@ArtsTvWorld - Arts TV - አርትስ ቲቪ
Open in Telegram
Official Arts Tv World Channel Arts Tv frequency11512V / 27500 http://www.artstv.tv Facebook, Youtube, Instagram & Twitter @ArtsTvWorld
Show moreThe country is not specifiedThe category is not specified
2 493
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
ከልብ የመነጨ ምስጋና ለ1,000,000 ወዳጆቻችን!! Heartfelt thanks to our 1,000,000 fans!! https://www.youtube.com/channel/UCSnwxtpNr-2QupM0qi11Y6Q?sub_confirmation=1
Continuing the relentless pursuit of becoming the voice of African Renaissance and Ethiopian steadfastness with journalistic integrity and artistic prominence, @ArtsTvWorld today passed the 1 million mark in YouTube subscriptions! Heartfelt thanks to our fans all over the world!!
"የሩሲያ የሚሳኤል ዶፍ"
ከተጀመረ 104 ቀናት የሆነው ጦርነት የስላም ምድራቸውን ወደ ጦር አውድማነት ለቀየሩት አገሮች ወደ ለየለት የከባድ መሳሪያ እና ሚስኤል ቡጢ ውስጥ ገብተዋል።
የአሜሪካን የአውሮፖን አይዞሽ ባይነት ተከናንባ ወደ ጦርነቱ የገባችው የዘለንስኪዋ ዩክሬን ሁኔታው ሁሉ ከድጡ ወደ ማጡ ሆኖባታል።ዛሬም ድረስ የመከላከል ብቃት እና ኃይላቸው ከተማዎቻቸውን ከፍርስራሽ፣ዜጎቻቸውን ከስደት፣ወታደሮቻቸውን ከሞት ሊታደግላቸው አልቻለም።
ቢቢሲ እንዳስነበበው በጦርነት ምክንያት ከ6 ሚሊየን በላይ ዩክሬናዊያን ከመኖሪያ ቀያቸው ርቀዋል። 20 በመቶ የዩክሬን ክፍልም በቭላድሜር ፑቲኗ ሀገር በሩሲያ ጦር ቁጥጥር ስር ወድቋል።
ወዲህ ደግሞ
ሩሲያ ጦርነቱን ከጀመርች እንስቶ ከሁለት ሺህ አንድ መቶ በላይ ሚሳኤሎችን ወደ በዩክሬን ምድር እንዳርከፈከፈች ተረጋግጧል።
በፈረንጆቹ ዘመን ስሌት በ1991 በሀንጋሪ ቼክ ሪፐብሊክ፣ ፖላንድ እና ስሎቫኪያ አቅፎ የተመሰርተው ቪስጋርድ (V4) የተባለው ተቋም አረጋገጥኩ እንዳለው የዩክሬን ምድር ካደባዩት ሁለት ሺህ አንድ መቶ በላይ ሚሳኤሎች መካከል ስድስት መቶዎቹ መነሻቸው ከቤላሩስ እንደሆነ ነው ያስቀመጠው።
የተመድን የረሀብ ስጋት ውትወታ ወዲያ ያለው ጦርነት
አሁን ለአለም የምግብ አቅርቦት ችግርን እንዳነገበ፣የፋይንሱን ስርዓት እያደፈረስ መጓዙን አላቋረጠም።
ከዚህም ጋር ተያይዞ ከሁለት ሺህ አንደ መቶ ሚሳኤሉ ባለፈ ሩሲያ “ዚርኮን” የተባለ አዲስ ሃይፐርሶኒክ ክሩዝ ሚሳዔል ለሙከራ ማብቃቷ ይበልጥ በቀጠናው
ውጥረትን መፍጠሩ የሚታወስ ነው።
ምንጭ ቢቢሲ
በብሔራዊ ባንክ ዕውቅና የተነፈገው ክሪፕቶከረንሲ እና የኢትዮጲያ ተጠቃሚዎች
