en
Feedback
Addis Standard Amharic

Addis Standard Amharic

Open in Telegram

አዲስ ስታንዳርድ በጃኬን አሳታሚ ኃ.የተ.የግ.ማ. ባለቤትነት ስር የሚታተም በኢትዮጵያ የሚገኝ ነፃ እና ገለልተኛ ሚዲያ ነው። አዲስ ስታንዳርድ አማርኛ የአዲስ ስታንዳርድ እንግሊዝኛ ሕትመት አካል ነው። ፌስቡክ: https://rb.gy/xwxb3 ትዊተር (X)፡ https://rb.gy/34uh4

Show more

📈 Analytical overview of Telegram channel Addis Standard Amharic

Channel Addis Standard Amharic (@addisstandardamh) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 20 446 subscribers, ranking 11 287 in the News & Media category and 1 690 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 20 446 subscribers.

According to the latest data from 08 September, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 573 over the last 30 days and by 14 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Verified (Officially confirmed by Telegram)
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 20.32%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 12.21% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 4 153 views. Within the first day, a publication typically gains 2 496 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 0.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
“አዲስ ስታንዳርድ በጃኬን አሳታሚ ኃ.የተ.የግ.ማ. ባለቤትነት ስር የሚታተም በኢትዮጵያ የሚገኝ ነፃ እና ገለልተኛ ሚዲያ ነው። አዲስ ስታንዳርድ አማርኛ የአዲስ ስታንዳርድ እንግሊዝኛ ሕትመት አካል ነው። ፌስቡክ: https://rb.gy/xwxb3 ትዊተር (X)፡ https://rb.gy/34uh4”

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 09 September, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the News & Media category.

20 446
Subscribers
+1424 hours
+797 days
+57330 days
Posts Archive
በ #ኬንያ በሆስፒታሎች የሥራ ጫና በመጨመሩ ምክንያት ሐኪሞች ነርሶች የጀመሩትን የሥራ ማቆም አድማ ለመቀላቀል አስጠነቀቁ በኬንያ የሚገኙ ሐኪሞች ስድስተኛ ሳምንቱን በያዘው የነርሶች የሥራ ማቆም አድ
በ #ኬንያ በሆስፒታሎች የሥራ ጫና በመጨመሩ ምክንያት ሐኪሞች ነርሶች የጀመሩትን የሥራ ማቆም አድማ ለመቀላቀል አስጠነቀቁ በኬንያ የሚገኙ ሐኪሞች ስድስተኛ ሳምንቱን በያዘው የነርሶች የሥራ ማቆም አድማ ምክንያት በሆስፒታሎች ውስጥ ከፍተኛ የሥራ ጫና እንደበዛባቸው በመጥቀስ፣ አድማውን ለመቀላቀል ማክሰኞ ዕለት አስጠነቀቁ። ነርሶቹ የሕብረት ስምምነት (CBA) እንዲተገበርላቸው ጥያቄ በማቅረብ ላይ ይገኛሉ። ይህ ስምምነት ከስድስት ወራት አድማ በኋላ በፈረንጆቹ 2017 የተፈረመ ቢሆንም፣ የመንግስት የበጀት እጥረት አለብኝ በሚል ምክንያት እስካሁን ሳይተገበር ቆይቷል። የኬንያ የሐኪሞች ማህበር ዋና ጸሐፊ ዶክተር ዳቭጂ ቢምጂ አተላህ ማክሰኞ ዕለት እንደገለፁት፣ ሐኪሞች ከመጠን በላይ የሥራ ጫና እንደወደቀባቸው እና "የነርሶችን ሥራ መሥራት አይችሉም" ብለዋል። ሆስፒታሎች ቀደም ሲልም የሐኪሞች እጥረት እንደነበረባቸው እና የጤናው ዘርፍ የተቀናጀ የቡድን ሥራን እንደሚፈልግ ገልጸዋል። ዶክተሩ በኤክስ (X) ገጻቸው ላይ ባሰፈሩት መልእክት፣ "ሕይወታችንን ሙሉ ለማገልገል የቆምንለት የጤና ስርዓት እንዲዳከም በዝምታ አንመለከትም። የአንዱ የጤና ዘርፍ አካል ሲጎዳ ሁላችንም እንጎዳለን፤ አንድ ላይ ስንቆም ደግሞ ታካሚዎቻችንን በጋራ እንጠብቃለን" ብለዋል። https://www.facebook.com/share/p/19BgrySiVq/

ዜና: በደቡብ ምስራቅ #ትግራይ በተፈጸመ የድሮን ጥቃት የአንዲት ሁለት ዓመት ህፃንን ጨምሮ የሶስት ሰዎች ህይወት አለፈ በደቡብ ምስራቅ ትግራይ ህንጣሎ ወረዳ ፍሬወይኒ አቅራቢያ በሚገኘው ማይሹመት አ
ዜና: በደቡብ ምስራቅ #ትግራይ በተፈጸመ የድሮን ጥቃት የአንዲት ሁለት ዓመት ህፃንን ጨምሮ የሶስት ሰዎች ህይወት አለፈ በደቡብ ምስራቅ ትግራይ ህንጣሎ ወረዳ ፍሬወይኒ አቅራቢያ በሚገኘው ማይሹመት አካባቢ በተፈጸመ የድሮን ጥቃት የአንዲት ሁለት ዓመት ህፃንን ጨምሮ የሶስት ሰዎች ህይወት ማለፉን እና አራት ሰዎች መቁሰላቸውን ትግራይ ቴሌቪዥን ዘገበ። ጥቃቱ ጳጉሜን 3 ቀን 2018 ዓ.ም. ከሌሊቱ 8፡00 ሰዓት ገደማ የተፈጸመ ሲሆን፣ የወረዳው አስተዳዳሪ ጎይቶም ተስፋይ የሲቪል መኖሪያ አካባቢ ሲሉ የገለጹት ስፍራ መምታቱን ተናግረዋል። አስተዳዳሪው ለትግራይ ቴሌቪዥን እንደገለጹት ጥቃቱ የሶስት ሰዎችን ህይወት የቀጠፈ ሲሆን በአራት ሰዎች ላይ ደግሞ ጉዳት አድርሷል። https://addisstandard.com/Amharic/?p=14030

