cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

كنوز الجنة

♥ አላህ መልካም የሻለትን ሰው ዲኑን ያስገነዝበዋል ♥ የተለያዩ ኢስላሚክ ዳዐዋ ማራኪ ቃራዖች የመለቀቁበት ቻናል join ብቻ

Show more
The country is not specifiedThe language is not specifiedThe category is not specified
Advertising posts
136
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

-የምታስበውን ነገር ልብ በለው ቃላቶች ይሆናሉና - ቃላቶችህን ልብ በላቸው ያንተ ተግባሮች ይሆናሉና - ተግባሮችህን ልብ በላቸው ከጊዜ ቡሀላ ልምድ ይሆናሉና - ልማዶችህን በደንብ ልብ ብለህ አስተውላቸው ቡሀላ ላይ ባህሪህ ይሆናሉና ባህሪህን ልብ በለው ምክኒያቱም መጨረሻህ የሚሆነው ባህሪህ ነውና
Show all...
ስለ እስራኤል መጮህ እኛን የጎዳ ለመሰላቸውና ለምን ስለ ፍልስጤም እንደምንጮህ ላልገባቸው አንዳንድ ርካሽ ካፊሮች የምትሰጧቸውን 5 መልሶች ላጋራችሁ 1) እኛ ከኢትዮዽያዊነታችን ሙስሊምነታች ይበልጥብናል 2) ነገ ጌታችን ፊት ለዲንህ ምን አረክ እንጂ ለሀገርህ ምን አረክ ተብለን አንጠየቅም 3) ለተቀደሰው መስጂድ የኔን ፋንታ እየተዋጉልኝ ስለሆነ ድጋፌ ያስፈልጋቸዋል። 4) ሙስሊም ሲበደልም ሲበድልም እርዳው ስለሚል ሀዲሱ (ሲበድል አስቁመው ሲበደል ድረስለት) 5) ስለ ሙስሊም ወንድሞቹ ሳይጨነቅ ተኝቶ ያነጋ ከኛ አይደለም ስለሚል ሀዲሱ ✍ አብዲ ሾዎ 👉 @hebre_muslim
Show all...
💐የዐለማችን ውብ ሴት ☞ ቁርኣንን በአእምሮዋ በመሸምደድ የሃፈዘችውና በውስጡ ያዘለውንም ህግጋት በተግባር ያዋለች... ☞ የአላህ መልእክተኛን (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) በመጎዳኘት በኢስላም ታሪክ ወደር የማይገኝለትን ታሪክ ያስመዘገቡ ሴቶችን (ሰሃቢያትን) አርኣያዎቿ ያደረገች … ☞ ከዚህም ከዚያም አየተጣሯት የጥብቅነቷን፣ የንፅህናዋንና የአይን-አፋርነቷን ሂጃብ ሊያስጥሏት ለሚጣሯት ጎትጓቾች ጥሪ መስሚያ የሌላት፣ ቦታ የማትሰጣቸው… ☞ ለወላጆቿ መልካሚት በመሆን እንደ ልጅም እን እናትም የምትንከባከባቸውና ለክብራቸው፣ ለስነልቦናቸው ቅድሚያ የምትሰጥ… ☞ ክብሩና ልዕልናው የላቀው አላህን በማያስቆጣ ነገር ላይ ባሏን የምትታዘዝ፤ ጥሩ ረዳትና ጓደኛም በመሆን የታማኝነት ፍቅርን የምትለግሰው… ☞ ሀያሉ አላህ ፊት በመቆም ልትሰግድለትና መልካም ምንዳውን እንዲሁም ትሩፋቱን ልትለምነው ስትል እንቅልፏን በመቀነስ ጣፋጭ ከሆነው ጣዕሙ ራሷን የምታቅብ… ☞ የአላህን ተባረከ ወተዓላ ውዴታና በረከቱን በመሻት የፍላጎት ፆሞችን የምትፆም… ☞ ምላሷን የምትጠብቅና የሰዎችን ክብር በሚነካ ጉዳይ ላይ የማትዘፈቅ… ☞ ክብሩና ልዕልናው የላቀው አላህ ሀራም ወዳደረገው ነገር ባለመመልከት ራሷን የምታርቅ… ☞ ኢስላምን ለመርዳት ስትል፣ አላህን ግዴታ ያደረገባትን ትእዛዝ ለመፈፀም ስትል በአላህ መንገድ ላይ ባሏን፣ ልጇን፣ ገንዘቧንና ህይወቷንም መስዋእት የምታደርግ… አላህ ሆይ ሙስሊም እንስቶቻችንን ባርክልን። ሁሉን ባያሟሉ እንኳን የቻሉትን ያህል የፈፀሙትን ስራዎቻቸውን ተቀበላቸው። አጋር የሚሆን ወንድም፣ ደጋፊ የሚሆን ባልና፣ ተባባሪ የሚሆን ማህበረሰብ ወፍቃቸው። በመንገድህም ላይ አፅናቸው። آمين ※::::::::::::::::::::::::::::::::::※
Show all...
