4 038
Subscribers
+824 hours
+347 days
+22230 days
Posts Archive
4 038
"ፈተናው ከስርቆትና ከኩረጃ ነጻ ሆኖ ተጠናቋል" ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋ
………………………………………………………
ሀምሌ 28/2015 ዓ.ም (የትምህርት ሚኒስቴር) የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ የፈተናውን መጠናቀቅ አስመልክቶ ዛሬ በሰጡት መግለጫ የ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል አገር አቀፍ ፈተና ከማንኛውም ፈተና ስርቆትና ኩረጃ ነጻ በሆነ መልኩ ተጠናቋል ብለዋል።
ሚኒስትሩ ፈተናው በተሳካ ሁኔታ መከናወኑን እና ተማሪዎችም ፈተናውን በሰላማዊና በተረጋጋ ሁኔታ መውሰዳቸውን ገልፀዋል።
በአጠቃላይ 840 ሺ 859 የማህበራዊ ሳይንስና የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች በ2 ሺ 785 የፈተና ጣቢያዎች ተፈትነዋል።
ከሀምሌ 19 እስከ ሀምሌ 28 ቀን 2015 ዓ.ም በሁለት ዙር በተሰጠው ፈተና ከ30ሺ 438 የሚበልጡ ፈተና አስፈጻሚዎች መሰማራታቸውንም አመላክተዋል፡፡
በህግ ጥላ ስር ላሉ 515 ተፈታኞችና በኢትዮጵያ ለሚማሩና በውጭ አገር ለሚኖሩ ተፈታኞች ከነሀሴ 23 እስከ 26 ድረስ የ12ኛ ክፍል ፈተና የሚሰጣቸው መሆኑንም አስረድተዋል፡፡
በትግራይ ክልል ከ2012 ዓ.ም የ2ኛ ክፍል አጠናቀው በተፈጠረው ችግር ምክንያት ያልተፈተኑ ተማሪዎች በአሁኑ ወቅት ማጠናከሪያ እና የማካካሻ ትምህርት እየተሰጣቸው በመሆኑ ከመስከረም 29 እስከ ጥቅምት 2 ቀን 2016 ዓ.ም ድረስ ፈተናውን ለመስጠት ዝግጅት እየተደረገ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡
በፈተናው በጉዞ ሂደት ያጋጠመ ቀላል የትራፊክ አደጋ፣ በህመም ፣ ተንቀሳቃሽ ስልክ እና ያልተፈቀዱ ቁሳቁሶችን ወደ ፈተና ጣቢያ ይዞ መግባት በመሞከር እና የስነ ምግባር ችግሮች ማጋጠማቸዉን ገለጸው ከዚህ ባሻገር በፈተና ሂደት የጎላ ችግር አለማጋጠሙንም ጠቁመዋል።
በጎንደር ዩኒቨርስቲ 3 ካምፓሶች ትናንት ባጋጠመ ችግር 16 ሺህ ተማሪዎች ፈተናውን ሳይፈተኑ መቅረታቸውን የጠቆሙት ሚኒስትሩ በቀጣይ በሚመቻች መርሀ ግብር የሚፈተኑ መሆናቸውንም አስታውቀዋል።
MOE
4 038
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የመጀመሪያው ራስ ገዝ ዩኒቨርስቲ ሆነ
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ሀምሌ 28/2015 ዓ.ም (የትምህርት ሚኒስቴር) የሚኒስትሮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው 23ኛው መደበኛ ስብሰባ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲን የራስ ገዝ ማቋቋሚያ ደንብ ላይ ተወያይቶ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የመጀመሪያው ራስ ገዝ ዩኒቨርስቲ እንዲሆን ወስኗል።
ውሳኔው የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የአካዳሚክ ነጻነት እንዲረጋገጥ፣ ከፖለቲካዊም ሆነ አስተዳደራዊ ጣልቃ ገብነት ነጻ ሆነው የመማር ማስተማር እና የምርምር ሥራዎችን በላቀ መልኩ መፈጸም እንደሚያስችላቸው የታመነበት በመሆኑ እንደሆነ ተገልጿል።
