en
Feedback
Abdurahim Ahmed

Abdurahim Ahmed

Open in Telegram

📈 Analytical overview of Telegram channel Abdurahim Ahmed

Channel Abdurahim Ahmed (@abdure99) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 10 773 subscribers, ranking 8 356 in the Religion & Spirituality category and 3 084 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 10 773 subscribers.

According to the latest data from 30 August, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by -62 over the last 30 days and by 0 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 0%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects N/A% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 0 views. Within the first day, a publication typically gains 0 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 0.

📝 Description and content policy

Channel description not provided.

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 31 August, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Religion & Spirituality category.

10 773
Subscribers
No data24 hours
-137 days
-6230 days
Posts Archive
ኡምራ ፓኬጅ የምታዘጋጁ አንዳንድ ድርጅቶች ሶሻል ሚዲያ ላይ በሚሰሩት ያፈነገጠ ድርጊቶች ለታወቁ ሰዎች እየከፈላችሁ ማስታወቂያ የምታሰሩ እባካችሁ ተው ይህ ተግባር ትክክል አይመስለኝም ። እነዚህን ወንድም እህቶች ''እየሰራችሁ ያለው ነውር ጥሩ ነው በርቱ እያላችሁ '' በገንዘብም ጭምር እየደገፋችሁ መሆኑን ታውቋችኋል ወይ ? በቃ ብዙ ተመልካች ስላላቸው ብቻ ከፍላችሁ ማስታወቂያ ታሰራላችሁ ? ኡምራ ማለት'ኮ እጅግ ትልቅ የሆነ ወደ አላህ መቃረቢያ የሆነ ታላቅ አምልኮ ተግባር ነው ። ሸአኢረል ኢስላም የእስልምና ትልቅ ምልክት ነው ። ኡምራ ስናከናውን ሶውፍ ተራራ ላይ ስንደርስ "إِنَّ الصَّفَا وَالْمَرْوَةَ مِن شَعَائِرِ اللَّهِ. ሶፋና መርዋ ከአላህ (ትዕዛዝ መፈጸሚያ) ምልክቶች ናቸው፡፡.... እንላለን ። የአላህ ዲን የሆኑ ምልክቶች እጅግ የተከበሩ ናቸው ። እናም እባካችሁ ተው ይቅርባችሁ። በስነ-ምግባር የወረዱ ሰዎችን ማስታወቂያ የምታሰሯቸው ከዚያ ድርጊታቸው እንዲመለሱ እድል ልትፈጥሩላቸው ቢሆን ጥሩ ነበር ። አሳዛኙ ነገር በዚያው ነውራቸው መካከል ላይ ኡምራውንም እንዲያስተዋውቁ ማድረጋችሁ ነው ። ተው ግዴላችሁም ወንድሞቼ እህቶቼ ኸይር ነገር እየሰራችሁ በበደል አትቀላቅሉ ። አላህ ሁላችንንም ያስተካክለን (አብዱረሂም አህመድ)

አቤ ቶክቻው ለሰጠኸኝ እውቅና አመሰግናለሁ Abebe Tolla Feyisaአቤ ቶክቼው ሃቅ እና ሳቅ የተመሰረተበትን 11ኛ ዓመቱን አስመልክቶ ባከበረበት ሰዓት ስምህን በመልካም አንስቷል ብሎ ወንድሜ ሸምሱ ነገረኝ ። እኔም ቪዲዮውን አየሁት እና ተገርምኩ ። በድምጻችን ይሰማ ትግላችን ውስጥ ትግላችን ሲደግፉ ከነበሩ መካከል ነው ። የዛሬ አስራ አንድ አመት ያሳየሁትን ነገር ይዞ ከ11 ዓመታት በኋላ ሲናገር መስማቴ ለኔ አስደንቆኛል ። የፖለቲካ የሃሳብ ልዩነት ቢኖረንም አመሰግናለሁ ለማለት እወዳለሁ !

