ሥነ ግጥም
Open in Telegram
925
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
-830 days
Posts Archive
925
ሐበሻ ነኝ...
.
.
.
ለመሞት ሲሆን ነፍስ የማያጥረኝ
ቁስል እንደ ልጥ ያስተሳሰረኝ
ታሪኬ ሁሉ መድማት መጨነቅ
ህመም ይቀዳል ወዜ ቢጨመቅ
.
.
ሐበሻ ነኝ
.
.
ቆርጬም ባልጥል ተስፋን እንደ እትብት
እጄ ላይ ደስታ የማይሰነብት
ህይወት ሳልቀምሳት የምትበርድብኝ
ከመኖር ይልቅ ሞት የሚያምርብኝ
.
.
ሐበሻ ነኝ
.
.
ከሰው ለይቶ በደም የሰራኝ
ለትግል ብቻ መርጦ የጠራኝ
ከታፈንኩበት ጭስ ሆኜ ሳመልጥ
ለግዜር ለሰይጣን የማልጨበጥ
.
.
ሐበሻ ነኝ ...
✍Tadiwos alemayehu
925
አልመከር አልን መካሪ በዝቶ...
ልብ ሂያጅ ቢያስስ የመጣን ትቶ
የእጅ እየጣልን የመሬት ለቅመን ብናንጠለጥል
መከራ መክሮ እያልመለሰን፡ ነዶ ቢያቃጥል
እያደር ጥሬ ከርሞ ልጅነት ናናው ካጓጓን
ከደገሰችው ልንካፈላት የሕይወት ሰርጓን
ምለናል እና ሐዘን መቃመስ ፡ እንባ መጠጣት
አንችልም በቃ :ከአንዳንዱ ገደል ሞክረን መውጣት!
ካፒቴነረ ግራ
925
ማነው የገነዘው የእመቤቴን ስጋ
እሳት አይደለም ወይ በሆዷ የረጋ!
ማን አረፈች ቢሉ እሷ ሁለቱም ነች
:
ልጄ ልጄ አሏት ድንግል ስለሆነች
እናቴም ተባለች ጌታን ስላቀፈች።
አረፈች መሰለኝ ጠፋ ድምጿ ባገር
እሷ እኮ በፊትም አትወደም መናገር !
ተከደነ አሉ ጌታን ያየ አይኗ
እሷ እኮ በፊትም መች ትላለች ቀና!
ምነው በየደጁ
ሰው ሁሉ ያለቅሳል ባይኑ እየሳላት
:
ለእናቷም ለአምላኳም አንድ ብቻ እኮ ናት!
🥺
(elias shitahun)
925
ተመስገን ዝም ብለን ላለፍናቸው ሀዘኖች ተመስገን ፈገግ ብለን ላለፍናቸው መገፋቶች ተመሰገን ከልባችን ለሳቅንባቸው ቀኖች ተመስገን መናገር ፈልገን ዝም ብለን እንኳንም ዝም አልን ላስባሉን ሁኔታዎች ተመስገን ጊዜ ለቀየራቸው ወዳጅነቶች ተመስገን እግዜር ለሰጠን ባለ ዕንቁ ልብ ሰዎች ተመስገን ላገኘነው ጠንካራ አቋማችን በዚ ሁሉ መውደቅ መነሳት ውስጥ ያልተወን አምላክ ይመስገን የተሻለ ነገ ይመጣል😊☺️
𝓲𝓶𝓪𝓱
925
"የብልጦች ሀገር ሁሉም መላጦች ናቸው"
'ብልጥ ለብልጥ ዐይን ፍጥጥ': ይሄ የማይስማማኝ አባባል ነው፡፡ ብልጥ ነን ባዮች መፋጠጥ ከጀመሩ በመፋጠጥ አያቆሙም፡፡ ተረቱ ብልጦች ተፋጠው አርፈው ቁጭ የሚሉ ያደርጋቸዋል፡፡ ጮሌዎች እየተያዩ ዝም አይባባሉም፡፡ ለመበላለጥ መሽቀዳደም ደንባቸው ነው፡፡
('ብልጥ' የሚለው ቃል ውስጥ የ'መበላለጥ' ፅንሰ-ሀሳብ ከመጀመሪያው ተካቷል)
