cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

ላሐ ማርያም

በዚህ ምህላፍ(ቻናል) #ግጥም #የተለያዩ ቁም ነገሮች እና መንፈሳዊ ትምህርቶች #ስለሀገራችን ጥንታዊ ታሪክ # የአባቶቻችን ገድላትን የምናቅበት በረከታቸው የምንካፈልበት መርጠው ስለተቀላቀሉን እናመሠግናለን

Show more
Advertising posts
189
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

አክሊለ ጽጌ.mp34.05 MB
4_5868595918290291975.ogg2.22 KB
*ዘመነ ጽጌ* (ክፍል ፩) ✝️  *ይህንን ጣፋጭ መልዕክት ያዘጋጁልን አባታችን ቀሲስ ደጀኔ ሽፈራው ዘካናዳን እመብርሃን ረጅም እድሜ እና ብዙ በረከት ታድልልን። መልዕክቱን በተረጋጋ ልቦና አንብበን በረከት እንድናገኝ ቸሩ መድኃኔዓለም ይርዳን።* ✝️ ማስተዋሉን ያድለን!                                                                                     ✝️ዘመነ ጽጌ፡-የአበባ ጊዜ ማለት ነው።በሀገራችን በኢትዮጵያ ዘመነ ክረምት መስከረም ፳፭ ቀን ሲያልፍ፣በማግሥቱ መስከረም ፳፮ ቀን ዘመነ ጽጌ ይጀምራል።    ✝ይህ ዘመን ጽጌያት (አበቦች) አብበው ሜዶችን እና ተራሮችን የሚያስጌጡበት ወቅት ነው።ይህም ለዓይናችን ፍሥሐ ለልባችን መደነቂያ ነው፥አንድም ከአበቦች ፍሬ ስለሚገኝ ለሰው ልጅ ትልቅ ተስፋ ነው። ✝️ቤተክርስቲያን ድንቅ በሆነው የዘመነ ጽጌ ዝማሬ ግዕዙ ወደ አማርኛ ሲተ ረጐም፦ “ምድርን በአበቦች ውበት ያስጌጥካት አምላካችን አቤቱ እናመሰግንሃለን፥ አቤቱ ስምህ የተመሰገነ የከበረ ነው።”እያለች ከሰማይ በተገኘ በኢትዮጵያዊው የቅዱስ ያሬድ ዜማ እግዚአብሔርን ታመሰግናለች። ✝️እስመለዓለም በሚባለው የዘመነ ጽጌ መዝሙርም፡- “እግዚአብሔርን አመሰግን ዘንድ ወደ ምድረ በዳ ወጥቼ የእግዚአብሔርን ኃይል አየሁ፥ ሥራው መልካም ነው፥ኃይሉም እንደ ሰው ኃይል አይደለም፣ሰማይን በከዋክብት ምድርንም በአበቦች ውበት አስጌጣት፥የእግዚአብሔር ልጅ (ወልድ) ሥራው ያማረ ነው።”እያለች ታደንቀዋለች። ✝️ከዚህም ጋር ምሥጢርን ከምሥጢር በማገናኘት በአበባ የሚመሰሉትን የጌታን እና የእመቤታችንን ስደት ከመስከረም ፳፮ እስከ ኅዳር ፮ ድረስ በማኅሌትና በቅዳሴ በልዩ ኹኔታ ታከብራለች።                                                                  ✝️ቤተክርስቲያን ጌታን እና እመቤታችንን በአበባ እየመሰለች የምታመሰግነው ከራሱ ከእግዚአብሔር አግኝታው እንጂ ልበ ወለድ አይደለም።