cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

Ministry of labor and skills

Show more
Advertising posts
854
Subscribers
No data24 hours
-17 days
+130 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

በአሁን ሰዓት  1Bitcoin  72,000$ ነው #Notcoin ..........    #Notcoin..... 💵💵💵💵💰💰💰💰🤑🤑🤑 ዕድላችሁን #ቶሎ ተጠቀሙበት #NOTCOIN        ✅ ብዙ ሰው Notcoin አሁን #Earn እያደረጉ ነው እናንተስ #ምን እየጠበቃቹ ነው  ትንሽ ጊዜ ነው የቀረው  10 #Million Notcoin = 950$ -2000$  ነው እንዳያመልጣቹ ፍጠኑኑኑኑኑ ✅ ከስር ባለው #Link መሠረት ቶሎ          ብላቹ Notcoin ሰብስቡቡ👇👇 👇👇👇 https://t.me/notcoin_bot?start=r_577266_34367090 ቴሌግራም ጉሩፓችን👇👇👇👇 👇👇👇 @Zolla23 https://youtube.com/@mulualemdergu?si=-oRy0LCsTIf-9A13 https://t.me/zollatub
Show all...
Notcoin

Probably nothing @notcoin

👍 2
https://t.me/notcoin_bot?start=r_577266_34367090 🎁 +2.5k Notcoin as a first-time gift 🎁🎁🎁 +50k Notcoin if you have Telegram Premium @PremiumBot
Show all...
Notcoin

