የተዋህዶ አርበኞች-Ye Tewahedo Arbegnoch
Open in Telegram
#ኢትዮጵያ_የዓለም_ብርሃን ክንድህን ኃይልህንም ጽድቅህንም እስክነግር ድረስ አቤቱ አትተወኝ #መዝሙር_ዳዊት 70 ( 71 ) 15 – 18 ++++++++++++++++++++++ "የመለከቱን ድምፅ የሚሰማ ሰዉ ባይጠነቀቅ፥ ሰይፍ መጥቶ ቢወስደዉ፥ ደሙ በራሱ ላይ ይሆናል። "የመለከቱን ድምፅ ሰምቶ ስላልተጠነቀቀ ደሙ በራሱ ላይ ይሆናል፤ ቢጠነቀቅስ ኖሮ ነፍሱን ባዳነ ነበር።" #ትንቢተ_ህዝቅኤል 33፡4-5
Show more2 752
Subscribers
-224 hours
-97 days
+3030 days
Posts Archive
🔥 የአባ አምኃ ኢየሱስ ገ/ዮሐንስ ቁጥር 7 - "አልጫዎቹ" መደበኛ ትምህርታዊ የጽሑፍ መልእክት እና አዋጅ። #ሙሉ_ክፍል
👉ሙሉ ክፍል በ👉VIDEO(በቀላል Size)
🌹ሐዲስ ሐዋርያ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ዘኢትዮጵያ🌹
“ቅዱሳን ጻድቃን በመንፈሳዊ አርአያነታቸው፣ በጸሎታቸውና በትምህርታቸው ከከበቡን የነፍስ ጠላቶች፤ ከርኲሳን መናፍስትና ከጨለማው ልጆች፣ ከክፉ ሰዎች ሽንገላና ተንኰል ለመሰወርና ለመጠበቅ ከእግዚአብሔር የተቀበሉት ሥልጣን ምንጊዜም ይሠራል፡፡ በጻድቃን መኖር ሀገር ከጥፋት ትድናለች፡፡ የጻድቃንን ስም ጠርቶ እግዚአብሔርን በመለመን በረከትና ረድኤት ይገኛል፡፡ ስለ ጻድቃን ብሎ እግዚአብሔርም ምሕረቱን ያድላል፡፡ ጻድቃንን ማሰብ ሥራቸውን መዘከር ክርስቲያናዊ ሕይወታችንን ያጐለምሳል፤ በነፍስ በሥጋ ይታደገናል፤ ይጠቅመናል፡፡
“ስለዚህም ቤተ ክርስቲያናችን ጻድቃንን እንድናስባቸው፣ በስማቸውም ለድሆች እንድንመጸውት፣ መታሰቢያቸውን እንድናደርግ የምትመክረን፤ የምታስተምረን (ማቴ.፲፥፵፩-፵፪)፡፡ ቅዱሳን ጻድቃን በሕይወተ ሥጋ ሳሉም ሆነ ከሞቱ በኋላ በዐጸደ ነፍስ ሆነው በጸሎታቸው ለሚታመኑ፣ በቃል ኪዳናቸው ለሚማጸኑ ምእመናን በመጸለይና ወደ እግዚአብሔር በማማለድ ድኅነተ ሥጋ፣ የድኅነት ነፍስን የሚያስገኙልን የችግር ጊዜ አማላጆቻችንና አስታራቂዎቻን ናቸው፤ ከእነዚህ ቅዱሳን መካከል ኢትዮጵያዊው ጻድቅ አቡነ ተክለ ሃይማኖት አንደኛው ናቸው፡፡