#የአቡ ዳቢ ብሔራዊ የነዳጅ ኩባንያ ከገልፍ ቀጠና ውጭ ያለውን እንቅስቃሴ ለማስፋፋት በአፍሪካ ትልቁ የነዳጅ ማጣሪያ ውስጥ ድርሻ ለመግዛት እያሰበ ነው። ቢዝነስ ኢንሳይደር በዘገባው የአቡ ዳቢ ብሔራ
#የአቡ ዳቢ ብሔራዊ የነዳጅ ኩባንያ ከገልፍ ቀጠና ውጭ ያለውን እንቅስቃሴ ለማስፋፋት በአፍሪካ ትልቁ የነዳጅ ማጣሪያ ውስጥ ድርሻ ለመግዛት እያሰበ ነው። ቢዝነስ ኢንሳይደር በዘገባው የአቡ ዳቢ ብሔራዊ የነዳጅ ኩባንያ ከፋርስ ባሕረ ሰላጤ ውጭ እንቅስቃሴውን ለማስፋፋት በአፍሪካ ትልቁ የነዳጅ ማጣሪያ ውስጥ ድርሻ ለመግዛት እያለመ መሆኑን የገለጸ ሲሆን የድፍድፍ ነዳጅ ደንበኞችን ለማፍራት እና የነዳጅ ንግድ እንቅስቃሴውን ለማስፋፋት በማለም በአፍሪካ እና በታይላንድ ከሚገኙ ዋና ዋና የነዳጅ ማጣሪያ ኩባንያዎች ጋር በንግዶቻቸው ላይ ኢንቨስት ለማድረግ የሚያስችል ውይይት እያደረገ እንደሚገኝ ከጉዳዩ ጋር ቅርበት ያላቸው ሰዎች ገልጸዋል። እነዚህ እጩ ኢንቨስትመንቶች በምርት መጠኑ በዓለም 12ኛው ትልቅ የነዳጅ ኩባንያ ለሆነው ለADNOC አዲስ አቅጣጫን የሚያመለክቱ ናቸው፤ ኩባንያው ለዓለም አቀፍ የነዳጅ ገበያዎች ምርት ለማቅረብ በዋነኝነት በተባበሩት አረብ ኤምሬትስ በሚገኘው ግዙፉ የሩዋይስ ማጣሪያው ላይ ይተማመን ነበር። የኩባንያ ወደ ተለያዩ አገራት ማስፋፋቱ አዳዲስ ደንበኞችን እንዲያገኝ፣ የንግድ እንቅስቃሴውን እንዲያጠናክር እና በፋርስ ባሕረ ሰላጤ በሚገኙ ክዋኔዎች ላይ ያለውን ጥገኝነት እንዲቀንስ ያስችለዋል ተብሎ ይጠበቃል። የብሉምበርግ ዘገባ እንደሚያመልክተው ኩባንያው ከዚህ ቀደም የናይጄሪያን በርሜሎች ጨምሮ የአፍሪካን ጥሬ ነዳጅ ለንግድ ዓላማ የገዛ ሲሆን፣ እንደ ኬንያ እና ኢትዮጵያ ላሉ ገበያዎች እንደ ዲዜል እና ቤንዚን ያሉ የተጣሩ ምርቶችን ሲያቅርብ ቆይቷል። https://www.facebook.com/100076048904470/posts/1103702045508082/?mibextid=rS40aB7S9Ucbxw6vl

የእርዳታ መቋረጥ በ #ሱዳን የሚገኙ ክሊኒኮች እንዲዘጉ በማስገደዱ ሚሊዮኖችን የህክምና አገልግሎት ማጣታቸውን የሃኪሞች ቢድን አስጠነቀቀ ዓለም አቀፉ ድንበር የለሽ ሀኪሞች ቡድን (MSF) የዓለም አቀ
የእርዳታ መቋረጥ በ #ሱዳን የሚገኙ ክሊኒኮች እንዲዘጉ በማስገደዱ ሚሊዮኖችን የህክምና አገልግሎት ማጣታቸውን የሃኪሞች ቢድን አስጠነቀቀ ዓለም አቀፉ ድንበር የለሽ ሀኪሞች ቡድን (MSF) የዓለም አቀፍ እርዳታ መቋረጥ በሱዳን የሚገኙ የጤና ተቋማት እንዲዘጉ ማስገደዱን ገለጸ። ይህም በሀገሪቱ በቀጠለው ጦርነትና የሰብዓዊ ቀውስ መካከል በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ሰዎች የህክምና አገልግሎት እንዳያገኙ ማድረጉን ድርጅቱ አስጠንቅቋል። ቡድኑ ባወጣው መግለጫ በመቶዎች የሚቆጠሩ ክሊኒኮች እየተዘጉ፣ ሆስፒታሎች የማስተናገድ አቅማቸውን እያጡ እና የመድኃኒት እጥረት በከፍተኛ ሁኔታ እየተከሰተ መሆኑን አስታውቋል። በሱዳን ከ33 ሚሊዮን በላይ ሰዎች የሰብዓዊ እርዳታ የሚያስፈልጋቸው ሲሆን፣ ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት የ2.87 ቢሊዮን ዶላር የሰብዓዊ ምላሽ እቅድ ውስጥ ማሳካት የተቻለው 41 በመቶ ያህሉን ብቻ ነው ብሏል። ድርጅቱ አክሎ እንዳለው በጤና ተቋማት ላይ የሚሰነዘሩ ጥቃቶች ቀውሱን እያባባሱት ይገኛሉ። እንደ ቡድኑ ሪፖርት በ2025 በሱዳን በሚገኙ የህክምና ተቋማት ላይ በተፈጸሙ ጥቃቶች 1 ሺህ 620 ሰዎች የተገደሉ ሲሆን፣ ይህም በዓለም አቀፍ ደረጃ በህክምና ተቋማት ላይ በተሰነዘሩ ጥቃቶች ከሞቱ ሰዎች መካከል 82 በመቶ ድርሻ ይዟል። የጤና አገልግሎቶች መዘጋታቸው አሁንም ክፍት በሆኑ ተቋማት ላይ ያለውን ጫና እየጨመረው መሆኑን ድንበር የለሽ የሀኪሞች ቡዶን ገልጿል። ከጥር እስከ ሚያዚያ 2026 ባሉት ወራት በማዕከላዊ ዳርፉር በሚገኙት የዛሊንጌ እና ሮኬሮ በቡድኑ ድጋፍ የሚደረግላቸው ተቋማት የታካሚዎች ቁጥር ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር በ22.5 በመቶ ጨምሯል። https://www.facebook.com/share/p/18Jn7ZiJdn/

የሁቲ ታጣቂዎች በደቡባዊ #ሳዑዲ_ዓረቢያ ላይ በሰነዘሩት ጥቃት 73 ሰዎች ቆሰሉ፤ የኃይል አቅርቦት ተቋማትም ተስተጓጎሉ በ #ኢራን የሚደገፉት የ #የመኑ ሁቲ አማፅያን ማክሰኞ ጳጉሜን 3 ቀን 2018
+1
የሁቲ ታጣቂዎች በደቡባዊ #ሳዑዲ_ዓረቢያ ላይ በሰነዘሩት ጥቃት 73 ሰዎች ቆሰሉ፤ የኃይል አቅርቦት ተቋማትም ተስተጓጎሉ በ #ኢራን የሚደገፉት የ #የመኑ ሁቲ አማፅያን ማክሰኞ ጳጉሜን 3 ቀን 2018 ዓ.ም. በደቡባዊ ሳዑዲ ዓረቢያ በሚገኙ የሲቪል እና የኢኮኖሚ ተቋማት ላይ የድሮን እና የሮኬት ጥቃቶችን መሰንዘራቸውን የሳዑዲ ባለስልጣናትን ጠቅሶ ሮይተርስ ዘግቧል። ጥቃቱ የተፈፀመው በአብሃ፣ በካሚስ ሙሻይት፣ በጃዛን እና በናጅራን ከተሞች ላይ ነው። በጥቃቱ ሴቶች እና ህፃናትን ጨምሮ 73 ሰዎች የቆሰሉ ሲሆን፣ በኃይል አቅርቦት ተቋማት ላይ እሳት በመቀስቀሱ ምክንያት በከፊል የነዳጅ እና የኃይል ምርት ስራዎች እንዲስተጓጎሉ አድርጓል። የሳዑዲ ዓረቢያ የኢነርጂ ሚኒስቴር በደቡባዊ የሀገሪቱ ክፍል የሚገኙ ተቋማት በጥቃቱ መጎዳታቸውን አረጋግጧል። በሳዑዲ የሚመራው ጥምረት ጥቃቱን አደገኛ መባባስ ሲል የኮነነው ሲሆን፣ ስጋቱን ለማስወገድ አስፈላጊውን እርምጃ እንደሚወስድ አስታውቋል። https://www.facebook.com/share/p/18PLkKUSzc/

