en
Feedback
ET_777

ET_777

Open in Telegram

ይህ የአዩ ዘ-ሀበሻ ትክክለኛ የቴሌግራም ቻናል ነው🇪🇹በዚህ ቻናል ወቅታዊ፣ታማኝ እና ፈጣን መረጃ ያገኛሉ ለማስታወቂያ እና ጥቆማ ለመስጠት@ayuzehabesha

Show more
Ethiopia11 745The category is not specified
1 581
Subscribers
No data24 hours
-127 days
-9130 days
Posts Archive
ET_777
1 581
መረጃ‼️ደሴ‼️ የደሴ መናኻሪያ በበደሴ ከተማ አስተዳደር በአዲስ መልክ ግንባታ እየተከናወነለት በመሆኑ የትራንስፖርት ስምሪት የሚሰጠው በሁለት ቦታዎች ነው። በዚሁ መሰረትም፦ 1ኛ. ቅድመ ትኬት የሚቆ
መረጃ‼️ደሴ‼️ የደሴ መናኻሪያ በበደሴ ከተማ አስተዳደር በአዲስ መልክ ግንባታ እየተከናወነለት በመሆኑ የትራንስፖርት ስምሪት የሚሰጠው በሁለት ቦታዎች ነው። በዚሁ መሰረትም፦ 1ኛ. ቅድመ ትኬት የሚቆረጥባቸው በከፍተኛ አገር አቋራጭና በባለ 44 መቀመጫ መለስተኛ ተሽከርካሪዎች የሚሸፈኑ መስመሮች ከደሴ አዲስአበባ፣ ባህር ዳር፣ ጎንደር፣ ላሊበላ፣ ሰቆጣ፣ አሳኢታ፣ ሎጊያ፣ ዱብቲ፣ አማራ ሳይንት፣ መሃል ሳይንት፣ ወግዲ፣ ከለላ ፣ መካነ ሰላምና ጃማ መስመሮች ደሴ ከፒያሳ በላይኛው አስፓልት ከማለዳው 11:00 ሰዓት ጀምሮ እስከ ጧቱ 1:00 ሰዓት፣ 2ኛ. በዕለቱ ስምሪት የሚሰጥባቸው መስመሮች ወይም ቅድመ ትኬት የማይቆረጥባቸው መስመሮች አነስተኛና ባለ 28 መቀመጫ መለስተኛ ተሽከርካሪዎች ሰኞ ገበያ መነኻሪያ አገልግሎት የሚሰጥ መሆኑን ተገልጋዮች አውቀው ይህን የአገልግሎቱ ተጠቃሚ እንዲሆኑ የደቡብ ወሎ ዞን ትራንስፖርት ጽ/ቤት አስታውቋል።

ET_777
1 581
አርቲስት ታሪኩ ብርሃኑ (ባባ) ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ። በተለያዩ የሀገራችን ፊልሞች ላይ በድንቅ ብቃት በመተወን በተለይ ደግሞ በአሁኑ ወጣቶች ዘንድ እጅግ የሚወደደው አርቲስት ታሪኩ ብርሃኑ (ባባ
አርቲስት ታሪኩ ብርሃኑ (ባባ) ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ። በተለያዩ የሀገራችን ፊልሞች ላይ በድንቅ ብቃት በመተወን በተለይ ደግሞ በአሁኑ ወጣቶች ዘንድ እጅግ የሚወደደው አርቲስት ታሪኩ ብርሃኑ (ባባ) ከዚህ ዓለም በሞት መለየቱን ለማረጋገጥ ተችሏል። አርቲስት ታሪኩ ብርሃኑ (ባባ) አርባ ያህል ፊልሞች ላይ የተወነ ሲሆን በህመም ምክንያት ህይወቱ ማለፉን የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት (ኢፕድ) ከአርቲስቱ የቅርብ ሰዎች ለማረጋገጥ መቻሉን አሳውቋል። አርቲስት ታሪኩ ብርሃኑ የአንድ ልጅ አባት ነበረ። አርቲስት ታሪኩ ብርሃኑ (ባባ) ፦ - ወጣት በ97፣ - ወንድሜ ያዕቆብ፣ - ላውንድሪ ቦይ፣ - ማርትሬዛ፣ - ይመችሽ-የአራዳ ልጅ 2 ፣ - ሞኙ የአራዳ ልጅ 4፣ -  አንድ ሁለት ፣ - ብር ርርር፣ - ወደው አይሰርቁ፣ - ወፌ ቆመች፣ -  እንደ ቀልድ ፣ - ወቶ አደር ፣ - አባት ሀገር - የሞግዚቷ ልጆች፣ - ይዋጣልን ፣ - ዋሻው፣ - ወሬ ነጋሪ እና ሌሎችም ፊልሞች ላይ ተውኗል።