۞ الله ۞ الرحمن ۞ الرحيم ۞ الملك ۞ القدوس ۞ السلام ۞ المؤمن ۞ المهيمن ۞ العزيز ۞ الجبار ۞ المتكبر ۞ الخالق ۞ البارئ ۞ المصور ۞ الغفار ۞ القهار ۞ الوهاب ۞ الرزاق ۞ الفتاح ۞ العليم ۞ القابض ۞ الباسط ۞ الخافض ۞ الرافع ۞ المعز ۞ المذل ۞ السميع ۞ البصير ۞ الحكم ۞ العدل اللطيف ۞ الخبير ۞ الحليم ۞ العظيم ۞ الغفور ۞ الشكور ۞ العلي ۞ الكبير ۞ الحفيظ ۞ المقيت ۞ الحسيب ۞ الجليل ۞ الكريم ۞ الرقيب ۞ المجيب ۞ الواسع ۞ الحكيم الودود ۞ المجيد ۞ الباعث ۞ الشهيد ۞ الحق ۞ الوكيل ۞ القوي ۞ المتين ۞ الولي ۞ الحميد ۞ المحصي ۞ المبدئ ۞ المعيد ۞ المحيي ۞ المميت ۞ الحي ۞ القيوم ۞ الواجد ۞ الماجد ۞ الواحد ۞ الأحد ۞ الصمد ۞ القادر ۞ المقتدر ۞ المقدم ۞ المؤخر ۞ الأول ۞ الآخر ۞ الظاهر ۞ الباطن ۞ الوالي المتعالي ۞ البر ۞ التواب ۞ المنتقم ۞ العفو ۞ الرءوف ۞ مالك ۞ الملك ۞ ذو ۞ الجلال ۞ والإكرام ۞ المقسط ۞ الجامع ۞ الغني ۞ المغني ۞ المانع ۞ الضار ۞ النافع ۞ النور ۞ الهادي ۞ البديع ۞ الباقي ۞ الوارث ۞ الرشيد ۞ الصبور @bayushh
Show all...