በዚሁ መሰረትም የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ራስ ገዝ ሆኖ አካዳሚያዊ እና አስተዳደራዊ ነፃነቱ ተጠብቆ መንቀሳቅስ እንዲችል፣ በትምህርት ዘርፍ ለተጀመረው የሪፎርም እንቅስቃሴ ፈር ቀዳጅ ሆኖ እንዲወጣ እድል ይፈጥርለታል ተብሏል።
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የራስ ገዝ ዩኒቨርስቲ ስርዓትን በቀዳሚነት ተግባራዊ እንደሚያደርግና ለሌሎች ዩኒቨርሲቲዎችም ተምሳሌት እንደሚሆን ይጠበቃል።
4 038
የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ የተፈጥሮ ሳይንስ ፈታና ተጠናቀቀ
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 28፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ የተፈጥሮ ሳይንስ ፈተና መጠናቀቁን የትምህርት ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡
የትምህርት ሚኒስትር ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) ጉዳዩን አስመልክተው በሰጡት መግለጫ÷ ፈተናው ከኩረጃና ስርቆት በጸዳ መልኩ መሰጠቱን አንስተዋል፡፡
በፈተና ወቅት የተከለከሉ ቁሶችን ወደ መፈተኛ ቦታዎች ይዞ መግባት፣ የቡድን ፀብ ማንሳት፣ የፈተና ወረቀት ሳይመልሱ ለመውጣት መሞከርና መሰል ችግሮች መስተዋላቸውን ተናግረዋል።
በፈተና ሒደቱ የሁለት ተፈታኝ ተማሪዎች ህይወት ማለፉን እና በጉዞ ወቅት በተሽከርካሪ አደጋ 13 ተማሪዎች ላይ ጉዳት እንደደረሰባቸው ገልጸዋል።
በሌላ በኩል በትግራይ ክልል በ2012 ዓ.ም የ12ተኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና መውሰድ ሲገባቸው ያልወሰዱ ተማሪዎች በቀጣይ ፈተና ላይ እንደሚቀመጡ ተናግረዋል፡፡
በክልሉ በቀጣይ መስከረም ወር የመልቀቂያ ፈተና እንደሚሰጥ ገልጸው÷አሁን ላይ የማጠናከሪያና የማካካሻ ትምህርት እየተሰጠ ነው ብለዋል፡፡
በታሪኩ ለገሰ
4 038
ቀን 24/11/2015 ዓ.ም
ደሴ/ኢትዮጵያ
አስደሳች ዜና
ለደሴና አካባቢዎች ከ9-12ኛ ክፍል ተማሪዎች በሙሉ
🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏
የመምህር አካለ ወልድ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ከ2016 ዓ.ም የትምህርት ዘመን ጀምሮ በትምህርት አቀባባል የተሻሉ ተማሪዎች የሚያስተናግድ Special classes በደሴ ከተማ ትምህርት መምሪያ እና ደሴ ከተማ አስተዳደር አማካኝነት የተፈቀደ በመሆኑ እንኳን ደስ ያላችሁ እያልን በደሴ ከተማ እና አካባቢዎች ያሉ ከ9-12ኛ ክፍል ተማሪዎችን በ2015 ዓ.ም ውጤት እና በመግቢያ ፈተና የሚቀበል መሆኑን በማወቅ አስፈላጊውን ዝግጅት እንድታደርጉ እያሳወቅን አጠቃላይ የመማር ማስተማር ሂደቱ ከአዳሪ ትምህርት ቤት የሚለየው በመኝታ እና ምግብ አገልግሎት ብቻ መሆኑን በማወቅ የእድሉ ተጠቃሚ እንድትሆኑ ከወድሁ እያሳወቅን አጠቀላይ የምዝገባ ሂደት በቀጣይ የምናሳውቅ መሆኑ ይታወቅ።
We Strive for quality !!