ጌታችን አምላካችን መድኃኒ ታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በጠቢቡ በሰሎሞን አድሮ ሲናገር፡-“እኔ የምድረ በዳ አበባ ነኝ፥በእሾህ መካከል ያለ የሱፍ አበባ ያማረ የተወደደ እንደሆነ ሁሉ አንችም በቈነጃጅት መካከል በእኔ ዘንድ እንደዚያ የተወደድሽ ነሽ።”ብሏል።መኃ፡፪ ቁ.፩። ✝️የአበባ ውበቱ ዓይንን እንደሚ ማርክ መዓዛውም ልብን እንደሚመስጥ፦ የክርስቶስም ውበቱና መዓዛ ትምህርቱ ነፍስን ይማርካል፥ልብንም ይመስጣል።አበባ ከምድር እንደሚበቅል ጌታም ከምድር (ከሰው ወገን ከሆነች ከእመቤታችን) ተወልዷል።ሰው ከምድር አፈር ስለተፈጠረ ምድር ይባላል። ምድረ በዳ የተባለው ደግሞ ፍሬ ጽድቅና ልምላሜ ሃይማኖት የታጣበት የሰው ሕይወት ነው።ጌታ በተዋህዶ ሰው ሁኖ ወደዚህ ዓለም የመጣው ይኸንን የደረቀ ሕይወት ለማለምለም ነው። ✝️አበባ ሲያቆስሉት (ሲያሹት) መዓዛው እንደሚበረታ ጌታም በመከራ መስቀል በመቁሰሉ መዓዛ ፍቅሩ ዓለሙን ዐውዷል። ✝️የዘመነ ጽጌ አቡን፡-“ክርስቶስ የዘለዓለም ንጉሥ ነው፥የሰማይን መሠረት አሳመረ፥አበቦችንም በልዩ ልዩ ኅብር አስጌጠ።……የቤተ ክርስቲ ያን ሙሽራዋ የቅዱሳን መዓዛቸው ነው፥ክርስቶስ መንግስቱ የማይሻር የዘለዓለም ንጉሥ ነው።”የሚለው ለዚህነው።                                                                                                             ✝️ጌታችን፡-“በእሾህ መካከል ያለ የሱፍ አበባ እንደሚያምርና እንደሚወደድ አንቺም በእኔ ዘንድ ከቈነጃጅት ሁሉ (ከሴቶች ሁሉ) ይልቅ የተወደድሽ ነሽ።”ያለው ስለ እመቤታችን ነው።ምክንያቱም ኃጢአት በሰፈነባት፥መርገመ ሥጋ እና መርገመ ነፍስም በወደቀባት ዓለም ተፈጥራ ለእርሱ ማደርያነት ንጽሕተ ንጹሐን ሆና ተገኝታለች። ቅዱስ ዳዊት ፡-“እግዚአብሔር ጽዮንን መርጦአታልና፥ማደሪያውም ትሆነው ዘንድ ወድዶአታልና፤”ያለው ለዚህ ነው።መዝ፡፻፴፩ ቁ.፲፫። ✝️እግዚአብሔር ጥሩ መዓዛ እንዳለው አበባ መዓዛ ድንግልና ዋን፥መዓዛ ንጽሕናዋን ወደደ።ከአበባ ፍሬ እንዲገኝ፥ለእናትነት የመረጣትና የወደዳት የሕይወት ፍሬ ኢየሱስ ክርስቶስ በመንፈስ ቅዱስ ግብር ከእርሷ ተወልዷል። ✝️ቅዱስ ኤፍሬም በውዳሴ ማርያም ድርሰቱ፡-“ከዕሴይ ሥር የወጣች መዓዛዋ ያማረ አበባ አንቺ ነሽ፤”ያለው ለዚህ ነው።ይህም የትንቢተ ኢሳይያስ ትርጉም ነው።ኢሳ፡፲፩ ቁ.፩። ✝️በኦሪቱ የነበረውን ምሳሌ ሲተረጉምም፡- “ሳይተክሏትና ውኃ ሳያጠጧት አብባ የተገኘች የአሮን በትር አንቺ ነሽ ።”እያለ በድንግልና ጸንሳ በድንግልና መውለዷን ቅዱስ ኤፍሬም መስክሯል። ይቆየን ክፍል ፪ ይቀጥላል ከእመቤታችን ረድኤት በረከት ያሳትፈን አሜን @laha_maryam
Show all...