ቀዳሚውና ተከታዩ ማን እንደሆነ መፈራረድ አለ፡፡ እስኪ ከእኩያ ቃል አቅጣጫ የተረቱን አጨራረስ እንይ፡፡
የብልጥ ተመሳሳይ 'ምላጭ' የሚለው ቃል ቢሆን፤ የሰከነ ተረት ከፈለግን መሆን ያለበት 'ምላጭ ለምላጭ ይላላጭ' ነው፡፡
ይሄም ጥሩ ተከታይ ታሪክ ይኖረዋል፡፡ የብልጦች ሀገር ሁሉም መላጦች ናቸው፡፡
ዛሬ ዛሬ አንዳንዶች ለመንደር ነጋ ጠባ ማቶስቶስን 'ንቃት' እያሉት ነው፡፡ በእንግሊዝኛ ሲያሳምሩት ናሽናል ኮንሸስነስ (National Consciousness) ይሉታል፡፡ ትክክሉ (tribal Consciousness) እንደሆነ ቢገባቸውም፣ በፅንሰ-ሃሳብና በመረጃ አልሆን ቢል በቃላት ያፋፉታል፡፡
በሌላ አባባል ብልጥ ሆኑ ማለት ነው፡፡ ብልጥ ራዕይ የለውም፡፡ በትክክል ምላጮች ናቸው፡፡ መአት የዚህ አይነት ምላጮች ሲሰባሰቡ አገሩ ጎፈሬ ማብቀል ይከብደዋል፡፡ ይሄን የሚደግፉ፣ በትንንሽ ዶላር የሚፎግሩን ባዴዎች ከዕለታት አንድ ቀን የተለየ ጭምብል ባጠለቁ ነጋዴዎች ለሁላችንም ሚዶና ጸጉር ሊሸጡልን ብቅ ይላሉ፡፡
***
📖የስንብት ቀለማት
አዳም ረታ
925
ለጮርቃ ሰው ላልበሰለ
በሂወት ጦር ላልቆሰለ
ባይድን እንኳን ላልታመመ
ባይደርስ እንኳን ላላለመ
ምን እያሉ ያወጉታል?
እርሱ ባይተው ይተዉታል
ለኔ ዓይነቱ ለከልካላው
ባይወድ እንኳን ለማይጠላው
ለሚያፈቅረው ጅል ለሆነ
ለማይረባው ለባከነ
እለት እለት
ለሚያገጠው የላይ ላዩን
ለሚውጣት ዓይነ ማዩን
ሆድ ሲብሰው
ለሚያለቅሰው ስቅስቅ ብሎ
ለማይዋሸው በእናት ምሎ
ለሚመከር
ጠላት ውደድ ለተባለው
እንኳን ለጠላት
ልቡ ለወዳጅ መሆን ላልቻለው
ምን እያሉ ያወጉታል?
አይዞህ እንጂ ምን ይሉታል?
........!
የአስቆሮጡ ይሁዳ
925
ይህም ኑሮ ሆነና
እኛም ሰዎች ተባልንና
ጦር - ህልማችን ላይ ቢሰቀሰቅ
ህይወት - እጃችን ላይ ብትሞቀሙቅ
ትኩስ ተስፋችን ሻገተ
ፀአዳ ልባችን ሸተተ
.
.
መከራ እንደ ሽርጥ ታጠቅን
ሰላም እንደ ጡት ተነጠቅን
ሀገር እንደቋት ተቦደሰች
ፅንስ እንደ እንሽርት አፈሰሰች
.
.
ቅጣት እንደዶፍ ይወርዳል
ሞት እንደ ኑሮ ይለመዳል
መሸሸጊያ መግቢያ የለም
ሰማይ ምድሩ ተጠምቷል ደም
ጫካው ገደሉ አይከለክል
ቤቱ ምሽጉ አያስጠልል
.
.
ልክ እንደ ትል እንደ ጉንዳን
ወጥቶ መቅረት ተፈርዶብን
የሚገድለን እንዳይራራ
እግራቸው ስር እኛን ሰራ
ታዲዎስ አለማየሁ
925
ፈውስ እየጠሉ ለሞት መስገብገብ
በፀበል ውሀ ቡትቶ ማጠብ
ዘራፍ ተብሎ የጠቅል አሽከር
ፀፀት በጫንቃ ይዞ መሽከርከር
ቆሎ እየናቁ አሻሮ መዝገን
ለግዞት ኑሮ ቆርጦ መጀገን
ምን ይሉት ግፍ ነው ምን ይሉት ፍርጃ
ለራስ ላይ በደል የለውም ምልጃ?