ሸይኽ ዶ/ር ፈውዛን ሰሞኑን በፍልስጤም ውስጥ ስለተከሰተው ጉዳይ የተናገሩት‼ ======================================================== «መስጅደ-ል-አቅሷን ከአይሁዶች እጅ ነፃ በማውጣት ረገድ ሁሉም ሙስሊም የሚችለውን ያክል ሊታገል ይገባል!» || ✍ ታላቁ የዘመናችን ዓሊም፣ የሳዑዲ ቋሚ የፈታዋና ዲናዊ ጥናቶች ኮሚቴ አባልና የታላላቅ ዑለማዎች አባል የሆኑት፣ በብዙዎች ዘንድ "የሰለፎች ቅሪት (በቂየቲ-ስ'ሰለፍ) የሚባሉት ሸይኽ ዶ/ር ሷሊሕ ፈውዛን ቢን ዐብደ-ል'ሏህ አል-ፈውዛን (አላህ ይጠብቃቸውና) ረመዷን ውስጥ በጠና ታመው የነበረ ቢሆንም አሁን ላይ በጥሩ ጤንነት ይገኛሉ። የዘንድሮውን ዒድ በሳዑዲው ታላቅ ሙፍቲ በሸይኽ ሷሊሕ ኣሊ-ሸይኽ (ሐፊዘሁ-ል'ሏህ) ቤት ከሌሎች ታላላቅ ዑለማዎች ጋር በመሆን ዚያራ በማድረግ አሳልፈዋል። ✔ ሰሞኑን በፍልስጤም ወንድሞቻችን ላይ በጽዮናዊያን እየደረሰ ያለውን ዘግናኝና ጭካኔ የተሞላበት ጥያት በተመለከተ «መስጅደ-ል-አቅሷን በመተናኮስ አለፍ ሲልም ለማውደም እየተደረገ ባለው ትግል ላይ የዑለማዎች፣ የዳዒዎችና ኻጢቦች ሚና ምንድን ነው?» ተብለው ተጠይቀው፤ እርሳቸውም እንዲህ ሲሉ መልሰዋል፦ «በዚህ ጉዳይ ላይ ግዴታው ትልቅ ነው። ሁሉም የሙስሊሞች መስጅዶች (መከበር አለባቸው)። ነገር ግን መስጅደ-ል-አቅሷ (ይበልጥ መከበር አለበት!)፤ ጓዝ ተጠቅልሎ ጉዞ መሄድ ከሚፈቀድባቸው ሦስት መስጅዶች መካከል አንዱ ነው። እርሱ የነቢያቶች (ሶላትና ሰላም በነርሱ ላይ ይስፈንና) መስጅድ ነው። (ጠላቶች) በመጡበት ሁሉ ከርሱ ሊመክቱ በሙስሊሞች ላይ ግዴታ ነው፤ ከከሃድያን አይሁዶች ወረራ ነፃ እስከሚያወጡት ድረስ! ይህ ከግለሰቦች መካከል በተወሰኑ ግለሰቦች ላይ ብቻ ግደታ የሚሆን ሳይሆን በሁሉም ሙስሊሞች ላይ ግድ የሆነ ነው። ሁሉም የሚችለውንና አቅሙ የፈቀደለትን ያክል (ሊታገል ግድ ይላል!)። ስለ ጉዳዩ በማብራራትና በመግለፅ ቢሆን እንኳ፣ ኃላፊነት ላላቸው ሰዎች በመደወል፣ ለሃገር መሪዎች መስጅደ-ል-አቅሷን ነፃ እንዲያወጡት በማነሳሳት፣ መስጅደ-ል-አቅሷን ከአይሁዶች እጅ ነፃ በማውጣት ረገድ ይህን ትልቅ ውግዝ ድርጊት በማውገዝ ሙስሊም የሚችለውን ያክል ይታገላል። ከሙስሊሞች ውጭ መስጅደ-ል-አቅሷን ማንም ነፃ አያወጣውም። በጭራሽ! እውነተኛ ሙስሊሞች እንጅ ማንም ነፃ አያወጣውም። ልክ ነቢያችን እንደነገሩን፤ የመጨረሻው ዘመን በሚሆን ጊዜ፤ ሙስሊሞች ይር'ረዳሉ (ድል ይጎናጸፋሉ!) ሙስሊሞች በየሁዶች ላይ ይር'ረዳሉ ብለዋል። መጥፎ አገዳደልን ይገድሏቸዋል። ከነርሱ መካከል አንዳቸው ከድንጋይ ወይም ከዛፍ ጀርባ ቢደበቅ እንኳ፤ አይሁዱ የተደበቀበት ድንጋይ ወይም ዛፍ "አንተ ሙስሊም ሆይ! ከጀርባዬ አይሁድ ተደብቋል! ና ግደለው!" ብሎ ይናገርበታል።…» ★ ኢንሻ አላህ‼ ይህ ወቅት አይርቅም። የፍልስጤም ወንድሞቻችን አንድ ቀን በአላህ ፈቃድ ነፃ ይወጣሉ። በተረፈ እጅግ በጣም ሚዛናዊና ጥበባዊ በሆነ ዕውቀት ተኮር ፈታዋቸው ልባችንን የሚያረጋጉልንን ታላላቅ ዑለማዎቻችንን አላህ ይጠብቅልን። "የሳዑዲ ዑለማዎች እንዲህ ናቸው!" ወዘተ በማለት የምታነውሩ አላህን ፍሩ። ከአላህ ባሮች ጋር ጦርነት የገጠመ ጦርነቱ ከርሱ ጋር ነው! አደብ ያዙ! ረጅም እድሜና ጤና ለሸይኻችን! አላህ ይጠብቃቸው‼ || t.me/MuradTadesse
Show all...