‹ተክል› ማለት ፍሬያማ ዕንጨት፣ ዛፍ፣ ቅመም፣ ቅጠላ ቅጠል፣ የሚበላ፣ የሚሸተት፣ ገነታዊ ዕፅ፣ እንዲሁም ሕግ፤ ሥርዓት ማለት ነው (ማቴ.፲፭፥፲፫)፡፡ ‹ሃይማኖት› ማለት ደግሞ በሀልዎተ እግዚአብሔር፣ እግዚአብሔር የሁሉ አስገኚ መሆኑን፣ በሥላሴ አንድነትና ሦስትነት፣ በቅዱሳን ተራዳኢነት ማመን አምኖም መመስከር ማለት ሲሆን ‹ተክለ ሃይማኖት› የሚለው ሐረግም የሃይማኖት ተክል፣ ይኸውም የጽድቅ ፍሬን ያፈራ፣ ከኃጢአት ሐሩር ማምለጫ ዛፍ፣ ምእመናንን በቃለ ወንጌል ያጣፈጠ ቅመም፣ መዓዛ ሕይወቱ የሚማርክ፣ ቢመገቡት ረኃበ ነፍስን የሚያስወግድ ቅጠል፣ የጻድቃን መጠለያ ዕፅ የሚል ትርጕም አለው፡፡‹‹ተክለ ሃይማኖት ማለት የአብ የወልድ የመንፈስ ቅዱስ ተክል ማለት ነው›› ሲል የጻድቁን ስም ይተረጕመዋል፡፡
“ጻድቁ አባታችን ሕይወታቸዉን ሙሉ ለእግዚአብሔር በመስጠት፣ እንደ በሬ ተጠምደው፣ እንደ ገበሬ ታጥቀው፣ ይህንን ዓለም ንቀው፣ በጾም በጸሎት ተወስነው በብሕትውና በመኖራቸው፤ እርሳቸው በአሚነ ሥላሴ ጸንተው ሌሎችንም እንዲጸኑና እንዲያምኑ በማድረጋቸው፤ እንደዚሁም እንደ ቅዱሳን ሐዋርያት ወንጌልን በመላው ኢትዮጵያ እየተዘዋወሩ በመስበክ በጌታችን በመድኃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ድውያነ ሥጋን በተአምራት፣ ድውያነ ነፍስን በትምህርት የፈወሱ ሰባኬ ወንጌል በመሆናቸው ‹‹ተክለ ሃይማኖት›› ተብለው ይጠራሉ፡፡
“አቡነ ተክለ ሃይማኖት በእግዚአብሔር ድንቅ ጥበብ፣ በሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ብሥራት፤ በኢትዮጵያ ምድር በሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ልዩ ስሙ ኢቲሳ በሚባል ቦታ ከአባታቸው ከካህኑ ጸጋ ዘአብና ከእናታቸው ከቅድስት እግዚእ ኀረያ መጋቢት ፳፬ ቀን ተፀንሰው ታኅሣሥ ፳፬ ቀን ፲፪፻፲፪ ዓ.ም ተወለዱ፡፡ በተወለዱ በሦስተኛው ቀን እሑድ ከጠዋቱ ሦስት ሰዓት ከእናታቸው ዕቅፍ ወርደው ‹‹አሐዱ አብ ቅዱስ፤ አሐዱ ወልድ ቅዱስ፤ አሐዱ ውእቱ መንፈስ ቅዱስ፤ አንዱ አብ ቅዱስ ነው፤ አንዱ ወልድ ቅዱስ ነው፤ አንዱ መንፈስ ቅዱስ ነው፤›› በማለት ሥላሴን አመስግነዋል፡፡ ወላጆቻቸው ያወጡላቸው ስም ‹‹ ፍሥሐ ጽዮን›› የሚል ሲሆን ‹‹ተክለ ሃይማኖት›› ደግሞ የእግዚአብሔር መልአክ ቅዱስ ሚካኤል ያወጣላቸው ስም ነው፡፡ በተወለዱ በ፲፭ ዓመታቸው ዲቊናን፤ በ፳፪ ዓመታቸው ደግሞ ቅስናን ከግብፃዊው ጳጳስ ከአባ ጌርሎስ (ቄርሎስ) ተቀብለዋል፡፡