+ ተማሪዎች ፈተና ከመፈተናቸው በፊት ይህን ይጸልዩ + ቅዱስ ቄርሎስ ሣድሳዊ ዘእስክንድርያ የደረሱት +++ ጸሎት +++ ‹‹ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ‹‹በችግርህ ቀን ጥራኝ ፤ አድንሃለሁ አንተም ታከብረኛለህ›› ብለህ የአንተን መጠጊያነት መፈለግን ስላስተማርከኝ አመሰግንሃለሁ! አሁንም ጌታ ሆይ! በዚህ የፈተና ሰዓት ጥበብና ማስተዋልን ትሰጠኝ ዘንድ እማጸንሃለሁ፡፡ ይህን ፈተና በሰላም አልፍ ዘንድ ጸጋን (ሞገስን) ስጠኝ፡፡ ፈተናውን በምሠራ ጊዜ ጥልቅ የሆነ ሰላምህንና በረከትህን ስጠኝ፡፡ ጌታዬ ኢየሱስ ውጤት በሚሰጡኝ ጊዜ በመምህራኖቼ ዓይን መወደድን ትሰጠኝና ልባቸውን ታለሰልስልኝ ዘንድ እለምንሃለሁ፡፡ የከበርከው ጌታእኔ ኃጢአተኛ ነኝ ፤ ዓመቱን ሙሉ አንተን ደስ አላሰኘሁህም ፤ ውስጤንም ጭምር ፤ ነገር ግን ከልቤ ደንዳናነትና ከኃጢአቶቼ የተነሣ ሳይሆን ከምሕረትህ እና ከርኅርኄህ የተነሣ እንድትረዳኝ እለምንሃለሁ፡ ጌታ ሆይ ‹‹ለምኑ ይሰጣችኋል፣ እሹ ታገኛላችሁ፤ አንኳኩ ይከፈትላችኋል›› ብለሃል፡፡ እናም እነሆኝ እየለመንኩ ነው፤ የምሕረትህንም ደጅ እያንኳኳሁ ነው፡፡ ‹‹ወደ እኔ የሚመጣውን ከቶ ከእኔ አላወጣውም›› ብለሃልና ጸሎቴን አትናቅ፡፡በቅድስት ድንግልና በመላእክትህ ሁሉ አማላጅነት መልስልኝ!! አሜን!" ለዘንድሮ ተፈታኝ ተማሪዎች እግዚአብሔር ከእናንተ ጋር ይሁን! ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ ጥቅምት 2014 ዓ.ም. ለዚህ ሰሞን ተፈታኞች ፈጣሪ መረጋጋትን ይሥጣችሁ። እመ ብርሃን ትከተላቹ አሜን ! @laha-maryam
Show all...
+ ተማሪዎች ፈተና ከመፈተናቸው በፊት ይህን ይጸልዩ + ቅዱስ ቄርሎስ ሣድሳዊ ዘእስክንድርያ የደረሱት +++ ጸሎት +++ ‹‹ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ‹‹በችግርህ ቀን ጥራኝ ፤ አድንሃለሁ አንተም ታከብረኛለህ›› ብለህ የአንተን መጠጊያነት መፈለግን ስላስተማርከኝ አመሰግንሃለሁ! አሁንም ጌታ ሆይ! በዚህ የፈተና ሰዓት ጥበብና ማስተዋልን ትሰጠኝ ዘንድ እማጸንሃለሁ፡፡ ይህን ፈተና በሰላም አልፍ ዘንድ ጸጋን (ሞገስን) ስጠኝ፡፡ ፈተናውን በምሠራ ጊዜ ጥልቅ የሆነ ሰላምህንና በረከትህን ስጠኝ፡፡ ጌታዬ ኢየሱስ ውጤት በሚሰጡኝ ጊዜ በመምህራኖቼ ዓይን መወደድን ትሰጠኝና ልባቸውን ታለሰልስልኝ ዘንድ እለምንሃለሁ፡፡ የከበርከው ጌታእኔ ኃጢአተኛ ነኝ ፤ ዓመቱን ሙሉ አንተን ደስ አላሰኘሁህም ፤ ውስጤንም ጭምር ፤ ነገር ግን ከልቤ ደንዳናነትና ከኃጢአቶቼ የተነሣ ሳይሆን ከምሕረትህ እና ከርኅርኄህ የተነሣ እንድትረዳኝ እለምንሃለሁ፡ ጌታ ሆይ ‹‹ለምኑ ይሰጣችኋል፣ እሹ ታገኛላችሁ፤ አንኳኩ ይከፈትላችኋል›› ብለሃል፡፡ እናም እነሆኝ እየለመንኩ ነው፤ የምሕረትህንም ደጅ እያንኳኳሁ ነው፡፡ ‹‹ወደ እኔ የሚመጣውን ከቶ ከእኔ አላወጣውም›› ብለሃልና ጸሎቴን አትናቅ፡፡በቅድስት ድንግልና በመላእክትህ ሁሉ አማላጅነት መልስልኝ!! አሜን!" ለዘንድሮ ተፈታኝ ተማሪዎች እግዚአብሔር ከእናንተ ጋር ይሁን! ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ ጥቅምት 2014 ዓ.ም. ለዚህ ሰሞን ተፈታኞች ፈጣሪ መረጋጋትን ይሥጣችሁ::
Show all...