በቱሉ ካፒ የወርቅ ፕሮጀክት በደረሰ የፀጥታ ችግር ምክንያት ኩባንያው ሥራውን አገደ ​የእንግሊዙ ከፊ ወርቅ እና መዳብ ልማት ኩባንያ በርካታ የፀጥታ አካላት፣ የአካባቢው ነዋሪዎች እና አንድ የኩባንያ
በቱሉ ካፒ የወርቅ ፕሮጀክት በደረሰ የፀጥታ ችግር ምክንያት ኩባንያው ሥራውን አገደ ​የእንግሊዙ ከፊ ወርቅ እና መዳብ ልማት ኩባንያ በርካታ የፀጥታ አካላት፣ የአካባቢው ነዋሪዎች እና አንድ የኩባንያው ሰራተኛ ሕይወታቸው ያለፈበትን የፀጥታ ክስተት ተከትሎ በኢትዮጵያ የሚያካሂደውን የቱሉ ካፒ ወርቅ ማውጣት ፕሮጀክት ማገዱን አስታወቀ። ​ኩባንያው ጳጉሜ 2 ቀን 2018 ዓ.ም. ባወጣው መግለጫ አደጋው የተከሰተው ነሐሴ 29 ቀን 2018 ዓ.ም. መሆኑን የገለጸ ሲሆን፣ በሰው ሕይወት መጥፋት በእጅጉ ማዘኑን በመግለጽ ለተጎጂዎች እና ለቤተሰቦቻቸው መጽናናትን ተመኝቷል። ​ከፊ ከአካባቢው የሕብረተሰብ ተወካዮች፣ ከኢትዮጵያ የመንግሥት አካላት እና ከፀጥታ ባለድርሻ አካላት ጋር በመወያየት ደኅንነቱ የተጠበቀ የሥራ አካባቢ እስኪፈጠር ድረስ ሁሉንም የፕሮጀክት ዝግጅት እና ልማት እንቅስቃሴዎች በጊዜያዊነት ማገዱን አስታውቋል። ​ኩባንያው በመግለጫው «የሰራተኞቻችን፣ የኮንትራክተሮች እና የአካባቢው ማህበረሰብ ደኅንነት ለኩባንያችን ከፍተኛው ቅድሚያ የሚሰጠው ጉዳይ ነው» ሲል ገልጾ፣ ደኅንነቱ የተጠበቀ የሥራ ሁኔታ መኖሩ እስካልተረጋገጠ ድረስ ወደ ሥራ እንደማይመለስ አረጋግጧል። ​https://www.facebook.com/share/p/1FZ5egZ7oi/

ሂውማን ራይትስ ዎች #ቢን_ዛይድ #በርሊንን በሚጎበኙበት ወቅት ጀርመን #ኤምሬትስ #በሱዳን ባላት ሚና ላይ ጥያቄ እንድታነሳ አሳሰበ ሂውማን ራይትስ ዎች (HRW) የጀርመን መሪዎች የተባበሩት አረብ
ሂውማን ራይትስ ዎች #ቢን_ዛይድ #በርሊንን በሚጎበኙበት ወቅት ጀርመን #ኤምሬትስ #በሱዳን ባላት ሚና ላይ ጥያቄ እንድታነሳ አሳሰበ ሂውማን ራይትስ ዎች (HRW) የጀርመን መሪዎች የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ ለሱዳን ፈጣን ደጋፊ ኃይሎች (RSF) ታደርጋለች የተባለውን ድጋፍ እና በሀገሯ ያለውን የሰብአዊ መብት አያያዝ የኤምሬትስ ፕሬዝዳንት ሼክ መሐመድ ቢን ዛይድ አል ናህያንን መስከረም 10 ቀን 2026 በርሊንን ከ መጎበኘታቸው አስቀድመው በግልጽ እንዲጠይቁ አሳስቧል። መስከረም 8 ቀን በወጣው መግለጫ፣ ድርጅቱ የጀርመን ቻንስለር ፍሪድሪክ ሜርዝ፣ ፕሬዝዳንት ፍራንክ-ቫልተር ሽታይንማየር እና ሌሎች ከፍተኛ ባለስልጣናት እ.ኤ.አ. ኤፕሪል 2023 በጀመረው የሱዳን ግጭት ውስጥ ኤምሬትስ በፈጸመቻቸው የሰብአዊ መብት ጥሰቶች ላይ ያላትን ሚና በተመለከተ ስጋታቸውን ማቅረብ እንዳለባቸው ገልጿል። ሂውማን ራይትስ ዎች(HRW) መስከረም 1 ቀን የታተመውን የተባበሩት መንግስታት የሐቅ አጣሪ ቡድን ሪፖርት የጠቀሰ ሲሆን፣ ሪፖርቱ ከኤምሬትስ ጋር ግንኙነት ያላቸው መረቦች የውጭ ሀገር ወታደራዊ ተቋራጮችን በመመልመል፣ በመደጎም፣ በማጓጓዝ እና ለRSF የሚጠቅሙ ወታደራዊ ድጋፎችን በማቅረብ ረገድ ተሳታፊ መሆናቸውን ያመለክታል። ኤምሬትስም የቀረበባትን ክስ አስተብላለች። የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ቡድኑ በተጨማሪም እ.ኤ.አ. ሜይ 2026 አገኘዉ ያለዉን መረጃ በመጥቀስ፣ አቡ ዳቢ የሚገኘው ግሎባል ሴኪዩሪቲ ሰርቪስ ግሩፕ በመቶዎች የሚቆጠሩ የኮሎምቢያ የግል ወታደራዊ ተቋራጮችን በመመልመል ከRSF ጎን ቆመው በሱዳን እንዲዋጉ ማሰማራቱን ገልጿል። https://www.facebook.com/share/p/1W96hvGKGJ/?mibextid=wwXIfr

