cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

ኢትዮ መረጃ - NEWS

ኢትዮጵያን መውደድ ባትችል አትጥላት ማክበር ባትችል አታዋርዳት ማራመድ ባትችል አታዘግያት መጠበቅ ባትችል አትበትናት። ይህን በማድረግ ታሪክ ባትሠራም ታሪክ አታበላሽም። ለአስታየት @ethio_merjabot @biruke_promotion

Show more
Advertising posts
58 444
Subscribers
+1024 hours
-327 days
+12330 days
Posting time distributions

Data loading in progress...

Find out who reads your channel

This graph will show you who besides your subscribers reads your channel and learn about other sources of traffic.
Views Sources
Publication analysis
PostsViews
Shares
Views dynamics
01
ጌታቸው ረዳ‼️ “ በየጊዜው ወጣቶች የምገብርበት የጦርነት ምዕራፍ መዘጋት አለበት “ - አቶ ጌታቸው ረዳ የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ በክልሉ ኮሚኒኬሽን ቢሮ በኩል ዛሬ መልዕክት አሰራጭተው ነበር። በዚህም ፤ “ የህዝባችን ሁለንተናዊ መብትና ጥቅም ከማረጋገጥና አስተማማኝ ከማድረግ የሚቀድም ሌላ አጀንዳ የለንም “ ብለዋል። “ የህዝባችን ጥቅምና መብት የሚያረጋግጥ መንገድ ሁሉ እንጓዘዋለን “ ያሉት አቶ ጌታቸው “ ጉዞው እንዲሳካ የህዝቡ ተሳትፎ ወሳኝ ነው “ ሲሉ አክለዋል። ፕሬዜዳንቱ ፤ “ ከሚገባው በላይ ያበረከተ ህዝብ በቅንነትና ታማኝነት ማገለገል ይገባል “ ሲሉም ገልጸዋል። “ ህዝቡ ከጦርነትና ጦርነት ወለድ ችግሮች በማላቀቅ ወደ አስተማማኝ ሰላም እንዲሸጋገር መስራት ይገባል “ ሲሉም አስገንዝበዋል። አቶ ጌታቸው ረዳ ፤ “ በየጊዜው ትኩስ ሃይል የሆኑትን ወጣቶች የምንገብርበት የጦርነት ምዕራፍ ተዘግቶ ፤ የልማትና የእድገት ፍላጎታችን እንዲሳካ መስራት አለብን “ ብለዋል።
4 5601Loading...
02
በምሥራቅ ወለጋ ዞን ሁለት ጭንቅላት ያለው ህጻን ተወለደ። በኦሮሚያ ምሥራቅ ወለጋ ዞን ሲቡ ሲሬ ወረዳ ትላንት ከቀኑ 10 ሰዓት ላይ አንዲት እናት በተደረገላት የቀዶ ህክምና ከአንገት በላይ ሁለት ጭንቅላት (Dicephalic parapagus) ያለው ወንድ ልጅ፤ ክብደቱ 4.2 ኪ.ግ የሚመዝን በሰላም ተገላግላለች። ልጁ የተወለደው በሲሬ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ውስጥ ሲሆን በሆስፒታሉ የህጻናት ሀኪም የሆኑት ዶ/ር ቶኩማ ባይሳ የልጁን ቀጣይ ህይወት ለመወሰን ወደ ከፍተኛ ሆስፒታል ሪፈር እንዲደረግ መወሰኑን ገልጸዋል። ዶ/ር ቶኩማ አክለውም፥ እናትየው የመጀመሪያ ልጇ እንደሆነ ጠቅሰው አሁን ላይ በጥሩ ጤንነት ላይ እንዳለች ገልጸዋል። ዘገባው የወረዳው ኮሚኒኬሽን ቢሮ ነው።
6 80417Loading...
03
"አንዱ ሰለ ሁሉ ሞተ።" (2ኛ ቆሮ ም. 5:14) ለመላው የክርስትና ዕምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለጌታችን ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የስቅለት በዓል በሰላም አደረሳቹ። አደረሰን። በዓሉ የሰላም፣ የፍቅርና የመተሳሰብ ይሁንልን።
6 4509Loading...
04
በአቃቂ የገበያ ማዕከል ትናንት ምሽት በደረሰ የእሳት አደጋ 16 ንግድ  ሱቆች ወደሙ ሚያዚያ 24 ቀን2016  ዓ.ም ምሽት 3:10 ሰዓት ላይ በአቃቂ ቃሊቲ ክ/ከተማ  ወረዳ 03 አቃቂ የገበያ  ማዕከል በተነሳ የእሳት አደጋ 16 የንግድ ሱቆች ሙሉ በሙሉና በከፊል መውደማቸውን የእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አስታውቋል። የእሳት አደጋዉን  ለመቆጣጠር አምስት የአደጋ መቆጣጠር ተሽከርካሪ ሁለት የዉሀ  ቦቴ  የተሰማራ ሲሆን እሳቱ ወደገበያ ማዕከሉ ተስፋፎቶ በሰዉና በንብረት ላይ የከፋ ጉዳት ሳይደርስ መቆጣጠር መቻሉን የኮሚሽኑ የህዝብ ግንኙነትና ባለሙያ አቶ ንጋቱ ማሞ ለብስራት ሬድዮ እና ቴሌቪዥን ተናግረዋል። አደጋዉን ለመቆጣጠር ሁለት ሰዓት ፈጅቷል። በአደጋ መቆጣጠሩ ሂደት የፌደራልና የአዲስ አበባ ፖሊስ አባላት ከፍተኛ ድጋፍ ያደረጉ ሲሆን በሰው  ላይ የደረሰ ጉዳት  የለም። አቃቂ የገበያ ማዕከል ትንሹ መርካቶ እየተባለ የሚጠራ የገበያ ማዕከል ሲሆን ገበያ ማዕከሉ በከተማ ደረጃ ለእሳት አደጋ ተጋላጭ ተብለዉ ከተለዩ አንዱ ነው። በገበያ ማዕከሉ በተደጋጋሚ የእሳት አደጋ እያጋጠመ በንብረት ላይ ጉዳት ሲደርስ መቆየቱንም አቶ ንጋቱ ጨምረው ነግረውናል።ኮሚሽኑ ገበያ ማዕከሉ ለአደጋ የተጋለጠባቸዉን ዝርዝር ጉዳዮችን የመፍትሄ ሀሳቦችን አካቶ ለገበያ ማዕከሉ ማህበራትና ለሚመለከታቸዉ አካላት ከዚህ ቀደም ያቀረበ ቢሆንም የማስተካከያ እርምጃዎች አልተወሰዱም። በመሆኑም በቀጣይ መሰል አደጋዎች እንዳያጋጥሙ መፍትሄ መስጠት አስፈላጊ መሆኑን ኮሚሽኑ አሳስቧል። ዳጉ_ጆርናል
7 1591Loading...