ዛሬም ብሩህ ተስፋ አለኝ ! በዚህ ሰዓት ከምንም በላይ ለዲናችን ትልቅ አስተዋጾ ያደርጋሉ ብየ ተስፋ የማደርግባቸው ከምንም በላይ ቅድሚያ ለዲናቸው የሚሰጡ፣የተለየ የቡድንም የሆነ የጀመዓ ፍላጎት የሌላቸው ዑለማዎች፣ምሑራን፣ተማሪዎች፣ነጋዴዎች የግልም የመንግስትም ሰራተኞች፣በሀገር ውስጥም በዲያስፖራውም የሚገኙ ናቸው ። በእለት ከእለት ከተዋጡበት ስራ ባሻገር እንደ ሀገር እንደ ዲን ያለባቸውን ሃላፊነት የሚያስታውሳቸው፣የሚያደራጃቸው፣መደራጀት እንዳለባቸው መንገዱን የሚጠቁማቸው ካገኙ አትጠራጠሩ እጅግ ምርጦች ሞልተዋል። ጥቂቶች እድል አግኝተን ስለተናገርን፣ስለታየን፣ስለተሰማን፣ቦታ ስለያዝን ሀገሩ ሰው የሌለው እንዳይመስለን ። እድሉን ያገኘነው አላህን ፈርተን አማናችንን እንወጣ ። እድሉን ያላገኛችሁ ከላይ የጠቀስኳቸው ትልቅ ሃላፊነት እንዳለባችሁ ተገንዘባችሁ ማንም እስኪጋብዛችሁ አትጠብቁ። ተንቀሳቀሱ ተነቃነቁ ፣ንቁ አነቃቁ ኢንሻአላህ በጥቂት አጋጣሚዎች አስተውያለሁ ። ለሀገራቸው ለዲናቸው ያላቸው ሞራላቸው ወኒያቸው ለኛም የሚጋባ ጭምር ነው ። አላህ ይጠብቃችሁ !

photo content

“ልጄ እስከ ሃያ ሰባት ዓመት እድሜው ድረስ ልጄ በእውቀት ያገኘው ነገር ከእኔ በሺሕ እጥፍ ይበልጣል፡፡ ሐፊዘል ቁርኣን ነው። ዐረብኛ ቋንቋ ያውቃል። ከኢማም ሙሐመድ ቢን ሱኡድ ዩኒቨርሲቲ ተመርቋል። አላህ ካልረዳው ግን ሁሉም ነገር ከንቱ ነው። እንዲህ እለዋለሁ፡- «የአላህን ርዳታ ማግኘት ይኖርብሀል። ያ በጣም በላጩ ነገር ነው:: የምሥክር ወረቀት ለመጨረሻው ዓለም ምንም ዋጋ የለውም። በምሥክር ወረቀት ምን ታደርጋለህ? የአላህን ርዳታ ለማግኘት ብቸኛው መንገድ ጠንክሮ _ መትጋት እና የምትወዳቸውን ነገሮች ለአላህ ስትል መስዋዕት ማድረግህን ማረጋገጥ ነው፡፡›› ልጆቼ የአላህን ርዳታ ለማግኘት የሚተጉ እንዲያደርጋቸው ሁልጊዜም አላህን እለምነዋለሁ። «አላህ ቢረዳችሁ ለእናንተ አሸናፊ የለም። ቢያዋርዳችሁም ያ ከርሱ (ማዋረድ) በኋላ የሚረዳችሁ ማነው በአላህም ላይ ብቻ ምእምናን ይመኩ።› ምሥጋና ለዓለማት ጌታ ለአላህ ይገባው። ዶክተር ዛኪር ናይክ የሕይዎት ታሪኬ ከጉልድፍ አንደበት እስከ ዳዒነት ከሚለው መፅሃፍ የተወሰደ

photo content

ራዕይ አለኝ ----------- ሩቅ ምጡቅ የማይደርቅ እንከን አለ ተብሎ የማይገታ ካምላክ የተሰጠኝ ስጦታ ራዕይ አለኝ እኔ ብርሃን እንዲሆን ዘመኔ የምፈጽመው በመጥኔ ነሐሴ 28/1995 የጻፍኩትን ግጥም የድሮ ፋይሎች ሳገላብጥ ያገኘሁት ነው ። የዛሬ 22 ዓመት ስምንተኛ ክፍል እያለሁ የተፃፈ ነው :: ዛሬም ራዕይ አለኝ :: ወደ ፊት ለመራመድ አንዳንዴ ወደ ኋላ መንደርደር ያስፈልጋል ! ኢንሻአላህ በአላህ እገዛ ይሳካል :: ጉዟችን ወደፊት ነው::

አሰላሙ አለይኩም ወራህመቱሏሂ ወበረካቱሁ ውድ ወንድሞቼ እና እህቶቼ ዛሬ ጁምዓ ነው:: የዱዓ ቀን ነው :: አደራ የምላችሁ ከምንም በላይ የናንተ ዱዓ የሚያስፈልገኝ ወቅት ላይ ነኝ :: አሏህ (ሱ.ወ) ፅናቱን ብርታቱን እንዲለግሰኝ ! በያዝኩት ኸይር ስራ ላይ ፀንቼ በእሱው ተወክየ የተሻለ ኸይር ስራ ከወንድሞቼ እህቶቼ ጋር እንድሰራ ዱዓ አድርጉልኝ :: ከምንም በላይ ኢኽላሱን እንዲወፍቀን ከልብ ነይታችሁ ዱዓ አድርጉልኝ ! በማወቅም ይሁን ባለማወቅ ላስከፋሁት ሁሉ አውፍታ እጠይቃለሁ --- አሏሁመ ኢኒ አኡዙቢከ ሚነል ሀሚ ወሚነል ሀዘን ወአዙቢኪ ሚነል አጅዚ ወሚነል ከሰል ወአኡዙቢከ ሚነል ጁብኒ ወሚነል ቡኹል ወአኡዙቢከ ሚን ኸለበቲ አድ ደይኒ..ወቃህሪ ሪጃል

