en
Feedback
ሊ/መ ቴዋድሮስ ዮሴፍ

ሊ/መ ቴዋድሮስ ዮሴፍ

Open in Telegram

እውነት እውነት እላቹሀለው ቻናሉ 100% መስራት ሲጀምር ገራሚ ገራሚ የታላቁ ዘማሪ ሊቀ መዘሙር ቴዎድሮስ ዮሴፍ አዳዲስ ና የቆዮ መዝሙሮች ይለቀቁበታል @Tewodros_yosef_mezmurs Join ይበሉት፡፡

Show more
The country is not specifiedThe category is not specified
7 085
Subscribers
+824 hours
+357 days
+11430 days
Posts Archive
+++ የመነኩሴው ፈሊጥ +++ መጾም ያቃተውን ሰው ጹም፣ መመጽወት የተሳነውን መጽውት፣ መራመድ የማይችለውን ሩጥ የሚሉ መካሪዎች ብዙ ናቸው፡፡ መራመድ የማይችል እንዴት መሮጥ እንዳለበት ከማሳየት ይልቅ ቀንበር ማክበድ ጠባያችን ሆኗል፡፡ ይህ የሚያሳየው ቃሉ እንጂ ተግባሩ የተለየን መሆኑን ነው፡፡ በተግባር መግለጥ ብንችል ኖሮ፣ ማገዝ ቢያቅተን እናሯሩጠውና ሰውነቱ ሞቆ ተጋድሎ ሲጀምር እናፈገፍግ ነበር፡፡ እኛ ግን ልምድ የሌለውን ሁሉ ተሸከም ማለት ይቀለናል፡፡ ከባለ ግመሉ ከአባ ቆሪር ምክር ለመመጽወት የሄደ ክርስቲያን ግመሉ ከሚችለው በላይ ስለጫነው አንተ አቅም አጥተህ ምክር ለመቀበል መጥተህ ሳለ ግመሉን ካለ አቅሙ ለምን ጫንከው ተብሏል፡፡ ከዐቅማቸው በላይ ተሸክመው የከበዳቸውን ሰዎች በማገዝ ሸክሙ ሳይከብዳቸው፣ ከክርስቲያናዊ ተጋድሎ ሳያፈገፍጉ በእምነት እንዲኖሩ ማገዝ ከዘመናችን የሃይማኖት ሰዎች የሚጠበቅ መሆኑን ለማስታወስ የአባ ዳንኤልን ፈሊጥ በአብነት እጠቅሰዋለሁ፡፡ አንድ አባ ዳንኤል የሚባል መነኩሴ ነበር፡፡ የደከመ ባገኝ አግዛለሁ እያለ በጨረቃ ከበዓቱ ወጥቶ ገዳማውያን በሚገኙበት በረሓ ይዞር ነበር፡፡ በአንድ ወቅት የማትሠራው ኃጢአት ያልነበር፣ ከጽድቅ ተግባር የማትተዋወቅ ሴት አገኘ፡፡ አባ ዳንኤልም ሴቲቱን ወደ ሴቶች ገዳም ወስዶ ልብላ ካለች ትብላ፣ ልተኛ ካለች ትተኛ፣ የፈቀደችውን ሁሉ ታድርግ፣ የገዳሙ ሕግ አይፈቅድም በማለት ቀንበር አንዳታከብዱባት ብሎ ለእመምኔቷ አስረክቧት ሔደ፡፡ እመምኔቷም እንደታዘዘችው አደረገች፡፡ ሴቲቱ በፈለገች ጊዜ ትበላለች፣ ስትፈልግ ትተኛለች፡፡ ያሰኛትን ታደርጋለች፡፡ ግን ደስታ የላትም፤ አብረዋት የሚኖሩት መነኮሳት ቤተ ክርስቲያን አድረው፣ በሥራ ተጠምደው ሲኖሩ ተመለከተች፡፡ እሷ በልታ ይርባታል፡፡ እነሱ ሳይበሉ አይራቡም፣ እሷ ተኝታ ይደክማታል፣ እነሱ ቆመው ውለው፣ ቆመው አድረው ድካም አያውቁም፡፡ ቀስ በቀስ መገረም፣ ከዚያም በሕይወታቸው መቅናት ጀመረች፡፡ ምግብ ሲያቀርቡላት እስከ ሦስት ሰዓት ልቆይ ማለት ጸሎት አድርጋ መብላት ተለማመደች፡፡ ቆየችና እስከ ስድስት ልቆይ አለቻቸው ከዚያም እስከ ዘጠኝ፣ ከዚያም በ24 ሰዓት አንድ ጊዜ መመገብ ጀመረች፡፡ ከዚያም ከሳምንት አንድ ቀን ብቻ መቅመስ በመጨረሻም በዓቷን ዘግታ በሦስት ሳምንትም፣ በወርም በሕይወት ለመቆየት ያህል መቅመስ ደረሰች እንዲህ ድክመታችን ታግሠው ለክብር የሚያበቁን ባለ ፈሊጥ መምህራን ማግኘት ለዚህ ዘመን እንዛዝላ ተሸካሚ ከዕንቊ የበለጠ ስጦታ ነው እላለሁ፡፡