05
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ማስተር ካርድ ለአምስት ዓመት የሚቆይ የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረሙ። ዛሬ ሚያዝያ 23 ቀን 2016 ዓ.ም በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ዋናው መስሪያ ቤት በተደረገው በዚሁ ስምምነት የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሚሰጠውን የካርድ ባንክ አገልግሎት በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገራት ለማስፋፋት እንደሚያግዘው ተነግሯል። በተጨማሪም አዳዲስ የካርድ አገልግሎቶችን ለማስጀመር እንደሚረዳም ተጠቁሟል።በዚህ የአምስት አመት ሰምምነት መሰረት የባንኩን ደንበኞች ፍላጎት በማሟላት ላይ የሚያተኩሩ እና አለም የደረሰበትን አዳዲስ አገልግሎቶችን በሀገር ውሰጥ በማስተዋወቅ ጥሬ ገንዘብ አልባ ማህበረሰብን ለመፍጠር ለሚደረገው ጥረት ከፍተኛ አስተዋጽዎ እንደሚያደርግ ይገመታል። ማስተር ካርድ ከ210 ሀገሮች በላይ የሚሰራ አለማቀፍ የክፍያ አቀላጠፊ ድርጅት ሲሆን ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጋር መስራት ከጀመረ እረጅም አመታት እንደሆነ ይታወቃል።
7 1810Loading...
06
They predicted yesterday the DUMP of Bitcoin Already in the channel published the dates of the next BTC PUMP! Click 👉 CHECK NEXT PUMP DATES 👈 Click 👉 CHECK NEXT PUMP DATES 👈 Click 👉 CHECK NEXT PUMP DATES 👈 JOIN FAST! Only the first 1000 people will be accepted! 🔥
7 1640Loading...
07
ተፈታች‼️ አርቲስት አዲስአለም ጌታነህ ከ21 ቀናት እስር በኋላ ዛሬ ተፈታለች። @sheger_press @sheger_press
7 8104Loading...
08
ተጨማሪ‼️ ሊቀ ማእምራን ብርሃኑ ተክለ ያሬድን ጨምሮ ሁለት የማኅበረ ቅዱሳን አመራሮች ታሠሩ በቅርቡ የደቡብና ምዕራብ አፍሪካ አህጉረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ ሆነው የተመደቡት ሊቀ ማእምራን ብርሃኑ ተክለ ያሬድ በዛሬው ዕለት ከጠዋቱ 12:00 በፌዴራል ፖሊስ ለጥያቄ ይፈለጋሉ በሚል ከቤታቸው ተወስደው መታሠራቸውን ቤተሰቦቻቸው ለሚዲያችን ገልጸዋል። በተያያዘ ዜና በኢትዮጵያ ኦርትዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደረጃ መምሪያ ማኅበረ ቅዱሳን ሰብሳቢ ሊቀ ትጉሃን ቀሲስ ዶ/ር ሙሉጌታ ስዩም እና የማኅበረ ቅዱሳን ዋና ጸሐፊ መምህር ዋሲሁን በላይ ዛሬ ሚያዚያ 24 ቀን 2016 ዓ.ም ከመኖሪያ ቤታቸው በጸጥታ አካላት መወሰዳቸውን የማኅበረ ቅዱሳን ብሮድካስት አገልግሎት ዘግቧል። @sheger_press @sheger_press
7 9554Loading...
09
ያሳዝናል‼️ ምጥ ይዟት ወደ ሆስፒታል እየሄዱ የነበሩ ሶስት የአንድ ቤተሰብ አባላት እና አንድ ጎረቤትን ጨምሮ የ4 ሰዎች ህይወት በትራፊክ አደጋ ህይወታቸው አለፈ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን የትራፊክ አደጋ መከላከል መረጃና ስታቲክስ ክፍል ኃረፊ ኢንስፔክተር ታምራት ደሳለኝ እንደገለፁት በሀዲያ ዞን ሾኔ ከተማ አስተዳደር ማዞሪያ ቀበሌ ሌሊት 11 ሰዓት 40 ከወላይታ ሶዶ ወደ አዲስ አበባ ይጓዝ የነበረ ፒካፕ መኪና በተቃራኒ አቅጣጫ ከሚጓዝ ባለሶስት እግር ባጃጅ ጋር ተጋጭቶ በውስጡ የነበሩ 3 የአንድ ቤተሰብ አባላት እና አንድ ጎረቤት በድምሩ የ4 ሰዎች ህይወት ማለፉን ተናግረዋል። በ2 ሰዎች ላይ ደግሞ ከባድ ጉዳት ደርሶባቸው የህክምና እርዳታ እየተደረገላቸው ነው። ከሟቾቹ መካከል ምጥ ይዟት ወደ ሆስፒታል እያመራች የነበረች እናት እንደምትገኝበት ነው ኢንስፔክተር ታምራት የገለጹት። የአደጋው መንስኤ በመጣራት ላይ መሆኑንም ኢንፔክተር ታምራት ጠቁመዋል።
8 5953Loading...
10
#ሰበር በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደረጃ መምሪያ ማኅበረ ቅዱሳን ሰብሳቢ ሊቀ ትጉሃን ቀሲስ ዶ/ር ሙሉጌታ ስዩም እና የማኅበረ ቅዱሳን ዋና ጸሐፊ መምህር ዋሲሁን በላይ ዛሬ ሚያዚያ 24/2016 ዓ.ም ከመኖሪያ ቤታቸው በጸጥታ አካላት መወሰዳቸው ታውቋል። የሁለቱ አገልጋዮች መኖሪያ ቤት መፈተሹም ተገልጿል። በአሁኑ ሰዓት ሜክሲኮ ፌዴራል ፓሊስ የወንጀል ምርመራ ቢሮ የሚገኙ ሲሆን የተያዙበት ምክንያት አልታወቀም። ምንጭ፦ የማህበረ ቅዱሳን የፌስቡክ ገፅ
8 7440Loading...
11
መንግሥት ያቋቋመው ብሄራዊ ኮሚቴ ትናንት ሳዑዲ ዓረቢያ ውስጥ በአስቸጋሪ ኹኔታ ላይ የነበሩ 1 ሺህ 180 ኢትዮጵያዊያን ፍልሰተኞችን መልሷል። ትናንት ከተመለሱት ፍልሰተኞች መካከል፣ 1 ሺህ 98ቱ ወንዶች፣ 79ኙ ሴቶች እንዲኹም ሦስቱ ጨቅላ ሕጻናት እንደኾኑ የሴቶችና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚንስቴር ባሠራጨው መረጃ አስታውቋል። 228ቱ ተመላሾች ዕድሜያቸው ከአስራ ስምንት ዓመት በታች ዕድሜ ያላቸው ናቸው ተብሏል። ኮሚቴው ከሚያዝያ 4 ጀምሮ እስከ ትናንት በጠቅላላው 13 ሺህ 900 ፍልሰተኞችን ከሳዑዲ ዓረቢያ መልሷል። @ethio_mereja_news @ethio_mereja_news
9 1770Loading...