ብሄራዊ ባንክ በክሪፕቶከረንሲ ወይም ምናባዊ ገንዘብን ለግብይት ወይም ለክፍያ መጠቀም በብሄራዊ ባንክ እውቅና ያልተሰጠው ህገወጥ ድርጊት መሆኑን ትናንት በመግለጫው አስታወቀ
ብሄራዊ ባንክ የክሪፕቶከረንሲ፣ ቢትኮይን እና የመሳሰሉት የምናባዊ ገንዘብ ወይም ቨርችዋል አሴት አገልግሎት በሃገራችን እየተስፋፋ መምጣቱንም በመግለጫው አስፍሯል።
ይህንን ተከትሎም ከብሄራዊ ባንክ እውቅና ውጭ ከፍተኛ የገንዘብ ዝውውር የሚደረግበት እና በተለይም በወንጀል የተገኘን ገንዘብ ለማሸሽ ምቹ ሁኔታን እየፈጠረ እንደሆነ ለመረዳት መቻሉን ብሄራዊ ባንክ ገልጿል።
አርትስ ቲቪ ያነጋገራቸው ግለሰቦች ከዚህ በፊት እንደ ቢትኮይን ያሉ የማይዳሰሱ ዲጂታል ገንዘብን በተለያዩ ባንኮች ከሃገር ውጭ በሚገኙ ሰዎች በዌስተርን ዩኒየን አማካኝነት የገንዘብ ልውውጥ እንደሚያደርጉ ገልጸውልናል።
የብሄራዊ ባንኩ በደነገጋቸው የብሄራዊ ባንክ ማቋቋሚያ አዋጅ ቁጥር 591/2000 እንዲሁም በ በክፍያ አዋጅ ቁጥር 718/2003 በብሄራዊ ባንክ በሌላ አኳኋን ካልተፈቀደ በስተቀር ማንኛውም የገንዘብ ኝኙነቶች በብር እንደሚሆን እና ያለ ብሄራዊ ባንክ ፍቃድ የገንዘብ ዝውውርም ሆነ ገንዘብ ነክ አገልግሎት መስጠት እንደማይቻል አስቀምጧል።
ብሄራዊ ባንኩ ይህን ፈጽመው በሚገኙ አካላት ላይ ህጋዊ እርምጃ እንደሚወስድ ገልጾ ህብረተሰቡ ከመሰል ተግባሮች እንዲቆጠቡ በመግለጫው አስፍረዋል።
ክሪፕቶከረንሲ በኦንላይን ብቻ የሚገኝ የማይዳሰስ ገንዘብ ሲሆን በአለማችን በብዙ ሺህ የሚቆጠሩ የክሪፕቶከረንሲ አይነቶች ይገኛሉ። ቢትኮይን፣ ኤቴሪየም፣ ቴዘር እና ካርዳኖ የተሰኙ ክሪፕቶከረንሲዎች ግንባር ቀደም የሚጠቀሱ ናቸው። በአፍሪካ ደግሞ ቢትኮይን ከፍተኛ ተጠቃሚ ያለው የክሪፕቶከረንሲ አይነት ነ
በብሔራዊ ባንክ ዕውቅና የተነፈገው ክሪፕቶከረንሲ እና የኢትዮጲያ ተጠቃሚዎች
ብሄራዊ ባንክ በክሪፕቶከረንሲ ወይም ምናባዊ ገንዘብን ለግብይት ወይም ለክፍያ መጠቀም በብሄራዊ ባንክ እውቅና ያልተሰጠው ህገወጥ ድርጊት መሆኑን ትናንት በመግለጫው አስታወቀ
ብሄራዊ ባንክ የክሪፕቶከረንሲ፣ ቢትኮይን እና የመሳሰሉት የምናባዊ ገንዘብ ወይም ቨርችዋል አሴት አገልግሎት በሃገራችን እየተስፋፋ መምጣቱንም በመግለጫው አስፍሯል።
ይህንን ተከትሎም ከብሄራዊ ባንክ እውቅና ውጭ ከፍተኛ የገንዘብ ዝውውር የሚደረግበት እና በተለይም በወንጀል የተገኘን ገንዘብ ለማሸሽ ምቹ ሁኔታን እየፈጠረ እንደሆነ ለመረዳት መቻሉን ብሄራዊ ባንክ ገልጿል።
አርትስ ቲቪ ያነጋገራቸው ግለሰቦች ከዚህ በፊት እንደ ቢትኮይን ያሉ የማይዳሰሱ ዲጂታል ገንዘብን በተለያዩ ባንኮች ከሃገር ውጭ በሚገኙ ሰዎች በዌስተርን ዩኒየን አማካኝነት የገንዘብ ልውውጥ እንደሚያደርጉ ገልጸውልናል።
የብሄራዊ ባንኩ በደነገጋቸው የብሄራዊ ባንክ ማቋቋሚያ አዋጅ ቁጥር 591/2000 እንዲሁም በ በክፍያ አዋጅ ቁጥር 718/2003 በብሄራዊ ባንክ በሌላ አኳኋን ካልተፈቀደ በስተቀር ማንኛውም የገንዘብ ኝኙነቶች በብር እንደሚሆን እና ያለ ብሄራዊ ባንክ ፍቃድ የገንዘብ ዝውውርም ሆነ ገንዘብ ነክ አገልግሎት መስጠት እንደማይቻል አስቀምጧል።