+++ ንጹሕ እጆች ግን ባዶ እጆች! +++ አንድ ሰዉ እጁን ወደ እግዚአብሔር አነሳና ፣ "ጌታ ሆይ! ተመልከት እጆቼ ንጹሖች ናቸዉ። አልሰረቁም ፤ አልገደሉም" አለ። እግዚአብሔርም ፣ "አዎ ልጄ እጆችኽ ንጹሖች ናቸዉ ምንም ኃጢአት አልሰሩም። ነገር ባዶ ናቸዉ። አልሰረቅህም ነገር ግን አልመፀወትክም። አልገደልክም ነገር ግን የተቸገረ አልረዳኽም" አለዉ። እናም እግዚአብሔር ከኛ የሚፈልገዉ መጥፎ ነገር አለማድረጋችንን ብቻ ሳይሆን መልካም ነገር ማደረጋችንንም ይፈልጋል!

መጋቤ ሐዲስ እሸቱ አለማየኹ የኾነ ጊዜ እንዲኽ ብለው ነበር ፦ በሀገራችን አሁን አሁን ከሰባ ሰባቱ ድርቅ የከፋ የነፍስ ረኃብ ወሮናል ። ችግሩ የነፍስ መራቆት እንደ ስጋው ገጦ አለመታየቱ ነው። በስጋ ምግብ ያጣ ኾድ እና ኾድ ያጣ ምግብ አለ። የደኻዎቹ ምግብ ያጣ ኾድ ሲኾን ፣ የሀብታሞቹ ደግሞ ኾድ ያጣ ምግብ ነው ፣ የነፍስ ጉዳይም ይህ ነው። መርጦ መመገብ ያሻል...ገንዘብ ሲበዛ አመጋገባችን እንደሚቀየር ኹሉ ግንዛቤም ሲበዛ የምናነበው በጥበብ እየነጠረ መሄድ ያሻዋል። ለዚህ ነው ዛሬ ዛሬ ዶ/ር እየገዙ የመጡ ሀብታሞች ገንዘብ እንጂ ግንዛቤ የሌላቸው ፣ ለሰፊ ግቢያቸው የሚመጥን ሰፊ ሀሳብ የሚያጥራቸው። ታዲያ የነዚህ ሰዎች ቤት ከመካነ እንሰሳት በምን ይለያል ትላላችሁ? የማያነብ ሰው ማለት በመብል እና መጠጥ የኑሮ ዘይቤው የተቀመመ መኖሩን በሚነዳው መኪና እና በስጋ ማረፊያው ቤቱ ልክ የሚሰፍረው ማንም እንዳሻው የሚቃኘው ስልት አልባ ክራር እንደማለት ነው። ስታነቡ ግን ትጠይቃላችሁ ፣ ትመረምራላችሁ እንጂ የማንንም ሀሳብ ማራገፊያ ቀፎ ሳጥን ልትኾኑ አትችሉም። ለራስ ክብር ማጣት የሚመነጨው ከንባብ እጦት ከነፍስ ረኃብ ነው። ለዚህ ነው ያላነበበ ሰው የሌላ ሰው የሃሳብ መስጫ ሳጥን የሚኾነው። ነፍስ ብርድ ብርድ ሲላት ለሙቀት መስጫነት ምግቧ ንባብ ነው!! ግን ማንኛውም መጽሐፍ የረኃቧ ማስታገሻ አይደለም። የነፍስ ምግብ ልክ እንደ ስጋ ምግብ ነው እንደ ቆሎ ፣ እንደ ጨው ፣ አልያም እንደ ተስማሚ ምግብ አንብበው አለምን በዕውቀታቸው የበረዙና የጠፉ አሉ እነሱ የተበከለ የነፍስ ምግብ የተመገቡ ናቸው። የሰው ልጅ አዕምሮው ታርዞ ቀፈቱ ቢጠቀጠቅ ረብ አልባና በነፍሱ ኳሻኮር የተመታ ግንብ ነው። የጠገበ ህዝብ ያለው ኅብረተሰብ የማንም ሃሳብ ማራገፊያ አይኾንም!ለዚህም ከድልድይ እና ድንጋይ ግንባታ ጎን ለጎን የአዕምሮ ግንባታ ጉዳይ ሊተኮርበት ይገባል!