12
የውጭ ጉዳይ ሚንስትር ደዔታ ምስጋኑ አረጋ የአውሮፓ ኅብረት ካውንስል ኢትዮጵያዊያን ዜጎች ላይ ያሳለፈው የቪዛ ገደብ ውሳኔ "የማይጠቅም ውሳኔ" ነው በማለት ቅሬታቸውን ገልጸዋል። ሚንስትር ደዔታው በ"ኤክስ" ገጻቸው ባሠፈሩት መልዕክት፣ ጉዳዩ በኢትዮጵያና አውሮፓ ኅብረት ግንኙነት ውስጥ "አዋኪ ጉዳይ መኾን ሊኾን አይገባውም" ብለዋል። አውሮፓ ኅብረት የኢትዮጵያ ጠንካራ አጋር መኾኑን የጠቀሱት ምስጋኑ፣ ችግሩ ባስቸኳይ ሊፈታ እንደሚገባው ገልጸዋል። ኅብረቱ በአውሮፓ አገራት ውስጥ የመቆየት ፍቃድ በሌላቸው ኢትዮጵያዊያን ላይ ከጣለው የቪዛ ገደብ በተጨማሪ፣ የዲፕሎማቲክና አገልግሎት ፓስፖርት ያላቸው ኢትዮጵያዊያን ያለ ክፍያ ቪዛ እንዳይሰጣቸው አግዷል። @ethio_mereja_news @ethio_mereja_news
9 0381Loading...
13
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል መንግስት የትንሳኤ በዓል ምክንያት በማድረግ ለ926 ታራሚዎች ይቅርታ አደረገ የክልሉ ፍትህ ቢሮ ሃላፊ አቶ እሸቱ ጎዴቶ እንደገለጹት÷ የክልሉ የይቅርታ ቦርድ በይቅርታ አዋጅ፣ ደንብና መመሪያ መሰረት መስፈርቱን የሚያሟሉ ታራሚዎችን ከመንግስት፣ ከህዝብና ከታራሚ ጥቅም አኳያ ሲመረምር ቆይቷል። በተደረገው ምርመራም በአጠቃላይ የይቅርታ ጥያቄ ካቀረቡ 978 ታራሚዎች መካከል መስፈርቱን ያሟሉ 926 ታራሚዎች ጥያቄያቸው ለክልሉ መንግስት ቀርቦ የይቅርታ ተጠቃሚ እንዲሆኑ መደረጉን ተናግረዋል። የይቅርታው ተጠቃሚ ከሆኑት መካከል 920 ታራሚዎች ከእስር የሚለቀቁ ሲሆን÷ስድስቱ ደግሞ የእስራት ጊዜያቸው የተቀነሰላቸው ናቸው። ታራሚዎቹ በማረሚያ ቤት በነበራቸው ቆይታ በአግባቡ ስለመታረማቸው፣ ስለመታነጻቸውና ስለመልካም ባህሪያቸው ምስክርነት የተሰጠባቸው መሆኑንም አመልክተዋል። @ethio_mereja_news @ethio_mereja_news
9 5130Loading...
14
ጦርነቱን ተከትሎ በአማራ ክልል ስር የተቋቋሙ አስተዳደሮች እስከ ሰኔ 30 መፍትሔ እንደሚያገኙ ጄነራል ታደሰ ተናገሩ የትግራይን ጦርነት ተከትሎ በአማራ ክልል ስር ተጠቅለው የተቋቋሙ አስተዳደራዊ መዋቅሮች እስከ ሰኔ 30/ 2016 ዓ.ም መፍትሔ እንደሚያገኙ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ምክትል ፕሬዚዳንት ጄነራል ታደሰ ወረደ ተናግረዋል። ጄነራል ታደሰ ባለፉት ሁለት ቀናት የፕሪቶሪያ ግጭትን በዘላቂነት የማቆም ስምምነት አተገባበር በተመለከተ የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ከመከላከያ እና ከፌደራል መንግሥት ባለስልጣናት ጋር ያደረጉትን ውይይት መሰረት በማድረግ ዛሬ በሰጡት መግለጫ ነው ይህንን የተናገሩት። የአማራ ክልል ይገባኛል በሚላቸው እና የትግራይን ጦርነት ተከትሎ ክልሉ ጠቅልሎ እንደ አዲስ ያዋቀራቸው የደቡብ ትግራይ እና ጸለምቲ ወረዳዎች መፍትሄ ለማበጀት እስከ ግንቦት 30/2016 ዓ.ም የጊዜ ሰሌዳ ስምምነት ላይ መደረሱን ጄነራል ታደሰ ገልጸዋል። በተጨማሪም በአማራ ክልል በኩል ወልቃይት ተብሎ በሚጠራው ምዕራብ ትግራይ እንደ አዲስ የተቋቋመው አስተዳደር እስከ ሰኔ 30 ባለው ጊዜ መፍትሔ ይበጅለታል ብለዋል። በዚህም ውይይት ላይ ትጥቅ መፍታትን አስመልክቶ የትኞቹ አስተዳዳራዊ መዋቅሮች መፍረስ እንዳለባቸው እና የተፈናቀሉ ዜጎች እንደሚመለሱ ዝርዝር እቅድ የወጣ ሲሆን ይህንንም የሚቆጣጠረው እና የሚያረጋግጠው የአፍሪካ ኅብረት የስምምነት ክትትል አረጋጋጭ እና አስከባሪ ኮሚቴ እንደሚሆን ተገልጿል። ኮሚቴው መቀለ ላይ ቢሮ እንዳለው ከዚህ ቀደም ጄነራል ታደሰ መናገራቸው ይታወሳል።     
9 3291Loading...
15
ኢሰመጉ፣ መንግሥት በኦሮሚያና አማራ ክልሎች የመንግሥት ጸጥታ ኃይሎችና ታጣቂ ቡድኖች የሚፈጽሟቸውን "ግድያዎች"፣ "ሕገወጥ እስሮች" እና "ድብደባዎች" እንዲያስቆምና ወንጀል ፈጻሚዎችን ለፍርድ እንዲያቀርብ አዲስ ባወጣው መግለጫ ጠይቋል። የመንግሥት ጸጥታ ኃይሎች ሚያዚያ 6 እና 7 በምሥራቅ ወለጋ ዞን ሰቡ ሲሬ ወረዳ 14 ነዋሪዎችን፣ ታጣቂዎች ደሞ በምዕራብ አርሲ ሽርቃ፣ ቃርሳ እና ኢተያ ወረዳዎች 5 ሰዎች መግደላቸውን ኢሰመጉ ገልጧል። የፌደራሉና የክልል መንግሥታት በሰላማዊ ዜጎች ላይ የሚፈጸሙ “አፈናዎችን” እንዲያስቆሙና “የሰዎችን በነጻነት የመንቀሳቀስ መብት" እንዲያስከብሩም ኢሰመጉ ጥሪ አድርጓል። የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ መርማሪ ቦርድም፣ አማራ ክልል ውስጥ የሚፈጸሙ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችን በማጣራት ወንጀለኞችን በሕግ እንዲጠየቁ ለመንግሥት የውሳኔ ሃሳብ እንዲያቀርብ ኢሰመጉ ጠይቋል። @ethio_mereja_news @ethio_mereja_news
10 0810Loading...
