en
Feedback
Tariku Abera

Tariku Abera

Open in Telegram

ኦርቶዶክሳዊ የወንጌል አገልግሎት

Show more
5 173
Subscribers
No data24 hours
-87 days
-2530 days
Posts Archive
photo content

photo content
+1

ሕዝቡ አብዛኛው እስካሁን ይህቺ የካህናቱ የጎጥ ሹክቻ አልገባችውም አብዛኛው ሕዝብ በየዋሕነት ለእመቤቴ ማርያም ነው የምታገልላለት እያለ ብርዱን ይጠጣል ካህናቱ ግን ዞር ብለው ብርዝ ይጠጣሉ።አብዛኛው ወጣትም ለቤተክርስቲያን ክብር እየታገለ እንዳለነው የሚነግሩት ይህቺን የቸርች ፓለቲካ ግን አይነግሩትም።በየዋሕነት ሲጮኽና ሲላተም የሚውለው ወጣት በጣም ብዙ ነው።እስካሁን አልባነነም።ጎጥኝነቱ ተመችቷቸው ወሎ፣ጎንደር፣ሸዋ ብለው ከካህናቱ በስተጀርባ ያሉ ትንሽ ፓለቲካ የገባቸው ሰዎች በሁሉም ወገን ደግሞ አሉ።አብዛኛው ሕዝብ ግን እስካሁን ተጋርዶበታል። አሁን ከሕዝቡ የሚጠበቀው መፍትሔ ሦስት አማራጭ ነው። 1ኛ ካህናቱን አንድ ሁኑ ብሎ መክሮና ገስጾ ማስማማት 2ኛ ካህናቱን በሙሉ አታስፈልጉንም ብሎ ጠርጎ ማባረር 3ኛ ቤተክርስቲያኒቱ እንድትከፈል የክፋት ተባባሪ ሆኖ ቤተክርስቲያኒቱን ለሁለት መክፈል። የለንደን ደብረ ጽዮን ካህናትን ለማስማማት የመጡት ብፁዓን ጳጳሳት በካህናቱ ግትርነትና እልኽኝነት እጅግ ልባቸው አዝኖ አልቅሰው ዕንባቸውን ረጭተውባቸው ነው የሄዱት በሁለቱም ወገን ያሉት ካህናት ይህንን ሐቅ ቤተክርስቲያን ዓውደ ምሕረት ላይ ለሕዝብ ተናግረዋል።ይህ የፈሰሰ ዕንባ የእግዚአብሔርን የቁጣ ፍርድ ሳያመጣባችሁ በፍጥነት ንስሐ ግቡ። «ልቡን እያሳተ እግዚአብሔርን የሚያመልክ የሚመስለው ማንም ቢኖር የእርሱ አምልኮ ከንቱ ነው።» ተብሎ በቅዱስ መጽሐፍ ተጽፏል።ያዕቆብ 1፥26 መ/ር ታሪኩ አበራ ክፍል 5 ይቀጥላል።

† ለንደን ደብረ ጽዮን ለሁለት የመከፈል አደጋ ከፊት ለፊቷ ተጋርጧል † ★የቤተክርስቲያኒቱ ትልቅ ፈተና የካህናቱ በጎጥ የመከፋፈል ችግር ነው።★ ክፍል 4 ይህንን ክፍል ስጽፍ ልቤ ክፉኛ እያዘነ፣ዓይኔም በዕንባ እየተሞላ ነው።የለንደን ደብረ ጽዮን የዓመታት እንቆቅልሽ እንዳይፈታ ትልቅ እንቅፋት ሆኖ የከረመው የካህናቱ በሦስት ጎጥ የመከፋፈል ችግር ነው።ክርስቶስ ከነገድና ከቋንቋ በደሙ ዋጅቶ አንድ ያደረገውን ሕዝብ የብሔር ፓለቲካና ጎጠኝነት የቤተክርስቲያንን አንድነትና የሃገርን ክብር ክፉኛ እየተፈታተነ ይገኛል። ይህ ለዘመናት በቤተክርስቲያኒቱ ውስጥ ሥር ሰዶ ውስጥ ለውስጥ እርስበርስ ሲያባላና ሲያናክስ የኖረ ጎጠኝነት ዛሬ ላይ ፊትለፊት ለይቶለት ቤተክርስቲያኒቱን ለከፋ የመለያየት አደጋ አፋፍ ላይ አድርሷታልና ሳይቃጠል በቅጠል ተረባርበን ልናስቆም ይገባል። የለንደን ደብረ ጽዮን ካህናት የሸዋ ተወላጅ፣የወሎ ተወላጅና የጎንደር/የጎጃም ተወላጅ በሚል በሦስት ጎጥ የተከፋፈሉ ናቸው። በአሁን ሰዓት የወሎና የጎንደር ተወላጅ ካህናቱ በአንድነት ሕብረት ፈጥረው የቆሙ ሲሆን የሸዋ ተወላጅ በሚል ያለው ክፍል ደግሞ ለብቻ ያለው ነው። ምንም እንኳ በቤተክርስቲያኒቱ ውስጥ ለጭቅጭቅና ለመለያየት ምክንያት የሆነው የውስጥ መተዳደሪያ ረቂቅ ደንብ ቢሆንም በፍርድ ቤት ክርክር የቤተክርስቲያኒቱ የንብረትና ሃብት አስተዳደር ስርዓት በእንግሊዝ ሃገር ሕግ መሠረት ከቻሪቲ ኮሚሽን ወደ CIO ሥርዐት ቢዘዋወርም።የካህናቱ እርስበርስ መለያየትና እልህ መጋባት ግን የፍርድቤቱን ውሳኔና የመፍትሔ አቅጣጫ እርባና ቢስ እያደረገው ይገኛል። እውነት ለመናገር ገና ከጅምሩ ካህናቱ የፍቅር ሰዎች ቢሆኑና ስለ ክርስቶስ መስቀል ብለው ሁሉን እርግፍ አድርገው ከብሔር ጎጠኝነት ወጥተው አንድ ቢሆኑ ኖሮ የቤተክርስቲያኒቱ የውስጥ መተዳደሪያ ደንብ በዚህ ደረጃ ለፍርድ ቤት የሚያበቃ ሕዝቡንም ለሁለት የሚከፋፍል አልነበረም። የካህናት መንፈሳዊ ሥልጣንና አገልግሎት በቅድስናና በፈሪሃ መለኮት ቢጠቀሙበት እንኳን የምድሩን እንቆቅልሽ የሰማዩን ደጅ የሚከፍቱበትና የሚዘጉበት መንፈሳዊ ሐብት ተሰጥቷቸው ነበር። አለመታደል ሆነና ካህናቱ እርስበርስ ጥርስ ስለተናከሱና ዓይንህ ለአፈር የተባባሉ ስለሆኑ የመተዳደሪያ ደንቡ ምክንያትና ሽፋን ሆኗቸው ሕዝቡንም ለሁለት ከፈሉት፣ ከ2 ሚሊየን ፓውንድ በላይ ማለትም ከ260 ሚሊየን ብር በላይ ለጠበቃ ክፍያ ሕዝቡ እንዲያወጣ አድርገው አሁንም አንታረቅም፣አንስማማም ብለው ቤተክርስቲያኒቱን ለሁለት የመከፈል አፋፍ ላይ አድርሰዋታል።ካህናቱ ራሳቸውን ዝቅ አድርገው «ሊከተለኝ የሚወድ ቢኖር ራሱን ይካድ መስቀሉንም ተሸክሞ ይከተለኝ ያለውን።»የክርስቶስ መለኮታዊ መመሪያ በሕይወታቸው ቢተገብሩ የቤተክርስቲያኒቱ ችግር በአንድ ቀን ይፈታ ነበር ሕዝቡንም በይቅርታና በፍቅር አንድ ማድረግ ይቻል ነበር።ካህናቱ ግን ራሳቸውን መካድ አልቻሉም ጎጠኝነት፣የክብር ጉዳይ፣የስልጣን ናፍቆት፣የገንዘብ ጥማት እልህ አጋብቷቸዋል።ጌታ መስቀሌን ተሸከሙ አላለም ሊከተለኝ የሚወድ ቢኖር መስቀሉን ይሸከም ነው ያለው እያንዳንዱ ሰው የራሱ መስቀል አለው ይህም ስለክርስቶስ ፍቅር የሚቀበለው የውስጡ ፈተናና ከውጪ የሚመጣበት መከራ ነው ካህናቱ ስለ ክርስቶስ ፍቅር የውስጣቸውን የሥጋ ፈተናና ከንቱ ምኞት ከውጪ የሚመጣባቸውንም መከራ እየተቀበሉ ቤተክርስቲያንን አንድ ለማድረግ ከመታገል ይልቅ ጎጠኝነት በልባቸው እንደ ጣዖት ነግሦባቸው ቤተክርስቲያንን በአሕዛብ ፊት እያዋረዷት ይገኛሉ። ካህናት አባቶቼና ወንድሞቼ ሆይ እኔ ታናሽ ወንድማቹ በክርስቶስ ደም እማጸናችኋለሁ እባካቹ በሁለቱም ወገን ያላችሁ ሁሉን እርግፍ አድርጋችሁ ተውትና በፍቅር አንድ ሁኑ ሁሉም ኃላፊ ጠፊ ነው።ሁሉን ትተን ወደ መቃብር የምንወርድ ደካማ ፍጥረቶች ነንና እልህ መጋባቱን ተውት።እልህና ጥላቻ ለማናችሁም እይጠቅምም። ወሎ ለሸዋ ወንድሙ ነው፣ ጎንደር ለሸዋ መከታው፣ጎጃም ለሸዋ አለኝታው ነው።ሸዋ ለወሎም ሆነ ለጎንደር እንዲሁም ለጎጃም ክንዱ ነው።እንደ አንድ አማራ ቆማችሁ ለቤተክርስቲያንም ሆነ ለሃገር ደጀን ሁኑ እንጂ እርስበርስ እየተባላችሁ ሕዝቡንም ከፋፍላችሁ ትውልድና ታሪክ ሲወቅሳችሁ አትኑሩ።በአሁን ሰዓት በኢትዮጵያ ወሎውም፣ጎንደሩም፣ጎጃሙም ሸዋውም እንደ አንድ አማራ መከራውን እየተቀበለ ብዙ ዋጋ እየከፈለ ባለበት ሰዓት እናንተ እርስበርሳችሁ እንዲህ ተከፋፍላችሁ ሕዝቡንም እርስበርሱ ስታባሉት መክረማችሁ እጅግ የሚያሳፍር ጥቁር አሻራ ነው።ይልቁንም እናንተ አንድ ሆናችሁ ሕዝቡንም አንድ አድርጋችሁ ሃገር ቤት በየቦታው እንደ ቅጠል እየረገፈ፣በረሃብና በጦርነት እየተፈናቀለ ለከፍተኛ ረሃብና እልቂት እየተዳረገ ላለው የአማራው ሕዝብ ተረባረቡለት።ወገኖቻችን በረሃብ እያለቁ እናንተ እዚህ ለእንግሊዝ ጠበቃ የምትረጩት ገንዘብ በወገናችሁ ደም ላይ እየቀለዳችሁ መሆኑን ግልጽ ማሳያ ነውና ወደ ልባችሁ ተመለሱ።ለስሙ ሁላችሁም የእንግሊዝ ፓስፓርት ይዛችሁ የእንግሊዝ ዜጋ ነኝ እያላችሁ እርስበርስ በጎጥ መከፋፈላችሁ የ21ኛው ክፍለ ዘመን ደናቁርት ተብላችሁ በታሪክ መዝገብ ላይ ስማችሁ መስፈሩ አይቀርም። እምቢ አሸፈረኝ ብላችሁ አንዳችሁ በአንዳችሁ ላይ ጣት እየጠቆማችሁ በመለያየታችሁ ከጸናችሁ መጨረሻችሁ የሚሆነው የቤተክርስቲያኒቱን ገንዘብና ንብረት ለሁለት መከፋፈልና መለያየት ነው።ይህም ከአባላቱ 75% ከተስማማ ነው።ይሄ ደግሞ በጣም የከፋ ነውር ነው በፍርድ ቤት ሕንጻ ቤተክርስቲያኑ ቢሸጥ ምን ያህል ሊያወጣ ይችላል ተብሎ መገመቱ አይቀርም ቤተክርስቲያኒቱ ካለችበት ሰፈርና ከህንጻው ስታንዳርድ፣ከጀርባ ያሉ ክፍሎችና ጋርደኑ ተደማምረው እስከ 10 ሚሊየን ፓውንድ እንኳ ቢገመት ተገንጥሎ ለሚወጣው ቡድን ግማሹን ሂሳብ እየከፈላችሁ እንድትኖሩ ፍርድቤት ይወስናል።በጣም አስተውሉ ህንጻ ቤተክርስቲያኑን ለመግዛት በደጉ ጊዜ ሁሉም ሕዝብ አንድሆኖ እያለ 1.7 ሚሊየን ብር ለማሰባሰብ ስንት ዓመት እንደፈጀባችሁ አስቡ።በፍርድ ቤት ስትካሰሱ ደግሞ 2 ሚሊየን ፓውንድ ለመሰብሰብ ከ12 ዓመት በላይ እንደፈጀባችሁም አትርሱ።አሁን ደግሞ ተገንጥሎ ለሚወጣው ቡድን 5 ሚሊየን ፓውንድ ለመክፈል ሌላ 10ና 15 ዓመት ይፈጅባችኋል።የሚያሳዝነው ደግሞ ይህንን ብር አምጣ የሚባለው ይህው መከረኛ ሕዝብ ነው።ካህናት እባካችሁ ሰውን ባታፍሩ እግዚአብሔርን ፍሩ ወደ ልባችሁ ተመለሱ እግዚአብሔር የሰጣችሁን እንጀራ በፍቅር በጋራ ተመገቡ እልህና ጎጠኝነት ለከፋ ኪሳራ ይዳርጋችኋል።አሁን ባለው ዕድሜያችሁ ላይ እስኪ 15 ዓመት ጨምሩበትና አስቡት ቤተክርስቲያንን ከፋፍላችሁ እንበላለን ብላችሁ ባሰባችሁት ዕድሜ ላይ ምናልባትም ቆማችሁ ማገልገል የማትችሉበት ደረጃ ላይ ትደርሳላችሁና ከዚህ ኪሳራ ላይ ከመውደቃችሁ በፊት ነገን ዛሬ ላይ ቆማችሁ ተመልከቱ።ለስልጣን የምትቋምጡም ከክርስቶስ ዝቅ ማለትን ልመዱ አንዱ ቡድን የጣለበትን ሲከፍል ሌላኛው ቡድን አዲስ ቤተክርስቲያን ለመቋቋም የተፈረደለትን ገንዘብ ለማግኘት ለዓመታት እየተቆነጠረ ሲንጠባጠብለት በመጠበቅ የካህናቱ ሕይወት እጅግ አስቀያሚና አሰልቺ የልመና ሕይወት ሆኖ በከንቱ ይገባደዳልና እባካችሁ አርቃችሁ አስቡ። ከሕዝቡ የሚጠበቀው መፍትሔ ሦስት ነው።