+ አባቴ! ጸሎቱን ልቀጥል ወይስ ልተወው? + ልቦናው ሰብስቦ መጸለይ አልችል ያለው ደቀመዝሙር አረጋዊውን እንዲህ ሲል ጠየቃቸው፦ "አባቴ ! የጸሎት መጽሐፌን ይዤ ስጸልይ ልቦናዬ አይሰበሰብልኝም። አፌ ቢጸልይም ልቦናዬ አይተረጉምም። እርሶ እንደነገሩኝ ደግሞ ቅዱሳን በፍፁም ሓሳባቸው እየጸለዩ ያራቀቃሉ እንባና ጸጸት እየጨመሩ እየደረሱ እኛ በልባችን ሌላ እያሰብን በአፋችን ብቻ እንደ እነሱ ብንናገር እንደ ገደል እንደ ዋሻ ሆነን በእግዚአብሔር እየቀለድን ነው ፤ ጸሎት አይሆንልንም። እንግዲህ የአፌ ጸሎት ቅድመ እግዚአብሔር የማይደርስ ከሆነ ጸሎቴን ብተወው ይሻላል ወይስ ብቀጥለው?" እርሳቸውም እንዲህ ሲሉ መለሱለት፦ "ዕውር ሰው በዘንጉ ምድር እየመታ ሲሄድ ከምንገድ ላይ ያለ እባብ ለጊዜው ድምጹን ሰምቶ ይመታኛል ብሎ እንደሚሸሽለት ሁሉ አንተም አስተውለህ ባትፀልይም በአፍህ ውስጥ ቃለ እግዚአብሔር ይንኳኳል። የቃለ እግዚአብሔሩን መንኳኳት የሰሙ አጋንንት መሸሻቸው አይቀርምና ምንም ቅድመ እግዚአብሔር ባይደርስም ጸሎትህን አትተው! አጋንንት ማባረር ጥቅም ነውና!! ብዙ ከምትጸልየው አንዳንድ ጊዜ ልብህ ከሚወድቅባት ቃል ተጠራቅማ ወደ እግዚአብሔር እንዲደርስልህ ምንም ዝርው ልብ ብትሆንም አፍህም ፍጥረት ነውና አንተም በዳይ አንተም አኩራፊ አትሁን በአፍህ ብቻ ቢሆንህን መናገር አትተው!!!!!" አሉት ይባላል።

+++ ከማየት ከመስማት ተጠበቅ! +++ ወደ ማየት ወደ መስማት የቀረበ ከጒድጓድ ከገደል አፋፍ ላይ የቀመ ጠላቱ ወርውሮ ገፍቶ ሊጥለው የሚቻለው ሰውን ይመስላል። ልጣላው ያለ ኹሉ አንድም ልጣለው ባለበት ጊዜ ሊጥለው ይቻለዋልና! ከማየት ከመስማት የራቀ ግን ከጒድጓድ ከገደል ርቆ ያለ ፣ ጠላቱ ስቦ ጎትቶ ጒድጓድ ሊያገባው ወርውሮ ገፍቶ ሊጥለው የማይቻለው ፣ ከጌታ ረዳት ስለማግኘት መብት የሚሰ 'ጠው ማለት ሣሩን እንጨቱን ጨብጦ ድንጊያውን ታቅፎ እርዱኝ የሚል ረዳት አግኝቶ የሚድንን ይመስላል። ምንጭ ፦ መጽሐፍተ መነኮሳት (ፊልክስዩስ) ተስእሎ ፻ ፣ ከገጽ ፻፴፬ - ፻፴፭