“አንድ ቀን ወደ ጫካ ለአደንበሔዱበት ዕለት ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ተገልጦላቸው ጸጋ መንፈስ ቅዱን አሰደረባቸው፤ እንደዚሁም ‹ሐዲስ ሐዋርያ› ብሎ ወንጌል ወዳልተዳረሰበት ቦታ እንደሚልካቸው ነገራቸው፡፡ ቅዱስ ሚካኤልም ከአውሬ አዳኝነት ሰውን ወደ እግዚአብሔር መንግሥት ለመመለስ እንደ ተመረጡና አጋንንትን የማውጣት፣ ተአምራትን የማድረግ ሥልጣን እንደ ተሰጣቸው፤ ስማቸውም ‹ተክለ ሃይማኖት› እንደሚባልና ትርጓሜውም ተክለ አብ፣ ተክለ ወልድ፣ ተክለ መንፈስ ቅዱስ ማለት እንደ ሆነ አስረዳቸው፡፡ ከዚህ በኋላም ወደ ቤታቸው ተመልሰው ያላቸውን ንብረት ሁሉ ለቤተ ክርስቲያንና ለነዳያን ሰጥተው ‹‹አቤቱ ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ! የመንግሥተ ሰማያትን በር ትከፍትልኝ ዘንድ እነሆ ቤቴን እንደተከፈተ ተውኩልህ›› በማለት ቤታቸውን ትተው ወንጌልን ለማስተማር ፈጥነው ወጡ፡፡ ከዚያ ጊዜ ጀምረው በመላው ኢትዮጵያ እየተዘዋወሩ ወንጌልን በመስበክና ተአምራትን በማድረግ ብዙ አሕዛብን ከአምልኮተ ጣዖት ወደ አምልኮተ እግዚአብሔር፤ ከገቢረ ኀጢአት ወደ ገቢረ ጽድቅ መልሰዋል፡፡ ቤተ ክርስቲያንንም አንጸዋል፡፡ ‹ሐዲስ ሐዋርያ› የተባሉትም በዚህ ተልእኳቸው ሲሆን፣ ትርጕሙም ሐዲስ ኪዳንን ወይም ሕገ ወንጌልን እየተዘዋወረ የሚያስተምር ሰባኬ ወንጌል፤ በክርስቶስ ስም ድንቅ ድንቅ ተአምራትን የሚደርግ የክርስቶስ ተከታይ (ሐዋርያ) ማለት ነው፡፡
“አባታችን ተክለ ሃይማኖት ሕይወታቸዉን ሙሉ ለእግዚአብሔር በመስጠት፣ እንደ በሬ ተጠምደው፣ እንደገበሬ ታጥቀው፣ ይህንን ዓለም ንቀው፣ በጾም በጸሎት ተወስነው፣ በብሕትውና ኖረዋል፡፡ በተጨማሪም እንደቅዱሳን ሐዋርያት ወንጌልን በመላው ኢትዮጵያ እየተዘዋወሩ የሰበኩ፣ በጌታችን በመድኃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ድውያነ ሥጋን በተአምራት፣ ድውያነ ነፍስን በትምህርት የፈወሱ ሐዋርያ ናቸው፡፡ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ከሚታወሱባቸው በዓላት መካከልም ታኅሣሥ ፳፬ ቀን የሚከብረው በዓለ ልደታቸው አንደኛው ነው፡፡ መጽሐፈ ስንክሳር ዜና ልደታቸውን ሲናገር ‹‹ሐዲስ ሐዋርያ›› በማለት በክብር ጠርቷቸዋል፡፡
“ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለደቀ መዛሙርቱ ‹‹እናንተን የሚቀበል እኔን ይቀበላል፤ እኔንም የሚቀበል የላከኝን ይቀበላል፡፡ ነቢይን በነቢይ ስም የሚቀበል የነቢይን ዋጋ ያገኛል፡፡ ጻድቅንም በጻድቅ ስም የሚቀበል የጻድቁን ዋጋ ያገኛል፡፡ማንም ከእነዚህ ከታናናሾቹ ለአንዱ ቀዝቃዛ ጽዋ ብቻ በደቀ መዝሙር ስም የሚያጠጣ እውነት እላችኃለሁ፤ ዋጋ አይጠፋበተም፤››(ማቴ. ፲፥፵-፵፪) በማለት የተናገረውን መለኮታዊ ቃል ኪዳን ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን መሠረት አድርጋ መጋቢት ፳፬ ቀን ፅንሰታቸውን፣ ታኅሣሥ ፳፬ ቀን ልደታቸውን፣ ጥር ፳፬ ቀን ስባረ ዐፅማቸውን፣ ግንቦት ፲፪ ቀን ፍልሰተ ዐፅማቸውን፣ ነሐሴ ፳፬ ቀን ደግሞ ዕለተ ዕረፍታቸውን በመንፈሳዊ ሥርዓት በደስታ ታከብራለች፡፡ የአቡነ ተክለ ሃይማኖትና የሁሉም ጻድቃን ጸሎት፣ በረከት፣ ረድኤትና ምልጃ በመላው ሕዝበ ክርስቲያን ላይ ለዘለዓለሙ ጸንቶ ይኑር፡፡
ወስብሐት ለእግዚአብሔር 🙏🏼
ምንጭ፡– ገድለ አቡነ ተክለ ሃይማኖት፤ መጽሐፈ ስንክሳር (ታኅሣሥ ፳፬፣ ጥር ፳፬፣ መጋቢት ፳፬፣ ግንቦት ፲፪ እና ነሐሴ ፳፬ ቀን)
📌በእስ*ላሞች ዘንድ በተለይም በዚሁ በመካ መዲና ዙሪያ እስላሞች ባሉበት ሁሉ የሚታመንና የሚነገር አንድ አባባል ወይም ትንቢት አለ ፡፡
እሱም እንዲህ ነው ፦
👉 ወደፊት በኢትዮጵያ ምድር የሚነሳ አንድ መላጣ የሆነ ንጉስ ይመጣል / ይነግሳል / ይህ ሰው እስል*ምናንና እንዲሁም ዋናውን ሥፍራ መካ መዲናን ያፈር*ሳል ጥቂት ሰው ብቻ ነው የሚተርፈው የተቀረው ይጠ*ፋል ብለው ያምናሉ ፡፡
ይህን አባባል የቀደሙ በእድሜያቸው የገፉ አባት እስላ*ሞች ባብዛኛው የሚያውቁት ነው ፡፡ ወጣቱ እስ*ላም ብዙም ቦታ አይሰጠውም ነገሩ ግን እውነት ነው ፡፡ መቼም በየዘመኑ እግዚአብሔር የሚወደው አንዳንድ የዋህ ሰው ከየትኛውም ሥፍራ አይጠፋምና አንዱ የዋህ እስ*ላም ተገልጦለት ይሆናል ፡፡ የሆነ ሆኖ እስል*ምና እጅግ ብዙ የንፁሃንን ደ*ም ያፈ*ሰሰ በመሆኑ በእርግጥም ይጠ*ፋሉ ይጠ*ረጋሉ ፡፡
✍ከኢትዮጵያ የአለም ብርሃን መልእክት 9 የተወሠደ፡፡
ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ
✝️✝️✝️
ነሐሴ 24 ቀን
በዓለ ዕረፍቷ ነው። እንኳን አደረሳችሁ። አደረሰን።
እግዚእነ ኢየሱስ ክርስቶስ
የክብሩን ጸዳል ያበራባት