photo content
+7

† በለንደን ደብረ ጽዮን የአባቶች ከባድ ርግማን አለ † “የአባት ርግማን አጥንት ይሰብራል ፣ የእናት ርግማን መሠረት ይነቅላል።” ክፍል 3 በክፍል 2 ጽሑፍ እንደገለጽኩት በለንደን ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን ለረዥም ዓመታት ሰላም፣ፍቅር፣አንድነት ጠፍቶ ካህናት ከካህናት ጋር ምዕመናን ከምዕመናን ጋር በጸብ ተለያይተው በፈረቃ ቅዳሴ መቀደስ ከተጀመረ ከ 10 ዓመት በላይ መሆኑን ገልጫለሁ።ይህ ጉዳይ በቅዱስ ሲኖዶስ፣በአስታራቂ ሽማግሌዎችና በእንግሊዝ ከፍተኛ ፍርድቤት ለመፍታት ተሞክሮ ምንም መፍትሔ የጠፋለት ችግር በጸሎትና በምህላም ቢሞከር እግዚአብሔር መልስ አልሰጥ ብሎ እስካሁን ድረስ ግራ በመጋባት ውስጥ እንገኛለን። በመንፈሳዊ ዕይታ የችግሩን እንቆቅልሽ ስንመረመር ግን በክፍል 2 እንደ ጠቀስኩት በግፍ የተገደሉት የሊቀ ጳጳሱ የአቡነ ዮሐንስ ደም ለዚህ ሁሉ መከራ ምክንያት እንደሆነ አብራርቻለው። በዚህ ክፍል የምናየው ሌላኛው የችግሩ ምክንያት ደግሞ የአባቶች ርግማን ነው።ብፁዓን አባቶች በዚህ ደብር እጅግ መሪር ርግማን ተራግመው ሄደዋል። ነገሩ እንዲህ ነው ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ በ2002 ዓ.ም(አ.አ.አ) በየካቲት ወር ወደ እንግሊዝ ሃገር ከስድስት ሊቃነ ጳጳሳት ጋር መጥተው ነበር።የመጡበትም ዋነኛ ዓላማ አንደኛ እንግሊዞች ከመቅደላ በዝርፊያ የወሰዷቸውን በርካታ ቅዱሳት መጻሕፍት፣ቅዱሳት ታቦታትና ልዩ ልዩ የሃገር ቅርሶች ለኢትዮጵያ እንዲመለሱ የእንግሊዝን መንግስትና የሚመለከታቸውን አካላት ለማነጋገር ሲሆን በሁለተኛ ደረጃ በለንደን በምትገኘውን ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን ተገኝተው ከብፁዓን አባቶች ጋር ሕዝቡን ለመባረክ ቀድሰው አቁርበው ወንጌል ሰብከው በስደት ያለውን ሕዝብ በቃለ እግዚአብሔር ለማጽናናት ሲሆን ከዚሁ ጋር ተያይዞ በለንደን የሚገኙ የካሪቢያን ተወላጅ የሆኑ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሃይማኖት ተከታይ የሆኑ ካህናትንና ምዕመናን ለመባረክ ወንጌል ለማስተማር ነበር ። እጅግ በሚያሳዝን ሁኔታ ፓትርያርኩና ብፁዓን አባቶች ወደ ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን ግቢ ውስጥ ሲገቡ ከምዕመናኑ ከፍተኛ የሆነ ተቃውሞ ገጠማቸው።ቲማቲምና እንቁላል እየወረወሩ ፓትርያርኩንና አባቶችን መቷቸው ሁሉም አረጋውያን አባቶች ደንግጠው ግራ ገብቷቸው ወደ ቤተክርስቲያን ውስጥ ሲገቡ ቤተ መቅደስ ውስጥ ሳይቀር ጫማ እየወረወሩ አባቶችን መቷቸው፣የጸሎት መጻሕፍትንና ቤተክርስቲያን ውስጥ የነበሩ መጽሐፍ ቅዱሶችን እየወረወሩ እናንተ ወያኔዎች ከቤተክርስቲያናችን ውጡ እያሉ መቷቸው የዓይን እማኞች እንደሚሉት የፓትርያርኩን እጅ ጠምዝዘው ሰዓታቸውን ሁሉ ከእጃቸው ላይ አውልቀው ወስደዋል። ሁሉም አረጋውያን አባቶች ቤተክርስቲያን ውስጥ እጅግ አምርረው አልቅሰዋል ያንንም ሕዝብና ቦታውን ረግመዋል።በኋላም ለፓሊስ ተደውሎ ፓሊሶች አባቶችን አጅበው ለማስወጣት ቢሞክሩም ከአቅማቸው በላይ እስኪሆን ድረስ ከፍተኛ ሁከትና ተቃውሞ ነበር በኋላም የእንግሊዝ ፓሊሶች ተጨማሪና ኃይልና ውሾችን ጨምረው በብዙ ትግል አባቶችን ወደ መኪና ሲያስገቡ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ የነበሩበትን መኪና ዘለው በጫማ ጥፊ ሲመቱ የነበሩ ሰዎችም ነበሩ። እንግዲህ እነዚህ አባቶች መሪር ዕንባቸውን ረጭተው በከባድ ርግማን ሐዝነው ከሄዱ ጀምሩ በዛ ቤታ በረከት፣ሰላም፣ፍቅር፣አንድነት ጠፍቶ ይኽው ሕዝቡ እርስበርሱ እየተካሰሰ፣እንደ ጠላት በዓይነ ቁራኛ እየተያየ በየፍርድ ቤቱ እየተንከራተተና ገንዘቡን ለጠበቃ እየረጨ የመከራ ሕይወት እየገፋ ይገኛል። እግዚአብሔር የምሕረት ፊቱን አልመልስ ብሎ የሚጸለየው ጸሎት፣የሚደርሰው ምህላ፣የሚያዘው ሱባዔ ሁሉ ከደመና በታች የቀረው ይሄ ያልሻረ ጽኑ ርግማን በቦታው ላይ ስላለ ነው።መጽሐፍ ቅዱስ እንዲህ ይላል። “በአባቷ፡የምታላግጥን፡የእናቷንም፡ትእዛዝ፡የምትንቅን፡ዐይን፡የሸለቆ፡ቍራዎች፡ይጐጠጕጧታል፥አሞራዎችም፡ይበሏታል።” ምሳሌ 30፥17 ስለዚህ እንደ እኔ አስተያየትና ምክር የለንደን ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም እንቆቅልሽ ተፈትቶ እውነተኛ ሰላምና አንድነት ሊመጣ የሚችለው በግፍ የፈሰሰው የአቡነ ዮሐንስ ደምና የአባቶች ርግማን እንዲሽር በቅዱስ ሲኖዶስ የአዋጅ ቀኖናና ንስሐ ታውጆ በእንደዚህ ዓይነት ርግማን ጊዜ ሊጸለይ የሚገባውን ጸሎት ቅዱስ ሲኖዶስ አዝዞ በቦታው ላይ ተጸልዮ እውነተኛ ሥርየት ሲደረግ ብቻ ነው።አሊያ በፍርድቤትም ሆነ በየፓሊስ ጣቢያው በመሮጥ የሚመጣ ሥርነቀል መፍትሔ የለም ትርፉ ከንቱ መባከና ገንዘብን ለበላተኛ መበተን ብቻ ነው። መ/ር ታሪኩ አበራ ክፍል 4 ይቀጥላል