ቅዱስ ሚካኤል አሸናፊ ነው በሰማይ ሰልፍ ዘንዶውን ጣለው የሚረዳን በመከራ ቀን ደጉ መላዕክ ያምላክ ባለሟል

#እንደ_እባብ_ልባሞች_እንደ_ርግብም_የዋሆች_ሁኑ። {{ማቴ ፲፥፲፮ }} እንደ እባብ ጠቢብ ኹን ሲል ምን ማለት ነው? እባብ ጭንቅላቱን (ራሱን) ለማዳን ሲል ሌላው ሰውነቱ እጅግ በጣም ብዙ ጉዳት ቢደርስበት ይመርጣል፡፡ ስለዚህ እንደ እባብ ጠቢብ ኹን ሲልህ ሃይማኖትህን ለመጠበቅ ስትል ሀብትህን፣ ዝናህን፣ ጓደኞችህን፣ ወይም ይህን የመሰለ ሌላ ነገር ማጣት ካለብህ እንኳን በዚህ ማዘን መቆርቆር የለበህም ሲል ነው፡፡ ሃይማኖትህ ራስህ ነውና - እውነትን የምታውቅበት! እውነት ደግሞ አርነት ያወጣሃል፡፡ ኾኖም እንደ እባብ ጠቢብ መኾን ብቻውን ለእኛ በቂያችን አይደለም፤ እንደ ርግብ ሐቀኞችና የዋሆች መኾንም ያስፈልገናል፡፡ በጎ ምግባር የሚኖረው ጥበብንም የዋህነትንም አስተባብሮ መያዝ ሲቻል ነውና፡፡ ለምን ቢሉ እንደ እባብ ጠቢብ የኾነ ሰው ስለ ሃይማኖቱ ሲል ብዙ መከራዎችን ሊቀበል ይችላል፡፡ መከራ በሚያደርሱበት ላይ ክፉን በክፉ አለመመለስ የሚችለው ግን እንደ ርግብ የዋህ መኾን ሲችል ነው፤ እንደ ርግብ የዋህ መኾን ማለት መከራ በሚያደርሱብን ላይ በበቀል አለመነሣሣት መቻል ማለት ነውና፡፡ የዋህነት በጥበብ ሚዛን ካልተመጣጠነ አንድ ሰው መከራ ሲቀበል መከራ በሚያደርስበት ላይ በበቀል እንዲነሣ ያደርጓልና፡፡ ጥበብ በየዋህነት ሚዛን ካልተመጣጠነም እንደዚሁ አላስፈላጊ ሰማዕትነትን እንዲቀበሉ ያደርጋልና፡፡ ስለዚህ ሃይማኖትህን ለመጠበቅ ስትል እንደ እባብ ጠቢብ ኹን፡፡ አብረህም መከራ በሚያደርስብህ ላይ ላለመበቀል ስትል እንደ ርግብ የዋህ ኹን፡፡ ኹለቱንም አዋሕደህ አስተባብረህ ያዝ!