#ኬንያ ሕጋዊ የመኖሪያ ፈቃድ ለሌላቸው #የምስራቅ_አፍሪካ ዜጎች ጊዜያዊ ምሕረት ሰጠች ኬንያ ከውጭ አገር በመጡ አነስተኛ ነጋዴዎች ላይ እርምጃ ሊወሰድ ይችላል የሚል ስጋት አድሮባቸው በመቶዎች የሚቆ
#ኬንያ ሕጋዊ የመኖሪያ ፈቃድ ለሌላቸው #የምስራቅ_አፍሪካ ዜጎች ጊዜያዊ ምሕረት ሰጠች ኬንያ ከውጭ አገር በመጡ አነስተኛ ነጋዴዎች ላይ እርምጃ ሊወሰድ ይችላል የሚል ስጋት አድሮባቸው በመቶዎች የሚቆጠሩ የቡሩንዲ ዜጎች ሰኞ ዕለት በናይሮቢ ወደሚገኘው የአገራቸው ኤምባሲ የጉዞ ሰነዶችን ፍለጋ በሄዱበት ወቅት ነው የኬንያ መንግሥት ሕጋዊ የመኖሪያ ፈቃድ ለሌላቸው የምስራቅ አፍሪካ ዜጎች ጊዜያዊ ምሕረት የሰጠው። የኬንያው ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ በባለፈው ሳምንት ከታክስ ማሻሻያ ጋር በተያያዘ ተቃውሞ ካቀረቡ የኬንያ ነጋዴዎች ጋር ከተወያዩ በኋላ፣ ባለሥልጣናት ከሰኞ ጀምሮ በውጭ አገር ነጋዴዎች የሚካሄዱ ሁሉንም አነስተኛ የንግድ እንቅስቃሴዎች እንዲዘጋ ጥሪ አቅርበው እንደነበር ይታወሳል። የኬንያ ንግድ ሚኒስቴር ያለ ሥራ ፈቃድ በሚሰሩ የውጭ አገር ዜጎች ላይ እንደሚተገበር የተናገረው ይህ ትዕዛዝ፣ ሰኞ እለት በቡሩንዲ ኤምባሲ ውጭ ሁከትና ብጥብጥ የቀሰቀሰ ሲሆን፣ የቡሩንዲ ዜጎች የሩቶን ንግግር ተከትሎ ከጎረቤቶቻቸው ማስፈራሪያ እንደደረሳቸው ተናግረዋል። ሰኞ ዕለት በናይሮቢ ምንም አይነት የእርምጃ ምልክቶች ያልታዩ ሲሆን፣ የሩቶ አስተዳደር ቃል አቀባይ በኋላ እንደተናገሩት፣ መንግሥት ማንኛውንም አይነት ትንኮሳ፣ ማስፈራራት ወይም የውጭ ዜጎች ጠልነትን በፍጹም የመታገስ ፖሊሲ እንደሌለው ገልጸው፣ ሕጋዊ የመኖሪያ ፈቃድ የሌላቸው የምስራቅ አፍሪካ አገራት ዜጎች፣ በተለይም የቡሩንዲ ዜጎች በኤምባሲዎቻቸው ሕጋዊ ምዝገባ እንዲያካሄዱ አሳስበዋል። "በዚህ በተወሰነው የምዝገባ ወቅት፣ ምዝገባ የሚያካሄዱ ግለሰቦች በኬንያ ሪፐብሊክ ውስጥ በሕጋዊ መንገድ እንደተገኙ ይቆጠራሉ። https://www.facebook.com/share/1F8kVg3bR6/?mibextid=wwXIfr

#ሶማሊያ - የ #ላፍታጋሬን ቃል አቀባይ የውጭ አገር ወታደራዊ አውሮፕላኖች እና መሣሪያዎች የክልሉን የወደፊት የፖለቲካ ዕጣ ፈንታ ሊወስኑ እንደማይችሉ ተናገሩ የቀድሞው የሶማሊያ ደቡብ ምዕራብ ክልል
#ሶማሊያ - የ #ላፍታጋሬን ቃል አቀባይ የውጭ አገር ወታደራዊ አውሮፕላኖች እና መሣሪያዎች የክልሉን የወደፊት የፖለቲካ ዕጣ ፈንታ ሊወስኑ እንደማይችሉ ተናገሩ   የቀድሞው የሶማሊያ ደቡብ ምዕራብ ክልል ፕሬዝዳንት አብዲአሲስ ላፍታጋሬን ቃል አቀባይ በባይዶዋ ዙሪያ ውጥረቶች በተፋፋሙበት ወቅት፤ የውጭ አገር ወታደራዊ አውሮፕላኖች እና መሣሪያዎች የክልሉን የወደፊት የፖለቲካ ዕጣ ፈንታ ሊወስኑ እንደማይችሉ ተናገሩ።   ጋሮዌ ኦንላይን እንደዘገበው፤ ከባይዶዋ ውጪ ሆነው የተናገሩት ኡጋስ ሀሰን አብዲ መሐመድ፣ በከተማዋ እና በዙሪያዋ ያሉ የወታደራዊ እንቅስቃሴዎችን ጨምሮ በደቡብ ምዕራብ ክልል ስለታዩት የቅርብ ጊዜ የፖለቲካ እና የጸጥታ ሁነቶች ገልጸዋል።   በተጨማሪም በደቡብ ምዕራብ ክልል ባሉ ቦታዎች በሚደረጉ እንቅስቃሴዎች የውጭ አገር ወታደራዊ አውሮፕላኖችን መጠቀምን የነቀፉ ሲሆን፣ የአውሮፕላኖች እና የውጭ ወታደራዊ ተሽከርካሪዎች መሰማራት በምድር ላይ ያለውን ሁኔታ እንደማይለውጥ ገልጸዋል። "የደቡብ ምዕራብ ሕዝቦች የመሬታቸውን እና የወደፊት ዕጣ ፈንታቸውን የሚወስኑት በራሳቸው ነው። የውጭ አውሮፕላኖችን እና ተሽከርካሪዎችን ማምጣት ትችላላችሁ፤ ነገር ግን የደቡብ ምዕራብ አካባቢዎች ውሳኔ እና ዕጣ ፈንታ በሕዝባችን እጅ እንደጸና ይኖራል" ሲሉም ተደምጠዋል።   ሀሰን የውጭ አገር ወታደሮች እና ወታደራዊ ቁሳቁሶች መሰማራት የክልሉን የፖለቲካ የወደፊት ዕጣ ፈንታ በመወሰን ረገድ የአካባቢውን ነዋሪዎች ሚና ሊተካ እንደማይችል የገለጹ ሲሆን፣ የፖለቲካ እና የጸጥታ ውጥረቶች እየጨመሩ በመጡበት በዚህ ወቅት በደቡብ ምዕራብ የሚገኙ ሕዝቦች በንቃት እና በአንድነት ሆነው እንዲቆዩ ጥሪ አቅርበዋል።   https://www.facebook.com/share/p/1EyvdYpLBp/