photo content

12ተኛ ክፍል ጨርሰው ለሚንከራተቱ ወጣቶች የውጭ የትምህርት እድል ሲያመቻች የነበረው የሙስሊም ወጣቶች ማህበር =============================== ያለፈን ጊዜ ገጽታ ለመረዳት በወቅቱ ይጻፉ የነበሩ ነገሮችን ማንበብ፣ሰዎችን መጠየቅ አንዱ መንገድ ነው ። ሰሞኑን በ1980ዎቹ ይታተሙ የነበሩ መጽሄቶችን ሳገላብጥ የማነበው ነገር እጅግ የሚያስገርም እና የሚያስደምም ሁኖ አግኝቼዋለሁ ። በሰዓቱ የነበሩ ኡለማዎች፣ምሁራን ምን ያህል ተራማጅ እንደነበሩ አርቆ አሳቢነታቸውን ጭምር ያስታውልኩበት ነው ። ምናልባት በአንዳንድ ጉዳዮች ላይ በዚህ ዘመን ራሱ የነሱን ያህል ሰፋ ያለ ራዕይ አለን ወይ ? ብየ ለማሰብ በግሌ እቸገራለሁ ። ለአብነት ያህል በ1980ዎቹ በሀገራችን ገነው ከነበሩ ማህበራት መካከል አንዱ የኢትዮጵያ ሙስሊም ወጣቶች ማህበር (ሙነዘማ ) አንዱ ነበር ። በሸይኽ ሰዒድ አህመድ ሙስጠፋ ይመራ የነበረው ይህ ታላቅ ማህበር በርካታ ተግባራትን ያከናወነ፣በሀገራችን የተለያዩ ቦታዎችም ላይ ቅርንጫፍ የነበረው ማህበር ነው ። ካስደነቁኝ ተግባራቱ መካከል ለዛሬ አንዱን ላካፍላችሁ ። ሙነዘማ በሰዓቱ በሶስት ቋንቋዎች በአማርኛ፣በእንግሊዝኛ እና በአረብኛ ያሳትመው የነበረ ዳዕዋ የተሰኘ መጽሄት ነበረው ። መጽሄቱ በሁለተኛ እትሙ ላይ ማህበሩ ያከናወናቸውን ተግባራት በተመለከተ ባወጣው ዜና ላይ እንዲህ ይላል ። የኢትዮጵያ ሙስሊም ወጣቶች ድርጅት ካሉት ዓላማዎች መካከል አንዱ እና ዋነኛው የሙስሊሙን ሁለተናዊ ግንዛቤ ማስፋት እና ለሀገር ግንባታ የበኩላቸውን አስተዋጾ እንዲያበርክቱ ማዘጋጀት ነው ። ይህንኑ ዓላማ በተግባር ለመተርጎም ወጥኖ ከያዛቸው ፕሮግራሞች መካከል የ12ተኛ ክፍል ፈተና አጠናቀው የሚንከራተቱ ወጣቶችን ለመርዳት ና የሙስሊም ምሁራንን ቁጥር ለማበርከት ከተለያዩ ዓለም አቀፍ ዩንቨርስቲዎች ጋር በመጻጻፍ ተማሪዎች የውጭ የትምህርት እድል እንዲያገኙ አድርጓል። በዚህም ጥረቱ 22 ተማሪዎችን ወደ ተለያዩ ቦታዎች አወዳድሮ መላኩ ይታወሳል ። ይህ በንዲህ እንዳለ 44 ወንዶች እና 11 ሴቶች በድምሩ 55 ወጣት ተማሪዎች በተመሳሳይ ሁኔታ የውጭ የትምህርት እድል እንዲያገኙ በማድረግ ሰሞኑን ለጉዞ በማዘጋጀት ላይ ይገኛል ይላል ። ---- ልብ በሉ ይህ እንግዲህ የዛሬ 30 አመት ገደማ የነበረው የኢትዮጵያ ሙስሊም ወጣቶች ማህበር ሲሰራ ከነበረው ስራ አንዱ ነው ። ዛሬ በዚህ ደረጃ ከፍ ያለ ውጥን ወጥነን እየሰራን ነው ወይ ? የሚለውን ራሳችንን እንጠይቅ ። በነገራችን ማህበሩ እንደዛ እያደረገ ወደ ውጭ ሲልካቸው የነበረው ዩንቨርስቲ መግባት ያልቻሉት ባክነው እንዳይቀሩ ነው ። ዛሬስ የት ነን ? የተማረው ቁጥር ከትላንት ዛሬ ቁጥሩ በርክቷል ። ከዚህ መካከል ለትውልዱ፣የትምህርት እድል፣የስራ እድል ላላገኘው የሚጨነቀው የትኛው ነው ? ከራሳችን አልፈን ለሌሎች ብርሃን እንሁን ። ከትላንት ከፍ እንበል ! የተቋቋመው የወጣቶች ካውንስል መሰል ስራዎችን ተጠናክሮ ይሰራል ብለን ተስፋ እናደርጋለን (አብዱረሂም አህመድ)

photo content

የአላህን ኒእማ የምናውቀው በደንብ የምናስተውለው ለተወሰነ ጊዜም ቢሆን ስናጣው ነው:: ዛሬ ከተከታታይ ስብሰባዎች መሃል ላይ ድምፄ ተዘጋ ! ጥሩነቱ የጋራ ዓላማ ያለን የሃሩን ሚዲያ ማኔጅመንት ባልደረቦቼ ባህሩ አባስ እና አብዱልመጅድ የሁልጊዜው አጋራችን ጠበቃ ሙስጠፋ በመኖራቸው ቀጥሎ የነበረውን ሂደት ከኔም በተሻለ የመሩት እነሱ ነበሩ ! ተቋም ተተኪ እየፈጠሩ በአላማ የሚተሳሰሩ ወንድሞች ማግኘት መታደል አልሃምዱሊላህ ! አላህ በሰጠን ኒእማ ሁሉ በሚገባ ተጠቅመንበት የምናልፍ ያድርገን ! የሚረዳን እስክናገኝ ቢያደክምም ጉዟችን ይቀጥላል ! አላህ ይርዳን አላህ ያግዘን !