Probably nothing @notcoin

💻📣 ሁሉንም የሥራ ማስታወቂያ በአንድ ቦታ ! የሥራ ማስታወቂያች በመላው ሀገራችን ላይ በተለያዩ ጋዜጦች :የቴሌግራም ቻናሎች እና የስራ ማስታወቂያ ድህረገጾች ላይ በተለያዪ ሙያዎችና ድርጅቶች ይወጣሉ እነዚህን ብዙ ሺ የስራ ዕድሎችን ካሉበት ሆነው ተንቀሳቃሽ ስልኮትን ብቻ በመጠቀም በአንድ ቦታ ማግኘት የምትችሉበትን ቴክኖሎጂ ከኢትዮጵያ ሥራ ገበያ መረጃ ስርዓት አንዱ ከሆነው ናሽናል ጆብ ፖርታል ፕላትፎርም (National Job Portal) ላይ በመግባት ማግኘት የምችሉበት ዕድል ተመቻችቷል! 👉 ቀጥታ ድህረ ገፃችን ላይ በመሄድ ይመዝገቡ :https://lmis.gov.et/auth
Show all...
👎 2
-- ማሳሰቢያ -- የሥራና ክህሎት ሚኒስቴርዜጎች በሃገር ውስጥ እና በውጭ በሚፈጠር የሥራ ዕድል በህጋዊ መንገድ መብታቸው ደህንነታቸው እና ጥቅማቸው ተጠብቆ መስራት እንዲችሉ የሰለጠነ እና በከፊል የሰለጠነ የሰው ሃይል ስምሪት ስምምነት በመፈፀም ለፓስፖርት እና ለጤና ምርመራ ከሚከፈል ክፍያ ውጪ በነፃ አገልግሎት እንዲያገኙ እያደረገ ይገኛል፡፡ በዚህ አገልግሎት በኢትዮጵያ የሥራ ገበያ መረጃ ስርዓት የባዮሜትሪክስ መረጃዎቻቸውን የሰጡ፣ ማንነታቸው የተረጋገጠ፣ ስልጠና የወሰዱ ከ189,430 በላይ ዜጎች ባለፉት 6 ወራት ወደ ተለያየ ሃገር ተሰማርተዋል፡፡ በስምሪቱ ከፍተኛ ስኬት ያስመዘገቡ ክልሎች እንደሚከተለው ይቀርባሉ፡፡  ኦሮሚያ ክልል = 94,106  አማራ ክልል = 39,205  ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል = 27,500  ደቡብ ኢትዮጵያ ክልል = 14,947  አዲስ አበባ ከተማ መስተዳደር = 6,331  ደቡብ ምዕራብ ክልል = 3,613  ሲዳማ ክልል = 1,430  ትግራይክልል = 822  ሐረር ክልል = 286  አፋር ክልል = 205  ድሬዳዋ ከተማ መስተዳደር = 193  ሱማሊ ክልል = 193  ቤንሻንጉል ክልል = 181  ጋምቤላ ክልል = 83 በዚህ በውጭ ሃገር የሥራ ስምሪት በመላው ኢትዮጵያ የሚገኙ ዜጎች ተጠቃሚ እንዲሆኑ አስፈላጊውን ግብዓት በማሟላት ከዚህ በፊት ወደ ውጪ ሃገር ሰራተኛ አሰማርተው የማያውቁ ክልሎች ጭምር የዕድሉ ተጠቃሚ የሚሆኑበትን ምቹ ሁኔታ የፈጠረ በመሆኑ የስምሪቱ ተጠቃሚ መሆን የምትፈልጉ ዜጎች በአቅራቢያቹ በቀበሌ ደረጃ በሚገኙ አንድ ማዕከላት በመሄድ እንድትመዘገቡ ጥሪ እናቀርባለን:: ከዚህ ውጪ የሚደረግ ወደ የትም ሃገር "ለስራ እናሰማራቸዋለን" እና "በቀላሉ ስራ እንድታገኙ እናማክራቸዋለን” የሚል ቅስቀሳ ዜጎችን ለከፋ አደጋ የሚጥል እንዲሁም ከፍተኛ የገንዘብ ማጭበርበር በመሆኑ ራሳቸውን እንድትጠብቁ እናሳስባለን፡፡ የባዮሜትሪክስ ምዝገባ የሚያከናውኑ አንድ ማዕከላትን ዝርዝር (https://lmis.gov.et/ossc-lists ) ከዚህ ላይ ማግኘት ይቻላል፡፡ የሥራ ባለቤት እርስዎ ነዎት!!