ብሄራዊ ባንኩ ይህን ፈጽመው በሚገኙ አካላት ላይ ህጋዊ እርምጃ እንደሚወስድ ገልጾ ህብረተሰቡ ከመሰል ተግባሮች እንዲቆጠቡ በመግለጫው አስፍረዋል።
ክሪፕቶከረንሲ በኦንላይን ብቻ የሚገኝ የማይዳሰስ ገንዘብ ሲሆን በአለማችን በብዙ ሺህ የሚቆጠሩ የክሪፕቶከረንሲ አይነቶች ይገኛሉ። ቢትኮይን፣ ኤቴሪየም፣ ቴዘር እና ካርዳኖ የተሰኙ ክሪፕቶከረንሲዎች ግንባር ቀደም የሚጠቀሱ ናቸው። በአፍሪካ ደግሞ ቢትኮይን ከፍተኛ ተጠቃሚ ያለው የክሪፕቶከረንሲ አይነት ነ
Amid tumult, rivalries of political, ethnic and religious extremities, threats of sanctions; in times of high optimism and uncertainty, Ethiopians of Christian faith will celebrate Easter tomorrow. Arts Tv wishes all faithful a Happy Easter: full of hope for a bright future!
"ኮረምቶ" - መውደድ ክብሩ - አዲስ የሙዚቃ ቪዲዮ በቅርብ ቀን - Arts Media Production
#Koremto #MewdedKibru #ArtsMusic #ArtsMediaProduction
ጋዜጠኛ ሄርሜላ አረጋዊ አዲስ አበባ ገባች
*****************
በ#NoMore ዘመቻ የኢትዮጵያን እውነታ ለዓለም ያሳወቀችው ጋዜጠኛ ሄርሜላ አረጋዊ አዲስ አበባ ገብታለች።
ጋዜጠኛ ሄርሜላ አረጋዊ ቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ስትደርስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የስራ ኃላፊዎች እና ሌሎች እንግዶች አቀባበል አድርገውላታል።
ጋዜጠኛዋ ኑሮዋን በአሜሪካ አድርጋ በኢትዮጵያ ላይ ሲደረግ የነበረውን ኢ-ፍትሐዊ አካሄድ ስትቃወም መቆየቷ ይታወቃል።
ሔርሜላ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ያቀረቡትን ጥሪ ተቀብለው እየመጡ ከሚገኙ የዲያስፖራዎች መካከል ናት።
ሰበር ዜና
የኢትዮጵያ የጸጥታ ኃይሎች ጥምረት የወልዲያ ከተማን ሙሉ በሙሉ ተቆጣጠረ::
የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት እንዳስታወቀው የኢትዮጵያ የጸጥታ ኃይሎች ጥምረት፣ በዘመቻ ለኅብረ ብሔራዊ አንድነት ከተማዋን ተቆጣጥሯል።
ኢትዮጵያን በዘር ተኮር ጭፍጨፋ ለመጠየቅ ታስቦ የነበረው ህግ መሰረዙ ይፋ ተደረገ፡፡
የኢትዮጵያ አሜሪካውያን የዜጎች ምክር ቤት ከከፍተኛ የአሜሪካ ባለስልጣናት ጋር ያደረገውን ስብሰባ መሰረት በማድረግ ሴናተር ጂም ኢንሆፍ ለምክር ቤቱ መረጃ መላኩ ታውቋል፡፡
በመረጃውም በኢትዮጵያ “የዘር ተኮር ጭፍጨፋ ተካሂዷል” በሚል ሀሰተኛ ውንጀላ ኢትዮጵያን ለመጠየቅ የሚረዳና በአሜሪካ ሴኔት ቢሮ የታሰበው ሕግ ማለትም ÷ #HR_4350 አንቀፅ_6464_ “Determination of Potential Genocide or Crimes Against Humanity” የሚለው ረቂቅ ህግ ሙሉ በሙሉ መሰረዙን ምክር ቤቱ ይፋ አድርጎል።
