውውይይት በይቅርታ እና በመተማመን ዘግቶ አንድነትን ማጽናት ይገባል ነው ያሉት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ቀዳማዊ ፓትርያርክ፡፡
✍️መሠረት ነቃ | 1 150 |
| 5 | No text... | 802 |
| 6 | አቶ አረጋ ከበደ የአማራ ክልል ርእሰ መሥተዳድር ሆነው ተሾሙ
ምክር ቤቱ የክልሉን ወቅታዊ የፀጥታ ሁኔታ ማዕከል አድርጎ ሲመክር ውሏል፡፡ ከውይይቱ በኋላ በክልሉ ወጥ የሆነ ሪፎርም ተግባራዊ ማድረግ እንደሆነ የጋራ መግባባት ላይ ደርሷል፡፡ የክልሉ ርእሰ መስተዳድር ይልቃል ከፋለ (ዶ.ር) ያቀረቡትን የመልቀቂያ ጥያቄ የተቀበለው ምክር ቤቱ በምትካቸው አቶ አረጋ ከበደን የክልሉ ርእሰ መሥተዳድር በማድረግ መሾማቸውን አሚኮ ዘግቧል፡፡ | 1 298 |
| 7 | የግብረ ሰዶም ወንጀል የፈፀመ ግለሰብ በፅኑ እስራት ተቀጣ❗️
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ በሶስት ህፃናት ላይ የግብረ ሰዶም ወንጀል የፈፀመ ግለሰብ በፅኑ እስራት እንዲቀጣ ውሳኔ ተላልፎበታል፡፡
...
የ43 ዓመት ዕድሜ ያለው ተከሳሹ ወንጀሉን የፈፀመው በክፍለ ከተማው ወረዳ 01 ልዩ ቦታው ማር ተራ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ መሆኑን ከአዲስ አበባ ፖሊስ ያገኘነው መረጃ አመላክቷል፡፡
...
ግለሰቡ የጎረቤቱ ልጆች የሆኑ የ5፣ የ6 እና የ10 ዓመት ዕድሜ ያላቸው ህፃናትን በተለያዩ ቀናት ከረሜላ እየገዛ በማታለል መኖሪያ ቤቱ ውስጥ አስገብቶ ወንጀሉን ፈፅሞባቸዋል ነው የተባለው፡፡
...
ወንጀሉ ከተፈፀመባቸው ህፃናት መካከል የ6 ዓመቱ ህፃን ስለሁኔታው ለወላጅ እናቱ በመናገሩ ግለሰቡ በፖሊስ ቁጥጥር ስር ሊውል ችሏል፡፡
...
ይህንን ተከትሎ ሌሎቹ 2 ህፃናትም ተመሳሳይ ድርጊት እንደፈፀመባቸው በመግለፃቸው በሶስት የምርመራ መዝገቦች ክስ ተመስርቶበት ጉዳዩ በፍርድ ቤት ሲታይ ቆይቷል፡፡
...
መዝገቡን ሲመረምር የቆየው የፌደራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ወንጀል ችሎት የተከሳሹን ጥፋተኝነት በሰው እና በህክምና ማስረጃ በማረጋገጡ በ19 ዓመት ከ6 ወር ፅኑ አስራት እንዲቀጣ ውሳኔ አስተላልፎበታል፡፡
ህብረተሰቡ ከህግና ከማህበራዊ እሴቶች ያፈነገጡ ህገ-ወጥ ተግባራት ሲያጋጥሙ ለፖሊስ ጥቆማ እንዲሰጥ ጥሪ ቀርቧል፡፡
...
ግብረ ሰዶማዊነት በሀገራችን ህግ ፍፁም የተከለከና በህግ የሚያስጠይቅ ተግባር በመሆኑ ከዚህ ጉዳይ ጋር የተያያዘ መረጃ እና ጥቆማ ያለው ማንኛውም ሰው በአቅራቢያው በሚገኝ ፖሊስ ጣቢያ በግንባር በመቅረብ እንዲሁም በነፃ የስልክ መስመር 991 እና 987 እንዲሁም በ011-1- 11-01-11 እና 011-5-52-63-02 በመጠቀም መረጃና ጥቆማ መስጠት እንደሚችል የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል፡፡
Ethio Fact Info | 1 381 |
| 8 | No text... | 1 039 |