ET_777
1 581
ሩሲያ ላይ ከባድ ጥቃት ተፈጸመ‼️ እያንዳንዷ ቀን ከሰላም እየራቀች ዓለም ወደ ግዙፍ ጦርነት እያመራች ነው ይባል ዘንድ ይህች ቀን አንዷ ማሳያ ነች። በሩሲያ ምድር ላይ የማይደፈረው ተደፍሯል። ከዩክሬን የኔቶ ድንበር በመቶ ኪሜትሮች ርቀት ለይ በሚገኘውና የስትራቴጂክ ቦምበሮች ማረፊያ ነሆነው ጥብቅ የሩሲያ የአየር ቤዝ ጥቃድ ደርሶበታል። የኒውክለር፣ የኮንቬንሽናል እንዲሁም ሚሳኤልና ቦምብ የሚያዘንቡት የሩሲያ TU 95 እና 143 ስትራቴጂክ የኒውክለር ቦምበሮች መነሻ ጥብቅ ቤዝ ላይ በተፈጸመ ጥቃት ቤዙ እሳት የተነሳበትና ሁለት TU 95 ስትራቴጂ ቦምበሮች እና እውቅ 3 ኢንጀነሮች መሰዋታቸው ሰበር ተብሏል። አብዛኞቹ ሚዲያዎች ጥቃቱ ከዩክሬን በተነሱ ድሮኖች (UK + US ) ተፈጽሟል ሲሉ ሩሲያ እያጣራው ነው ብላለች። እያጣራው ነው ያለችው ሩሲያም የዩክሬንን ሰባት ከተሞች እሳት እየለቀቀችባቸውም ነው። የአሜሪካና የደቡብ ኮሪያን የጦር ልምምድ ያየችው ሰሜን ኮሪያ ልምምድን እንድታቆም ለደቡብ በስልክ ማስጠንቀቂያ ከሰጠች በኋላ 130 አርተሪዎችን አምዘግዝጋለች። ይኽን ተከትሎ በጥቁር በሕርም በኮሪያ ፔንሶሎና ውጥረት ነግሷል። © አዩ ዘሀበሻ ================

ET_777
1 581
ጉትን ከተማ አሁናዊ መረጃ‼️ የሀገር መከላከያ ሰራዊት ወደጉትን ከተማ ሲገባ በመዘጋጃ ውስጥ ሆነው ወደ ከተማዋ በከባድ መሳሪያ ሲኩስ የነበረውን የኦሮሚያ ልዩ ሃይል እጅ እንዲሰጥ በመጠየቅ ለተወሰነ
ጉትን ከተማ አሁናዊ መረጃ‼️ የሀገር መከላከያ ሰራዊት ወደጉትን ከተማ ሲገባ በመዘጋጃ ውስጥ ሆነው ወደ ከተማዋ በከባድ መሳሪያ ሲኩስ የነበረውን የኦሮሚያ ልዩ ሃይል እጅ እንዲሰጥ በመጠየቅ ለተወሰነ ሰዓት ከፍተኛ የተኩስ ልውውጥ ከተደረገ በኋላ ሙሉ በሙሉ ተኩሱ ቆሟል። በአሁኑ ሰዓት በከተማዋ በርካታ ሰዎች በተባራሪ ጥይት ሞተዋል። ቆስለዋል። በብርቱ ተጋድሎ በጀግንነት ሲፋለሙ የዋሉ የአከባቢው ሚኒሻዎች ቦታውን ለሀገር መከላከያ ሠራዊት አስረክበዋል። አስቱቲ ሰላም እደሩ🙋 የሀገሬ ነገር ግን😥 ህዳር 24/2015 ዓ.ም