#ሶማሊላንድ በ #ኢትዮጵያ አዲስ አምባሳደር ሾመች የሶማሊላንድ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አምባሳደር ሸርማርኬ አሕመድ ሙሁመድ ገሌ በኢትዮጵያ አምባሳደር ሆነው መሾማቸውን አስታወቀ። አምባሳደሩ በሁለቱ ወ
#ሶማሊላንድ በ #ኢትዮጵያ አዲስ አምባሳደር ሾመች የሶማሊላንድ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አምባሳደር ሸርማርኬ አሕመድ ሙሁመድ ገሌ በኢትዮጵያ አምባሳደር ሆነው መሾማቸውን አስታወቀ። አምባሳደሩ በሁለቱ ወገኖች መካከል ያለውን ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ታሪካዊ ግንኙነት የማጠናከር ኃላፊነት ተጥሎባቸዋል። እንደ ሚኒስቴሩ ገለጻ፤ አምባሳደር ገሌ በሶማሊላንድ መንግሥት እና በዓለም አቀፍ ግንኙነቶች ውስጥ የ15 ዓመታት ልምድ ያላቸው ዲፕሎማት እና የሕዝብ አገልጋይ ናቸው። አዲሱ የሥራ ኃላፊነታቸውም ሶማሊላንድ በመላው አፍሪካ የምታደርገውን ሰፊ ዲፕሎማሲያዊ ተሳትፎ በማሳደግ ላይ የሚያተኩር ይሆናል ተብሏል። አምባሳደር ገሌ እ.ኤ.አ. ከ2015 እስከ 2016 በፕሬዚዳንት ጽሕፈት ቤት የካቢኔ ሴክሬታሪዎች ኃላፊ ሆነው ያገለገሉ ሲሆን፣ በካቢኔ ደረጃ የሚሰጡ ውሳኔዎችን በማገዝ እና በመንግሥት ተቋማት መካከል የፖሊሲ ትግበራዎችን በማቀናጀት ረገድ ሚና ተጫውተዋል። በመቀጠልም የሕዝብ አገልግሎት እና የመንግሥት አሠራርን ውጤታማነት፣ ተጠያቂነትን እና አገልግሎት አሰጣጥን ለማሻሻል ያለሙ ተቋማዊ ማሻሻያዎችን በመምራት የሶማሊላንድ ሲቪል አገልግሎት ኮሚሽንን በሊቀመንበርነት መርተዋል። https://www.facebook.com/share/p/1CwK2vF3op/

#ኢትዮጵያዊቷ የሚስ ወርልድ ተወዳዳሪ በእህቷ ግድያ ያሳለፈችውን ሕመም ይፋ አደረገች የኢትዮጵያ ሚስ ወርልድ ተወዳዳሪዋ ሩት ይርጋለም ወልደሥላሴ የታላቅ እህቷን እገታ እና አሰቃቂ ግድያ ተከትሎ፣ በ
#ኢትዮጵያዊቷ የሚስ ወርልድ ተወዳዳሪ በእህቷ ግድያ ያሳለፈችውን ሕመም ይፋ አደረገች የኢትዮጵያ ሚስ ወርልድ ተወዳዳሪዋ ሩት ይርጋለም ወልደሥላሴ የታላቅ እህቷን እገታ እና አሰቃቂ ግድያ ተከትሎ፣ በዓለም አቀፉ የቁንጅና ውድድር መድረክ ላይ በሴቶች ላይ የሚፈጸሙ ጥቃቶችን ለማጉላት እየሠራች መሆኑን ኤኤፍፒ (AFP) ዘገበ። ቅዳሜ ዕለት ከተካሄደው የመጨረሻው ዙር ውድድር አስቀድሞ 111 ተወዳዳሪዎች በተገኙበት በቬትናሟ ንሃ ትራንግ (Nha Trang) ከተማ የምትገኘው የ25 ዓመቷ ሩት፣ ሀዘኗን ወደ ማህበረሰብ አገልግሎት እና ጥበቃ ለመቀየር ማቀዷን ለዜና ወኪሉ ተናግራለች። የሩት የ29 ዓመት ታላቅ እህት ቅድስት ይርጋለም ወልደሥላሴ፣ ሩት ወደ ቬትናም ለመጓዝ በማዘጋጀት ላይ በነበረችበት ወቅት ለቤዛ ክፍያ ተጠልፋ እንደነበር ተገልጿል። የቅድስት አስከሬን በሐምሌ ወር መጨረሻ ላይ በሁለት ሳጥኖች ተከፍሎ የተገኘ ሲሆን፣ ከተፈጸመው ድርጊት ጋር በተያያዘ የሩት የቅርብ ጓደኛ እና የጓደኛዋ የፍቅር አጋርን ጨምሮ 10 ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ሩት ለኤኤፍፒ ገልጻለች። ይህ አሰቃቂ አጋጣሚ ሩት በኢትዮጵያ በሴቶች እና ህፃናት ላይ በሚፈጸሙ ጥቃቶች ላይ ትኩረት የመስጠት ቁርጠኝነቷን ያጠናከረው ሲሆን፣ የማህበራዊ ተፅዕኖ ፕሮጀክቶቿ በህፃናት የአእምሮ ጤና እና በወላዶች ጤና ጥበቃ ላይ ትኩረት አድርገዋል። https://www.facebook.com/share/p/194Ud7B4X4/

ዜና: #ህውሓት የአባሳንጆን የሸምግልና ጥረት ገለልተኝነት እና ተጨባጭ ይዘት ይጎለዋል ሲል ተቸ ህውሃት የቀድሞው የናይጄሪያ ፕሬዚዳንት ኦሉሴጉን አባሳንጆ በትግራይ ሰላም ለማውረድ የሚያደርጉትን ጥረ
ዜና: #ህውሓት የአባሳንጆን የሸምግልና ጥረት ገለልተኝነት እና ተጨባጭ ይዘት ይጎለዋል ሲል ተቸ ህውሃት የቀድሞው የናይጄሪያ ፕሬዚዳንት ኦሉሴጉን አባሳንጆ በትግራይ ሰላም ለማውረድ የሚያደርጉትን ጥረት የተቸ ሲሆን፣ አሸማጋይነታቸው «ገለልተኝነት፣ ተጨባጭ ሀሳብ» እና ወደ ትርጉም ያለው ውይይት የሚያመራ ግልጽ መንገድ የጎደለው ነው ሲል ከሰሰ። ህውሃት ጳጉሜ 1 ቀን 2018 ዓ.ም. ባወጣው መግለጫ ለሰላማዊ ውይይት ዝግጁ መሆኑን ገልጾ፣ የኦሉሴጉን አባሳንጆ የሰላም ጥረት ከፌደራል መንግሥት ተፅዕኖ ነፃ ስለመሆኑ ጥያቄ አንስቷል። ድርጅቱ ማንኛውም የሰላም ሂደት ወገንተኛ ባልሆነ እና በገለልተኛ አሸማጋይ ሊመራ እንደሚገባ ጥሪ አቅርቧል። መግለጫው አባሳንጆ በፌደራል መንግሥት እና በትግራይ ባለሥልጣናት መካከል ውይይት ለማመቻቸት ቀደም ሲል ያደረጓቸውን ጥረቶች ተቃውሟል። ኦሉሴጉን አባሳንጆ ሰኔ 2018 ዓ.ም. በትግራይ ያደረጉትን ጉብኝት እና በአንድ ወይም በሁለት ሳምንታት ውስጥ ለመመለስ ገብተውት የነበረውን ቃል በማስታወስ፣ ሆኖም ከሁለት ወራት በኋላ መመለሳቸውን ጠቁሟል። https://addisstandard.com/Amharic/?p=14022