እንጃለት ብቻ ፤ አከራረሙን
አያያዝ ጠፍቶት ቢቀናው እርሙን
ያመናትላል መና እንደ ኩርማን
ቅዳሴ ቆሞ ለርሀብ ቁርባን
እንጃለት ብቻ እንጃለት እሱን
እርም እየበላ ይገፋል ምሱን
እንጃለት ብቻ...
ታዲዎስ አለማየሁ
925
(በውቀቱ ስዩም)
ከማዶ ሚመጣው ዘመድ ነው እንግዳ
ከላይ የተለጋው ኳስ ነው ወይስ ናዳ፣
ብየ መች ጠየኩኝ
መጪውን ጠበኩት
ድንጋይ ላይ ቁጭ ብዬ፣ጸሐይ እየሞኩኝ፣
መከራም አላጣም፣ተድላም አልጎደለኝ፣
ደንታ ነው የሌለኝ፣
በአካል በስሜትም ታሞ ላገገመ፣
ወድቆ ለተነሳ እየደጋገመ፣
ለገንዛ ጉድጓዱ፣አጽሙን ለሚለቅም፣
ሞቱም ብርቅ አይደለም፣ትንሳኤም አይደንቅም።
925
ደራሲስ አውቃለሁ
ባለቅኔ አውቃለሁ በቃላት የሚጽፍ
:
አይቼ አላውቅም
ህይወት የሚቀይር እንደሚካኤል ክንፍ።
- - - - / - - - -
የዓይን እማኝ
ነኝ!
(elias shitahun)
925
አንዳንድ ነገሮችም ሳይ በጣም ይገርመኛል እንደ ሀገር እንደማህበረሰብም የወረደ የተጨማለቀ ሆነናል ሀበሻ ሲባል የሚመጣልኝ defination አሁን ለራሴም ይገርመኛል ስርዓት አልባነት እና ልቅነት ባህል አድርገናል የ5ብር ፓኬጅ ሞልተም smart ስልክ ስለያዝን በ social media መጨማለቅ ራሳችንን እንደ አዋቂ እንድንቆጥር እያደረገን ነው እኔ ምለው ሀገራችን ብለን የምንመካበት ኩራታችን ብለን የምናወራለት ህዝብ የሚወደደው ምኑ ነው? እውነት እዚች ሀገር ላይ የሚያጓጓው ነገርስ ምንድነው? አውሮፓ አሜሪካ....እኮ ቢቀብጡም ሰርተው ነው ደሞኮ ማን እንደሀገር ሌላውን ስላላያችሁት ነው የምትሉ ሰዎች እስኪ ይሄ ይለየናል በሉ ባህላችን አትሉም መቼም? የትኛው ባህል ተደብቆ የኖረው የመሰዳደብ ባህል? ወይስ አብሮ መብላት መጠጣት እንዳትሉ በቀን 1 ለመብላት እንኳን ችግር የሆነበት ሀገር ላይ እየኖርን አሁን ድንበር ተከፍቶ እዚህ ሀገር መኖር የማትፈልጉ ውጡ ቢባል እኮ የሚቀር ያለ ይመስል😒
925
ያልሆነውን ናችሁ ተብለን ስንከሰሰ ባልሰማ ለራሳችን ጥብቅና ሳንቆም የምናልፈው እውነት ጠበቃ ስለማያስፈልጋት ዳኛም የቀረበለትን ማስረጃ ስለሚያምን ቢሆንስ?
𝓲𝓶𝓪𝓱
925
ጠብቄሽ ነበረ
[ደበበ ሰይፋ]
መንፈሴን አንጽቼ
ገላዬን አጥርቼ
አበባ አሳብቤ
አዱኛ ሰብስቤ
ጠብቄሽ ነበረ ...
ብትቀሪ ጊዜ
መንፈሴን አሳደፍኩ
ገላዬን አጎደፍኩ
አበባው ደረቀ
አዱኛው አለቀ
ብትቀሪ ጊዜ ...
የጣልኩብሽ ተስፋ
እኔን ይዞኝ ጠፋ
925
..ታውቂያለሽ መውደዴ ካንቺ ብቻ አልነበረም ፡ አንቺን ከሚያስታውሱኝ ሁነቶች ፡ ወደ አንቺ ከሚያደርሱኝ መንገዶች ጋርም ጭምር እንጂ ...
Woretaw wase