የመስቀል ደመራ በዓል ታሪክና አከባበር በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! የመስቀል ደመራ በዓል ታሪክና አከባበር ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የሰውን ልጅ ከወደቀበት መርገም ያድነው ዘንድ ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም ተወልዶ በ33 ዓመቱ በራሱ ፈቃድ በመስቀል ላይ ተሰቀለ፡፡ በመገረፉ ቁስል እኛ ተፈወስን (1ጴጥ 2፥24):: በስቅለቱም ዲያብሎስን ድል ነሥቶ በወህኒ /በሲዖል/ ለነበሩ ነፍሳት ነጻነትን ሰበከላቸው (1ጴጥ 3፥18-19):: የሰው ልጅ በሙሉ ከዲያብሎስ ባርነት ፍጹም ነጻ ወጣ:: ሰላምንም ያደርግ ዘንድ ጥልንም በመስቀሉ ገድሎ ሕዝብና አሕዛብን በአንድ አካል ከራሱ ከእግዚአብሔር ጋር አስታረቀ (ኤፌ 2፥16)፡፡ ከፍተኛ ወንጀል የሠሩ ሰዎች ብቻ ይሰቀሉበት የነበረው መስቀል ከጌታ ስቅለት በኋላ የመዳን ምልክት ሆነ:: ዳሩ ግን ጌታ የተሰቀለበት መስቀል ተአምራትን በማድረጉ የታወኩ አይሁድ መስቀሉን ከሰዎች እይታ ለመሠወር ወሰኑ:: ጉድጓድ ቆፍረው ቀበሩት:: መስቀሉ የተቀበረበትን ቦታ ለ300 ዓመታት ያህል የቆሻሻ መጣያና ማከማቻም አደረጉት:: ምንም እንኳን አይሁድ ለጊዜው መስቀሉን ከዐይን ለመሰወር ቢችሉም ከክርስቲያኖች ልቡና ግን ሊያወጡት አልቻሉም:: የመስቀሉ ብርሃን በልቡናቸው የሚያበራ ክርስቲያኖች እየበዙ መጡ:: መስቀሉንም መፈለግ ጀመሩ:: የንግሥት እሌኒ ድካምና ፍሬ ንግሥት እሌኒ ልጇን ቆስጠንጢኖስን ከልጅነቱ ጀምሮ ስለ ክርስትና ሃይማኖትና ስለ ክርስቲያኖች መከራ ታስተምረው ስለነበር በክርስቲያኖች ላይ የነበረው አመለካከት በሮም ከነገሡት ቄሣሮች ሁሉ የተሻለ ነበር፡፡ ቆስጠንጢኖስ የሮም ንጉሠ ነገሥት ከሆነ በኋላ በ300 ዓመታት ውስጥ ለመጀመርያ ጊዜ ለክርስቲያኖች የነጻነት ዐዋጅ ዐወጀ፡፡ ክርስትናም ብሔራዊ ሃይማኖት ሆነች፡፡ ንግሥት እሌኒም የተፈጠረውን አመች ሁኔታ በመጠቀም የጌታችንን መስቀል ከተቀበረበት ለማውጣት በ327 ዓ/ም ወደ ኢየሩሳሌም ሔደች፡፡ ንግሥት እሌኒ ልጇ ቆስጠንጢኖስ ክርስቲያን ከሆነላት ወደ ኢየሩሳሌም ሔዳ መስቀሉን ለመፈለግ እንዲሁም በኢየሩሳሌም ያሉ ቅዱሳት መካናትንና አብያተ ክርስቲያናትን ለማሳነፅ ለእግዚአብሔር ተሳለች፡፡ ከዚህ በኋላ ቆስጠንጢኖስ አምኖ በ337 ዓ/ም ተጠመቀ፡፡ ቅድስት እሌኒም ወደ ኢየሩሳሌም ሔደች እንደደረሰችም ስለ ክብረ መስቀል መረመረች ጠየቀች፡፡ ቦታውን የሚያስረዳት ግን አላገኘችም፡፡ አይሁድ የተቀበረበትን ቦታ ለማሳየት ባይፈልጉም በኋላ ባደረገችው ጥረት አረጋዊው ኪራኮስ የጎልጎታን ኮረብታ አመላከታት ዳሩ ግን ኪራኮስ ዘመኑ ከመርዘሙ ጋር ተያይዞ በአካባቢው ከነበሩት ከሦስቱ ተራሮች ውስጥ መስቀሉ የሚገኝበት የትኛው እንደሆነ ለይቶ ማወቅ አልቻለም፡፡ ንግሥት እሌኒ ከሦስቱ ተራሮች የቱ እንደሆነ ለመለየት በእግዚአብሔር መልአክ እርዳታ ደመራ አስደምራ ብዙ እጣንም በመጨመርና በማቃጠል ጸሎት ተያዘ፡፡ የእጣኑ ጢስ ወደ ሰማይ በመውጣት በቀጥታ ተመልሶ መስቀሉ ባለበት ተራራ ላይ በማረፍና በመስገድ መስቀሉ ያለበትን ትክክለኛ ስፍራ አመለከታት፡፡ ቅዱስ ያሬድም ጢሱ ሰገደ ብሎታል፡፡ ከዚያም መስከረም 16 ቀን ቁፋሮው እንዲጀመር አዘዘች፡፡ ሰባት ወር ያህል ከተቆፈረ በኋላ መጋቢት 10 ቀን ሦስት መስቀሎች በአንድነት ተገኙ፡፡የክብር ባለቤት ጌታችን የተሰቀለበት የትኛው እንደሆነ ለማወቅ ተቸገሩ፡: መስቀሎቹን ወስደው በሞተ  ሰው በተራ ቢያስቀምጡ ጌታችን የተሰቀለበትና በዕለተ ዐርብ ተሰቅሎ የዋለበትና በደሙ መፍሰስ የተቀደሰው መሰቀል የሞተውን ሰው በማስነሣት በሠራው ተአምር ሌሎቹ ሁለቱ ታምራት ባለማድረጋቸው የጌታን መስቀል ለይቶ ማወቅ ተችሏል። እሌኒና ክርስቲያኖች ሁሉ ለመስቀሉ ሰገዱለት፡፡ በየሀገሩ ያሉ ክርስትያኖች ሁሉ የመስቀሉን መገኘት በሰሙ ጊዜ መብራት አብርተው ደስታቸውን በመግለጥ ለዓለም እንዲታወቅ አደረጉ፡፡ ንግሥት እሌኒ ለመስቀሉ ቤተ መቅደስ ከሠራችለት ጊዜ ጀምሮ በመስከረም 17 ቀን አሁን በኢትዮጵያ እንደሚከበረው በክርስቲያኖች ዘንድ መስቀል ይከበር ነበር። ግማደ መስቀሉ ወደ ኢትዮጵያ እንዴት መጣ?  የጌታ መስቀል ለብዙ ዓመታት በኢየሩሳሌም ከቆየ በኋላ ነገሥታት መስቀሉን ለመውሰድ ጠብ ፈጠሩ፡፡ በዚህ ጊዜ የአንጾኪያ፣ የኤፌሶን፣ የአርማንያ፣ የግሪክ፣የእስክንድርያ፣ የመሳሰሉት የሃይማኖት መሪዎች ጠቡን አበረዱት:: ከዚያም አያይዘው በኢየሩሳሌም የሚገኘውን የክርስቶስን መስቀል ለዐራት ከፍለው በስምምነት ተካፍለው ከሌሎች ታሪካዊ ንዋያተ ቅድሳት ጋር በየሀገራቸው ወስደው በክብር አስቀመጡት:: የቀኝ ክንፉ የደረሰው ለአፍሪቃ ስለነበር ከታሪካዊ ንዋየ ቅድሳት ጋር በግብፅ የሚገኘው የእስክንድርያ ፓትርያርክ ተረክቦ ወስዶ በክብር አስቀመጠው፡፡ ኢትዮጵያዊው ንጉሥ ዳግማዊ ዳዊት የግብፅ ክርስቲያኖች በአማሌቃውያን ከሚደርስባቸው ተጽዕኖ ነጻ እንዲወጡ በማድረጋቸው የግብፅ ፓትርያርክ የከበሩ ስጦታዎችን ላኩላቸው:: ንጉሥ ዳግማዊ ዳዊት ግን የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን የምትፈልገው ወርቅ ሳይሆን ጌታ የተሰቀለበትን መስቀሉን እንደሆነ ገለጹላቸው:: በመሆኑም የግብፅ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ግማደ መስቀሉን ከሌሎች ንዋየ ቅድሳት ጋር ለኢትዮጵያ ሰጥታለች:: ይህ ግማደ መስቀል በግሸን ማርያም ገዳም በእግዚአብሔር አብ ቤተ ክርስቲያን ሆኖ ኢትዮጵያን እየባረከ ይገኛል:: የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መስቀልን ከሐዋርያት በተማረችው መሠረት የወርና የዓመት በዓል ሠርታ ታከብረዋለች:: መስከረም 16 ቀን ደመራ ደምራ ጸሎትና ምሥጋና ታቀርባለች። ቅዱስ መስቀል ከተቀበረበት መሬት በእሌኒ አማካኝነት መገኘቱን ስታስብ በአሁኑ ዘመን ከብዙ ሰዎች ልቡና የተሠወረው መስቀል እንዲገለጥላቸው ትጸልያለች:: በመስቀል የሚገኘውን በረከት እየተቀበለች በመስቀል የሚመሰለውን መከራ ሁሉ ትታገሣለች:: መስቀል በካህናት በምእመናንና በምእመናት ልቡና ተስሏል:: በአንገታቸውና ልብሳቸውም መስቀል አለ:: ሥራ ሲጀመርና ምግብ ሲቀርብ በመስቀል አምሳያ ይማተባል:: መስቀል ለሁሉም ነገር መጀመሪያና መጨረሻ  ነው:: “እኔን መከተል የሚወድ ቢኖር ራሱን ይካድ መስቀሉንም ተሸክሞ ይከተለኝ” (ማቴ 16፡24) እንዳለ ጌታችን ቤተ ክርስቲያናችን ዕለት ዕለት መስቀሉን ትሸከማለች። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በየዓመቱ መስከረም 16 ቀን የምትደምረው ደመራ አገራዊ አንደምታም አለው:: የመስቀል ደመራ በተባበሩት መንግስታት የትምህርት: የሳይንስና የባህል ድርጅት (ዩኔስኮ) እውቅና ተሰጥቶት ዓለም አቀፋዊ ቅርስ ተብሎ ተመዝግቧል:: ከሀገር ቤት ርቀን የምንገኝ ኢትዮጵያውያንም የበዓሉን ታላቅነት ለልጆቻችንና ለምንኖርበት የኖርዌይ ኅብረተሰብ ማስረዳትና የበዓሉ ታዳሚ እንዲሆኑ ማድረግም ይጠበቅብናል። «የመስቀሉ ቃል ለሚጠፉት ሞኝነት ለእኛ ለምንድን ግን የእግዚብሔር ኃይል ነው» (1ቆሮ 1፥18) እያልን ልናከብረውና ልንጠብቀው ይገባናል። ወስብሐት ለእግዚአብሔር! @laha_maryam
Show all...
5b1c367a68cc492254c60eab6221e954.mp39.53 KB
“ደጋግመህ ኃጢአት ብትሠራም ደጋግመህ ንስሐ ግባ፡፡ ቤተክርስቲያን ሐኪም ቤት እንጂ ፍርድ ቤት አይደለችምና፡፡” ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ @yedingelsitota21 @yedingelsitota21 @yedingelsitota21
Show all...
Photo unavailableShow in Telegram
Choose a Different Plan

Your current plan allows analytics for only 5 channels. To get more, please choose a different plan.