የ #ሱዳን ጦር በሰሜን ኮርዶፋን ግዛት የምትገኘውን ሐምራት አል ዊዝ ከተማን ተቆጣጠረ የሱዳን ጦር (SAF) እና አጋር ኃይሎች እሑድ ዕለት በሰሜን ኮርዶፋን ግዛት የምትገኘውን ሐምራት አል ዊዝ ከተ
የ #ሱዳን ጦር በሰሜን ኮርዶፋን ግዛት የምትገኘውን ሐምራት አል ዊዝ ከተማን ተቆጣጠረ የሱዳን ጦር (SAF) እና አጋር ኃይሎች እሑድ ዕለት በሰሜን ኮርዶፋን ግዛት የምትገኘውን ሐምራት አል ዊዝ ከተማን የተቆጣጠሩ ሲሆን፣ የፈጥኖ ደራሽ ኃይሎችን (RSF) ከአካባቢው በማስወጣት ወደ መዲናዋ ካርቱም የሚወስደውን ወሳኝ የአቅርቦት መስመርንም በእጃቸው አስገብተዋል። ​ይህ የወታደራዊ ግስጋሴ የተካሄደው ሐምሌ ወር መጨረሻ ላይ የተሰነዘረውን ፈጣን የማጥቃት እርምጃ ተከተሎ ሲሆን፣ በወቅቱ የፈጥኖ ደራሽ ኃይሎች (RSF) ከሰፊ የግዛቱ ክፍሎች እንዲወጡ ተደርጓል። ይህም ወሳኝ የሆነውን የወጪ ንግድ መስመር (Export Road) ቁጥጥር ለማስመለስ ያስቻለ ከመሆኑም በላይ፣ ከዳርፉር አዋሳኝ አካባቢዎች አቅራቢያ ወደሚገኙት ምዕራባዊ ምሽጎች ታጣቂዎቹ እንዲያፈገፍጉ አስገድዷቸዋል። ​ሐምራት አል ዊዝን መቆጣጠር ጦሩ በጀብራት አል ሼክ እና በባራ ወታደራዊ ከተሞች ዙሪያ ያለውን የመከላከል አቅም የሚያጠናክርለት ሲሆን፣ ሰሜን ኮርዶፋንን ከካርቱም ጋር የሚያገናኘውን ዋና መንገድ ለንግድ እና ለዜጎች እንቅስቃሴ ደኅንነቱ የተጠበቀ ያደርገዋል። ​https://www.facebook.com/share/p/18ssvwWyXs/

#ደቡብ_ኮሪያ #አዲስ_አበባን ጨምሮ በአንዳንድ የ #ኢትዮጵያ አካባቢዎች ላይ ጥላው የነበረውን ልዩ የጉዞ ማስጠንቀቂያ አነሳች የደቡብ ኮሪያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አርብ ዕለት ባወጣው መግለጫ፣ በኢት
#ደቡብ_ኮሪያ #አዲስ_አበባን ጨምሮ በአንዳንድ የ #ኢትዮጵያ አካባቢዎች ላይ ጥላው የነበረውን ልዩ የጉዞ ማስጠንቀቂያ አነሳች የደቡብ ኮሪያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አርብ ዕለት ባወጣው መግለጫ፣ በኢትዮጵያ ያለውን የጤና ሁኔታ እና የኢቦላ ቫይረስ በሽታ አለመኖሩን በተመለከተ ግምገማ በማድረግ አዲስ አበባን ጨምሮ በአንዳንድ የሀገሪቱ አካባቢዎች ላይ ተጥሎ የነበረውን የጉዞ ማስጠንቀቂያ ማንሳቱን አስታወቀ። ሚኒስቴሩ በመስከረም ወር ያበቃሉ ተብለው የታቀዱትን ልዩ የጉዞ ማስጠንቀቂያ ማራዘም በሚያስፈልግበት ሁኔታ ላይ ክለሳ ማድረጉን የገለጸ ሲሆን፣ በኢትዮጵያ፣ ታይላንድ፣ ቱርክ እና አዘርባጃን ውስጥ የሚገኙ የተወሰኑ አካባቢዎችን ሁኔታ በመገምገም ማዕቀቦቹን ለማንሳት መወሰኑን አስረድቷል። ኢትዮጵያን በተመለከተ የተላለፈው ይህ ውሳኔ፣ የደቡብ ኮሪያ ባለሥልጣናት በሀገሪቱ ውስጥ እስካሁን የተረጋገጠ የኢቦላ ቫይረስ በሽታ አለመኖሩን ከረጋገጡ በኋላ የተሰጠ ነው። በኢቦላ ስርጭት ስጋት ምክንያት አዲስ አበባን ጨምሮ በበርካታ አካባቢዎች ላይ ግንቦት 19 ቀን 2018 ዓ.ም. ተጥሎ የነበረው ልዩ የጉዞ ማስጠንቀቂያ የተነሳ ሲሆን፣ ለአካባቢዎቹ የተሰጠው የጉዞ ስጋት ደረጃ ወደ ደረጃ 2 ዝቅ እንዲል ተደርጓል። ይህም መንገደኞች አስፈላጊውን ጥንቃቄ እንዲያደርጉ የሚያስጣነቅቅ ነው። https://www.facebook.com/share/p/1Ed85LGt1U/