photo content
+2

† ብፁዕ አቡነ ዮሐንስን ማን ገደላቸው ? † «የወንድምህ ደም ከምድር ወደ እኔ ይጮኻል» ዘፍ4፥10 ክፍል 2 በክፍል 1 ጽሐፍ ስለ ለንደን ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን አመሠራረት ታሪካዊ ደኃራውን ተምልክተናል በዚህ ክፍል ደግሞ በቤተክርስቲያኒቱ ለዓመታት ሰላምና መረጋጋት የጠፋበትን ምክንያት በጥቂቱ እንመለከታለን። የርዕሰ አድባራት ለንደን ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም ካህናት በጸብ ለሁለት ተከፍለው በፈረቃ መቀደስ ከጀመሩ 10 ዓመታትን አስቆጥረዋል በቤተክርስቲያንቱ የተፈጠረው አስተዳደራዊ አለመግባባት ሕዝቡን እርስበርሱ ከከፋፈለውና ሆድና ጀርባ ካደረገው ደግሞ 12 ዓመታትን አስቆጥሯል።ይህ አስተዳደራዊ ችግር እንዲፈታ ያልተሞከረ መፍትሔ የለም የእንግሊዝ ከፍተኛ ፍርድ ቤት በሁለቱም ወገን ያለውን ጥያቄና አለመግባባት ግራና ቀኙን በሚገባ አዳምጦ በኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ስርዓትና በእንግሊዝ ሃገር ሕግ መሠረት መፍትሔ ይሆናል ብሎ ብይን ቢሰጥም ካህናቱና ሕዝቡ ውስጣቸው በቂም በቀል የተሞላ በመሆኑ የፍርድቤቱ ውሳኔ ሰላምና እርቅን ማምጣት አልቻለም።በሁለቱም ወገን ለጠበቃ ክፍያ ከ 2 ሚሊየን ፓውንድ በላይ ማለትም ከ260 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ አድርገው ቢሟገቱም ፍቅር፣ሰላምና አንድነት ግን እስካሁን ድረስ እንደ ሰማይ ርቋቸዋል። የተለያዩ ሽማግሌዎች ከሁለቱም ወገን ተውጣጥተው እንደ ኢትዮጵያዊ ባህላችንና እንደ ሃይማኖት ሥርዓታችን ለማስታረቅና ለማስማማት በተደጋጋሚ ቢሞክሩም ችግሩ እየባሰ ሄደ እንጂ ምንም ሊፈታ አልቻለም። ቅዱስ ሲኖዶስም በጉዳዩ ላይ ከፍተኛ ትኩረት ሰጥቶ የካህናቱንና የሕዝቡን ሰላም በመመለስ በፍቅርና በአንድነት እንዲያመልኩ በተለያየ ጊዜ ብፁዓን አባቶችን ከኢትዮጵያና ከአውሮፓ በመላክ መፍትሔ ለመስጠት ቢሞክርም ካህናቱና ሕዝቡ እየባሰባቸው ሄዱ አንጂ አንድ መሆን አልቻሉም። በቦታው ላይ በየጊዜው ሱባዔ እየተያዘ በተከፋፈሉት በሁለቱም ወገን ስለ ሰላምና እርቅ ምህላ ቢደርስም በካህናቱና በምዕመናኑ ቢጸለይም እስካሁን እግዚአብሔር መልስ ሳይሰጥ ችግሩ ቀጥሏል።ለመሆኑ የዚህ ቦታ እንቆቅልሽ እንዲህ አልፈታ ያለበት ምክንያት ምን ይሆን? እግዚአብሔር የምህረት ፊቱን አልመልስ ያለበት ምሥጢርስ ምን ድነው? ብለን በንሥር ዓይን የውስጡን መንፈሳዊ ችግሮች ስንመርምር የሚከተሉትን አሳዛኝ ክስተቶች እናገኛለን።"መንፈሳዊ ሰው ሁሉን ይመረምራል። እሱ ግን በማንም ሊመረመር አይችልም።" 1ቆሮ 2፥15 1. ብፁዕ አቡነ ዮሐንስ በግፍ ተገድለዋል የለንደን ደብረጽዮን ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን ከተመሠረተችበት ጊዜ ጀምሮ ለረዥም ዓመታት ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይሉ በብርድና በዝናብ፣ በጭጋግና በበረዶ እየተመላለሱ ቤተክርስቲያኒቱን በቅድስና ሲያገለግሉ የነበሩ አባት በ1990 ዓ.ም በታህሳስ ወር በጾመ ነቢያት ቀን ሙሉ ሲጸልዩና ሲጾሙ ውለው ቤታቸው እህል ለመቅመስ በገቡበት ሰዓት ሞተው ተገኝተዋል።በወቅቱ ቤታቸው ውስጥ አስከሬናቸው የተገኘው መሐል አናታቸው ተፈነካክቶ ደማቸው በሰውነታቸው ላይ ፈሶ ቤቱን ደማቸው አጥልቅልቆት በሚያሳዝን ጭካኔ እጃቸው ላይ ስልክ እንደ ጨበጡ ሞተው ተገኝተዋል። እኚህ አባታ በምንኩስና ስማቸው አባ አረጋዊ የሚባሉ ሲሆን እ.አ.አ ከ1974 ዓ.ም ጀምሮ ለንደን ደብረ ጽዮንን በአስተዳዳሪነት፣በቀዳሽነትና በስብከተ ወንጌል በከፍተኛ ትጋት ሲያገለግሉ ነበር ከአገልግሎታቸው ትጋት የተነሳ በወቅቱ ምዕመናን ከቤተክርስቲያን በተለያየ ምክንያት ሲቀሩ በየቤታቸው እየሄዱ የሚፈልጉ የሕዝቡን ችግር ዝቅ ብለው እየሄዱ የሚያወያዩ የሰዎችን ችግር በጸሎትና ምዕመናንን በማስተባበር የሚፈቱ ደግ ፣ርኅሩኅ መንፈሳዊ እረኛ ነበሩ። እጅግ የሚያሳዝነው እኚህ አባት በመላ አውሮፓ እየተዘዋወሩ እንዲያገለግሉና ቤተክርስቲያንን እንዲያጠናክሩ ወደ ኢትዮጵያ ተጠርተው በፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ እጅ የጵጵስና ማዕረግ ተቀብለው ብፁዕ አቡነ ዮሐንስ ተብለው ወደ ለንደን ሲመለሱ ብዙ ሰዎች ይቃወሟቸው ጀመር ምክንያታቸው ደግሞ እንዴት በወያኔ ፓትርያርክ እጅ ጵጵስና ትሾማለህ የሚል ጥላቻ ነበር።እርሳቸውም ልጆቼ እባካችሁ እኔ መንፈሳዊ አባታችሁ ነኝ ለረዥም ዓመታትም ሳገለግላችሁ የቆየው እረኛቹ ነኝ ምንም ዓይነት የፓለቲካ ዓላማ የለኝም ቅድስት ቤተክርስቲያንን በመላው አውሮፓ እየተዘዋወርኩ እንዳገለግል በቅዱስ ሲኖዶስ ምርጫ የተሰጠኝ ኃላፊነት ነውና እባካችሁ ይህንን መንፈሳዊ አገልግሎት ከፓለቲካ ጋር አታያይዙት ቢሉም ሊሰሟቸው አልቻሉም።እንደውም የቤተክርስቲያናችንን የአስተዳዳሪነት ቦታ ይልቀቁ የሚል ጫና እየበረታባቸው መጣ እርሳቸውም ለንደን ደብረ ጽዮን መንበረ ጵጵስና ነች ማረፊያዬም እዚሁ ነው ስለዚህ ይህችን ቤተክርስቲያን ትቼ የትም አልሄድም የሚል ምላሽ ቢሰጡም ይህ ጭቅጭቅ በተነሳ በወራት ጊዜ ውስጥ ቤታቸው ውስጥ በሚዘገንን ጭካኔ ተገድለው ተገኝተዋል። እንግዲህ ትልቁ እንቆቅልሽ ያለው እዚህ ጋር ነው ይህ የንጹሕ አባት ደም ዛሬም ድረስ ወደ እግዚአብሔር ይጮኻል፣ገዳያቸው እስካሁን አልታወቀም፣ደማቸው ግን እንደ አቤል ደም ፍረድልኝ እያለ ወደ አርያም ይጣራል።የእንግሊዝ ፓሊስ እስካሁን ድረስ ፋይላቸውን ክፍት እንዳደረገው መረጃዎች ይጠቁማሉ። የእኚህ አባት ደም ፍትሕ አጥቶ በግፍ ከተገድሉበት ጊዜ ጀምሮ ቤተክርስቲያኒቱ ሰላም አጥታለች፣ ሕዝቡ በረከት እርቆታል፣ካህናቱ ፍቅርና አንድነት እንደ ሰማይ እርቋቸዋል፣የሚጸለየው ጸሎት፣የሚደርሰው ምህላ፣የሚያዘው ሱባዔ ሁሉ ምንም መልስ ማምጣት አልቻለም። እግዚአብሔር ገጸ ምህረቱን ከልክሎ ይኸው በየፍርድቤቱ ሕዝቡ ሲንከራተት ገንዘቡን ለጠበቃ ሲበትን ይኖራል። የእግዚአብሔር ቃል እንዲህ ይላል፦ « ሰንበታችኹን፡በጉባኤ፡መሰብሰባችኹን፡አልወድ፟ም፤በደልንም፡የተቀደሰውንም፡ጉባኤ፡አልታገሥም። 14፤መባቻችኹንና፡በዓላቶቻችኹን፡ነፍሴ፡ጠልታለች፤ሸክም፡ኾነውብኛል፥ልታገሣቸውም፡ደክሜያለኹ። 15፤እጃችኹንም፡ወደ፡እኔ፡ብትዘረጉ፡ዐይኔን፡ከእናንተ፡እሰውራለኹ፥ልመናንም፡ብታበዙ፡ አልሰማችኹም፤እጆቻችኹ፡ደም፡ተሞልተዋል። 16፤ታጠቡ፡ሰውነታችኹንም፡አንጹ፤የሥራችኹን፡ክፋት፡ከዐይኔ፡ፊት፡አስወግዱ፤ክፉ፡ማድረግን፡ተዉ፥ 17፤መልካም፡መሥራትን፡ተማሩ፥ፍርድን፡ፈልጉ፥የተገፋውን፡አድኑ፥ለድኻ፡አደጉ፡ፍረዱለት።» ኢሳ 1፥14 እንግዲህ ልብ በሉ እግዚአብሔር አልለመን ያለበት ዋነኛው ምክንያት ይህ ነው።በግፍ ደም ያፈሰሱ ሰዎችና ተባባሪዎቻቸው ሁሉ በይፋ ይቅርታ ሊጠይቁና የንስሐ አዋጅ ሊታወጅ ይገባል የእኚህ አባት ደም እያመጣብን ካለው ፍርድ እግዚአብሔር እንዲታረቀን በግልጽ በደለኛነታችንን ልናሳውቅ ይገባል።ቃየን ወንድሙን አቤልን ከገደለ በኋላ በምድር ላይ ዘመኑን ሙሉ ተቀብዝባዥ እንደነበረ መጽሐፍ ቅዱስ በግልጽ ይነግረናል ስለዚህም የካህናቱና የሕዝቡ በየፍርድ ቤቱና በየአደባባዩ መቅበዝበዝ እንዲያበቃ በጋራ ንስሐ እንግባ።« በምድርም ላይ ኰብላይና ተቅበዝባዥ ትሆናለህ።» ዘፍጥረት 4፥12 https://youtu.be/bvjAwMFbZdU?si=pu_w3XaxKLAOBBKY (የአቡነ ዮሐንስ ጸሎተ ፍትሐት ) ክፍል 3 ይቀጥላል መ/ር ታሪኩ አበራ