Murad Tadesse (Official Channel)✅☪🇪🇹

ትክክለኛው ኢስላማዊ አስተምህሮ፦ 1) ከቁርኣን፣ 2) ከሐዲሥ፣ [በሰለፎች አረዳድ] 3) ከታማኝ ዑለማዎችና 4) ከትክክለኛ ቂያስ ተጠናቅሮ ይቀርብበታል። √ አዳዲስና ወቅታዊ ኢስላማዊ የሆኑ ጉዳዮችም ይዳሰሳሉ። √ አላማዬ በዲኔ ላይ ያለውን የመረጃ ክፍተት መሙላት ነው። ማንኛውም አስተያዬት ሲኖራችሁ @Murad_Tadesse ላይ አስፍሩልኝ። ስህተትም ባያችሁ ጊዜ አርሙኝ። ጀዛኩሙል`ሏህ ኸይራ!

ገለባ ነው ፈቅዶ ላይጠላ - መርጦ ላይፈቀር፣ ፀሃይ ለማቶጣ - ብጠራት ለማትቀር፣ አለም ለማትሞላ - ሞት ለማይቀር ነገር፣ አንዱም በኔ ላይሆን - ስለምን ልቸገር? ኖሬስ ክፍሌ ነው ብል - መጨነቅ ምኔ ነው፣ ከልክ ያለፈ ሃሳብ - ፍሬው ገለባ ነው!!
Show all...
ነፍስን ማጥራት ይቀድማል። ሁላችንም ለውጥን ከራሳችን እንጀምር። ሞትን ዘውትር እናስታውስ። በርካቶች ድንገት ሲሞቱ እየተመለከትን ፣ መገሰፅና መመለስ አቅቶናል። ህይወታችን ከተግባር ይልቅ በወሬ የተሞላ ሆኗል። አላህ ይምራን
Show all...
ለመናገር ፍልስጤማዊ መሆን አይጠበቅብህም ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው ′′ አላህ ሆይ በፍልስጤም ወንድሞቻችንን ድል አድርግልን
Show all...
🍦🍦ቆይ ግን የት ሁነህ ነው?🍦🍦 የምታስጠብቀኝ መምጣትህ ላይቀር ምታጨናንቀኝ! እሽ ምን ይዞህ ነው ! ምንስ ቢገጥምህ ነው! እድህ ልቤን ሰቅለህ የጠፍሀው የት ነው! ለፍትና ስጋለጥ ቁመህ የምታየኝ! በሰው አፍ ስፍጠጥ የማትገላግለኝ ! መጥተህ ሳስበው የምናየው ሂይወት! ኑረን ነው የምናልፈው የዱኒያውን ጀነት ! በለይሉ ክፍል ላይ ቀድሜ ነቅቸ ! ስቀሰቅስህ ሳይ ውሀህን እረጭቸ! በሚያምረው ውብ ድምፅህ ተሀጁድ ስንሰግድ! ላሂራው ቤታችን ስጠይቅ በሱጁድ በእንባ የታጠበን!