#ትህትና 👉ትህትና እኔ ከሁሉ ታናሽ ነኝ ማለት ነዉ እንደ #ዮሃንስ ፡ 👉ትህትናስ እኔ ትል ነኝ ማለት ነዉ እንደ #ዳዊት ፡ 👉ትህትናስ ኃጢያተኛ ነኝ ማለት ነዉ እንደ #ጴጥሮስ ፡ 👉ትህትናስ እኔ ጭንጋፍ ነኝ ማለት ነዉ እንደ #ጳውሎስ ፡ 👉ትህትናስ እኔ አፈርና አመድ ነኝ ማለት ነዉ እንደ #አብርሃም 👉ትህትናስ ባሪያ ነኝ ማለት ነዉ እንደ ያእቆብ " ራሱን ከፍ የሚያደርግ ሁሉ ይዋረዳልና፥ ራሱንም የሚያዋርድ ከፍ ይላል።" (የሉቃስ ወንጌል 14:11) ራሱን ከፍ የሚያደርግ ሁሉ ዝቅ ይላል : ራሱን ዝቅ የሚያደርግ ሁሉ ከፍ ይላል » ትህትና ክብርን ትቀድማለች።መጸሐፈ ምሳሌ18- 12። 👉 የሚገርመው ግን እራሱን የሚያዋርድ ከፍ ይላል የሚለውን ቃሉን እግዚአብሔር ለ ቅዱሳኑ ሲፈጽምላቸው በመጸሐፍቅዱስ ውስጥ እናያለን። + ለምሳሌ ቅዱስ ዮሐንስ ስለ ኢየሱስ ሲናገር እኔ የጫማውን ጠፍር ልፈታ ዘድን የሚገባኝ አይደለሁም ብሎ ራሱን ዝቅ ሲያደርግ።፡ + ኢየሱስ ግን አክብሮት መጥምቀ መለኮት ለመባል አበቃው።ማቴዎስ ምህራፍ 3 ቁጥር 11 ዮሐንስ 1 -26-27 👉 ቅዱስ ጴጥሮስም ራሱን በማዋረዱና ዝቅ ከማድረጉ የተነሳ እንዲህ ብሎአል« ጌታ ሆይ እኔ ኃጢያተኛ ነኝና ከኔ ተለይ» አለው። + ክርስቶስ ግን አክብሮት ጴጥሮስን ሊቀ ሐዋርያት አደረገው ሉቃስ 5 -8። ዮሐንስ 21 -17 ። 👉 ቅዱስ ዳዊትም እራሱን ዝቅ ሲያደግ እንዲህ አለ « እኔ ትል ነኝ ሰውም አይደለሁም አለ። + እግዚአብሔር ግን አክብሮት እንዲህ አለው« እንደ ልቤ የሆነ ዳዊት» ብሎ አከበረው።

ለሰው ልጆች ሁሉ የሚራራ ልብሱ እደ መብረቅ የሚያበራ ካምላክ አለቅነት የተሰጠው የመላዕክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል ነው

ባለንበት እንቁ በእምነት በተስፋ ገብርኤል ይመጣል እሳቱን ሊያጠፉ የስሙ ትርጓሜ ሰው የሆነ አምላክ ነው ደስታን ያበሰረን ገብርኤል እሱ ነው

✞ብርና ወርቅ ሳይዙ✞ ብርና ወርቅ ሳይዙ ዓለማትን ዞሩ ቅዱሳን ሐዋርያት ቃሉን እየዘሩ ሙታን እያስነሡ ድውያን ፈወሱ ስሙን ብቻ ይዘው(፪)ታምነው በንጉሡ ከቀራጩ መደብ ከሐጥያት ገበታ ከጥብርያዶስ ባሕር ከጠራቸው ጌታ ስሙን ተሸክመው ቃሉን መሰከሩ በመንፈስቅዱስ ኃይል ድንቅን እየሠሩ አዝ= = = = = የነገስታቱን ቃል ዛቻውን ሳይፈሩ የመንግስቱን ወንጌል ለዓለም አስተማሩ ይሻለናል አሉ ማድላት ለእግዚአብሔር ለሰው ከመታዘዝ ዘላለም ለማይኖር አዝ= = = = = ቆዳቸው ተገፎ በሰይፍ ተሰየፉ ስለጌታ ፍቅር በመከራ አለፉ የድንጋዩን ናዳ የእሣቱን ነበልባል የጀርባን ግርፋት በእምነት ታግሰዋል አዝ= = = = = ስደት ነው መከራ ረሀብ ነው ወይስ ጥም ከክርስቶስ ወንጌል ከእውነት የሚያስቆም በእርሱ ስላመኑ በጽድቅ ተጋደሉ ደግሞም በእርሱ በላይ እንዳለ በቃሉ አዝ= = = = = በዙርያችን ከበው ካሉ እንደ ደመና እነርሱን እያሰብን በእምነት እንፅና በእውነት እንደኖሩ መሥለው ክርስቶስን እኛም በኑሮችን እንምሰል እነርሱን ሊቀ መዘምራን ዲያቆን ቴዎድሮስ ዮሴፍ "..ብርና ወርቅ የለኝም፤ ይህን ያለኝን ግን እሰጥሃለሁ፤ በናዝሬቱ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ተነሣና ተመላለስ አለው።" ሐዋ፫፥፮