ET_777
1 581
መንግስት የሰው ደም ካልፈሰሰ፣የንፁሃን ሀብት ንብረታቸው ወድሞ ካልተፈናቀሉ በአጥፊ ላይ እርምጃ የማይወሰድበት ምክንያት ለገዳይ ከመተባበር ተለይቶ የሚታይ አይመስለኝም። ለምሳሌ ምስራቅ ወለጋ አንገር ጉትን ከተማ ከነቀምት ያለው ርቀት 2:30—3:00 ሰዓት ይፈጃል።መከላከያ ሠራዊቱ በዚህ ቦታ ላይ እያለ አንገር ጉትን ለ24 ሰዓታት ዜጎች ሲገደሉ ዝም ተብሎ ዛሬ ከሰዓት በኋላ ነው የተላከው።አሁንም ዙሪያውን አልቆመም።መንግስት የዜጎቹን ደህንነት ካላስጠበቀ ገዥነቱ ጥያቄ ውስጥ ነው።

ET_777
1 581
ሰበር ዜና‼️ በስብሰባ ላይ ያሉ ባለስልጣናት ተከበቡ "ከባድ ተኩስ ተጀምሯል" ሳይጠበቅ አልሻባብ በስብሰባ ላይ ያሉ ባለስልጣናትን በመክበብ ከባድ ተኩስ ከፈተ‼️ በሶማሊያ ሞቃድሾ በዚህ ሰዓት ባለስልጣናቱ በተሰበሰቡበት ከቤተመንግስቱ በቅርብ ርቀት የሚገኘው ቪላሮዝ ሆቴል ከየት መጣ ያልተባለ የአልሻባብ የሽብር ቡድን ቦታውን በመክበብ ከባድ የተኩስ ሩምታ መክፈቱን አልጄዚራን ጨምሮ አለም አቀፍ ሚዲያ በሰበር ዜና ዘግበዋል። በጉዳዩ ላይ ከዚህ በላይ ዝርዝር መረጃ ለመስጠትም አስቸጋሪ ነገር መፈጠሩን ዘገባው ጠቁሟል። ©አዩ ዘሀበሻ