ዱአችንን አርገን! በቀረን ደቂቃ ሱሁራችንን በልተን ! ለፈጁሩ ሶላት ስል መስጅድ ሸኝቸህ አለሁ አተ በጀመአ እኔ ደግሞ ቤቴ እጠብቅሀለሁ! ሰኞና ሀሙስ ፃም በጉጉት ጠብቀን ! ለማፍጠሪያ ሚሆን ሚገርም ምግብ ሰርተን ! ቤቱን ፏ አድርጌ እጠብቅሀለሁ! ከስራ መልስ መተህ አብረን እድናፈጥር እጋብዝሀለሁ ! በሀላሉ ብርህ በለፍሀው ጉልበት! ቤቱን ስታሞላ ሀራም ሳትከትበት ! ናፈቀኝ ያ ጊዜ ይሄን የምልበት! ናፈቀኝ ያ ጊዜይሄን የምልበት ! ጁመአ ላይ ደግሞ ውብ ቀናችንን በካፍ በሰለዋት ልናይ! ኢዳችንን ቤት ሰራርቸ ባዘጋጀሁት ላይ! ሰደቃውን ይዘን ስሰጥ ከላይ ከላይ ! በጊዜ ተጥደን ሁጥባን ለማዳመጥ ተትነን ! ስሰማ ስንዘጋጅ ለለውጥ በሀፈዝነው ቁረአን! ሙራጅአ ሳናልፍ ከመግሪብ ኢሻ ወቅት ! በቀን በቀን ሳናርፍ በሚያምር ቅላፄ! እያነበነብን ተፍሲሩን ባግርሞት እየተነተንን! በሚያነሳው ሀሳብ እየተደመምን! ስቀራው ታይቶኛል እየተደሰትን ! የረሱልን ዘመን ወደኋላአይተን ! በነ ኡመር ናፍቆት እየተገረፍን ! ስስለውታይቶኛል እየተገረምን! ዚያራ የሚባል ሳሰለችስንጓዝ ! በብር በስጦታ ሰወችን ስናግዝ! ለዱንያ ተላላ ልባችንን ሳሰጥ ! በአሄራ ጉዳይ ላይ ቢዚ ሁነን ለለውጥ! ልጆችን በአፍያ ወልደን ስናሳድግ! ሀፍዝ አሊም አርገን ስናደርስ ለማእረግ! ተጣልተን ሳንቆይ ሳላኮርፍ ሳታኮርፍ ! ተግባብተን ስፈታ ምንም ስአት ሳንፈጅ! ታየኝ ያጊዜ የምኖረው ሂይወት! ወደ አሏህ ተጠግተን ሳናይ ምንም ጭቀት ! ሙሲባ ሲመጣ በሶብርአሳልፈን ! እኮን ሊያሳስበን በምዳው ተደስተን ! የምናሳልፈው ጊዜኮ ናፈቀኝ እሽ የት! ሁነህ ነውእድህ የጠፍሀው ሀጃህን አሳክተህ ልትመጣ አስበህ ነው እሽ! ጥሩ አርገል እኔም እስማማለሁ በመዘግየትህ ነው ብዙ ተምሪለሁ! አሁን ግን ይበቃል ስአቴን አትፍጀው! ይልቅ ቶሎ ናና ጌታየን ልገረው! ዱአ ተቀባይ ነህ ሰሚነህ ልበለው! ዱአየ ተሳክቶል ብየ ላመስግነው።
Show all...