16
ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ፣ በአዲስ አበባ የመንገድ ኮሪደር ልማት አፈጻጸም ዙሪያ ዛሬ ከከተማ አስተዳደሩ አመራሮች እና የኮሪደር ልማት ሥራው አስተባባሪዎች ጋር መምከራቸውን አስታውቀዋል። ዐቢይ፣ የከተማዋ የመንገድ ኮሪደር ልማት በከተማዋ የላቀ ምቹ እና ዘላቂ የመኖሪያ ከባቢ የመፍጠር ጥረቶች እንደሆኑ ገልጸዋል። ፕሮጀክቱ፣ አረንጓዴ ልማትን በማስፋትና መሰረተ ልማቶችን በማሻሻል የሕዝቡን ጤና ለመጠበቅና የስራ ዕድል ለመፍጠር እንደሚያስችልም ዐቢይ ጠቅሰዋል። ጠቅላይ ሚንስትሩ፣ ካንድ ወር በፊት የኮሪደር ልማቱ በሚገኝበት ደረጃ ዙሪያ ከከተማዋ አስተዳደር ሃላፊዎች ጋር አጠቃላይ ግምገማ ማድረጋቸው አይዘነጋም። @ethio_mereja_news @ethio_mereja_news
10 7440Loading...
17
ሹመት‼️ ርእሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ ለአብን ከፍተኛ አመራር ሹመት ሰጡ! የአማራ ክልል ርእሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) ከፍተኛ አመራር ለሆኑት ለአቶ መልካሙ ፀጋዬ ሹመት ሰጥተዋል። ርእሰ መሥተዳድሩ አቶ መልካሙ ጸጋዬን የክልሉ ባሕል እና ቱሪዝም ቢሮ ኃላፊ አድርገው መሾማቸውን በብልጽግና ፓርቲ የአማራ ክልል ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት መረጃ አመላክቷል።
11 2251Loading...
18
የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር፣ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የአገራዊ ምክክር ኮሚሽኑን ማቋቋሚያ ሲያጸድቅ ትግራይ አልተወከለችም የሚል ቅሬታ ማቅረቡን ኮሚሽኑ እንደገለጠ ሸገር ዘግቧል። የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ይህን ቅሬታ ያቀረበው፣ ኮሚሽኑ ከጊዜያዊ አስተዳደሩ ርዕሰ መስተዳድር ጌታቸው ረዳ ጋር በተወያዩበት ወቅት እንደሆነ ዘገባው አመልክቷል። የኮሚሽኑ አንዱ ኮሚሽነር ዶ/ር ዮናስ አዳዬ ግን፣ በወቅቱ ሕወሃት በሂደቱ አልተሳተፈም ማለት ትግራይ አልተወከለችም ማለት አይደለም በማለት ለጣቢያው ተናግረዋል። ኮሚሽኑ እስካሁን በትግራይ ክልል በይፋ ሥራ እንዳልጀመረ ይታወቄል። ኮሚሽነር ዶ/ር ዮናስ አያይዘውም፣ በተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች አመራሮችና አባላት ላይ የሚፈጸሙ እንግልቶች እንዲቆሙ ኮሚሽን ለመንግሥት ጥያቄ ማቅረቡን ገልጠዋል። @ethio_mereja_news @ethio_mereja_news
11 0102Loading...
19
የአዉሮፓ ህብረት ፤ "የኢትዮጵያ መንግስት ለአመታት በህብረቱ አባል ሀገራት ዉስጥ በህገወጥ መንገድ የኖሩ ዜጎቹን ለመመለስ ቸልተኛ ነበር" ሲል ኢትዮጵያዊያን ቪዛ የሚያገኙበትን መንገድ አጠበቀ የኢትዮጵያ ዲፕሎማቶች እና ባለስልጣናት አሁን ለጉዞ ቪዛ መክፈል አለባቸውም ተብሏል የአዉሮፓ ህብረት ፤ የኢትዮጵያ መንግስት ለአመታት በህብረቱ አባል ሀገራት ዉስጥ በህገወጥ መንገድ የኖሩ ዜጎቹን ለመመለስ ቸልተኛ ነበር ሲል ወቅሷል። በዚህም የተነሳ ኢትዮጵያዊያን ቪዛ የሚያገኙበትን መንገድ ማጥበቁን አስታዉቋል። ዳጉ ጆርናል ከአሶሴትድ ፕረስ ዘገባ እንደተመለከተው ፤ የአውሮፓ ህብረት ዋና መስሪያ ቤት ለኢትዮጵያውያን ዜጎች ቪዛ ለመስራት የሚፈጅባቸዉን ጊዜ በሶስት እጥፍ መጨመሩን ነዉ። ከዚህ ቀደም ኢትዮጵያዊያን በ15 ቀናት ዉስጥ ቪዛ ያገኙ ነበር የተባለ ሲሆን በዚሁ ዉሳኔ መሰረት ወደ 45 ቀናት ከፍ እንዲል ተደርጓል። ይህም የኢትዮጵያ መንግስትን በህገወጥ መንገድ በአዉሮፓ ይኖራሉ የተባሉ ዜጎችን እንዲመልስ ጫና ለመፍጠር ነዉ ብሏል ዘገባው። ወደ ኢትዮጵያ እንዲመለሱ ከታዘዙ ሶስት ሰዎች መካከልም አንዱ ብቻ መመለሱ በህብረቱ የመንግስትን ተባባሪነት ጎድሎታል የሚለዉን ክስ ለማሳያነት ቀርቧል። ይህም በፈቃዳቸዉም ይሆን ካለፍላጎታቸዉ ህገወጦችን ለመመለስ የሚደረገዉን ሂደት አጓቶታል ብሏል። በዚህ ዉሳኔ መሰረትም የኢትዮጵያ ዲፕሎማቶች እና ባለስልጣናት አሁን ለጉዞ ቪዛ እንዲከፍሉ ይገደዳሉ መባሉን ዳጉ ጆርናል ከዘገባው ተመልክቷል። አብዛኞቹ ኢትዮጵያዊያን የቪዛ ቀናቸዉም ቢያልፍ የአዉሮፓ ምድርን ለቅቀዉ እንደማይወጡ ህብረቱ ገልጿል። @sheger_press @sheger_press
11 0888Loading...