photo content

አባ አረጋዊ ወልደገብርኤል ሎንደን ደብረ ጽዮን ቅደስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን አስተዳዳሪ ሁነው እንደመጡ በቀጥታ በእንግሊዝ ሀገር የሃይማኖት ጉዳዮችን ከሚመለከታቸው የሥራ ክፍሎች የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ተወካይ መሆናቸውን በመግለጽ ግኑኝነት ጀመሩ። በየጊዜው በሚደረገው የካውንስል ሕዝባዊ ስብሰባዎችና ትዕይንቶች በክብር እንግድነት እየተጋበዙ ተካፋይ ይሆኑ ነበር። በወቅቱ ከነበሩት የአንገሊካን ቤተ ክርስቲያን ሊቀ ጳጳስ ዶክተር ሩብሲ ጋር ጥሩ ግኑኝነት አድረገው ነበር ። ከዚያም ብዙ ሳይቅዩ የጸሎተ ቅዳሴው ሳምንታዊ መንፈሳዊ አገልግሎቱ እንደተጠበቀ ሆኖ በየሳምንቱ እሁድ ከስዓት በኋላ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት መርሐግብር እንዲሁም ለአፍሪካ ካረብያን ተወላጆች የአማርኛ ትምህርት እንዲማሩ ከፍተኛ መንፈሳዊ አገለግሎት አበርክተዋል። ከዚያም የቤተ ክርስትያኑ መንፈሳዊ አገለግሎት ይበልጥ እየተጠናከረ በመምጣቱ ሎንደን ደብረ ጽዮን ቅደስት ማርያም በአውሮፓ ቀደምት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን መንፈሳዊ ገልግሎቱ በጥሩ ሁኔታ የሚገለገልባት ትልቅ ቦታ እንድትሆን ከፍተኛውን አስተዋጾዖ ያደረጉ ከመሆናቸውም በላይ ቤተ ክርስቲያኗ በስደት ሀገር ለሚገኘው ማህበረሰብ የእምነት ቦታ እና የማህብረሰቡ መገናኛ ብቸኛ ማዕከል በማድረግ ይበልጥ እንደትታወቅ አድርገዋል። አባ አረጋዊ ወለደገብርኤል (ቆሞስ) በቅዱስ ሲኖዶስ ምርጫና ውሳኔ በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነጳጳሳት ዘኢትዮጵያ አንብሮተ እድ ብፁዕ አቡነ ዮሐንስ ተብለው መንብረ ጵጵስናቸውን ሎንደን ደብረ ጽዮን ቅደስት ማርያም ቤተ ከርስቲያን አድርገው የአውሮፓ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ሆነው ተሾሙ። ከዝያም አገልግሎታቸውን በማስፋፋትና በማጠናከር በምድረ አውሮፓ በመዘዋወር ሐዋርያዊ ተልዕኳቸውን እስከለተ ሞታቸው ታህሣስ 10 ቀን 1990 ዓ.ም ድረስ ያከናወኑ እጅግ በጣም ትጉህና በሁሉም ለሁሉም የተወደዱ አባት ነበሩ። ከብፁዕ አቡነ ዮሐንስ እረፈት በኋላ ብፁዕ አቡነ ሰላማ፣ ብፁዕ አቡነ መለከ ጼዴቅ እና ብጽዕ አቡነ ኢሳይያስ መንበረ ጵጵስናቸውን ሎንደን ደብረ ጽዮን አድርገው የአውሮፓ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በመሆን ሐዋርያዊ ተግባራቸውን አከናውነዋል። ከካህናትም መካከል እነ ሊቀ ብርሃናት ቀሲስ ሰሎሞን ገብረሥላሴ የመሳሰሉ ልምድ ያላቸው ካህናት አገልግለዋል።ሊቀ ብርሃናት ቀሲስ ሰሎሞን ገብረ ሥላሴ ለጃማይካዎቹ ለጽርሐ ጽዮን ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን በአስተዳደርነት ቢላኩም በተፈጠረ አለመግባባት ወደ ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን መጥተው ነበር። እንደ እ.አ.አ 1977 ብጹዕ አቡነ ጎርጎሬዎስ የሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስን የርዕሰ አደባራት ሎንደን ቅደስት ማርያም ቤተ ክርስቲያንን ጎብኝተዋል። ብጹዕነታቸው በወቅቱ «እምነትና ሥርዓት» በሚል ርዕስ በእንግሊዝ ሀገር ለሚገኙ አፍሪካ ካረብያን ተወላጆች ስለ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን እምነትና ሥርዓት በስፋትና በጥልቀት አስተምረዋል። ከዚያም የቤተክርስቲያኑ አባላት ቁጥር በየጊዜው እየጨመረ መጣ። ★ በምራዕብ ሀገር የተወለዱ የአፍሪካ ካረብያን ተወላጆች ሥልጣነ ክህነት ማግኘት★ እ.አ.አ 1987 በምራብ ሀገራት በስደት ተወልደው ካደጉት የአፍሪካ ካረብያን ተወላጆች መካከል አራት ወጣቶች ተመርጠው ለአንድ ዓመት ወደ ኢትዮጵያ ተጋብዘው ብፁዕ አቡነ ጎርጎሬዎስ ባስፋፉት ዝዋይ ቅዱስ ገብርኤል ለግብረ ዲቁና የሚያበቃውን መንፈሳዊ ትምህርት የተከታተሉ አራቱ ወጣቶች ማዕረገ ዲቆና ተቀበሉ። ቆይተውም ዲያቆናቱ እ.አ.አ በ30 ጥር 1988 በብፁዕ አቡነ ተክለሃይማኖት ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ቡራኬ ማዕረገ ቅሥና ተቀብለው በተለይም በምዕራቡ ሀገር ተወልደው ያደጉትንና አዲስ የሚወልዱትን በመንፈሳዊ ትምህርት በማነጽ እና ቀድሶ በማቁረብ ሕግ ቤተክርስቲያንን ጠብቀው በማስጠበቅ አገልግሎታቸውን በማስፋት እስካሁን አስደናቂ በሆነ መንፈሳዊ ተግባር ላይ ይገኛሉ። ከዚህ ቀጥሎ በወቅቱ ኢትዮጵያ በነበረው የኮሚኒስት ሥርዓት እየሸሹ የሚመጡና ጥገኝነት የሚጠይቁ ኢትዮጵያውያን ቁጥር እየጨመረ፤ የምዕመናን ቁጥር በዚያው መጠን እየበዛ ሲመጣ የቋንቋ፣ የአስተዳደር እና የዘር መከፋፈል ውስጥ ውስጡን አደገ። ከዚያም በሚደርሰው ልዩነትና ያለተቋረጠ ችግር ምክንያት የአፍሪካ ካረብያን ተወላጆች ጽርሐ ጽዮን ቅደስት ማርያም ቤተክርስቲያን ብለው አቋቋሙ፤ በሌላ በኩል በአብዛኛው ኢትዮጵያውያን የሚገኙበት በአሁኑ ጊዜ ብዙ ካህናት፣ ወጣት ሰንበት ትምህርት ቤት አባላት እና በሁሉም አማኞች ትብብርና አንድነት ትልቅ ሕንጻ ቤተ ክርስቲያን ተገዘቶ የሚገኘው በደቡብ የሎንደን ክፈለ ከተማ ባተርሲ ተብሎ የሚታውቀው ቦታ ያለችው ርዕሰ አደባራት ሎንደን ደብረ ጽዮን በመባል የምትታወቅ የአውሮፓ ቀደምት ቤተ ክርስቲያን ሆነች። ★ የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ጉብኝት።★ እ.አ.አ በጥር ወር 1993 ቅዱስነታቸው ከስደስት ሊቃነ ጳጳሳት ጋር በመሆን በእንግሊዝ ሀገር ባደረጉት ሐዋርያዊ ጉብኝት ምንም እንኳን አቀባበሉ ከልዩ ልዩ ምክንያቶች ጋር ተያይዞና ከፓለቲካ ጋር ተሳስሮ ክርስቲያናዊ ያልሆነ ሁከት ቢፈጠርም በለንደን ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስትያን ተገኝው ቃለ ምዕዳንና ጽሎተ ቡራኬ ሰጥተዋል። በጽርሐ ጽዮን ቅደስት ማርያም ቤተ ክርስቲያንም ተገኝተው ተመሳሳይ መፈሳዊ አገልግሎት ሰጥተው ተመልሰዋል። ★የብፁዕ አቡነ እንጦንስ የሰሜን ምራብ አውሮፓ ሀገረ ስበከት ሊቀ ጳጳስ መሾም★ ብፁዕ አቡነ እንጦንስ በቅዱስ ሲኖዶስ ወሳኔና በቅዱስ ፓትርያርኩ ትእዛዝ የሰሜን ምራብ አውሮፓ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ሆነው ተሹመው ወደ እንግሊዝ ሀገር ሲመጡ በካረብያን ተወላጆች በኩል አቀባበል የተደረገላቸው ቢሆንም መንበረ ጵጵስናው የርዕሰ አደባራት ደብረ ጽዮን እንደመሆኑ መጠን በወቅቱ በሥራ ላይ ላለው የሰበካ ጉባዔ መምጣታቸውን አሳወቁ። ይሁን እንጂ የቀረበላቸው ጥያቄ እኛ «ቅዱስ ሲኖዶሱን እንቀበላለን፤ ፓትርያርኩን አንቀበልም» ይህን መመሪያችን ተቀብለው የሚስማሙ ከሆነ እንቀበሎታለን የማይቀበሉ ከሆነ አንቀበሎትም የሚል ነበር። ብጹዕነታቸው ቅዱስ ሲኖዶስ ያለፓትርያርክ፤ ፓትርያርክም ያለቅዱስ ሲኖዶስ የለም።» የቤተ ክርስቲያን ሕግ የማይፈቅደው በመሆኑ ይህን ተቀብሎ ማገልገል አልችልም በማለት ገልጸው ቀሩ። ይሁን እንጂ መንበረ ጵጳስናቸውን ጽርሐ ጽዮን አድርገው በብፁዕ አቡነ ሙሴ ሊቀ ጳጳስ ቡራኬ አዲስ የተተከለውን የለንደን ደብረ ገነት ቅደስት ሥላሴን ቤተ ክርስቲያንን በማጠናከር ሌሎችንም በለንደንና ከለንደን ውጭ አዳዲስ አብያተከርስቲያናትን ባርኮ በመክፈትና በማስፋፋት በሰላምና በፍቅር መንፈሳዊ አገልግሎት በመስጠት ቆዩ። ክፍል 2 ይቀጥላል