photo content

አላህ ያዘነለት ሰው ሲቀር ይህ ያለንበት ወቅት ፈተናው የበዛበት፣ቁልቁል ወደ ታች መውረድ ቀላል የሆነበት፣ተራራውን ሳይለቁ መቆም ብዙ ዋጋ የሚያስከፍልበት ጊዜ ነው ። ምርኮ የምንከፋፈልበት ጊዜ የደረሰ መስሎን ተራራውን ለቀን የወረድንበት፣በነፍሲያ፣በገንዘብ፣በራስ አምልኮ፣ በእምነት በብሄር ስም የጥቅም ቁርኝነት የተበከልንበት፣ በማስመሰል ራሳችንንም ሌሎችንም እያታለልን ፣ ወንድምን እህትን በመናቅ፣አማና በማጉደል አብዛሃኛዎቻችን በራሳችን ላይ በደል እየፈጸምን ያለንበት ወቅት ነው። ሌላው ላይ ጣት መቀሰርንጅ እኔስ ምን ላይ ነኝ ብለን ራሳችንን ማየት ያቆምንበት ሰዓት ነው። ትስስራችን የሊላህ ሳይሆን የጥቅም የሆነበት፣እሴት እና መርህ ሳይሆን ጥቅም አሳድጅነት የተካንበት ሁኗል።ሌላው ላይ ጣት ከመቀሰር ባሻገር ለዚህ ዲን ለሀገራችን እኔስ በአግባቡ ድርሻየ ምንድን ነው ? የሚለውን ለይተን አድምተን መስራት የተውንበት፣እስልምና የሁላችን ነገር ግን ማንም የሌለው የሆነበትም ዘመን ነው። ዱንያስ ዱንያ ነው እንዲሁ እንዳልን እናልፋለን። የሚያሳስበው አኺራ ላይ ምንም የላችሁም መባል ከምንም በላይ ያስፈራል። አላህ (ሱ.ወ) ሁላችንንም አላህ እንዲያስተካክለን እማጸነዋለሁ።ከዚህ ፈተና ነጃ እንዲለን ዱዓ እንተዋወስ ! --- ቴሌግራም ቻናሌን ጆይን በማድረግ እንወያይ እንመካከር https://t.me/abdure99

በሙስሊሙ ጉዳይ እንዲሁም በሀገራችን ጉዳይ ላይ የሚያሳስቡኝን ጉዳዮች ብንሰራባቸው፣ብንመክርባቸው ብየ የማስባቸውን ጉዳዮች ከፌስቡክ ባሻገር ቴሌግራም ላይም በጽሁፍም በድምጽም ጭምር አንዳንዴ ለማቅረብ የናንተንም ወርቃማ ሃሳቦች ግብአት ለመውሰድም እንዲያመች የቴሌግራም ቻናሌን ጆይን እንድታደርጉሌሎችንም እንድትጋብዙልኝ በአክብሮት እጋብዛለሁ አብዱረሂም አህመድ ነኝ https://t.me/abdure99