20
የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና የሚሰጥበት ቀን ይፋ ሆነ። የ2016 የትምህርት ዘመን የኢትዮጵያ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ (12ኛ ክፍል) ፈተና የሚሰጥበት ቀን ይፋ ሆኗል። የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ከሐምሌ 3 እስከ ሐምሌ 5 ለማህበራዊ ሳይንስ ፤ ከሐምሌ  9 እስከ ሐምሌ 11/2016 ዓ/ም ለተፈጥሮ ሳይንስ ተፈታኞች በበይነ መረብ (Online) እና በዩኒቨርሲቲ ውስጥ በወረቀት ይሰጣል። በወረቀት ላይ የሚፈተኑ የማህበራዊ ሳይንስ ተፈታኞች ከሰኔ 30 እስከ ሐምሌ 01/2016 ዓ/ም እንዲሁም የተፈጥሮ ሳይንስ ከሐምሌ 6 እስከ 7/2016 ዓ/ም ወደ ዩኒቨርስቲ የሚገቡ ይሆናል።  መረጃው የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ነው። @sheger_press
10 98957Loading...
21
የአውሮፓ ህብረት #ለኢትዮጵያውያን በጊዜያዊነት ወደ አውሮፓ የመግቢያ ቪዛ ፈቃድ መከከሉን አስታወቀ‼️ ለዚህ ውሳኔ መነሻው ከመንግስት በቂ ትብብር እያገኘሁ ባለመሆኑ ነው ብሏል። የአውሮፓ ህብረት ምክር ቤት ለኢትዮጵያውያን በጊዜያዊነት ወደ አውሮፓ የመግቢያ ቪዛ ፈቃድ መስጠት የሚከልክል ውሳኔ አሳለፈ። ለክልከላው የሰጠው ምክንያት ከኢትዮጵያ መንግስት በቂ ትብብር እያገኘሁ ባለመሆኑ ነው ብሏል። በተጨማሪም የአውሮፓ ህብረት ኮሚሽን እዚህ ውሳኔ ላይ ያደረሰው በህብረቱ ሀገራት በህገወጥነት በሚቆዩ ኢትዮጵያውያን ዜጎች ዙሪያ ከሀገሪቱ መንግስት በቂ ትብብር እያገኘሁ ባለመሆኑ ነው ብሏል። በዚህም የህብረቱ ለአባል ሃገራት ከዚህ በኋላ ኢትዮጵያውያን ቪዛ አመልካቾች ቪዛ ሲፈልጉ - አስፈላጊ ሰነዶችን እንዲያቀርቡ እና በአውሮፓ ህብረት ህግ የተቀመጠውን መደበኛ መስፈርቶች እንዲያሟሉ እንደሚገደዱ ተጠቁሟል። ውሳኔው ለምን ያክል ግዜ እንደሚቆይ ያለው ነገር የለም፤ መደበኛው ቪዛ ለማግኘት የሚጠበቀው የ15 ቀን ጊዜ ወደ 45 ቀን አራዝሞታል። ይህ ውሳኔ የተወሰነው የህብረቱ ምክር ቤት ባደረገው ግምገማ መሰረት ኢትዮጵያ በህገ-ወጥ መንገድ በአውሮፓ ህብረት የሚቆዩ ዜጎቿን በማስመለስ ረገድ የምታደርገው ጥረት በቂ ባለመሆኑ እንደሆነ ተነግሯል።(Alain)
10 30111Loading...
22
የዩትዩብ ገፃችንን subscribe በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ👇👇 https://youtube.com/@Megenagnadaily?si=hYe79ngYPK8k3nbM
9 3591Loading...
23
በአዲስ አበባ በተከሰተ የጎርፍ አደጋ የ4 ሰዎች ሕይወት አለፈ በአዲስ አበባ ከተማ ዛሬ ንጋት ላይ በጣለው ዝናብ ሳቢያ በተከሰተ የጎርፍ አደጋ በቦሌ ክ/ከተማ ወረዳ 11 ወረገኑ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ የ4 ሰዎች ሕይወት አልፏል። የከተማ አስተዳደሩ ማስተር ፕላናቸውን ያልተከተሉ የወንዝ ዳርቻ ግንባታዎች ሕብረተሰቡን ለጎርፍ አደጋ እንደሚያጋልጡ በጥናት መለየቱ ተገልጿል፡፡ ይህንን የአደጋ ስጋትና ተጋላጭነት በመሠረታዊነት የሚፈቱ ፕላኑን የጠበቁ ዘላቂ የመፍትሄ ሥራዎችን እያከናወነ እንደሚገኝም ተጠቁሟል፡፡ በመሆኑም ተመሳሳይ አደጋዎች እንዳያጋጥሙ ከከተማ አስተዳደሩ እና ከእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን የሚተላለፉ የጥንቃቄ መልዕክቶች ተግባራዊ እንዲደረጉ ጥሪ መቅረቡን የኮሚሽኑ መረጃ ያመላክታል፡፡ ኤፍ ቢ ሲበመዲናዋ በተከሰተ የጎርፍ አደጋ የ4 ሰዎች ሕይወት አለፈ በአዲስ አበባ ከተማ ዛሬ ንጋት ላይ በጣለው ዝናብ ሳቢያ በተከሰተ የጎርፍ አደጋ በቦሌ ክ/ከተማ ወረዳ 11 ወረገኑ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ የ4 ሰዎች ሕይወት አልፏል። የከተማ አስተዳደሩ ማስተር ፕላናቸውን ያልተከተሉ የወንዝ ዳርቻ ግንባታዎች ሕብረተሰቡን ለጎርፍ አደጋ እንደሚያጋልጡ በጥናት መለየቱ ተገልጿል፡፡ ይህንን የአደጋ ስጋትና ተጋላጭነት በመሠረታዊነት የሚፈቱ ፕላኑን የጠበቁ ዘላቂ የመፍትሄ ሥራዎችን እያከናወነ እንደሚገኝም ተጠቁሟል፡፡ በመሆኑም ተመሳሳይ አደጋዎች እንዳያጋጥሙ ከከተማ አስተዳደሩ እና ከእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን የሚተላለፉ የጥንቃቄ መልዕክቶች ተግባራዊ እንዲደረጉ ጥሪ መቅረቡን የኮሚሽኑ መረጃ ያመላክታል፡፡ ኤፍ ቢ ሲ
11 2809Loading...