† የለንደን ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን እንቆቅልሽ አሁንም አልተፈታም። ለምን ይሆን ? † ክፍል 1 ★ በዚህ ደብር ከ12 ዓመት በላይ ካህናት ተለያይተዋል፣ምዕመናን ተጣልተው ተከፋፍለዋል።★ ★ የእንግሊዝ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ለማስታረቅ ሞክሮ አልተሳካለትም፣በቅዱስ ሲኖዶስ በተደጋጋሚ ችግሩን ለመፍታት በብፁዓን አባቶች ተሞክሮ አልተሳካም፣ብዙ ጸሎት ተይዞም አልተፈታም ችግሩ ምን ይሆን ? ★ ★ በቀጣይ ክፍል 2 ላይ በቦታው ለዘመናት ተዳፍኖ የኖረ ከባድ ርግማን፣መሪር ዕንባ የተረጨበት ግፍና በአሰቃቂ ሁኔታ የተገደለ የንጹሕ ሰው ደም መኖሩን በስፋት እናያለን እግዚአብሔርም ዝም ያለው፣ጸሎትና ምህላው ሁሉ መልስ ያጣው ይህ ሁሉ ግፍ በቤቱ ስለተፈጸመ ነው። በዚህ ክፍል 1 ጽሑፍ የቦታውን አመሠራረት ታሪክ መጀመሪያ እንመልከት ★ በምዕራብ አውሮፓ ቀደም ብሎ በተፈጠረው የጥቁር ሕዝብ ጉልበት ብዝበዛና በልዩ ልዩ ምክንያት ከተውለዱበት ሀገር በስደት የሚገኙትን አጠቃላይ የአፍሪካ ካሪብያን ወገኖቻችንን ወደ ጥንታዊው የአባቶቻቸው እምነት ለመመለስና በሃይማኖት ለመጠበቅ መንፈሳዊ አገልግሎት ለመስጠት ታሰበ። በአውሮፓ በስደት የሚገኘውን የአፍሪካ ካሪብያን ሕዝብ ወደ ቀዳሚው የአባቶቹ እምነት ለመመለስ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን ተከትሎ መንፈሳዊ አገለግሎት ማግኘት እንዳለበት በአፈሪካ ካሪበያን ዘንደ ዕቅድ ወጣ። ከመጽሐፍ ቅዱስ እንደ ተማርነው እግዚአብሔር ለአግልግሎቱ የመረጣቸው እስራኤላውያን ለአራት መቶ ሠላሳ ዘመን በእግዚአብሔርን ስም የተሰጣቸውን መጠሪያ ለውጠው በግብጽ የባርነት ቀንበር ወስጥ ወድቀው በስደት ሀገር የፈርዖን አገልጋዮች ሆነው የመከራ አገዛዝ እንዳሳለፉና እግዚአብሔርም በሙሴ አማካኝነት ነጻ ካወጣቸው በኋላ ሕዝበ እግዚአብሔር ብሎ የመጀመሪያ ስማቸውን እንደ መለሰላቸው እናነባለን። ነቢዩ ኢሳያስ «ስሜን መልሰህ አምጣ ደቡብንም አትክልት፤ ወንዶች ልጆቼንም ከሩቅ፤ ሴቶች ለቼንም ከምድር ዳርቻ፣ በስሜ የተጠራውን፣ ለክብሬም የፈጠርሁትን፣ የሠራሁትንና ያደረኩትን ሁሉ አምጣ እለዋለሁ» ኢሳያስ43፡7 በጨለማ የተቀመጠው ሕዝብ ታላቅ ብርሃን አየ፤ በሞት ሀገርና ጥላ ለተቀመጡትም ታላቅ ብርሃን ወጣላቸው።» ኢሳያስ 9፤24 ከሚለው አማናዊ የእግዚአብሔር ቃል ጋር ተገናዝቦ ሊታይ የሚችል መንፈሳዊ እና ታሪካዊ ተግባር ነው። የዘመናችን ሰማዕት ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ቴዎፍሎስ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ በደርግ በግፍ የተገደሉ አባታችን። በዚህም መሠረት የአፍሪካ ካረብያን ተወላጆች በእንግሊዝ ሀገር ከእናት ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ጋር እንደ እ.አ.አ ከ 1970 -1973 በተደረገው ቃል በቃል ምክክርና የደብዳቤ ልውውጥ እንዲሁም ጊዜውን ጠብቆ በአካል በመገናኘት የተደረገው ውይይት እየዳበረ መጥቶ በእንግሊዝ ሀገር ውስጥ አፍሪካ ካረብያን አማኞች የሚገለገሉበት አንድ ቤተ ክርስቲያን ለመትከል እንደታሰበ ጥያቄ ቀረበ፤ ጥያቄውም ከፍተኛ ትኩረት ተሰጥቶት በብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ቴዎፍሎስ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ በአጀንዳ ተይዞ እንዲታይ ትእዛዝ ተሰጠ። ወቅቱ የፓለቲካው የለውጥ ማዕበል ንጉሠ ነገሥቱን ለመቀልበስ የተነቃነቀበት ጊዜ ቢሆንም ቅዱስ ፓትርይርኩ በለንደን የሚደረገውን የቤተ ክርስቲያን ምሥረታ እንቅስቃሴ ያበረታቱ ነበር። ከዚያም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ከርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት የቀረበውን መንፈሳዊ ጥያቄ ተቀብሎ በስደት ለሚገኙ ወገኖች ወንጌል የሚያስተምር ካህን መላክ እንዳለበት ተወሰነ። ይህን መነሻ በማድረግ በአውሮፓ ታዋቂ የአፍሪካ ካረብያን ተወላጆችን በአካተተ መለኩ በየጊዜው መሰባሰብ እና ስለ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ከርስቲያን እምነትና ሥርዓት የመማማር መንፈሳዊ አገልግሎት ተጀመረ። በሎንደን የሚደረገው የስብከተ ወንጌል መንፈሳዊ አገልግሎት እየተጠናከረ መጣ በተለይም እ.አ.አ በ1973 በወቅቱ የሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ አቡነ ሳሙኤል ወደ ሀገረ እንግሊዝ ለወንጌል አገልግሎት ተልከው እንደሚመጡ በተሰማ ጊዜ በጣም ታልቅ ደስታ ሆነ፤ ሊቀ ጳጳሱ ወደ እንግሊዝ ሀገር በመጡበት ጊዜ በአፍሪካ ካረቢያ ተወላጆች ታላቅ መንፈሳዊ አቀባበል ተደርጎላቸዋል። እሳቸውም በቀላሉ ተግባቢ መንፈሳዊ አባት በመሆናቸው ከአፍሪካ ካረብያን ምዕመናን ጋር ጊዜ ሳይወስደባቸው በቀላሉ ተግባቡ በተለይም በመጀመሪያው የስብከተ ወንጌል መንፈሳዊ አገልግሎታቸው «እናንተ ስለ ነገርኳችሁ ቃል አሁን ንጹሐን ናችሁ በእኔ ኑሩ፤ እኔም በእናንተ» ዮሐንስ 15፤4 «በእኔ ብትኖሩ ቃሎቸም በእናንተ ቢኖሩ የምትወዱትን ሁሉ ለምኑ ይሆንላችሁማል።»የሐንስ 15፡7 የሚለውን ቃል በማጣቀስ ሁላችንም እራሳችን ለመንፈስ ቅዱስ በማስገዛት ለእኛ የተሰቀለውን፣ የሞተውን፣ ከሙታን ተለይቶ የተንሳውን ኢየሱስ ከርስቶስን አምነን እሱን ማዕከል በማድረግ በእንግሊዝ ሀገና በመላው አውሮፓ በስደት ሀገር የሚገኘውን ማህበረሰባቸን ማሰባሰብ፣ ማደራጀት እና ማጠናከር አለብን የሚል ነበር ። ★ የቤተ ክርስቲያኑ አመሠራረትና ደብረ ጽዮን የሚለው ስያሜ ★ ቀደም ብሎም የቤተ ከርስቲያኑ መተከል አስፈላጊነት ከታሰበበት ጊዜ ጀምሮ እ.አ.አ ከ1968/70 በእንግሊዝ በሚኖሩ ለአፍካ ካረብያንን የማጠናከርና የማደራጀት ሥራ ተከናውኗል። እግዚአብሔር ብርታቱን በሰጣቸው በመንፈስ ጠንካራ የሆኑ ምዕመናን አማካኝነት ሥራውን እየሰራ ሎንደን ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን ታሪካዊ በሆነ ቦታ ተመሠረተች። ቦታውን ታሪካዊ የሚያደረገው ቤተ ክርስትያኑ የተመሰረተበት ቦታ ከመሆንኑም በተጨማሪ እጅግ በጣም ዝነኛ የሆነው አፍሪካ ካረቢያን ክቡር ማርቆስ ጋአርቨይ ይኖሩበት በነበረው ቦታ በመሆኑ ታሪኩን ይበልጥ ያጠናክረዋል። ጋአርቨይ የግል ሕይወታቸው እንደሚያመለክተው በስደተ ለሚገኘው አፍሪካ ካረብያን ማህበረሰብ ክርስትና እና በተለይም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን ታሪክ ያስተምሩ የነበሩ በመሆናቸውም ጭምር ነው። ደብረ ጽዮን የሚለው የቤተክርስቲያናችን ስያሜ የተሰጠው እ.አ.አ 1972- 73 ብፁዕ አቡነ ይስሐቅ በተገኙበት ነው። ብፁዕ አቡነ ይስሐቅ ቀደም ብሎም ቢሆን የምዕራቡ ዓለም ክፍል ሊቀ ጳጳስ በመሆናቸው በአፍሪካ ካረብያን ዘንድ በጣም ይታወቃሉ፤ በተለይም በራስ ተፈሪያን በኩል ይበልጥ የተወደዱ ነበሩ፣ ሊቀ ካህናት አባ ላዕከ ማርያም ማንደፍሮ (ቆሞስ) ካሪቢያኖቹ አባ ማንደፍሮ እያሉ ይጠሯቸው ነበር።በኋላ ብፁዕ አቡነ ይስሐቅ አማካኝነት ቤተክርስትያናችን «ጽዮን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን» የሚለው ስያሜ ያገኘችው በእሳቸው ፈቃድ ነበር። ★ የአባ አረጋዊ ወልደ ገብርኤል (ቆሞስ) መምጣት★ ሌላው የሎንደን ደብረ ጽዮን ቅደስት ማርያም ቤተክርስቲያን ታሪካዊ ገጽታ ይበልጥ ጎልቶ የታየው እ.አ.አ ግንቦት 1974 አባ አረጋዊ ወልደገብርኤል በኋላ ብፁዕ አቡነ ዮሐንስ ሊቀ ጳጳስ መቀመጫቸውን እንግሊዝ አድርገው የደብረ ጽዮን ቤተ ክርስቲያን አስተዳዳሪ፣ በእንግሊዝ ሀገር የአፍሪካ ካረብያን ምዕመናን መንፈሳዊ መምህር እና ባለሙሉ ሥልጣን ሁነው እንዲያገለግሉ በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ቴዎፍሎስ መልካም ፈቃድ ተሾሙ። ወቅቱ አባ አረጋዊ ወልደገብርኤል (ቆሞስ) በሩሲያ የሚሰጠውን የምሥራቅ ኦርቶዶክስ አብያተክርስትያናት የሃይማኖት ትምህርታቸውን ያጠናቀቁበት ጊዜ ነበር።