ET_777
1 581
ፓስፖርት‼ ክፍያ የፈጸሙ ተገልጋዮች ሁሉ አስቸኳይ ፓስፖርት እንዲያገኙ ሊደረግ ነው። የኢሚግሬሸንና ዜግነት አገልግሎት አስቸኳይ ፓስፖርት ለማግኘት የተቀመጡ ቅድመ ሁኔታዎችን በማንሳት፣ ክፍያ የፈጸሙ ተገልጋዮች ሁሉ በአስቸኳይ እንዲያገኙ ለማድረግ በዝግጅት ላይ መሆኑን ማስታወቁን ሪፖርተር ጋዜጣ ዘግቧል። ቅድመ ሁኔታዎች ሲነሱ አሁኑ ላይ አስቸኳይ ፓስፖርት ለማግኘት ተገልጋዮች ማቅረብ ሚጠበቅባቸውን የሕክምና ደብዳቤ ፣ ነፃ የትምህርት ዕድል ማስረጃ... የመሳሰሉትን ማቅረብ አይጠበቅባቸውም፡፡ በቅርቡ በሚኒስትሮች ም/ቤት በፀደቀው የአገልግሎት ክፍያ ተመን ላይ ፓስፖርት በአንድና በአምስት ቀናት ውስጥ በአስቸኳይ ለማግኘት የተቀመጠውን ክፍያ " መክፈል የቻለ ሁሉ " ፣ የአገልግሎቱ ተጠቃሚ እንደሚሆን የኢሚግሬሽን ዜግነት አገልግሎት ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ታምሩ ግንበቶ መናገራቸውን ሪፖርተር ገልጿል። ምክትል ዋና ዳይሬክተሩ ለሪፖርተር ጋዜጣ በሰጡት ቃል የተናገሩት ፦ ✔ በአስቸኳይ_ፓስፖርት ለማግኘት የተቀመጡትን ቅድመ ሁኔታዎችን ለማንሳት ዝግጅት እየተደረገ ያለው የአስቸኳይ ፓስፖርት አሰጣጡ ከሙስናና ከብልሹ አሠራር ጋር የተያያዘ በመሆኑ ነው፡፡ -✔ " አስቸኳይ ፓስፖርት ከውስጥ ሠራተኞች ተነጋግረን እናስጨርሳለን " የሚሉ ደላሎች አሉ ከብልሹ አሠራሮች ጋር በተያያዘ ፣ በዓመት ግፋ ቢል ከ50 ሰዎች በላይ እያባረርን ነው። ከአስቸኳይ ፓስፖርት አሰጣጥ ጋር የተያያዙ ችግሮችን ሥር ነቀል በሆነ መንገድ ለመፍታት ያስችላል ተብሎ የታሰበው መፍትሔ አገልግሎቱን ለማግኘት የተቀመጡ ቅድመ ሁኔታዎችን ማንሳት ነው። -✔ አሁን ባለው አሠራር ፓስፖርት በአስቸኳይ ለማግኘት ከሚያስችሉ ማስረጃዎች መካከል ፦ ✔ ወደ ውጭ ሄደው መታከም እንዳለባቸው የሚገልጽ የሕክምና ደብዳቤ ፣ ✔  ለሁለተኛ ዲግሪና ከዚያ በላይ የሆነ የትምህርት ዕድል ማግኘትን የሚገልጽ ደብዳቤ ✔ የዲቪ ሎተሪ ዕድል ማግኘትን የሚያሳይ ማስረጃ ተጠቃሽ ናቸው፡፡ እነዚህ ቅድመ ሁኔታዎች ተነስተው ሥራ ሲያስጀምር ደንበኞች የሚስተናገዱት በአዲሱ የክፍያ ተመን ይሆናል። - ቅድመ ሁኔታዎችን አንስቶ አገልግሎቱን ለመጀመር ጥናት ተጠንቷል፤ ይህንን አገልግሎት ለማስጀመር የፓስፖርት ወረቀት ፣ ላምኔት ፣ የማተሚያ ቀለም እና የቴክኖሎጂ ሥርዓቱ መለዋወጫዎችን ... የመሳሰሉ ግብዓቶች መሟላት እንዳለባቸው በጥናቱ ታይቷል። የሚግሬሸንና ዜግነት አገልግሎት የኦንላይን ፓስፖርት ቡድን መሪ አቶ ዳንኤል የሻነው ለሪፖርተር የሰጡት ቃል ፦ ✔ በአገልግሎቱ ዋና መሥሪያ ቤት ውስጥ የአስቸኳይ ፓስፖርት የሚሰጥባቸው መስኮቶች ሁለት ናቸው የአስቸኳይ ፓስፖርት አገልግሎትን ያለገደብ ለማስጀመር እንዲቻል ቢያንስ ስድስት መስኮቶች መኖር አለባቸው። ✔ አገልገሎቱን ለማስጀመር ሚያስፈልጉ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች ተጀምሯል ፤ ምን ያህል ብር እንደሚጠይቅም አዘጋጅተን ለሚመለከተው ክፍል አቅርበናል። ✔ አገልግሎቱ እንዲጀመር ተጨማሪ በጀት ይጠይቃል ፤ በጀቱ የሚፈቀድልን ከሆነ #በቅርብ_ወራት ውስጥ ይኼንን አስጀምረን አገልግሎት አሰጣጡን እናሻሽላለን። አሁን ያለው የአስቸኳይ ፓስፖርት ክፍያና የሚሻሻለው ክፍያ ምን ይመስላል ? አሁን በሥራ ላይ ባለው አሠራር መሠረት ባለ 32 ገጽ ፓስፖርት በ5 ቀናት ውስጥ በአስቸኳይ ለማግኘት 2,186 ብር የሚከፈል ሲሆን፣ ይኼንኑ ፓስፖርት በሁለት ቀናት ውስጥ ለማግኘት 3,279 ብር ክፍያ ይፈጸማል፡፡ በቅርቡ በሥራ ላይ መዋል ይጀምራል የተባለው አዲስ የአገልግሎት ክፍያ ተመን በ5 ቀናት ውስጥ ባለ 32 ገጽ ፓስፖርት ለማግኘት የሚጠየቀውን ገንዘብ ወደ 5,000 ብር አሳድጎታል፡፡ ፓስፖርቱን በአንድ ቀን ለማግኘት ደግሞ 6,500 ብር ክፍያ መፈጸም እንዳለበት ደንቡ ያስረዳል፡፡ የባለ 64 ገጽ ፓስፖርት በ5 ቀናት ውስጥ ለማግኘት 6,500 ብር የሚከፈል ሲሆን፣ በአንድ ቀን ለማግኘት የሚከለፈለው ክፍያ 8,000 ብር ይደርሳል። ዘገባው የሪፖርተር ጋዜጣ ነው።

ET_777
1 581
"…ትጥቅ አንፈታም…" የሕወሃት ቃል አቀባይ ጌታቸው ረዳ የኢትዮጵያ መንግሥት የኤርትራ ወታደሮች እና ሌሎች ኃይሎች ከትግራይ መውጣታቸው እስኪያረጋግጥ ሕወሃት ትጥቅ አይፈታም ሲሉ መናገራቸውን ቢቢሲ ዘግቧል። አንድ ስማቸው ያልተገለጸ የመንግሥት ባለሥልጣን ደሞ፣ መከላከያ ሠራዊት በድንበር አካባቢዎች ላይ ከሠፈረ በኋላ የኤርትራ ጦር ጉዳይ መፍትሄ ያገኛል ማለታቸውን ዘገባው ጠቅሷል። በግጭት ማቆም ስምምነቱ መሠረት፣ የሕወሃት ኃይሎች ትጥቅ መፍታት ከመከላከያ ውጭ ያሉ እና የውጭ ኃይሎች መውጣት ጋር ጎን ለጎን ይፈጸማል ይላል። ጌታቸው የኤርትራ ኃይሎች ሰላማዊ ሰዎችን እየገደሉና የንብረት ዘረፋ እየፈጸሙ ነው ሲሉ ከሰዋል።(Wazema)

ET_777
1 581
ተጨባጭ መረጃ‼️ የህወሓት ታጣቂዎች በአንዳንድ አካባቢዎች ምሽግ እየቆፈሩ ነው፣እንዋጋለን የሚሉ አርሚዎች አሉ አይ አንዋጋም የሚሉም እንደዛው።  አዲግራት አካባቢ በገጠራማው ስፍራ የሚገኙ የህወሓት ታጣቂዎች በመከላከያ ሰራዊት ላይ የከበባ እንቅስቃሴ አድርገዋል። ሁኔታው ምንም ሊገባኝ አልቻለም፣በርካታ መስዋዕትነት ተከፍሎበት የመጣው የሰላም ስምምነት በከንቱ እንዳይቀር ህወሃት ከፍተኛ ስራ ይጠበቅበታል፣ ለሰላም ቁርጠኛ ከሆነ ማለቴ ነው። ©አዩ ዘሀበሻ