24
በትግራይ ታጣቂዎች ቁጥጥር ስር በዋሉ የራያ እና አላማጣ አካባቢዎች ህይወት ምን ይመስላል? ካሳለፍነው ሳምንት ጀምሮ የትግራይ ታጣቂዎች ወደ ራያ እና አላማጣ አካባቢዎች መግባታቸውን ተከትሎ የዳግም ጦርነት ስጋት ደቅኗል። የአማራ ክልል በህወሃት ታጣቂዎች ወረራ ተፈጽሞብኛል ቢልም የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳድር ግን ተግሩን እየፈጸሙ ያት የፕሪቶርያ የሰላም ስምምነት ጠላቶች ናቸው ብሏል። የራያ እና አላማጣ አካባቢ ነዋሪዎች በፌደራል መንግስት “ተከድተናል የሚል ስሜት ውስጥ መግባታቸውን” ተናግረዋል። የትግራይ ታጣቂዎች ከአላማጣ 15 ኪሎ ሜት ራዲያስ ውስጥ ሆነው በየቀኑ ተጨማሪ ሀይል እያስገቡ እንደሆነም ነው ነዋሪዎቹ የሚናገሩት። ካሳለፍነው ሳምንት ጀምሮ የትግራይ ታጣቂዎች ወደ ራያ እና አላማጣ አካባቢዎች መግባታቸውን ተከትሎ የዳግም ጦርነት ስጋት ደቅኗል። የአማራ ክልል በህወሃት ታጣቂዎች ወረራ ተፈጽሞብኛል ቢልም የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳድር ግን ተግሩን እየፈጸሙ ያት የፕሪቶርያ የሰላም ስምምነት ጠላቶች ናቸው ብሏል። የራያ እና አላማጣ አካባቢ ነዋሪዎች በፌደራል መንግስት “ተከድተናል የሚል ስሜት ውስጥ መግባታቸውን” ተናግረዋል። የትግራይ ታጣቂዎች ከአላማጣ 15 ኪሎ ሜት ራዲያስ ውስጥ ሆነው በየቀኑ ተጨማሪ ሀይል እያስገቡ እንደሆነም ነው ነዋሪዎቹ የሚናገሩት። @ethio_mereja_news @ethio_mereja_news
11 1632Loading...
25
አትሌት ቀነኒሳ በቀለ አቀባበል ተደረገለት አትሌት ቀነኒሳ በቀለ በሆሳዕና እለት ወደ ሀገሩ ሲገባ በቤተሰቡ፣ በወዳጆቹ ቀነኒሳ ሆቴል አቀባበል ተደረገለት። አትሌት ቀነኒሳ በቀለ በፈታኙ ሎንዶን ማራቶን 2.04.15 በመግባት ሁለተኛ ሆኖ ውድድሩን ማጠናቀቁ ይታወሳል።
12 1725Loading...
26
መወያየት ብቻውን በቂ አይደለም፤ መተግበር አለበት። በኢትዮጵያ መናናቅ እና የት ይደርሳል ማለት ችግር ሲፈጥር እየታየ መሆኑንም መወያየት ብቻውን በቂ አይደለም።ውጤቱ መተግበር ይኖርበታል። እንደ ሀገር የመወያየት ችግር ባይኖርም መሠረታዊ ችግሩ አፈፆፀም ላይ ነው።ኢትዮጵያ ውስጥ ብዙ መስራት ያስፈልጋል።ብዙ ጊዜ የሚስተዋለው  እንወያይ እንጋገር ከማለት የዘለለ አይደለም>> ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የሴቶችን ተሳፎ በተመለከተ በትናንትናው ዕለት ባዘጋጀው የውይይት መድረክ ላይ ተገኝተው ከተናገሩት የተወሰደ @ethio_mereja_news @ethio_mereja_news
11 8950Loading...
27
ሆሳዕና በአርያም 🌴 እንኳን አደረሳችሁ የ “ሆሳዕና በአርያም” በዓል በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ እና በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን አማኞች ዘንድ ዛሬ በድምቀት እየተከበረ ነው፡፡ ሆሳዕና በአርያም ከፋሲካ በፊት ያለው እና የዐቢይ ጾም የመጨረሻው ሣምንት ሲሆን÷ “አቤቱ እባክህ አሁን አድን፣ አቤቱ እባክህ አሁን አቅና፣ በእግዚአብሔር ስም የሚመጣ ብሩክ ነው” የሚሉ ትርጉሞችም እንዳሉት የዕምነቶቹ አባቶች ያስተምራሉ። የዕምነቶቹ ተከታዮች በሆሳዕና በአርያም በዓል መሪው ተመሪውን ዝቅ ማለትን ያስተማረበት እና ተመሪውም የሚመራውን ጨርቁን እያነጠፈ እና ዘንባባ እየጎዘጎዘ ያከበረበት የትህትና እና የፍቅር በዓል ተደርጎ የሚወሰድ ነው፡፡ ሆሳዕና በአርያም ኢየሱስ ክርስቶስ በአህያ ጀርባ ተቀምጦ ወደ ኢየሩሳሌም ሲገባ በተለይም÷ አረጋውያን፣ ሴቶች፣ ወንዶች፣ ወጣቶች እና ሕጻናት “ሆሳዕና ለዳዊት ልጅ፣ ሆሳዕና በዓርያም” በማለት በክብር መቀበላቸው የሚታወስበት በዓል ነው፡፡
11 68218Loading...
28
አማጺው የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት፣ መከላከያ ሠራዊት ምዕራብ ኦሮሚያን "ከበባ ውስጥ በማስገባት ሕዝቡን በጅምላ እየቀጣ ነው" በማለት ከሷል። ኦሮሚያ ክልል የአገሪቱ አብዛኛው ሃብት ምንጭ ናት ያለው አማጺው ቡድን፣ ኾኖም የፌደራሉ መንግሥት "ኦሮሚያን ለረጅም ጊዜ ሙሉ ከበባ ውስጥ ማስገባት አይችልም፤ አይፈልግምም" ብሏል። መንግሥት ከምዕራብ ሸዋ ዞን ጀምሮ በመላው ምዕራብ ኦሮሚያ ባኹኑ ወቅት እየወሰደ ያለው ርምጃ፣ "የአማጺው ቡድን ተዋጊዎች ቤተሰቦችና ቡድኑን ይደግፋሉ ተብለው የሚጠረጠሩ ሰዎች በመንግሥት የሕክምና ጣቢያዎች፣ ትምህርት ቤቶች፣ ፍርድ ቤቶችና የቀብር ቦታዎች አገልግሎት እንዳያገኙ ማድረግ" እንደኾነ ቡድኑ ገልጧል። @ethio_mereja_news @ethio_mereja_news
11 1323Loading...
29
Ready to empower the next generation of learners? Join us on Edtech Mondays for an eye-opening discussion on Financing EdTech Startups in Ethiopia! Discover how investors are igniting innovation and driving change in the education landscape, overcoming unique challenges to support promising ventures. From bridging the digital divide to enhancing learning outcomes, explore the transformative potential of investing in EdTech startups. Tune in and be part of the movement to revolutionize education in Ethiopia! Monday, April 29th at 8:10 pm on Fana FM 98.1 for insights that matter. #EdTechEthiopia #EducationInnovation #JoinTheConversation #Ethiopia #DigitalLiteracy #TechnologyInEducation #EdTechMondaysEthiopia #EquityInEducation #Ethiopia #DigitalLiteracy #ShegaMedia #MastercardFoundation
3 9850Loading...
30
ፈተናው በኦላይን ይሰጣል ተብሏል የ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና በተመረጡ ከተሞች በኦን ላይን ለመስጠት እየተሠራ መሆኑን ተገልጿል። የትምህርት ሚኒስትሩ ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ በአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ምክክር መድረክ ላይ ባደረጉት ንግግር የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና በተመረጡ ከተሞች በኦንላይን ለመስጠት እየተሠራ መሆኑን ገልፀዋል ። የ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ሙሉ በሙሉ በኦንላይን ለመስጠት ባይቻልም በሁሉም ክልሎች በተመረጡ ከተሞች ለመስጠት እየተሠራ መሆኑን ተናግረዋል። በዚህም በሁሉም ክልሎች ያሉ የተመረጡ ተማሪዎች በኦንላይን ፈተናቸውን የሚወስዱ ሲሆን ቀሪዎቹ ደግሞ በተለመደው አግባብ ፈተናቸውን ይወስዳሉም ብለዋል። የሀገር አቀፍ ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር (ዶ/ር) እሸቱ ከበደ በበኩላቸው ፈተናውን በኦንላይን ለመሥጠት የሚያስችል የቅድመ ዝግጅት ሥራ እየተሠራ መሆኑን ገልፀዋል። ተማሪዎች የሙከራ ፈተና የሚለቀቅላቸው ሲሆን ደጋግመው እንዲሞክሩና እንዲለማመዱ ይደረጋልም ከሚኒስቴሩ የተገኘው መረጃ ያመላክታል። ለዚህም እንዲረዳ የአሰልጣኞች ስልጠና በመሥጠት ተማሪዎች ተደጋጋሚ ስልጠና እንደሚሠጣቸውም ዋና ዳይሬክተሩ ገልፀዋል። ከቀጣይ ሳምንት ጀምሮ የአሰልጣኞች ስልጠና መስጠት እንደሚጀምርም በመድረኩ ተገልጿል።
9 83915Loading...
Photo unavailableShow in Telegram
ጌታቸው ረዳ‼️ “ በየጊዜው ወጣቶች የምገብርበት የጦርነት ምዕራፍ መዘጋት አለበት “ - አቶ ጌታቸው ረዳ የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ በክልሉ ኮሚኒኬሽን ቢሮ በኩል ዛሬ መልዕክት አሰራጭተው ነበር። በዚህም ፤ “ የህዝባችን ሁለንተናዊ መብትና ጥቅም ከማረጋገጥና አስተማማኝ ከማድረግ የሚቀድም ሌላ አጀንዳ የለንም “ ብለዋል። “ የህዝባችን ጥቅምና መብት የሚያረጋግጥ መንገድ ሁሉ እንጓዘዋለን “ ያሉት አቶ ጌታቸው “ ጉዞው እንዲሳካ የህዝቡ ተሳትፎ ወሳኝ ነው “ ሲሉ አክለዋል። ፕሬዜዳንቱ ፤ “ ከሚገባው በላይ ያበረከተ ህዝብ በቅንነትና ታማኝነት ማገለገል ይገባል “ ሲሉም ገልጸዋል። “ ህዝቡ ከጦርነትና ጦርነት ወለድ ችግሮች በማላቀቅ ወደ አስተማማኝ ሰላም እንዲሸጋገር መስራት ይገባል “ ሲሉም አስገንዝበዋል። አቶ ጌታቸው ረዳ ፤ “ በየጊዜው ትኩስ ሃይል የሆኑትን ወጣቶች የምንገብርበት የጦርነት ምዕራፍ ተዘግቶ ፤ የልማትና የእድገት ፍላጎታችን እንዲሳካ መስራት አለብን “ ብለዋል።
Show all...
👍 19 5😁 4👎 3🔥 1
በምሥራቅ ወለጋ ዞን ሁለት ጭንቅላት ያለው ህጻን ተወለደ። በኦሮሚያ ምሥራቅ ወለጋ ዞን ሲቡ ሲሬ ወረዳ ትላንት ከቀኑ 10 ሰዓት ላይ አንዲት እናት በተደረገላት የቀዶ ህክምና ከአንገት በላይ ሁለት ጭንቅላት (Dicephalic parapagus) ያለው ወንድ ልጅ፤ ክብደቱ 4.2 ኪ.ግ የሚመዝን በሰላም ተገላግላለች። ልጁ የተወለደው በሲሬ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ውስጥ ሲሆን በሆስፒታሉ የህጻናት ሀኪም የሆኑት ዶ/ር ቶኩማ ባይሳ የልጁን ቀጣይ ህይወት ለመወሰን ወደ ከፍተኛ ሆስፒታል ሪፈር እንዲደረግ መወሰኑን ገልጸዋል። ዶ/ር ቶኩማ አክለውም፥ እናትየው የመጀመሪያ ልጇ እንደሆነ ጠቅሰው አሁን ላይ በጥሩ ጤንነት ላይ እንዳለች ገልጸዋል። ዘገባው የወረዳው ኮሚኒኬሽን ቢሮ ነው።
Show all...
👍 24 3🔥 1
Photo unavailableShow in Telegram
"አንዱ ሰለ ሁሉ ሞተ።" (2ኛ ቆሮ ም. 5:14) ለመላው የክርስትና ዕምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለጌታችን ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የስቅለት በዓል በሰላም አደረሳቹ። አደረሰን። በዓሉ የሰላም፣ የፍቅርና የመተሳሰብ ይሁንልን።
Show all...
63👍 18🥰 2😁 2
Photo unavailableShow in Telegram
በአቃቂ የገበያ ማዕከል ትናንት ምሽት በደረሰ የእሳት አደጋ 16 ንግድ  ሱቆች ወደሙ ሚያዚያ 24 ቀን2016  ዓ.ም ምሽት 3:10 ሰዓት ላይ በአቃቂ ቃሊቲ ክ/ከተማ  ወረዳ 03 አቃቂ የገበያ  ማዕከል በተነሳ የእሳት አደጋ 16 የንግድ ሱቆች ሙሉ በሙሉና በከፊል መውደማቸውን የእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አስታውቋል። የእሳት አደጋዉን  ለመቆጣጠር አምስት የአደጋ መቆጣጠር ተሽከርካሪ ሁለት የዉሀ  ቦቴ  የተሰማራ ሲሆን እሳቱ ወደገበያ ማዕከሉ ተስፋፎቶ በሰዉና በንብረት ላይ የከፋ ጉዳት ሳይደርስ መቆጣጠር መቻሉን የኮሚሽኑ የህዝብ ግንኙነትና ባለሙያ አቶ ንጋቱ ማሞ ለብስራት ሬድዮ እና ቴሌቪዥን ተናግረዋል። አደጋዉን ለመቆጣጠር ሁለት ሰዓት ፈጅቷል። በአደጋ መቆጣጠሩ ሂደት የፌደራልና የአዲስ አበባ ፖሊስ አባላት ከፍተኛ ድጋፍ ያደረጉ ሲሆን በሰው  ላይ የደረሰ ጉዳት  የለም። አቃቂ የገበያ ማዕከል ትንሹ መርካቶ እየተባለ የሚጠራ የገበያ ማዕከል ሲሆን ገበያ ማዕከሉ በከተማ ደረጃ ለእሳት አደጋ ተጋላጭ ተብለዉ ከተለዩ አንዱ ነው። በገበያ ማዕከሉ በተደጋጋሚ የእሳት አደጋ እያጋጠመ በንብረት ላይ ጉዳት ሲደርስ መቆየቱንም አቶ ንጋቱ ጨምረው ነግረውናል።ኮሚሽኑ ገበያ ማዕከሉ ለአደጋ የተጋለጠባቸዉን ዝርዝር ጉዳዮችን የመፍትሄ ሀሳቦችን አካቶ ለገበያ ማዕከሉ ማህበራትና ለሚመለከታቸዉ አካላት ከዚህ ቀደም ያቀረበ ቢሆንም የማስተካከያ እርምጃዎች አልተወሰዱም። በመሆኑም በቀጣይ መሰል አደጋዎች እንዳያጋጥሙ መፍትሄ መስጠት አስፈላጊ መሆኑን ኮሚሽኑ አሳስቧል። ዳጉ_ጆርናል
Show all...