ቅድስናዋ የተገለጠው በቤትዋ ገና ምናኔ ሳትወጣ ሰምረ ጊዮርጊስን አግብታ 12 ወልዳ በኖረችበት ትውልድ ቦታዋ እግዚአብሔር ደግነትዋን በገድልዋ ያልተገለጸ እሷና ፈጣሪዋ የሚያውቁት ስውር ገድሏ የትሩፋት ስራ አበጋዝ መሆንዋን ጽኑ ዕምነትዋን ተመልክቶ ሙት ያነሳላት ክብርት እመቤት ናት።
ዳግማዊ ቂርቆስ የተባለውን
የመጨረሻ ልጅዋንና አበዛዋን (የቤት አገልጋዪዋን) ይዛ በምናኔ ወደዜጋመል ከጉር እስከ ሸመን በቃል ኪዳን በታጠረው ደብረ ሊባኖስ ገብታለች።
ኋላም በጽኑ ብሕትውና በተሐራሚነት ወደኖረችበት በሞተ ሥጋ እስክታንቀላፋ በገድል በስግደት በጾም ጸሎት ወደኖረችበት ወዝ ላብዋ ወደነጠበበት ባሕረ ጣና በመግባት ኖራለች።
ክብር ይግባውና ጌታችንና አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በማይታበል ቃሉ ቃልኪዳን ገብቶላታል።
እናታችን የጽናት የትዕግስት መድብል በዓለምም ከእግዚአብሔር ጋር ሆኖ መኖር እንደሚቻል በተግባር የሰበከች ታላቅ ወንጌል የተተረጎመባት አትሮስ ናት።
ቤተክርስቲያን እንዲህ ኮከብ የሆነ ከወንዶቹ እኩል በምግባር በእምነት የለመለሙ በትሩፋት ያጌጡ በገድል የተቀጠቀጡ ከሞቀ ቤት እመር ብለው የወጡ መስቀለ ክርስቶስን ተሸክመው በምናኔ የኖሩ በተጋድሎዋቸው በጽኑ እምነታቸው ለነጽሮተ ሥሉስ ቅዱስ የበቁ እማት ቅዱሳን አንስት ማህደር ናት ቤተክርስቲያን ቤተ ሥላሴ።!!!
የዘመኗን ፍጻሜ በጽኑ ተጋድሎ የኖረችው በባሕረ ጣና
በሚገኘው ገዳሟ ነው በዚህ ቅዱስ መካን ዛሬ ክቡር
አጽሟ ይገኛል።
የእናታችን ምልጃ ጸሎት ከጨለማ አበጋዞች
ከውሉደ መርገም መዳፍ ይታደገን
አሜን አሜን አሜን
+4
††† የጻድቁ አባታችን ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት የቅድስናና የክብር ስሞች †††
1.ተክለ አብ: ተክለ ወልድ: ተክለ መንፈስ ቅዱስ
2.ፍስሐ ፅዮን
3.ሐዲስ ሐዋርያ
4.መምሕረ ትሩፋት
5.ካህነ ሠማይ
6.ምድራዊ መልዐክ
7.እለ ስድስቱ ክነፊሁ (ባለ ስድስት ክንፍ)
8.ጻድቅ ገዳማዊ
9.ትሩፈ ምግባር
10.ሰማዕት
11.የኢትዮዽያ መነኮሳት አለቃ
12.ፀሐይ ዘበፀጋ
13.የኢትዮዽያ ብርሃኑዋ
14.ብእሴ እግዚአብሔር (የእግዚአብሔር ሰው)
15.መናኒ
16.ኤዺስ ቆዾስ (እጨጌ)
††† እነዚህ የአባታችን ስሞች እንደዘመኑ ሰው ለመሞጋገስ የወጡ ሳይሆኑ ሁሉም በትክክል ሥራዎቹንና ለቤተ ክርስቲያን የሆነላትን የሚያዘክሩ ናቸው:: †††