photo content

† ክርስቶስ ለዓለሙ ሁሉ ቤዛ ሊሆን ሰው ሲሆን ከአብና ከመንፈስ ቅዱስ ለቅጽበተ ዓይን ያህል እንኳ አልተለየም† “መቼም ቢሆን እግዚአብሔርን ያየው አንድ ስንኳ የለም፤ በአባቱ እቅፍ ያለ አንድ ልጁ እርሱ ተረከው።” ዮሐ 1፥18 አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ ከዘለዓለም ዘመናት በፊት ዓለም ሳይፈጠር ዘመን ሳይቆጠር ፍጥረታት ካለመኖር ወደመኖር ሳይመጡ ፣የፍጥረታት መቁጠሪያ፣የወቅታት መለያ የሆነው ጊዜ ራሱ ሳይፈጠር ሥላሴ ለዓይን ጥቅሻ ያህል እንኳ ሳይለያዩ በክብር ፣በምሥጋና ፣በጌትነት ይኖሩ ነበር ።ዓለም ከተፈጠረ ዘመን ከተቆጠረም በኋላ ሦስትነታቸው አንድነታቸውን ሳይከፍለው አንድነታቸው ሦስትነታቸው ሳይጠቀልለው በሥልጣን፣በአገዛዝ፣በመለኮት፣በባሕርይ ፣በህልውና አንድ በስም፣በግብር በአካል ደግሞ ሦስት ሆነው የሚታየውንና የማይታየውን ፣ረቂቅና ግዙፉን ዓለም በሙሉ እየመገቡ እያስተዳደሩ አሉ።ወደፊትም ለዘለዓለም ይኖራሉ። እግዚአብሔር አንድ ነው። በኲነታት ሲገለጽ አብ ልብ ፣ወልድ ቃል ፣መንፈስ ቅዱስ እስትንፋስ ነው።አንድ ሰው ልብ፣ቃል፣እስትንፋስ ስላለው ሦስት ሰው አይባልም አንድ ሰው ይባላል እንጂ።እግዚአብሔርም አብ፣ወልድ፣መንፈስ ቅዱስ ስለተባለ ሦስት አማልክት፣ሦስት እግዚአብሔሮች አይባልም አንድ አምላክ፣አንድ እግዚአብሔር ይባላል እንጂ ።ሰው ሦስት ነገር አለው ይኽውም ነፍስ፣መንፈስና፣ሥጋዊ አካል እነዚህ ሦስት ንገሮች ስላሉት አንድ ሰው ሦስት ሰው አይባልም አንድ ሰው ይባላል እንጂ እግዚአብሔርም ልቡ አብ፣ቃሉ ወልድ፣እስትንፋሱ መንፈስ ቅዱስ ስለተባለ ሦስት እግዚአብሔር አይባልም አንድ እግዚአብሔር ይባላል እንጂ። "ሰውን በመልካችን እንደ ምሳሌያችን እንፍጠር።" ያለው ይህንን ሲያስረዳን ነው።ዘፍ 1፥26 የሥላሴ አካል ከሰው አዕምሮና ከመላዕክት ኅሊና በላይ የሆነ ረቂቅ አካል ነው።ይህንን ያህላል፣ይህንን ይመስላል ተብሎ ተመርምሮ የማይደረስበት ረቂቅ መለኮታዊ አካል ነው።እግዚአብሔርን እግዚአብሔር ያሰኘው ከሰው አዕምሮ በላይ መሆኑ ነው።በሰው አዕምሮ ተመርምሮ ከተደረሰበትማ ፍጡር ሊሆን ነው።እግዚአብሔርን ስሙ እንኳ ሊገልጸው የማይችል ከስሙ በላይ የሆነ ባሕርይው የማይመረመር፣ህልውናው ከህልውናችን የረቀቀ፣ነፍሳችን እንደ ውሃ የምትጠማው ፣መንፈሳችን በመቃተት የሚያመልከው መለኮት ነው። ፍጥረታት ሁሉ የየራሱ አካል አላው እግዚአብሔርም የራሱ የሆነ መለኮታዊ አካል አላው።ዓሳ ከፍጥረታትት አንዱ ነው የራሱ አካል አለው፣አንበሳ ፍጥረት ነው የራሱ አካል አለው፣ሰው ፍጥረት ነው የራሱ የሆነ አካል አለው የአንዱ ፍጥረት አካል ከሌላው በብዙ የተለየ ነው የእግዚአብሔርም መለኮታዊ አካል ደግሞ ከፍጥረታት ሁሉ የተለየ ነው።ከነፋስ ይልቅ ነፍስ ትረቃለች፣ከነፍስ ይልቅ ደግሞ መላዕክት ይረቃሉ፣ከመላዕክት ይልቅ ደግሞ ሥላሴ ይረቃሉ።በምድራችን ያለውን ረቂቅ አየር መኖሩን ያረጋገጥነው አካሉን ዳሰነው ፣ጨብጠነው ሳይሆን በዙሪያችን በሚሰራው ሥራ ነው።ለፍጥረት ሕይወት ሲሰጥ ፣ባህሩን ሲያነዋውጽ፣ዕፅዋትን ሲያንቀሳቅስ ነፋስ አለ ብለን እንመሰክራለን።ከነፋስ፣ከነፍስና ከመላዕክት በላይ የሚረቀውን እግዚአብሔር አለ ብለን የምናምነው።ከአዕምሮ በላይ የሆኑ ፍጥረታትን በመፍጠሩና በተፈጥሮ ሥርዓት ዓለምን እያስተዳደረ በመኖሩ ነው። ወልድ ወደ ምድራችን ዓለምን ለማዳን ሲመጣ ከባህርይ አባቱ ከአብ ከባህርይ ሕይወቱ ከመንፈስ ቅዱስ ለቅጽበተ ዓይን ያህል እንኳ አልተለየም።በድንግል ማርያም እቅፍ ውስጥ ሆኖ ሰብአ ሰገል ሲሰግዱለት በጽርሐ አርያም በዙፋኑ ላይም ሆኖ በሱራፌልና በኪሩቤል አንድበት ቅዱስ ፣ቅዱስ፣ቅዱስ እየተባለ ከአብና ከመንፈስ ቅዱስ ጋር ይመለክ ነበር።በዮርዳኖስ ሲጠመቅ፣በደብረ ታቦር ክብሩን ሲገለጥ ከየማነ አብ ፣ከዘባነ ኪሩብ ለዓይን ጥቅሻ ያህል እንኳ አልተለየም። ወልድ በዮርዳኖስ ሲጠመቅ፣በደብረ ታቦር ክብሩን ሲገልጥ አብ "የምወደው ልጄ ይህ ነው እርሱን ስሙት እያለ ሲናገርበት የነበረው ቃል እርሱ በሥጋም የተገለጠው በመለኮትም ከአባቱ ጋር ህልው ሆኖ ያለው ወልድ ነው። ቃል ሥጋ ሆነ ከተባለና ሥጋን የተዋሐደው ቃል እርሱ ወልድ በዮርዳኖስና በደብረ ታቦር ከታየ ታዲያ አብ በምን ቃል ነው የተናገረው ? ብለን መጠየቅ አለብን አብ የተናገረበት ቃል ከአብና ከመንፈስ ቅዱስ ጋር በህልውና አንድ ሆኖ የሚኖረው በተለየ አካሉ በሥጋ የተገለጠው እርሱ ራሱ ወልድ ነው። ልብ በሉ! ወልድ የእግዚአብሔር ቃል ነው። ቃል በአንደበት ወጥቶ ሲነገር ከልብ ተለይቶ አይደለም። ወልድ በተለየ አካሉ ከድንግል ማርያም ሥጋን ተዋሕዶ ሲገለጥ ከአብና ከመንፈስ ቅዱስ ህልውና ሳይለይ ነው። ለምሳሌ የፀሐይ ብርሃን ወደ ምድር መጥቶ ለፍጥረታት ሙቀትና ልምላሜ የሚሰጠው ከአካሉ ከፀሐይ ሳይለይ ነው።ፀሐየ ጽድቅ ኢየሱስ ክርስቶስም ወደዚህ ዓለም መጥቶ ለፍጥረት ሁሉ ሕይወትና ድኅነትን የሰጠው ከላይ ከአብና ከመንፈስ ቅዱስ ሳይለይ ነው።ስለዚህም ክርስቶስ ሠላሳ ሦስት ዓመት ከሦስት ወር በምድራችን ሲመላለስ በአርያም ከአብና ከመንፈስ ቅዱስ ሳይለይ በህልውና አንድ ሆኖ ዓለምን እያስተዳደረ ነው።