photo content
+7

ትግሉ የፅኑዎች ነው ! የታል ጽናታችን ? ጽናት በፈተና ብቻ ሳይሆን በድሎት ጊዜ ጭምር ነው ። (ኮመንት የምትጽፉ በጥሩ ኒያ ስሜታችሁን ተቆጣጥራችሁ ኒያችሁን አስተካክላችሁ መፍትሄ የምትሉትን ጻፉ ፣በማንም ላይ ድንበር እንዳታልፉ ) ከሚገባው በላይ ዋጋ የተከፈለበትን ብዙዎች ሸሒድ የሆኑበትን (ሸሂድነታቸውን አላህ ይቀበላቸው) እልፎች የተገረፉበትን፣የተሰደዱበትን ዋጋችንን አናራክሰው አናሳንሰው ይህ ጥቂት ከፊት ለመጡ መድረክ ላይ ለወጡ ብቻ ሳይሆን ለሁላችን የምጠይቀው ጥያቄ ነው ። ምሑራኖቻችን የታላችሁ ? ዛሬም ከዳር ሁናችሁ እየታዘባችሁ እየተቻችሁ እያማችሁ ትቀጥላላችሁ ወይስ በምትችሉት አሻራችሁን ታሳርፋላችሁ ? ዑለማዎቻችን ዛሬም እንደ ትላንት ይቀጥላል ወይስ የተደናገረውን ዑማ የኡማ አማናችሁን ትወጣላችሁ የፌድራል፣የክልል መጅሊሶች ከታችም ያላችሁ ዛሬም ለወንበር ትሻኮታላችሁ ወይስ አላህ ፊት የምትጠይቁበትን አማና ትወጣላችሁ ? ብሔርተኞች ከዲናችሁ ብሔራችሁን አስቀድማችሁ፣ከዚያም አለፍ ሲል በጎጥ ተከፋፍላችሁ በዚያው ትራኮታላችሁ ወይስ አላህን ፈርታችሁ ለነገ ቤታችሁ ትሰራላችሁ ? ብሔርተኝነት ሲባል ሁሉንም ይመለከታል ዛሬም ሁሉ በየጎጡ ተወሽቋል ። በፈተና ላይ ወድቋል ህዝቡስ መሪውን ይታዘዛል በቻለው ድርሻውን ይወጣል ? ወይስ ዛሬም ከላይ ያሉትን እየረገመ፣እያማ ይቀጥላል በየቢሮክራሲው፣በየተቋማቱ ያላችሁ፣ነጋዴዎች፣ ተማሪዎች እንደ ሀገር አሻራችንን እናሳርፋለን ወይስ እንቀልዳለን ? ሁላችንም ያገኘነውን እድል ተጠቅመን እንደ ሀገር ሚናችንን እንወጣለን ወይስ ?!! ሀገር እየፈረሰ እየተሰራ ነው :: ትርክት እየተሻረ እየተቀየረ ነው :: ለዚህ የኔ ድርሻ ይኼ ነው ብለን ሚናችንን እንወጣለን ወይስ እንቀልዳለን ? ማሳረጊያየ ጥያቄየን ለሁላችንም የሱረቱ ተካሱር የቁርዓን አንቀጽ ላድርግ ثُمَّ لَتُسْـَٔلُنَّ يَوْمَئِذٍ عَنِ ٱلنَّعِيمِ : ከዚያም ከድሎታችሁ ሁሉ በዚያ ቀን ትጠየቃላችሁ፡፡ እስኪ አስተያየት የምንሰጥ ሰዎች በጨዋነት አላህን ፈርተን በጥሩ ኒያ አስተያየታችንን እንፃፍ ለውይይት ኮመንት ተከፍቷል በአደብ በስርአት ኮመንት ለሚፅፍ ተፈቅዷል ሌላ ነገር ለሚፖስት አደብ ጥሶ የሚሳደብ ድንበር የሚያልፍ ይባረራል :: በጥሩ ኒያ እንወያይ (አብዱረሂም አህመድ)

በቅርቡ ሳዑዲ የሚኖሩ አንድ ወዳጄ ጋር ስንጨዋወት የሚያስገርም ነገር ነገሩኝ። በአሁኑ ጊዜ በቡና ኤክስፖርት፣ሃላል ስጋ ለማቅረብ ራሱ ደንበኞችን እንዲያገናኟቸው ፣ሳኡዲ መጥተው ኢንቨስት ለማድረግ የሚጠይቋቸው ሙስሊም ያልሆኑ ነጋዴዎች እንደሆኑ አጫወቱኝ ። ሙስሊም ነጋዴዎች ደግሞ ኡምራ ተደራጅተው ይመጣሉ። ቤተሰቦቻቸውንም ይዘው ሄዳሉ ማሻአላህ አላህ ይጨምርላቸው ። ነገር ግን ለኡምራ ከፍተኛ ቅንጡ ሆቴሎችን በመያዝ ከፍተኛ ገንዘብ ያወጣሉ።ትልልቅ ውድ ሱቆች ሾፕ በማድረግ ይፎካከራሉ። በቅርቡ አንድ ወንድማችን ለረመዷን መጨረሻዎቹ ቀናት ከ80 ሺ ዶላር በላይ ወጪ እንዳወጣ ሰምቻለሁ። ያላቸውን ገንዘብ አላህ ይባርክላቸው ፡። አላህ ይጨምርላቸው ። ከመሆኑም ጋር ግን ራሳችሁን የበለጠ በሁሉም መስክ ራሳችሁን ማሳደጉ ላይም ብትሰሩ። ሌሎች ተደራጅተው ረዥም ርቀት እየሄዱ ነው። ብታስቡበት ለማለት ያህል ነው ። (አብዱረሂም አህመድ)

photo content