=>አምላከ ቅዱሳን በወዳጆቹ ምልጃ ክብራቸውን ያድለን:: በረከታቸውም በዝቶ ይደርብን::
=>ነሐሴ 24 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት=
1.ቅዱስ አቡነ ተክለ ሃይማኖት (መምሕረ ትሩፋት)
2.ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ (ጻድቅት)
3.ቅዱስ ቶማስ ዘመርዐስ
4.አበው አብርሃም: ይስሐቅና ያዕቆብ
=>ወርኀዊ በዓላት
1.አቡነ ዘዮሐንስ ጻድቅ ዘክብራን
2.ቅዱስ አጋቢጦስ (ጻድቅ ኤዺስቆዾስ)
3.ቅዱስ አብላርዮስ ታላቁ
4."24ቱ" ካኅናተ ሰማይ (ሱራፌል)
5.ቅዱስ አባ ሙሴ ጸሊም
=>††† ነቢይን በነቢይ ስም የሚቀበል የነቢይን ዋጋ ይወስዳል:: ጻድቅን በጻድቅ ስም የሚቀበል የጻድቁን ዋጋ ይወስዳል:: ††† (ማቴ.10:40)
<<< ወስብሐት ለእግዚአብሔር >>>
‹‹ነሐሴ 24›› በዚህ ዕለት የአባታችን የአቡነ ተክለሃይማኖት የዕረፍታቸውን መታሰቢያ በዓል ነው።
“ተክለሃይማኖት” ማለት ‹‹የሃይማኖት ተክል፣ ተክለ አብ፣ ተክለ ወልድ፣ ተክለ መንፈስ ቅዱስ›› ማለት ነው።
አቡነ ተክለሃይማኖት በቡልጋ ደብረ ጽላሎሽ ከቅዱሳኑ አባታቸው ጸጋ ዘአብ እና እናታቸው እግዚእ ኃርያ ተወለዱ። የቤት ስማቸው ፍስሐ ጽዮን ሲሆን ትርጓሜውም የጽዮን ደስታና ተድላ ማለት ነው።
በ15 ዓመታቸው ድቁናን፣ በ22 ዓመታቸውም ቅስናን ከአቡነ ቄርሎስ ተቀበሉ። ወላጆቻቸው በአምስት ቀን ልዩነት ካረፉ በኋላ በእጅጉ አዝነው ወደ ዱር ሄዱ። በዚያም ጌታችን ተገልጦ “ከእንግዲህ ነፍሳትን እንጂ እንስሳትን አታድንም፤ ስምህም ተክለሃይማኖት ይባላል” ብሎ መረጣቸው።
ከዚያም ቤታቸውን ትተው ወንጌልን እያስተማሩ፣ ተአምራትን እያደረጉ፣ አብያተ ክርስቲያናትን እያሰሩ 10 ዓመት አገለገሉ። ከዚያም ወደ ደብረ ዳሞ ሄደው ከአባ ዮሐና ምንኩስናን ተቀብለው 12 ዓመት አገለገሉ።
በ1267 ዓ.ም. በዓት አድርገው ለ22 ዓመት ቆመው በመጸለይ ከቆዩ በኋላ፣ አንድ እግራቸው ተሰበረ። በአንድ እግራቸውም ለ7 ዓመት በጸሎት ቆመው በጠቅላላው 29 ዓመት በጸሎት ቆዩ። በ99 ዓመት ከ10 ወር ከ10 ቀን የምድር ኑሮአቸውን ፈጽመው ነሐሴ 24 ቀን አረፉ።
በዚችም ዕለት የእናታችን የቅድስት ክርስቶስ ሰምራ የዕርፍት መታሰቢያ በዓሏ ነው።
ከአባታችን የአቡነ ተክለሃይማኖት ከእናታችን ከቅድስት ክርስቶስ ሰምራ ምልጃና በረከት አይለየን። 🙏
#የተስፋ_ቃል!!!