ታስቦ የነበረውን ህግ ለማሰረዝ በሴናተር ጂም እና በሲቪል ምክር ቤቱ መካከል አጀንዳ ሆኖ ክርክር ተደርጎበት ነበር።
የኢትዮጵያ አሜሪካውያን የዜጎች ምክር ቤት ፕሬዚዳንት ዲያቆን ዮሴፍ ተፈሪ ለሴናተር ጂም ኢንሆፍ ምስጋና ማቅረባቸውን የሀገር ውስጥ መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል፡፡
በኢትዮጵያ ላይ የተለያዩ ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ጫና ለማሳደር ሲል የፕሬዚዳንት ባይደን አስተዳደር እየተከተላቸው ከነበሩት መንገዶች መካከል ይህ የተለያዩ ሚዲያዎችን የሀሰት መረጃ መሰረት አድርጎ ሲዘጋጅ የነበረው ህግ አንዱ ነበር።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለ1 ሚሊዮን ዲያስፖራዎች ያደረጉት ጥሪ
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ለ1 ሚሊዮን ዲያስፖራዎች ጥሪ አቀረቡ
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ 1 ሚሊዮን ዲያስፖራ ኢትዮጵያዊያንና ወዳጆች ወደ ኢትዮጵያ እንዲገቡ የሚደረገውን ጥሪን እንዲቀላቀሉ ጠየቁ፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቲውተር ገፃቸው የአውሮፓዊያኑን አዲስ ዓመት በኢትዮጵያ ለማክበር መንግሥት ያቀደውን 1 ሚሊዮን ዲያስፖራ ኢትዮጵያዊያንና የኢትዮጵያ ወዳጆች ወደ አገር ቤት እንዲገቡ የማድረግ ጥሪን እንዲቀላቀሉ ነው የጠየቁት፡፡
ሐኪም አበበች ግንባር ድረስ በመሄድ ለቁስለኛው መድሃኒት በማቅረብ ለማከም እና ስንቅ ለማቅረብ እንደሚዘምቱ አስታወቁ፡
ሐኪም አበበች ግንባር ድረስ በመሄድ ለቁስለኛው መድሃኒት በማቅረብ ለማከም እና ስንቅ ለማቅረብ እንደሚዘምቱ አስታወቁ፡
በእርዳታ ስም የሚደረግን ጣልቃ ገብነት መንግሥት አስጠነቀቀ
በእርዳታ ስም የራሳቸውን የውጭ ፖሊሲ የሚያራምዱ አንዳንድ አገራት ከድርጊታቸው ሊጠነቀቁ እንደሚገባ መንግሥት አሳሰበ፡፡
የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን አገልግሎት በሰጠው መግለጫ ኢትዮጵያዊያንና ትውልደ ኢትዮጵያዊያን እንዲሁም የኢትዮጵያና የእውነት ወዳጆች ሰልፍም ይህንኑ በተለያዩ ሰበቦች በኢትዮጵያ ጉዳይ ጣልቃ የመግባት ፍላጎትን የሚቃወም እንደሆነ አሳውቋል፡፡
ሰልፈኞቹ ጣልቃ የሚገቡ አገራት በኢትዮጵያ ላይ እያደረሱ ያለውን ጥፋት ሊያጤኑ እንደሚገባ ስለመግለፃቸው ሚኒስትር ዴኤታዋ ሰላማዊት ካሳ ገልጸዋል፡፡
በዲያስፖራው በኩል ኢትዮጵያን ለመደገፍ የሚስተዋለው መነሳሳት የሚደነቅ ነው ብለዋል
መንግሥት የዲያስፖራውን ተነሳሽነትና የድጋፍ ጥያቄ በማስተባበር ይሰራልም ብለዋል፡፡
አገሪቱ ላይ የሚደረገውን ጫና በራሳቸው ተነሳሽነት ለዓለም ያሳወቁ ሰልፈኞችን ተመስግነዋል፡፡