ሃማስ እና እስራኤል የተኩስ አቁም ስምምነት አደረጉ በእስራኤል መንግሥት እና በፍልስጥኤሙ ታጣቂ ቡድን ሃማስ መካከል የተኩስ አቁም ስምምነት ከትላንት ሀሙስ ጀምሮ ተግባራዊ ተደረገ። ተኩስ አቁሙ ከተተገበረ በኋላ በርካታ ፍልስጥኤማዊያን በጋዛ ጎዳናዎች ላይ ደስታቸውን ለመግለፅ የወጡ ሲሆን አንድ የሃማስ ባለስልጣን ‹‹አሁንም ጥይታችንን እንዳቀባበልን ነው›› ሲሉ ተደምጠዋል። ከመስጊዶች የሚሰሙ የድምፅ ማጉያዎች ‹‹ በእየሩሳሌሙ ሰይፍ› ውጊያ ትግላችን ድል አስገኝቷል›› የሚሉ መልክቶችን አስተጋብተዋል። ሁለቱም አካላት በፍልሚያው አሸናፊነታቸውን አውጀዋል። የአሜሪካው ፕሬዘዳንት ጆ ባይደን የተኩስ አቁሙ ‹‹ለለውጥ ሃቀኛ እድል የሚሰጥ ነው›› ሲሉም ስምምነቱን ገልፀውታል። ለ11 ቀናት የቆየው ይህ ግጭት እስካሁን የ240 ሰዎችን ሕይወት የቀጠፈ ሲሆን አብዛኛው ህልፈት የተመዘገበው በጋዛ ነው። በግጭቱ 100 ሴቶች እና ህፃናትን ጨምሮ 232 ሰዎች በጋዛ ህይወታቸውን አጥተዋል። እስራኤል ከዚህ ውስጥ ቢያንስ 150 ያህሉ ተዋጊዎች ናቸው ብላለች። ሃማስ እስካሁን ድረስ የሞቱ ተዋጊዎቹን ቁጥር ይፋ አላደረገም። ትላንት ሃሙስ ብቻ እስራኤል 100 የሚጠጉ የአየር ጥቃቶችን በተለይም በሰሜናዊ ጋዛ ያሉ ሃማስ ይጠቀምባቸዋል ባለቻቸው መሰረተ ልማቶች ላይ የፈፀመች ሲሆን ሃማስ በአፀፋው ሮኬት ተኩሷል። በእስራኤል በተያዙ ምስራቃዊ የኢየሩሳሌም አካባቢዎች ለሳምንታት እየጋለ የሄደው ውጥረት ከ11 ቀናት በፊት ወደ ውጊያ ማደጉ ይታወሳል። የእስራኤል የፖለቲካ ካቢኔ የተኩስ አቁሙን ሃሳብ በሙሉ ድምፅ ማፅደቁን ገልጿል። አክሎም ‹‹ የፖለቲካ ክፍላችን የዘመቻው ቀጣይነት የሚወሰነው በመሬት ላይ ባለው ሁኔታ ነው ሲል አፅንኦት ሰጥቷል›› ሲልም አክሏል። የእስራኤሉ የመከላከያ ሚኒስቴር ቢኒ ጋንትስ የጋዛው ጥቃት ‹‹ያልተጠበቁ ትርፎችን አስገኝቶልናል›› ሲሉ በትዊተር ገፃቸው ላይ አስፍረዋል። አንድ የሃማስ ባስልጣን ለአሶሺየትድ ፕረስ እንደገለፁት እስራኤል የተኩስ አቁም ማድረጓ እንደትልቅ ድል የሚቆጠር እና ይህም ለእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤኒያሚን ኔታኒናሁ ሽንፈት ነው ብለዋል። ነገር ግን በሃማስ ዓለም አቀፍ ግንኙነት ምክር ቤት አባል የሆኑት ባሴም ናይም ስለተኩስ አቁሙ ዘላቂነት ጥርጣሬ እንዳላቸው ለቢቢሲ ተናግረዋል ። ‹‹ለፍልስጥኤማዊያን ፍትህ ሳይመጣ፣ እስራኤልን ወረራዋን እና በእየሩሳሌም በሕዝባችን ላይ የምትፈፅመውን የጭካኔ ተግባር ሳታቆም የሚደረግ የተኩስ አቁም ጠንካራ መሰረት አይኖረውም›› ብለዋል። የሃማስ የፖለቲካ ቢሮ አባል ኢዛት አል-ረሺቅ ለእስራኤል ማስጠንቀቂያ ሰጥተዋል። "እርግጥ ነው ውጊያው ዛሬ ቆሟል። ነገር ግን ኔታኒያሁ እና መላው ዓለም እጃችን በተቀባበለው ጠብመንጃችን ላይ መሆኑን እና ትግላችንም ተጠናክሮ እደሚቀጥል ማወቅ አለባቸው›› ሲሉ ለሮይተርስ የዜና ወኪል ተናግረዋል ። ‹‹ለኔታኒያሁ እና ለሰራዊቱ መግለፅ የምንፈልገው ከተመለሳችሁ እኛም እንደምንመለስ እወቁ ›› ሲሉ አክለዋል።
Show all...