4 038
ለክረምት የማጠናከሪያ ትምህርት
እንግሊዝኛ በመምህር አብይ ፀጋዬ
ኬምስትሪ በመምህር መሸሻ ታደሰ
ሒሳብ በመምህር ታደሰ መኮነን
ለመማር የተመዘገባችሁ ና አዲስ ለመመዝገብ የምትፈልጉ ሁሉ ዛሬ ትምህርት የተጀመረ ሲሆን ቀጣይ ክላስ ሰኞ መሆኑን አዉቃችሁ በሰአቱ መምህር አካለወልድ ት/ቤት ትገኙ ዘንድ እናሳስባለን
4 038
መምህር አካለወልድ ት/ቤት በአሁን ሰዓት የ12ኛ ክፍል ናቹራል ብሔራዊ ፈተና ተፈታኞችን ወደ ወሎ ዩንቨሪስቲ በመሸኘት ላይ ይገኛል ለሁሉም በደሴ ከተማና በመላው ሀገራችን ለሚገኙ ተፈታኞች በሙሉ የመምህር አካለወልድ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት መምህራንና ሰራተኞች መልካም ፈተና እንዲሆንላችሁ ከልብ እንመኛለን።
4 038
ከቀጣዩ አመት ጀምሮ በግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የሚተገበር አስገዳጅ መመሪያ ተዘጋጀ
የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የመውጫ ፈተና ከሚወስዱ ተማሪዎቻቸው ቢያንስ 25 በመቶዎቹን ማሳለፍ ካልቻሉ የትምህርት መስኮቻቸው እንዲታጠፉ የሚያስገድድ መመሪያ ተግባራዊ ሊደረግ ነው።
የትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን ከ2016 ዓ.ም ጀምሮ በግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ተግባራዊ የሚደረግ አዲስ መመሪያ መዘጋጀቱን ገልጿል።
በባለስልጣኑ የከፍተኛ ቴክኒክና ሙያ ትምህርት ክትትል እና ቁጥጥር መሪ ስራ አስፈፃሚ አቶ ከፍያለው አድነው ለፋና ብሮድካስቲንግ እንደተናገሩት፥ የመማር ማስተማር ስራው ጥራቱ የተጠበቀ እንዲሆን አዲስ መመሪያ እና መስፈርት ተዘጋጅቷል።
የሚታዩ ክፍተቶችን በመሙላት የሚጠበቀውን ደረጃ እና ጥራት ማስጠበቅ ያስችላል የተባለው አዲስ መመሪያ እና መስፈርትም ከ2016 ዓ.ም ጀምሮ ተግባራዊ ይደረጋል ነው ያሉት።
በመመሪያው የትምህርት ጥራቱን ለማስጠበቅ በርካታ መለኪያዎች የተቀመጡ ሲሆን፥ አንዱ የመውጫ ፈተናን የሚመለከት መሆኑንም አስረድተዋል።
በዚህም እያንዳንዱ ተቋም ለመውጫ ፈተና ከሚያስቀምጣቸው ተማሪዎች በየትምህርት መስኩ ቢያንስ 25 በመቶዎቹ ማለፍ እንደሚጠበቅባቸው በማንሳት ይህ ካልሆነ ግን የትምህርት ፕሮግራሙ ይሰረዛል ብለዋል።
በተጨማሪም የትምህርት ተቋማቱ ለማስተማር የሚመዘግቧቸውን ተማሪዎች ለባለስልጣኑ የማሳወቅ ግዴታ አለባቸው ተብሏል።
ዘንድሮ በተሰጠው የዩኒቨርሲቲ የመውጫ ፈተና ከግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የመውጫ ፈተናውን ከወሰዱ 72 ሺህ ተማሪዎች ውስጥ የማለፊያ ውጤት 50 እና ከዛ በላይ ያመጡት 12 ሺህ 422 ወይም 17 ነጥብ 2 በመቶ ብቻ መሆናቸው ይታወቃል።