👍 19😭 6👎 1 1
Photo unavailableShow in Telegram
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ማስተር ካርድ ለአምስት ዓመት የሚቆይ የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረሙ። ዛሬ ሚያዝያ 23 ቀን 2016 ዓ.ም በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ዋናው መስሪያ ቤት በተደረገው በዚሁ ስምምነት የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሚሰጠውን የካርድ ባንክ አገልግሎት በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገራት ለማስፋፋት እንደሚያግዘው ተነግሯል። በተጨማሪም አዳዲስ የካርድ አገልግሎቶችን ለማስጀመር እንደሚረዳም ተጠቁሟል።በዚህ የአምስት አመት ሰምምነት መሰረት የባንኩን ደንበኞች ፍላጎት በማሟላት ላይ የሚያተኩሩ እና አለም የደረሰበትን አዳዲስ አገልግሎቶችን በሀገር ውሰጥ በማስተዋወቅ ጥሬ ገንዘብ አልባ ማህበረሰብን ለመፍጠር ለሚደረገው ጥረት ከፍተኛ አስተዋጽዎ እንደሚያደርግ ይገመታል። ማስተር ካርድ ከ210 ሀገሮች በላይ የሚሰራ አለማቀፍ የክፍያ አቀላጠፊ ድርጅት ሲሆን ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጋር መስራት ከጀመረ እረጅም አመታት እንደሆነ ይታወቃል።
Show all...
👍 18 2
They predicted yesterday the DUMP of Bitcoin Already in the channel published the dates of the next BTC PUMP! Click 👉 CHECK NEXT PUMP DATES 👈 Click 👉 CHECK NEXT PUMP DATES 👈 Click 👉 CHECK NEXT PUMP DATES 👈 JOIN FAST! Only the first 1000 people will be accepted! 🔥
Show all...
👍 5 1
Photo unavailableShow in Telegram
ተፈታች‼️ አርቲስት አዲስአለም ጌታነህ ከ21 ቀናት እስር በኋላ ዛሬ ተፈታለች። @sheger_press @sheger_press
Show all...
👍 54 9😁 2
ተጨማሪ‼️ ሊቀ ማእምራን ብርሃኑ ተክለ ያሬድን ጨምሮ ሁለት የማኅበረ ቅዱሳን አመራሮች ታሠሩ በቅርቡ የደቡብና ምዕራብ አፍሪካ አህጉረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ ሆነው የተመደቡት ሊቀ ማእምራን ብርሃኑ ተክለ ያሬድ በዛሬው ዕለት ከጠዋቱ 12:00 በፌዴራል ፖሊስ ለጥያቄ ይፈለጋሉ በሚል ከቤታቸው ተወስደው መታሠራቸውን ቤተሰቦቻቸው ለሚዲያችን ገልጸዋል። በተያያዘ ዜና በኢትዮጵያ ኦርትዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደረጃ መምሪያ ማኅበረ ቅዱሳን ሰብሳቢ ሊቀ ትጉሃን ቀሲስ ዶ/ር ሙሉጌታ ስዩም እና የማኅበረ ቅዱሳን ዋና ጸሐፊ መምህር ዋሲሁን በላይ ዛሬ ሚያዚያ 24 ቀን 2016 ዓ.ም ከመኖሪያ ቤታቸው በጸጥታ አካላት መወሰዳቸውን የማኅበረ ቅዱሳን ብሮድካስት አገልግሎት ዘግቧል። @sheger_press @sheger_press
Show all...
👍 18😭 8👎 5 2
Photo unavailableShow in Telegram
ያሳዝናል‼️ ምጥ ይዟት ወደ ሆስፒታል እየሄዱ የነበሩ ሶስት የአንድ ቤተሰብ አባላት እና አንድ ጎረቤትን ጨምሮ የ4 ሰዎች ህይወት በትራፊክ አደጋ ህይወታቸው አለፈ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን የትራፊክ አደጋ መከላከል መረጃና ስታቲክስ ክፍል ኃረፊ ኢንስፔክተር ታምራት ደሳለኝ እንደገለፁት በሀዲያ ዞን ሾኔ ከተማ አስተዳደር ማዞሪያ ቀበሌ ሌሊት 11 ሰዓት 40 ከወላይታ ሶዶ ወደ አዲስ አበባ ይጓዝ የነበረ ፒካፕ መኪና በተቃራኒ አቅጣጫ ከሚጓዝ ባለሶስት እግር ባጃጅ ጋር ተጋጭቶ በውስጡ የነበሩ 3 የአንድ ቤተሰብ አባላት እና አንድ ጎረቤት በድምሩ የ4 ሰዎች ህይወት ማለፉን ተናግረዋል። በ2 ሰዎች ላይ ደግሞ ከባድ ጉዳት ደርሶባቸው የህክምና እርዳታ እየተደረገላቸው ነው። ከሟቾቹ መካከል ምጥ ይዟት ወደ ሆስፒታል እያመራች የነበረች እናት እንደምትገኝበት ነው ኢንስፔክተር ታምራት የገለጹት። የአደጋው መንስኤ በመጣራት ላይ መሆኑንም ኢንፔክተር ታምራት ጠቁመዋል።
Show all...
😭 56👍 23 5
Photo unavailableShow in Telegram
#ሰበር በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደረጃ መምሪያ ማኅበረ ቅዱሳን ሰብሳቢ ሊቀ ትጉሃን ቀሲስ ዶ/ር ሙሉጌታ ስዩም እና የማኅበረ ቅዱሳን ዋና ጸሐፊ መምህር ዋሲሁን በላይ ዛሬ ሚያዚያ 24/2016 ዓ.ም ከመኖሪያ ቤታቸው በጸጥታ አካላት መወሰዳቸው ታውቋል። የሁለቱ አገልጋዮች መኖሪያ ቤት መፈተሹም ተገልጿል። በአሁኑ ሰዓት ሜክሲኮ ፌዴራል ፓሊስ የወንጀል ምርመራ ቢሮ የሚገኙ ሲሆን የተያዙበት ምክንያት አልታወቀም። ምንጭ፦ የማህበረ ቅዱሳን የፌስቡክ ገፅ
Show all...
👍 19😭 16👎 4 2