ET_777
1 581
#የወንዶች የዘር ፍሬ መጠን ከ50 በመቶ በላይ መቀነሱ ተሰማ!!! @የወንዶች የዘር ፍሬ ቁጥር በፍጥነት እየቀነሰ መሆኑን ተመራማሪዎች ገለጹ፡፡ @ለሰው ልጅ መጸነስ ዋነኛ መሰረት የሆነው የወንዶች የ
#የወንዶች የዘር ፍሬ መጠን ከ50 በመቶ በላይ መቀነሱ ተሰማ!!! @የወንዶች የዘር ፍሬ ቁጥር በፍጥነት እየቀነሰ መሆኑን ተመራማሪዎች ገለጹ፡፡ @ለሰው ልጅ መጸነስ ዋነኛ መሰረት የሆነው የወንዶች የዘር ፍሬ ወይም ስፐርም ቁጥር በፍጥነት እየቀነሰ መሆኑን ሳይንቲስቶች ገልጸዋል፡፡ @አንድ ጤነኛ የሆነ ሰው (ወንድ) በአማካኝ በጾታዊ ግንኙነት ወቅት ከ20 እስከ 150 ሚሊዮን ሚሊ ሊትር የዘርፍሬ የሚረጭ ሲሆን ለእርግዝና ከ40 እስከ 50 ሚሊዮን ሚሊ ሊትር የዘር ፍሬ በቂ እንደሆነ ተመራማሪዎች ይገልጻሉ፡፡ @ባለፉት 100 ዓመታት ውስጥ ያለው የወንድ የዘር ፍሬ መጠን በየጊዜው እየቀነሰ መምጣቱን ዩሮ ኒውስ ተመራማሪዎችን ዋቢ አድርጎ አስነብቧል፡፡ @ይህ ጥናት በ53 የዓለማችን ሀገራት ላይ ባሉ ከ53 ሺህ በላይ ወንዶች ላይ በተደረገ ጥናት የወንዶች የዘር ፍሬ መጠን ከ100 ዓመት በፊት ከነበረው ጋር ሲነጻጸር ከግማሽ በላይ ቀንሷል ብሏል፡፡ ለፈጣን መረጃ‼️ የቻናሌ ቤተሰብ ይሁኑ፣ለሌሎች ጋብዙ👇👇👇👇👇👇 http://t.me/ayuzehabeshaofficial http://t.me/ayuzehabeshaofficial http://t.me/ayuzehabeshaofficia

ET_777
1 581
+2
ሼር❗❗❗ ዛሬ እጣ የወጣባቸው የ20/80  የጋራ መኖሪያ ቤቶች የባለ እድለኞች ዝርዝር =ለፈጣን መረጃ የቻናሌ ቤተሰብ ይሁኑ፣ለሌሎች ጋብዙ👇👇👇👇👇👇 http://t.me/ayuzehabeshaofficial http://t.me/ayuzehabeshaofficial http://t.me/ayuzehabeshaofficial

ET_777
1 581
መቀሌ‼️ በመቀሌ የሰላም ስምምነቱን ባልተቀበሉ መካከል በተፈጠረ ግጭት በመቀሌ ከተማ ከባድ የቦንብ ፍንዳታ እንደነበር የደረሰኝ መረጃ ያመላክታል። ©አዩ ዘሀበሻ ህዳር 2/2015 ዓ.ም

ET_777
1 581
ነፍስ ይማር አርቲስት አሊ ቢራ! ለብዙ ግዜ ቢሟረትበትም በመጨረሻ ወደማይቀረው ሄዷል።
ነፍስ ይማር አርቲስት አሊ ቢራ! ለብዙ ግዜ ቢሟረትበትም በመጨረሻ ወደማይቀረው ሄዷል።