Show all...
👍 3👎 1
20 ሚሊዮን ወጣቶችን ተጠቃሚ የሚያደርግ ፕሮጀክት ስምምነት ተፈረመ። በስምንት ዓመት የትግበራ ሂደት 20 ሚሊየን ወጣቶችን በልቦና ውቅር አሰልጥኖ ለማብቃት ያለመ የለውጥ ትውልድ ፕሮጀክት ስምምነት ተፈረመ። ስምምነቱን የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ዲኤታ ወይዘሮ ሙና አህመድና የብሬክስሩ ትሬዲንግ ዳይሬክተር አቶ አብዱልፈታህ ሁሴን ተፈራርመዋል። የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ዶክተር ኤርጎጌ ተስፋዬ በመድረኩ ላይ እንደገለጹት:-እንደ ሀገር ለውጥ ለማምጣት ወጣቶች የልቦና ውቅራቸው በሥነ ሥርዓትና ሥነ ምግባር የተዋቀረ ሊሆን ይገባል። መንግስት ሁሉን አቀፍ የወጣቶች ተሳትፎና ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ እየሰራ ይገኛል ያሉት ዶክተር ኤርጎጌ በተለይም ወጣቶች በመልካም ስብዕና የታነጹ ለማድረግ ከተለያዩ አካላት ጋር እየተሰራ ነው ብለዋል። የለውጥ ትውልድ ፕሮጀክት 20 ሚሊየን ወጣቶችን አሰልጥኖ ለማብቃት ያለመ መሆኑን ጠቅሰው ፕሮጀክቱ ለስምንት ዓመት የትግበራ ሂደት ያለው በመሆኑ በ10 ሺህ አሰልጣኞች ስልጠና የሚሰጥበት መሆኑን ገልጸዋል። የብሬክስሩ የቦርድ ሰብሳቢ አቶ ነጻነት ዘነበ በበኩላቸው፤ የለውጥ ትውልድ ፕሮጀክት ዓላማ ባለራዕይ ቅን አጋዥ ብቃት ያለውና ባለጸጋ ትውልድ ለሀገር ማፍራት ነው። ፕሮጀክቱ  በ2023 ዓ.ም 20 ሚሊዮን ወጣቶችን በማሰልጠን 2 ሚሊየን የተለወጡ ወጣቶችን በማፍራት አንድ ሚሊየን የሥራ እድሎችን ለመፍጠር ያለመ መሆኑን ገልጸዋል። ስልጠናው በመጀመሪያው ዓመት በ13 ከተሞች ላይ ለ10 ሺህ ወጣቶች እንደሚሰጥ ገልጸው ፕሮጀክቱ ወጣቱ ለራሳቸው ዋጋ እንዲሰጡ በስነ ምግባር የታነጹ እንዲሆኑ በማድረግ ሰርቶ መለወጥ የሚችል ወጣት ለማፍራት እንደሚያስችል አስረድተዋል። #ኢፕድ Share share
Show all...
"ፕሮግራሙ ወጣቶች በተጨባጭ የሥራ ልምድ ብቁና ተወዳዳሪ ለመሆን የሚያስችል ክህሎትን የሚያላብሳቸው ነው፡፡" ክቡር አቶ ሰለሞን ሶካ የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ብቃት የወጣቶች የሥራ ላይ ልምምድ ፕሮግራም የመጀመሪያው ዙር ማጠቃለያ እና የሁለተኛ ዙር ምዕራፍ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር በድሬደዋ ከተማ ተከናውኗል። በመድረኩ ላይ መልዕክት ያስተላለፉት በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የሥራ ፣ ሥራ ስምሪትና ገበያ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ሰለሞን ሶካ እንደገለፁት፤ መንግስት የሥራ አጥነት ምጣኔን ለመቀነስ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ነው። የሥራና ክህሎት ሚኒስቴርም የሥራ ዕድል ፈጠራ ሥራው ክህሎት መር እንዲሆን አቅጣጫ አስቀምጦ በዘርፉ ሰፊ ርብርብ በማድረግ ላይ ይገኛል፡፡ በዚህም ሚኒስቴር መ/ቤቱ በመደበኛ የሥራ ዕድል ፈጠራ ከሚያከናውናቸው ተግባራት በተጓዳኝ ከዓለም ባንክ ጋር በመተባበር "ብቃት የወጣቶች የሥራ ላይ ልምምድ ፕሮግራም" ተግባራዊ በማድረግ  ትምህርታቸውን በተለያየ ምክንያት ያቋረጡ ወጣቶችን ተጠቃሚ ሲያደርግ ቆይቷል፡፡ ይህ ፕሮግራም ወጣቶች በሥራ ገበያ ላይ ተወዳዳሪ የሚያደርጋቸውን አቅም ከመገንባት አንፃር በርካታ ልምድና ተሞክሮዎች የተገኘበት ነው፡፡ ፕሮግራሙ ወጣቶች በተጨባጭ የሥራ ልምድ ብቁና ተወዳዳሪ ለመሆን የሚያስችል ክህሎትን የሚያላብሳቸው ነው ብለዋል። ለፕሮግራሙ ስኬት አበርክቶ ለነበራቸው የዘርፉ አመራሮች፣ ባለድርሻ አካላትና ባለሙያዎች ምስጋና ያቀረቡት ክቡር ሚኒስትር ዴኤታው በፕሮግራሙ አንደኛ ዙር ትግበራ የተገኙ ተሞክሮዎችን ቀምሮ በሁለተኛው ዙር የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ መረባረብ እንደሚገባቸው አሳስበዋል። የድሬዳዋ ከንቲባ ክቡር አቶ ከድር ጁዋር በበኩላቸው፣ መርሃ ግብሩን በጋራ እውን ላደረጉት ለሥራና ክህሎት ሚኒስቴር እና ለዓለም ባንክ ምስጋና አቅርበው በከተማ የጀመረው መርሃ ግብር ወደ ገጠር አካባቢም እንዲሰፋ ጠይቀዋል። የድረዳዋ ከተማ አስተዳደር የሥራና ክህሎት እና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው በመድረኩ ላይ እንደገለፁት፤  ብቃት የሥራ ላይ ልምምድ ከተሳተፉት ወጣቶች መካከል 96 በመቶ የሚሆኑትን ቋሚ የስራ  ዕድል ባለቤት ማድረግ ተችሏሏ። ከዚህ ባለፈም ለሁለተኛ ዙር ትግበራ መሰረት የጣለ፣ የመንግስት እና የግሉን ዘርፍ አጋርነት ያጎለበተ እና የሥራ ላይ ልምምድ ባህል እንዲዳብር ያስቻለ ስኬታማ ፕሮግራም ነው ብለዋል። የካቲት 09/2016 ዓ.ም የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ለወቅታዊ ትኩስ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር
Show all...
Log in or sign up to view