...ምድራችን እዉነትን በማያዉቁ አመጸኞችና ወንጀለኞች የዲያብሎስ ልጆች ስለተሞላች በግድ መጽዳት አለባት። ለቅዱሳንም የተመቸችች የበረከት ምድር ልትሆን ይገባል! ስለሆነም ይኸዉ የፈጣሪ ፈቃድ ይፈጸማል።
በኢትዮጵያ የሚደርሰው የሚፈጸመው ሁሉ እነሆ ይመጣል! እግዚአብሔር የቀባቸው በምድሪቱ ላይ ሲነግሱ ያኔ ብቻ የእረፍት ጅማሮ ይሆናል። ይህ እስኪሆን ግን ዓለም አይታ የማታውቀውን ጥፋትና ውድመት
ታስተናግዳለች በዚህን ጊዜ ሁሉም የሚጮኸው የፈጣሪ ቁጣ እንዲቆምለት ብቻ ነው። ያ ደግሞ የሚሆነው የታዘዘው ሁሉ ሲፈጸም የእግዚአብሔርም ሕዝቦች ነጻ ሲወጡ ብቻ ነው።
የታመኑ የፈጣሪ ልጆች በዓለም ሁሉ ፊት የሚያበራውን ከጌታ የተሰጣቸውን ስልጣን ሲያፀኑ! ሁሉም ሲንበረከክና ለፈጣሪና ላከበራቸው ሲገዛ ብቻ ነው! ሰላም፣ በረከት፣ ቸርነት፣ የሚሆነው ይኸው ሲሆን ብቻ ነው። ይህ ደግሞ ከብዙ ጉዳት በህዋላ የሚፈጸም ነው።
ምክንያቱም የሰው ልጅ ትእቢቱንና አውቃለሁ ባይነቱን ቶሎ አይጥልምና!! ዓለም ሁሉ በታላቅ እንባና ጩኸት ይሞላል። ከቁጣው ብርታት የተነሳ ዓለም ያለፈች እስኪመስል ድረስ፤ አሁንም ደግሜ እለዋለሁ! በኢትዮጵያና በዙሪያዋ ባሉ ተራሮች (ሀገሮች) ሁሉ የብርሃን ዙፋኑን የሚዘረጋው ጌታ ልጆቹን ከዙፋኑ ላይ ሲያስቀምጥ ብቻ ነው ቁጣው መስከን የሚጀምረው ከዚህ ውጪ የሚመጣ አንዳችም ነገር የለም።
✍ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት 2
#ኢትዮጵያ_የሥላሴ_የክብራቸው_መገለጫና_መመስገኛ_ምድር
#ኢትዮጵያ_ርስተ_ድንግል_ማርያም
#ኢትዮጵያ_የዓለም_ብርሃን
#ኢትዮጵያ_የዓለሙ_ገዥ
🔥የአባ አምኃ ኢየሱስ ገ/ዮሐንስ ቁጥር 7 - አልጫዎቹ መደበኛ ትምህርታዊ የጽሑፍ መልእክት እና አዋጅ።
በ👉AUDIO(በድምፅ) #ክፍል_6
🔥 የአባ አምኃ ኢየሱስ ገ/ዮሐንስ ቁጥር 7 - "አልጫዎቹ" መደበኛ ትምህርታዊ የጽሑፍ መልእክት እና አዋጅ። #ክፍል_6
በ👉VIDEO(በቀላል Size) #ክፍል_6
🔥የአባ አምኃ ኢየሱስ ገ/ዮሐንስ ቁጥር 7 - አልጫዎቹ መደበኛ ትምህርታዊ የጽሑፍ መልእክት እና አዋጅ።
በ👉AUDIO(በድምፅ) #ክፍል_5
🔥 የአባ አምኃ ኢየሱስ ገ/ዮሐንስ ቁጥር 7 - "አልጫዎቹ" መደበኛ ትምህርታዊ የጽሑፍ መልእክት እና አዋጅ። #ክፍል_5
በ👉VIDEO(በቀላል Size) #ክፍል_5
🔥የአባ አምኃ ኢየሱስ ገ/ዮሐንስ ቁጥር 7 - አልጫዎቹ መደበኛ ትምህርታዊ የጽሑፍ መልእክት እና አዋጅ።
በ👉AUDIO(በድምፅ) #ክፍል_4
🔥 የአባ አምኃ ኢየሱስ ገ/ዮሐንስ ቁጥር 7 - "አልጫዎቹ" መደበኛ ትምህርታዊ የጽሑፍ መልእክት እና አዋጅ። #ክፍል_4
በ👉VIDEO(በቀላል Size) #ክፍል_4