#ትግራይ: #በራያ ዞን #ጨርጨር ወረዳ #ኢርባ ቀበሌ የተገነባው የፓምፕ መስኖ ፕሮጀክት ተጠናቆ ለተጠቃሚ አርሶ አደሮች በይፋ ተሰጠ ትግራይ ቴሌቪዥን የትግራይ ክልል ውሃና ኢነርጂ ቢሮን ጠቅሶ እንደ
+3
#ትግራይ: #በራያ ዞን #ጨርጨር ወረዳ #ኢርባ ቀበሌ የተገነባው የፓምፕ መስኖ ፕሮጀክት ተጠናቆ ለተጠቃሚ አርሶ አደሮች በይፋ ተሰጠ ትግራይ ቴሌቪዥን የትግራይ ክልል ውሃና ኢነርጂ ቢሮን ጠቅሶ እንደዘገበው፤ በስነ-ስርዓቱ ላይ የውሃና ኢነርጂ ቢሮን እና በዓለም ባንክ የሚደገፈው የምግብ ስርዓት ማጠናከሪያ ፕሮግራም (FSRP) ፕሮግራምን ወክለው የተገኙት ኢንጂነር ገብረሚካኤል አስመሮም፣ ፕሮጀክቱ 30 ሄክታር የታረሰ መሬት በመስኖ ለማልማት የሚያገለግል መሆኑን ገልጸዋል። አያይዘውም ፕሮጀክቱ ድርቅን ለመከላከል፣ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ እና የአርሶ አደሮችን ኑሮ ለማሻሻል ከፍተኛ ሚና እንደሚኖረው ተናግረዋል። ኢንጂነሩ የ"ዓሊ ሳሊሕ" የመስኖ ማህበር አባላት የውሃ ጉድጓድ ቁፋሮ እና የኤሌክትሪክ ትራንስፎርመር ዝርጋታ ስራዎች እንዲሟሉ ላደረጉት አስተዋጽኦ እና ላሳዩት ጥረት ምስጋና በማቅረብ፣ ይህ አርአያነት ያለው ተግባር በሌሎች አርሶ አደሮችም ሊደገም እንደሚገባ ጥሪ አቅርበዋል። የ"ዓሊ ሳሊሕ" የመስኖ ማህበር አስተባባሪ አቶ ሃለፎም በበኩላቸው ለተደረገላቸው ድጋፍ ምስጋና አቅርበው፣ ፕሮጀክቱ የአርሶ አደሮችን ኑሮ ለማሻሻል ትልቅ አስተዋጽኦ እንዳለው በመግለጽ የተጀመረው ድጋፍ በተጠናከረ ሁኔታ እንዲቀጥል መጠየቃቸውን የትግራይ ክልል ውሃና ኢነርጂ ቢሮ መረጃ ያመለክታል። በአሁኑ ወቅት በብዙ የትግራይ ክልል አካባቢዎች በኤልኒኞ (El Niño) የአየር ጠባይ ምክንያት በተከሰተው ድርቅ ሳቢያ የእንስሳት እልቀት እና የሰብል ውድመት እየደረሰ ይገኛል፤ ይህም የመስኖ ፕሮጀክቱን ለአካባቢው አርሶ አደሮች ወቅታዊ እና አስፈላጊ ያደርገዋል ተብሎ ይገመታል።

የ #ሱዳኑ ጦር አዛዥ በሁለት ወራት ጊዜ ውስጥ ለሁለተኛ ጊዜ በ #ኤርትራ ጉብኝት አደረጉ የሱዳን የጦር ኃይሎች ጠቅላይ አዛዥ እና የሉዓላዊ ምክር ቤት ሊቀመንበር ሌተናል ጄነራል አብደል ፋታህ አል
የ #ሱዳኑ ጦር አዛዥ በሁለት ወራት ጊዜ ውስጥ ለሁለተኛ ጊዜ በ #ኤርትራ ጉብኝት አደረጉ የሱዳን የጦር ኃይሎች ጠቅላይ አዛዥ እና የሉዓላዊ ምክር ቤት ሊቀመንበር ሌተናል ጄነራል አብደል ፋታህ አል ቡርሃን ከኤርትራው ፕሬዚዳንት ኢሳይያስ አፈወርቂ ጋር ለመመካከር አርብ ዕለት አስመራ ገብተዋል። ይህ ጉዞ በሁለት ወራት ጊዜ ውስጥ ወደ ሀገሪቱ ያደረጉት ሁለተኛው ጉብኝት ነው። አል ቡርሃን ቀደም ሲል ነሐሴ 10 ቀን ከፕሬዚዳንት ኢሳይያስ ጋር ውይይት ለማድረግ በአስመራ ተገኝተው የነበረ ሲሆን፣ የሉዓላዊ ምክር ቤቱ አርብ ዕለት ባወጣው መግለጫ የሁለቱን ሀገራት የሁለትዮሽ ግንኙነት ለማጠናከር ያለመውን የዕለቱን ጉዞ «ወንድማማችነትን መሠረት ያደረገ» ሲል ገልጾታል። በመግለጫው መሠረት ሁለቱ ወገኖች በሱዳን እና በኤርትራ መካከል ስላለው ግንኙነት፣ የጋራ ጥቅሞቻቸውን በሚያስከብሩ መልኩ ትብብርን እና ቅንጅትን ማሳደግ በሚቻልባቸው መንገዶች ላይ መክረዋል። በሱዳን ጦርነት ከተቀሰቀሰበት ጊዜ ጀምሮ በካርቱም እና በአስመራ መካከል ያለው ግንኙነት እያደገ የመጣ ሲሆን፣ ሁለቱ ሀገራት ፖለቲካዊ እና የደኅንነት ቅንጅቶቻቸውን በማጠናከር ላይ ይገኛሉ። ኤርትራ ከሱዳን ጋር ከ600 ኪሎ ሜትር (370 ማይል) በላይ የሚሸፍን ድንበር የምትጋራ በመሆኗ በሱዳኑ ቀውስ ውስጥ ከፍተኛ ተፅዕኖ ያለው ሚና በመጫወት ላይ እንደምትገኝ ሱዳን ትሪቢዩን ዘግቧል።

#የሱዳን ጦር አዛዥ በሁለት ወራት ውስጥ ለሁለተኛ ጊዜ ያደረጉት #የኤርትራ ጉብኝት የሱዳን ጦር አዛዥ እና የሉዓላዊነት ምክር ቤት ሊቀመንበር አብደል ፈታህ አል-ቡርሃን ከኤርትራው ፕሬዚዳንት ኢሳይያ
+1
#የሱዳን ጦር አዛዥ በሁለት ወራት ውስጥ ለሁለተኛ ጊዜ ያደረጉት #የኤርትራ ጉብኝት የሱዳን ጦር አዛዥ እና የሉዓላዊነት ምክር ቤት ሊቀመንበር አብደል ፈታህ አል-ቡርሃን ከኤርትራው ፕሬዚዳንት ኢሳይያስ አፈወርቂ ጋር ለመወያየት አርብ ዕለት አስመራ ደርሰው ተመልሰዋል። ይህም በሁለት ወራት ጊዜ ውስጥ ወደ አገሪቱ ያደረጉት ሁለተኛው ጉብኝታቸው ነው። አል-ቡርሃን ቀደም ሲል በሐምሌ 10 ቀን 2016 ዓ.ም. ወደ ኤርትራ መዲና በማቅናት ከፕሬዚዳንት ኢሳይያስ ጋር ተወያይተው ነበር። የሉዓላዊነት ምክር ቤቱ አርብ ዕለት ባወጣው መግለጫ ጉብኝቱን ከኤርትራው መሪ ጋር በሁለትዮሽ ጉዳዮች ላይ ለመምከር የተደረገ "ወንድማማችነታዊ" ጉብኝት ሲል ገልጾታል። በመግለጫው መሠረት ሁለቱ ወገኖች በሱዳን እና በኤርትራ መካከል ስላለው ግንኙነት፣ በተለይም “የጋራ ጥቅሞቻቸውን በሚያስከብሩ” መንገዶች ላይ በትብብር እና በቅንጅት መስራት በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ተወያይተዋል። በሱዳን ጦርነት ከተቀሰቀሰ ወዲህ በካርቱም እና በአስመራ መካከል ያለው ግንኙነት እየጠበቀ የመጣ ሲሆን፣ ሁለቱ አገራት የፖለቲካ እና የደህንነት ቅንጅታቸውን ማጠናከራቸውን ቀጥለዋል። ኤርትራ ከሱዳን ካሳላ እና ቀይ ባሕር አዋሳኝ አካባቢ ከ600 ኪሎ ሜትር በላይ የሚዘልቅ የየብስ ወሰን የምትጋራ በመሆኗ በሱዳን ቀውስ ውስጥ ከፍተኛ ተፅዕኖ ያለው ሚና ትጫወታለች በመባል ይዘገባል።