ይሄ እንዴት ሊሆን ይችላል? በምድርም በሰማይም እንዴት በአንድ ጊዜ መገኘት ቻለ ? ብለን እንዳንመረምር የእግዚአብሔር ባሕርይና ህልውና ከሰው አዕምሮ ከመላዕክት ኅሊና በላይ ነውና መርምረን አንደርስበትም፣መጻሕፍት የነገሩንን ቅዱስ መንፈስ የገለጠልንን ያህል ተረድተን ዕፁብ ድንቅ እያልን ስናመሰግነው እንኖራለን። ቅዱስ ያሬድ በአንቀጸ ብርሃን ድርሰቱ ላይ እንዲህ ብሏል "ፍጥረቱን ሁሉ ሰብስቦ የያዘና ፍጥረቱን ሁሉ የሚመግብ ጌታቸው በክንድሽ ተቀምጦ ጡትሽን እንደ ሕጻን ሲጠባ ባዩ ጊዜ በአርያም ፈለጉና በዚያ እንደ ቀድሞው ከአባቱና ከመንፈስ ቅዱስ ጋር አገኙ።የጌታን ትሕትናውን ባዩ ጊዜም ዓይኖቻቸውን ወደ ላይ ወደ አርያም ከፍ ከፍ አደረጉ ክንፋቸውንም ዘርግተው ለሁሉ ጌታ ላንተ በሰማይ ምስጋና ይገባሃል እያሉ ጌታቸውን አመሰገኑ።" ጌታ እኔ መንገድም ፣እውነትም፣ሕይወትም ነኝ በእኔ በቀር ወደ አብ የሚመጣ የለም ያለውም በሥጋ ያልተገለጠውን አብን ማመንና ማመልክ የምንችለው በሥጋ ተገልጦ በታየን በወልድ በኩል ነው።በሥጋ የተገለጠው ወልድን አምላክ፣አዳኝ፣ፈጣሪ ብሎ ያመነ ሁሉ ረቂቁ አብን አምላክ፣ፈጣሪ ብሎ ለማመን መንገድ አግኝቷል።ወልድን ያላመነ ግን አብ እንኳ የለውም።በመጽሐፍ "እግዚአብሔርን ያየው አንድስ እንኳ የለም በአባቱ እቅፍ ያለ ልጁ እርሱ ተረከው እንጂ የተባለው ለዚህ ነው።" ሥላሴ ሁላችንን ይባርከን። መ/ር ታሪኩ አበራ ለሌሎችም ሼር አድርጉት

photo content
+1

† የዲያብሎሳውያን ዕቅድ በቅድስት ቤተክርስቲያን ላይ ቃል በቃል እየተፈጸመ ነው ወገን ንቃ!!! † የሚኩራሩበትን ቅርሳቅርስ ጎበኝ ሆነን ሄደን በፈሳሽ ጠብታ እየሰነጣጠቅን በማግስቱ ደግሞ ጥምቀት መስቀላቸውን በዩኒስኮ እየመዘገብን በደስታም እያስጨፈርን የማይፈርሱትን በልዑላችን አምልኮ ውስጣቸውን እየቀየርን የእኛን ሰዎች እየሾምን የማይዳሰስ በዓላቸውን በዩኒስኮ መዝገብ በመዘገብን ማግስት የሚዳሰሰውን ታርካዊ ቦታዎቻቸውን እየወሰድን ለሌሎች እያስረከብን በዓሉንም ባህሉንም እያዳከምን ሃይማኖታዊ ሥራዓቱን በብሔረሰብ ባህላዊ በዓላት እየተጫንን እያከሰምን እንቀጥላለን።............ አስተዉሉ ህሊና ያላችሁ!!!!!!!!! < የሚኩራሩበት ቅርሳቅርስ ጎበኝ መስለን በጠብታ እንሰነጣጥቃለን> ማሳያ የቅዱስ ላሊበላ ውቅር ቤተ/ያን ብዙ መቶ ክፍለ ዘመናትን ከቆየ በኃላ በዘመናችን ስደርስ ተሰነጠቀ ተብሎ የተነገረው ቅርብ ጊዜ ነው አስተዉል ከዛ እነሱኑ ጠግኑልን ተብሎ የፈርንሳይ መንግስት እንድጠግንልን ተብሎ አሳልፈው ጭራሽ እንደተሰጠ ሁላችሁም ልብ በሉ። < ጥምቀት እና መስቀል በዓል በማይዳሰስ ቅርስነት በዩኒስኮ እንመዘግባለን> ማሳያ:- የመስቀል እና የጥምቀት በዓል በዩኒስኮ በማይዳሰስ ቅርስነት የተመዘገበው ቅርብ ጊዜ መመዝገቡ ይታወቃል። < የማይዳሰስ ቅርሳቸውን እየመዘገብን በደስታ እያስጨፈርን> ማሳያ:- የቤተ/ያንቱ ርዕስ ነው ብለው ብዙዎች የምተማመኑት ቤተክህነት በስኖዶስ ደረጃ መግለጫ በማውጣትና አደባባይ ሰላማዊ ሰልፍ በመውጣት በየ በዓላቱ በየአደባባዩ በዓላችንን በዩኒስኮ ተመዝግቧል ስለዚህ እንኳን ደስ አላችሁ በማለት ብዙ መንጋዎችን ማስጨብጨባቸውና በደስታ መፈንጨታቸው የቅርብ ጊዜ ትዝታችን ነው። አሁንም ልብ በሉ!!!! < የማይዳሰሰውን (መስቀልና ጥምቀት)በዓላቸውን በዩኒስኮ በመዘገብን ማግስት የሚዳሰሰውን ታርካዊ ቦታቸውን ነጥቀን ለሌሎች እንሰጣለን> ማሳያ:- ትናንት እንዲህ ብለው ያቀዱልን ሰዎች ቤተክህነት ተብየዎች ከፊታችን ጋረጣ ሆነው ተቀምጠው ታርካዊ የሆነው የመስቀል አደባባዩ ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ኦርቶዶክስ ተነጥቆ ለሌሎች ተሰጥቶ ዛሬ የማን መጨፈርያ እንደሆነ ዓይን ያለው ሁሉ የምያየው ጆሮ ያለው ሁሉ የምሰማው የአደባባይ ጉዳይ ነው። <በዓሉንም ባህሉንም እያዳከምን ሃይማኖታዊ ሥራዓቱን በብሔረሰብ ባህላዊ በዓላት እየተጫንን እያከሰምን እንቀጥላለን> ማሳያ:- ከዛሬ አምስት አመት ጀምሮ በይፋ የባህል(የድሮ የሰይጣን አምልኮ) ከመቼውም ጊዜ በላይ የተስፋፋበትና የተጠናከረበት ጊዜ እንደሆነ አደባባይ ሀቅ ነው። ለምሳሌም ብንወስድ ዛፍ ቅቤ መቀባት, ወንዝ ዳር ሄዶ ጥቁሩ አምላክ ብሎ ማምለክ, አተቴ ጨሌ, ወዘተ ይዞ አደባባይ ወጥቶ በባህል ስም እግዚአብሔር የምቆጣበትን የሰይጣን አምልኮ እነ ጻድቁ አቡነ ተክለ ሃይማኖት በነፍሳቸው ተወራርደው በወንጌል እርሻ በቅዱስ ቃሉ ያጠፉትን የጣኦ##ት አምልኮ ዳግም በመንግስት ደረጃ የተስፋፋበትና የተደራጀበት ከየጉድጓዱ ወጥተው አደባባይ ሰይጣንን ያመለኩበት ዘመን ሆኗል። እንዲህ እየተደረገ በጉን እውነተኛ የእግዚአብሔር በዓል የሆነውን የጥምቀትና የመስቀል በዓላችንን ለማክበር በምንዘጋጅበት ቀናት የተለያዩ መሰናክሎችን በመፍጠርና ምዕመናንን በቃልኪዳኑ ታቦታ ፊት ጭምር በመግደል በማስገደል በማስር በዓሉ በድምቀት እንዳይከበር እየተጫኑ እንደሆን ፀሐይ የሞቀው ሀቅ ነው። ስለዚህ ነቃ ወገኔ!!!!! በመጨርሻም ይህ የቤተክህነት እንዝህላልነትና ቸልተኝነት የሕዝቡም ዝምታ በዚሁ ከቀጠለ ነገ ተዋህዶ ኦርቶዶክስ በኢትዮጵያ የመኖር ህልውናዋ ያሳስባል። እነሱ አሁን የስልጣን የሹመት ስካር ላይ ስለሆኑ ቅድስት ቤተክርስቲያን ልጆች ምዕመናን እረኛ እንደሌላችሁ ሁላችውም እመኑና ሃይማኖታችሁን በተጠንቀቅ ጠብቁ አልያ ነገ ተረት ሆነን እንዳንቀር ታርካዊ ኃላፊነት እንዳለብን ሁላችንም ማወቅ አለብን። ለሌሎችም ሼር አድርጉት