4 038
ዩኒቨርሲቲዎች ሁሉንም የትምህርት ዓይነቶች እየሰጡ እንደማይቀጥሉ የትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል፡፡
===========================
ሚኒስቴሩ የውስጥ አቅምና የአካባቢ ኢኮኖሚያዊ ኮሪደሮችን መሠረት በማድረግ የዩኒቨርሲቲዎችን ተልዕኮና የትኩረት መስክ ልየታ እየሰራ መሆኑን ገልጿል፡፡
በዚህም ዩኒቨርሲቲዎች አሁን የሚሰጧቸውን ፕሮግራሞች ይዘው እንደማይቀጥሉ ተገልጿል፡፡
ዩኒቨርሲቲዎችን በትኩረትና በተልዕኮ የመለየት ሥራው ከ2014 ዓ.ም ጀምሮ በስፋት እየተሰራበት መሆኑን የትምህርት ሚኒስትር ዲኤታ ሳሙኤል ክፍሌ (ዶ/ር) ገልጸዋል፡፡
የኢትዮጵያ ዩኒቨርሲቲዎች አመሠራረታቸው በተልዕኮ የተለየ እንደነበር ያስታወሱት ሚኒስትር ዲኤታው፤ ባሕር ዳር (ፖሊ ቴክኒክ)፣ ጎንደር (ጤና ሳይንስ)፣ አርባ ምንጭ (ውሃ ጥናት)፣ ሐረማያ (ግብርና)... እየተባሉ መደራጀታቸውን ጠቁመዋል፡፡
"አሁን ያሉን ዩኒቨርሲቲዎች የሚሰጡትን ፕሮግራሞች በሙሉ ይዘው አይቀጥሉም፡፡ በጣም ጥሩ የሆኑባቸውን ውስን ፕሮግራሞች ብቻ ይዘው ነው የሚቀጥሉት" ብለዋል፡፡
ዩኒቨርሲቲዎች በተለዩባቸው ፕሮግራሞች ላይ በትኩረት ለመሥራት አንዳንድ ፕሮግራሞችን የመዝጋትና ሠራተኞችን የማዘዋወር ስትራቴጂካዊ ዕቅድ ማዘጋጀታቸውን ጠቁመዋል፡፡ #ሪፖርተር
➧ የምርምር ዩኒቨርሲቲዎች (8)
➧ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲዎች (2)
➧ የተግባር ሳይንስ ዩኒቨርሲቲዎች (15)
➧ አጠቃላይ ዩኒቨርሲቲዎች (21)
➧ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ (1)
MOE
4 038
የ12ኛ ክፍል የማህበራዊ ሳይንስ ብሔራዊ ፈተና ተጠናቀቀ
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 21፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ባለፉት ሶስት ቀናት ሲሰጥ የነበረው የ12ኛ ክፍል የማህበራዊ ሳይንስ ብሔራዊ ፈተና በሰላምና በስኬት መጠናቀቁን የትምህርት ምዘና እና ፈተናዎች አገልግሎት አስታውቋል፡፡
የትምህርት ምዘና እና ፈተናዎች አገልግሎት በሂደቱ ለተሳተፉ ሁሉ ምስጋና አቅርቧል፡፡
የተፈጥሮ ሳይንስ ተፈታኞች ቅዳሜና እሁድ ወደ መፈተኛ ማዕከል (ዩኒቨርሲቲ) እንደሚገቡ እና መጪ ሰኞ ደግሞ ገለጻ (ኦሬንቴሽን) እደሚሰጣቸው ተጠቁሟል፡፡
ፈተናቸውን ከማክሰኞ ጀምሮ እስከ አርብ ድረስ እንደሚወስዱም ከአገልግሎቱ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡
FBC
4 038
Repost from N/a
dormitory Placement Natural science male and Female (2015).xlsx3.56 KB