See posts, photos and more on Facebook.

በኢትዮጲያ የሥራ ገበያ መረጃ ስርዓት(E-LMIS) የተሻለ አፈጻጸም ያስመዘገቡ አንድ ማዕከላት ተግባራዊ እየተደረገ በሚገኘው የኢትዮጵያ የሥራ ገበያ መረጃ ስርዓት (E-LMIS) በተለያዩ የኢትዮጵያ ክልሎች የባዮሜትሪክስ ምዝገባ ካደረጉት ውስጥ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸውን ተመዝጋቢዎች የመዘገቡ 30 የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫ ጣቢያዎች እና ሠራተኞችን እውቅና ስንሰጥ በታላቅ ደስታ ነው !! የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የኢትዮጲያ የሥራ ገበያ መረጃ ሥርዓቱን ለማዘመን ባደረገው ጥረት ወደ ሥራ ከገቡ አንድ ማዕከላት መካከል የላቀ አፈፃፀም በማስመዝገብ ግንባር ቀደም በመሆናችሁ እንኳን ደስ አላችሁ። ይህ የላቀ አፈፃፀም የምትሰጡትን አገልግሎት ፈጣን፣ ቀልጣፋና ፍትሃዊ በማድረግ የተገልጋዩን እርካታ ለማሳደግ እና ሥራውንም ለማዘመን ካላችሁ ቁርጠኝነትና ትጋት የሚመነጭ መሆኑ እሙን ነው። የእናንተ ትጋትና ቁርጠኝነት የኢትዮጵያ የሥራ ገበያ መረጃ ስርዓቱን ወደ ላቀ ደረጃ ለማድረስ እና በቴክኖሎጂ የታገዘ የሰው ሀብት አስተዳደር፣ የክህሎት ልማት እና የሥራ እድል ፈጠራ ላይ የሪፎርም ስራዎችን በማከናውን ረገድ ትልቅ ሚና ይጫወታልና ስለምታደርጉት አስተዋፅዖ ከልብ እናመሰግናለን ! የሥራ ባለቤት እርስዎ ነዎት 𝙨𝙝𝙖𝙧𝙚 𝙨𝙝𝙖𝙧𝙚 𝙨𝙝𝙖𝙧𝙚 𝙨𝙝𝙖𝙧𝙚
Show all...
2👍 1👎 1
"ሥራ በክህሎት ይመራ!" "ሥራ በክህሎት ይመራ!" በሚል መሪ ሀሳብ በሠመራ እየተካሄደ የሚገኘው የ2016 በጀት ዓመተ የመጀመሪያ ስድስት ወራት የዕቅድ አፈፃፀም የግምገማ እና የምክክር መድረክ እንደቀጠለ ነው። በመድረኩ የክህሎት ልማት፤ የሥራ፣ ሥራ ስምሪትና ገበያ እንዲሁም የአሠሪና ሠራተኛ ዘርፎች የየክልሉን የዕቅድ አፈፃፀም እያቀረቡ ይገኛል። ይህን ተከትሎ በክህሎት ልማት፣ ሥራ ዕድል ፈጠራ እና የአሠሪና ሠራተኛ ዘርፉ ላይ የተገኙ መልካም አፈፃፀሞችን ማላቅ፣  ዝቅተኛ አፈፃፀሞችን ማሻሻል እና ምርጥ ተሞክሮዎችን መለየት የሚያስችል ውይይት የሚካሄድ ሲሆን የቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎች ይለያሉ ተብሎ ይጠበቃል። ጥር 30/2016 ዓ.ም የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ለወቅታዊ ትኩስ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር በድረገጽ፡- http://mols.gov.et/ Youtube https://youtube.com/@mulualemdergu?si=-oRy0LCsTIf-9A13
Show all...
👍 1
"ኢትዮጵያ ከመቼውም ጊዜ በላይ ሰላምና መረጋጋትን እንዱሁም ሥራ ፈጣሪ ዜጎችን የምትፈልግበት ወቅት ላይ ትገኛለች።" ክቡር አቶ አወል አርባ የአፋር ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ርዕሰ መስተዳድር የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ከክልል እና ተጠሪ ተቋማቱ ጋር የሚያካሂደው  የ2016 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ስድስት ወራት ዕቅድ አፈፃፀም የግምገማ እና የምክክር መድረክ በአፋር ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት መካሄድ ጀምሯል። በመድረኩ ላይ መልዕክት ያስተላለፉት የአፋር ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ርዕሰ መስተዳድር ክቡር አቶ አወል አርባ እንደገለፁት፤ ኢትዮጵያ ከመቼውም ጊዜ በላይ ሰላምና መረጋጋትን እንዱሁም ሥራ ፈጣሪ ዜጎችን የምትፈልግበት ወቅት ላይ ትገኛለች። ድህነት፣ ሥራ አጥነትና ህገ ወጥ ስደት የህዝባችን መሠረታዊ ከሚባሉት ችግሮች መካከል ዋና ዋናዎቹ ናቸው። ይህንን ትርጉም ባለው መልኩ ለመቀነስ የጋራ ርብርብን ይጠይቃል። "ሥራ በክህሎት ይመራ!" በሚል መሪ ሀሳብ የሚካሄደው ይህ መድረክ ይህንና መሰል ችግሮችን በመፍታት ሰላምና መረጋጋት እንዲሠፍንና የታቀደው ልማትና ብልፅግና እውን እንዲሆን ፋይዳው የላቀ ነው ብለዋል። የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የሥራ፣ ሥራ ሰምሪት እና ገበያ ዘርፍ ሚንስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ንጉሡ ጥላሁን በበኩላቸው፤ መድረኩ ሰኬቶቻችንና የጋጠሙ ተግዳሮቶች የምንፈትሽበት እና ለቁልፍ ችግሮቻችን ቁልፍ የሆኑ መፍትሄዎች የሚቀመጡበት ነው ብለዋል። ጥር 30/2016 ዓ.ም የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር https://youtube.com/@mulualemdergu?si=-oRy0LCsTIf-9A13
Show all...
👍 3
"ባለፉት ስድስት ወራት ለአንድ ሚሊዮን ዜጎች የሥራ ዕድል ተፈጥሯል፡፡ ከ150 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች ደግሞ በውጭ አገራት የሥራ ዕድል ስምሪት ተመቻችቶላቸዋል፡፡ ኢንቨስትመንትን በማሳብ ረገድም ከ 1 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር በላይ ኢንቨስትመንት መሳብ ተችሏል፡፡" ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ጥር 28/2016 ዓ.ም የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ለወቅታዊ ትኩስ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴርhttps:
Show all...
youtube.com/@mulualemdergu?si=-oRy0LCsTIf-9A13
https://t.me/+VzyNHNBcj-tQQu6d