photo content
+3

† ቤተክርስቲያንን የምትወዱ ምዕመናን አስቡበት † የግብጽ ኮፕቲክ ቤተክርስቲያን እንደ አሁኗ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በሙስና እና ለዓለም በሚያደሉ አባቶች ታጭቃ መንፈሣዊ አገልግሎቷ ወደ መቅመቅ ሲወርድ የግብጽ ወጣቶች አንድ የድፍረት መላ ዘየዱ። በነውጥ የቤተክርስቲያኒቷ የበላይ እረኛ የሆኑትን አባት ቅዱስ ፓትርያሪኩን ከመንበራቸው በጉልበት አንስተው በገዳም እንዲወሰኑ ማድረግ እና ቤተክርስቲያኒቷ ዳግም በአዲስ እረኛ እንድታብብ ማድረግ። ይህንንም ነውጥ አደረጉ። ሞት ከፍለው ተሳካላቸው። እንደ እነ አቡነ ሺኖዳን(በረከታቸው ይደርብን) የመሰሉ ታላቅ አባት ከድኅረ ነውጥ እንቅስቃሴ በኃላ አፈሩ። ዛሬ ላይ ከ6 እህት አብያተክርስቲያናት መሃከል በተፈሪነቷም በተጽዕኖዋም ግንባር ቀደም ቤተክርስቲያን ሆነች። **" የህንድ ማላክራ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በሐዋርያዊ አገልግሎት እጅግኑ ተዳክማ ከህንድ ምድር ልትጠፋ ስትደርስ ምዕመናንን እና ቅን የሆኑ ካህናቱ አንድ ዘዴ ዘየዱ። ቤተክርስቲያንን ለካህናት አባቶች ብቻ አሳልፎ ከመስጠት ይልቅ ጊዜውን የዋጀ የምዕመናንን እና የካህናት አባቶችን ፓርላማ መስርተው ለኤጴስ ቆጶስነት ጭምር የሚመረጡ መኖኮሳት በእዚህ የመንፈሣዊ ፓርላማ ግምገማ እንዲያልፍ አደረጉ። ይህ ስርዓት ካህናትን ፈላጭ ቆራጭ ሳይሆን ትሁት አደረገ። ሁሉም ቤተክርስቲያን ውስጥ ገደብ እና መብት እንዳለው ተሰመረለት። ዛሬ ላይ የህንድ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን አንድም ተመጽዋች ምዕመን የሌላት በኢኮኖሚ እና በመንፈሣዊነት ለህዝብ እና አህዛብ አርዓያ የሆነች ቤተክርስቲያን ሆነች። *** የኤርትራ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን በተ*ድሶ እንቅስቃሴ ቁምስቅሏን አይታ ስትዝል ብዙዋን አገልጋዮች ለእንቅስቃሴው አርምሞን አሳዩ። ስርዓተ ቅዳሴ እየተካሄደ በቅጥረ ቤተክርስቲያን ድንኳን ተክለው የሚጮኹ ተሃድ*ች እስከመፈጠር ተደረሰ ። ይህን ጊዜ የኤርትራ እናቶች በዛለው ጉልበታቸው አንድ ነገር ወሰኑ። የተሃድሶን እንቅስቃሴ በጉልበት የማስቆም ነውጥ ጠሩ። ድንኳን ሰባሪዎች የሚል ቅጽል ስምም ተሰጣቸው። በቅጥረ ቤተክርስቲያን የተተከሉ ድንኳኖችን ከእነአንቀሳቃሾች ሊያጠፉ ቻሉ። *** ዛሬ ላይ የኢ/ኦ/ተ/ ቤተክርስቲያን ገዳማት በቅባት እና ጸጋ ተወርሰዋል። መና*fiqan በዘር ማልያ ተሰግስገው ያለከልካይ መሰረቷን እየቦረቦሩ ነው።ዛሬ ላይ አገልጋይን በአስተምሮት ስትከሰው በዘር ፊሽካ የሚያሰልፈው ነገድ ፈጥሯል ። የታጠቀ ኃይል ሁሉ ቃታ መሳቢያ አድርጓታል። ስለዚህ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን የቱን መንገድ ትምረጥ? እንደ ግብጽ ወጣቶች፣እንደ ኤርትራ እናቶች ወይንስ እንደ ህንድ ምዕመናንን እና ካህናት። አሁን ላይ ቤተክህነቱ እረኛ የሚል ስም በያዙ ነጋዴዎች ተሞልቷል።ከጠቅላይ ቤተክህነት እስከ ወረዳ ቤተክህነት ድረስ ሙስና እና ዘረኝነት ከዓለም በላይ ገኖ ጠንብቶ ይሸታል። በሙሴ ብትር ለፈርዖን የሚያገለግሉ ግለሰቦች በኩራት ተገልጠዋል። ቤተክርስቲያን አይናችን እያየ እየመነመነችብን ነው። መንፈስቅዱስ የሚሰራብን ነልጆች ወይም ለመንፈስ ቅዱስ የምንመች ምዕመን መሆን አቅቶናል። ለሌሎችም አጋሩት

photo content

★ ፕሮቴስታንት ፀብ መጫራችሁን አቁሙ !! ★ † መስቀል አደባባይ የኦርቶዶክሳውያን መንፈሳዊ በዓል ማክበሪያ ሥፍራ ነው።† ጊዜና ወቅት እየጠበቃችሁ በኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ላይ እየፈጸማችሁ ያላችሁት ትንኮሳን የጸብ አጀንዳ ብዙ ዋጋ ሊያስከፍላችሁ እንደሚችል ከወዲሁ እወቁ። መንግሥት ሆን ብሎ የቤተክርስቲያን አባቶችንና የመምሪያ ኃላፊዎችን በከፋፋይ አጀንዳ ወጥሮ እየያዘ እናንተ በኦርቶዶክስ አደባባይ ላይ እንዳሻችሁ እንድትፈነጩ ፈቃድ በመስጠት ከለላ የሚያደርግላችሁ ለፓለቲካ ቁማር እንጂ ለእግዚአብሔር ክብር እንዳልሆነ እኛም እናንተም ጠንቅቀን እናውቃለን። ስለዚህም ካልጠፋ ቦታ በመስቀል አደባባይ ለማዘጋጀት ያቀዳችሁት ፕሮግራም የፀባ ጫሪነት አጀንዳ በመሆኑ ቦታ ትቀይሩ ዘንድ አጥብቀን እናሳስባለን። መንግስትም ሆን ብሎ በቅድስት ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሃይማኖት ሉዓላዊ ክብር ላይ እየፈጸመ ያለውን የሽብር ደባ እንዲያቆም እናሳስባለን። የኦርቶዶክስ እምነት ተከታይ የሆናችሁ ሁሉ ኦርቶዶክሳውያን አባቶቻችን በብዙ መስዋዕትነትና ትግል አስከብረው ያስረከቡንን ርስታችንን ባለን ኃይል ሁሉ የማስጠበቅና የማስከብር አደራችንን እንወጣ። ለሌሎችም ሼር አድርጉ

photo content