#ርዕሰ_አንቀጽ: የመድፍ ቀለብ መሆን ይብቃ! የአንድ አገር መንግሥት ወይም ባለሥልጣናት ዜጎች ለሚያምኑበት ዓላማ እንዲታገሉ ማሳመን አቅቷቸው፣ ለማያምኑበት ጦርነት በኃይል ማገድ ሲጀምሩ፣ ያ ክስተት
#ርዕሰ_አንቀጽ: የመድፍ ቀለብ መሆን ይብቃ!   የአንድ አገር መንግሥት ወይም ባለሥልጣናት ዜጎች ለሚያምኑበት ዓላማ እንዲታገሉ ማሳመን አቅቷቸው፣ ለማያምኑበት ጦርነት በኃይል ማገድ ሲጀምሩ፣ ያ ክስተት በአገሪቱ ውስጥ ትልቅ የፖለቲካ እና የሞራል ውድቀት መኖሩን ፍንትው አድርጎ የሚያሳይ ነው።   ዜጎችን ለወታደራዊ ተግባር በኃይል የመመልመል አደገኛ አካሄድ ወደ ኢትዮጵያ የፖለቲካ ምህዳር ዳግም ከተመለሰ ሰንበትበት ብሏል።   ወጣቶች በሚጓዙበት ወይም በሚሠሩበት ወቅት ይያዛሉ፤ አርሶ አደሮች ወደ ወታደራዊ ስልጠና እንዲገቡ ይገደዳሉ፤ ቤተሰቦች የታሰሩ ዘመዶቻቸውን ለማስፈታት ከፍተኛ ገንዘብ እንዲከፍሉ ይደረጋሉ፤ ለአካባቢ ባለስልጣናት የሰው ቁጥር ኮታ ይሰጣቸዋል፤ ወጣቶች ወደ ወታደራዊ ካምፖች ሲያመሩ የቤተሰብ መኖሪያና ህይወት ይናጋል።   ይህ አገራዊ ህዳሴ ሳይሆን አገራዊ ውድቀት ነው!   https://addisstandard.com/Amharic/?p=14012

ዜና: #ጣሊያን በ #ዓባይ_ውኃ ዙሪያ #በግብፅና #በኢትዮጵያ መካከል የሚደረግን ውይይት ለማመቻቸት ጥያቄ አቀረበች ጣሊያን በዓባይ ውኃ ዙሪያ በግብፅና በኢትዮጵያ መካከል የሚደረግ ውይይት ለማመቻቸት
ዜና: #ጣሊያን በ #ዓባይ_ውኃ ዙሪያ #በግብፅና #በኢትዮጵያ መካከል የሚደረግን ውይይት ለማመቻቸት ጥያቄ አቀረበች   ጣሊያን በዓባይ ውኃ ዙሪያ በግብፅና በኢትዮጵያ መካከል የሚደረግ ውይይት ለማመቻቸት ፍላጎት ያሳየች ሲሆን፣ ሁለቱ ሀገራት በዓለም አቀፍ ሕግ መሠረት ፍትሐዊና ዘላቂ በሆነ በድርድር የሚገኝ መፍትሔ ላይ እንዲደርሱ ጥሪ አቀረበች። የጣሊያን ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒዮ ታጃኒ ይህንን ጥያቄ ያቀረቡት በግብፅ ኤል አላሜይን ከግብፅ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ባድር አብደላቲ ጋር ከተወያዩ በኋላ በጋራ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ነው። አንቶኒዮ ታጃኒ፣ ሁለቱም ሀገራት ከተስማሙ ሮም ለማሸማገል ወይም ውይይቱን ለማመቻቸት ዝግጁ መሆኗን ገልጸው፣ ጣሊያን ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ግንኙነት የረጅም ጊዜ ውዝግቡን ለመፍታት ለሚደረጉ ጥረቶች እንደ አንድ  á‰ áŒŽ ግብአት ጠቅሰዋል።   https://addisstandard.com/Amharic/?p=14019

#ናሚቢያ ከ #ኢትዮጵያ አየር መንገድ ጋር በጋራ ብሔራዊ አየር መንገድ ለማቋቋም የምታደርገው ውይይት በምክክር ደረጃ ላይ እንደሚገኝ አስታወቀች የናሚቢያ መንግሥት «ናሚቢያ ኤር» የተሰኘ አዲስ ብሔራ
#ናሚቢያ ከ #ኢትዮጵያ አየር መንገድ ጋር በጋራ ብሔራዊ አየር መንገድ ለማቋቋም የምታደርገው ውይይት በምክክር ደረጃ ላይ እንደሚገኝ አስታወቀች የናሚቢያ መንግሥት «ናሚቢያ ኤር» የተሰኘ አዲስ ብሔራዊ አየር መንገድ ለማቋቋም ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ጋር ውይይት እያደረገ መሆኑን ያረጋገጠ ቢሆንም፣ እስካሁን ምንም ዓይነት ስምምነት ላይ አለመደረሱን አስታወቀ። ቸ-አቪዬሽን (ch-aviation.com) የሀገሪቱን የሥራ እና ትራንስፖርት ሚኒስቴር ዋቢ አድርጎ እንደዘገበው፣ ከኢትዮጵያ አየር መንገድ፣ ከሀገሪቱ የአቪዬሽን ተቋማት እና ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር የሚደረጉ የምክክር መድረኮች አየር መንገዱን ለማቋቋም የሚያስችል አትራፊ እና ዘላቂ ሞዴልን ለመቅረጽ የተዘጋጁ ቅድመ-ግምገማዎች ናቸው። ሚኒስቴሩ «ዊንድህክ ኦብዘርቨር» በተሰኘው ጋዜጣ ይፋ የተደረገውን የውስጥ ሰነድ ሕጋዊ እውቅና የሌለው ሲል ውድቅ ያደረገ ሲሆን፣ ዘገባው የመንግሥትን ይፋዊ ውሳኔ ወይም ስምምነት እንደማይወክል ገልጿል። አክሎም ማንኛውም በቀጣይ የሚደረግ ስምምነት በቴክኒካዊ፣ ፋይናንሳዊ እና ንግዳዊ ግምገማዎች ላይ ተመስርቶ አስፈላጊውን አጽደቆት የሚያገኝ እንደሚሆን አስታውቋል። እንደ ሚኒስቴሩ ገለጻ ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ጋር የሚደረገው ውይይት፣ ቀደም ሲል የነበረው ብሔራዊ አየር መንገድ «ኤር ናሚቢያ» ለኪሳራ የተዳረገበትን አሰራር ላለመድገም እና አዲሱ ተቋም በፋይናንስ ረገድ ዘላቂ እና አትራፊ የሚሆንበትን መንገድ ለመቀየስ ያለመ ነው። https://www.facebook.com/share/p/18ksqcbNCx/