ET_777
1 581
ጠቅላይ ሚንስትሩ ግብፅ ገቡ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ እና ልዑካቸው ግብፅ፣ ሻርም አል-ሼይክ ደርሰዋል።የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባዔ ላይ ለመሳተፍ ነው ግብጽ የተ
ጠቅላይ ሚንስትሩ ግብፅ ገቡ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ እና ልዑካቸው ግብፅ፣ ሻርም አል-ሼይክ ደርሰዋል።የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባዔ ላይ ለመሳተፍ ነው ግብጽ የተገኙት፡፡ 27ኛው የአየር ንብረት ለውጥ ጉባዔ ከነገ ጀምሮ ይካሄዳል፡፡

ET_777
1 581
ኦባሳንጆ፤ የኔ ቆንጆ አንተ ባትኖር፤ ልንገድልም ልንሞትም …ነበር በመናጆ‼ (ገጣሚና ጠበቃ መንግስቱ ዘገዬ)
ኦባሳንጆ፤ የኔ ቆንጆ አንተ ባትኖር፤ ልንገድልም ልንሞትም …ነበር በመናጆ‼ (ገጣሚና ጠበቃ መንግስቱ ዘገዬ)

ET_777
1 581
ይህን እንድናይ አስተዋፅኦ ላደረጋችሁ ሁሉ ምስጋና ይገባል❗ ይሄ ጦርነት ለደቂቃ ቢቆም ምን ያህል ወጣት እንደሚድን ማሰብ በቂ ነው። ቢዘገይም ጥሩ ጅምር ነው። ሰላም ለኢትዮጵያ ሀገራችን፣ሰላምን ያፅ
ይህን እንድናይ አስተዋፅኦ ላደረጋችሁ ሁሉ ምስጋና ይገባል❗ ይሄ ጦርነት ለደቂቃ ቢቆም ምን ያህል ወጣት እንደሚድን ማሰብ በቂ ነው። ቢዘገይም ጥሩ ጅምር ነው። ሰላም ለኢትዮጵያ ሀገራችን፣ሰላምን ያፅናልን።

ET_777
1 581
ኢትዮጵያ በእናንተ አላፈረችም፣በእናንተ አይተኬ መስዋዕትነት እዚህ ደርሳለች። ክብር ለሀገር መከላከያ ሰራዊት፣ለአማራ ልዩ ሀይል፣ለአፋር ልዩ ሀይል፣ፋኖ እና ሚሊሻ፣ከሁሉ በለይ ደጀኑ ህዝብ❗❗ በተለይ ደግሞ ሰሜን ዕዝ በተካደ በሁለት አመቱ የኢትዮጵያ አሸናፊነት መፃፉ...... ጥቅምት 24 (ነገ) መቼም አይረሳም። የትግራይ ህዝብም ነፃ ለመውጣት ተቃርቧል። ለአስተያየት እና ጥቆማ👉

ET_777
1 581
የህወሃት መዋቅር ፈርሶ በትግራይ ክልል ጊዚያዊ አስተዳደር ይመሰረታል። የህወሓት ከፍተኛ ወታደራዊ አመራሮች እና የፌደራሉ መንግሥት ከፍተኛ ወታደራዊ አመራሮች በትጥቅ ማስፈታት ሂደቱ ላይ ዝርዝር የአፈፃፀም መመሪያ ለማዘጋጀት በ24 ሰዓት ውስጥ በአመቺ ቦታ ስብሰባ ያደርጋሉ። ©አዩ ዘሀበሻ

ET_777
1 581
ሰበር መረጃ‼️ ቁልፍ የስምምነት አጀንዳዎች❗ ህወሓት ሙሉ በሙሉ ትጥቅ ለመፍታት መስማማቱን፦ በስምምነቱ መሰረት ከዛሬ ጀምሮ በሰላሳ ቀናት ውስጥ ቡድኑ ሙሉ በሙሉ ትጥቅ እንደሚፈታ፤ ይህንን ውሳኔ ተግባራዊ ለማድረግ የሁለቱ ወገን ከፍተኛ ወታደራዊ አመራሮች በ24 ሰዓት ውስጥ አመቺ ቦታ መርጠው ንግግር ያደርጋሉ፤ ስምምነቱ በተፈረመ አምስት ቀናት ውስጥ የሁለቱ ወገን ወታደራዊ አመራሮች የትጥቅ ማስፈታት ሂደቱ የሚመራበትን ዝርዝር አፈጻጻም በጋራ በማውጣት ተግባራዊ ሥራዎችን መሥራት ይጀምራሉ፤ የሁለቱ ወገን ከፍተኛ ወታደራዊ መኮንኖች በተገናኙ አስር ቀናት ውስጥ ህወሓት ያሉትን ሁሉንም የቡድን እና ከባድ መሣሪያዎች ለመከላከያ ሠራዊት ያስረክባል፤ ስምምነቱ በተፈረመ ሰባት ቀናት ውስጥ የፌደራል መንግሥት መቀሌን ተረክቦ በከተማው ውስጥ እና ዙሪያ ሁሉንም አይነት የጦር መሣሪያ ያስፈታል፤ በአጭር ቀናት ውስጥ አሁን ያለው የህወሓት መዋቅር ፈርሶ የፌደራል መንግሥት የሚመራው የጊዜያዊ አስተዳደር ይቋቋማል። በሚዋቀረው ጊዜያዊ አስተዳደር ውስጥም የትግራይን ሕዝብ የሚወክል አካል ይሳተፋል፤ የሀገር መከላከያ ሠራዊት ከጎረቤት ሀገራት የሚያዋስኑ የድንበር አካባቢዎችን ደኅንነትና ሰላም የሚያረጋግጥ ስምሪት የሚያደርግ ይሆናል። መከላከያ ሠራዊቱ በማንኛውም የትግራይ አካባቢዎች ተንቀሳቅሶ ሕግ የማስከበር ስልጣኑን ከህወሓት ሙሉ በሙሉ ይቀበላል። ህወሓት ለተግበራዊነቱ ምንም አይነት እንቅፋት እንደማይፈጥር ተስማምቷል። የሚመሰረተው ጊዜያዊ አስተዳደር በሁሉም የትግራይ አካባቢዎች የማኅበራዊ አገልግሎቶች በፍጥነት እንዲጀመሩ ሁኔታዎች ያመቻቻል፤ ተግባራዊነታቸውን ያረጋግጣል፤ ህወሓት ያለ ፌደራል መንግሥት እውቅና ከማንኛውም የውጭ አካል ጋር ግንኙነት ማድረግ ያቆማል። እንዲህ አይነት ተግባር የሚፈጹ ግለሰቦች ካሉ በሀገሪቱ ሕግ የሚጠየቁ ይሆናል።

ET_777
1 581
#Update " መግለጫው ዘግይቷል ፤ ነገር ግን ወደ በኃላ ይሰጣል " ዛሬ ከሰዓት ሊሰጥ የነበረው የአፍሪካ ህብረት መግለጫ #መዘግየቱን ነገር ግን መግለጫው ወደ በኃላ እንደሚሰጥ የደቡብ አፍሪካ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት አሳውቋል። መግለጫው ለምን ሊዘገይ እንደቻለ የተሰጠ ማብራሪያ የለም። ወደ በኃላ ይባል እንጂ ትክክለኛ ሰዓቱም አልተገለፀም። በደቡብ አፍሪካ ፕሪቶሪያ ከተማ ውስጥ እየተካሄደ ካለው የኢትዮጵያ መንግስት እና ህወሓት " የሰላም ንግግር " ጋር በተያያዘ አጠቃላይ እስካሁን ስላለው ሂደት ለመገናኛ ብዙሃን መግለጫ የሚሰጡት በአፍሪካ ህብረት የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ የቀድሞ የናይጄሪያ ፕ/ት ኦሊሴንጉን ኦባሳንጆ ናቸው። በርካቶች እየጠበቁት ያለው መግለጫ በደቡብ አፍሪካ የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት #የተረጋገጠ የፌስቡክ ገፅ ላይ በቀጥታ እንደሚተላለፍ በመ/ቤቱ ገልጿል