✞መመኪያ ዘመዳችን✞ አዘክሪ ለኃጥአን ወአኮ ለጻድቃን አዘክሪ ለርሱአን ወአኮ ለንጹሐን ትርጉም ለጻድቃን ያይደለ ለኃጥአን አሳስቢ ለንጹሐን ያይደለ ለተዳደፉት አሳስቢ መመኪያ ዘመዳችን(፪) ልጇ የሆነልን እርሷ ናት/ድንግል ማርያም/(፪) እመቤታችን የታተመች ጉድጓድ ንጽይት በድንግልና በኀልዮ ነቢብ ገቢር ጽድቅ ቅድስና ከሆነች እመቤት እንበለ ዘር ተወልዶ ያለ እናት ቀዳማይ ልደቱን ሊገልጽልን ወዶ ሰይጣን ካሳተበት ከላቀ ምስጢሩ ለእሳተ መለኮት ሆነችው መንበሩ አዝ= = = = = እግዚአብሔር ዘርን ባያስቀር ከድሮ እንደ ሰዶም በሆንን ገሞራንም በመሰልን ኖሮ ያቺ ዘር በአዳም ሆድ ከዕንቁ ስታበራ ከመርገም ለይቷት ዘመናት ስትጠበቅ ኖራ ምዕራግ ሆነችና ሰማይ የደረሰ የፍጥረት መጀመሪያ በእርሷ ታደሰ አዝ= = = = = ከእንግዲህ አናፍርም በሔዋን ስህተት አግኝተናልና በልጇ በድንግል መድኃኒት ይኸው ተፈጽሟል የአዳም ምኞቱ በእሪና አምላክ የሰውንም ልጅ በማየቱ የእናት አማላጅ መመኪያ የሰጠን ወልደ አብ ወልደ ማርያም ዘላለም ይመስገን በዋሽንግተን ዲሲ የምሥራቀ ፀሐይ ቅዱስ አቡነ ተክለሃይማኖት ቤ/ክ/ሰ/ት/ቤት "የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር ዘርን ባያስቀርልን ኖሮ እንደ ሰዶም በሆንነ እንደ ገሞራም በመሰልነ ነበር" ኢሳ ፩፥፱

✞እመቤቴ ማርያም✞ እመቤቴ ማርያም እለምንሻለው በለቅሶ ዋይታ ፊትሽ ወድቄአለው እመቤቴ ስሚኝ ተማጽኜሻለው(፪) ሐዘኔን ጭንቀቴን ለማን እነግራለው ችግሬን ጉዳቴን ለማን አዋያለሁ እመቤቴ ስሚኝ ተማጽኜሻለው(፪) ሐዘኑ በዛብኝ መከራው ከበደኝ እንደምን ልቻለው እኔ ብቻዬን ነኝ የአማኑኤል እናት ፈጥነሽ ድረሽልኝ(፪) በጣም ተንገዳገድኩ ልወድቅ ነው እኔ እመ አምላክ ደግፊኝ ቁሚልኝ ከጎኔ ምንም አጋር የለኝ ከአንቺ በቀር ለእኔ(፪) መዝሙር ይልማ ኃይሉ "የምድር ባለጠጎች አሕዛብ ኹሉ በፊትሽ ይማለላሉ" መዝ ፵፬፥፲፪

ኪዳነ ምሕረት የ ረፍቴ እናት # ዘማሪ አቤል መክብብ

✞ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሀገር ናት በውሀ ግድግዳ በደም መሰረት ለክብሩ የመረጣት በስሙ የጠራት ቤተክርስቲያን ተዋህዶ ናት አትፈርስም ጉልላቷ እርሱ ነው የቀደሳት የሰራት ደሙ ነው ብትፈተን በእሳት በመከራ ትኖራለች ሁሉንም ተሻግራ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ሀገር ናት የሰጠች ክብር ነፃነት /2/ አዝ________________ የማጠፋ በእሳት የተሰራች ከምድር ሆና ሰማይ የደረሰች የእግዚአብሔር የፀጋው ግምጃ ቤት ተዋህዶ ስንዱዋ እመቤት ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ሀገር ናት /2/ የሰጠች ክብር ነፃነት /2/ አዝ________________ የፅድቅ ቤት የድህነት መርከብ መጠሪያ ነች ለሀገር እና ለሕዝብ ሕይወት ያላት እውነት የምትገልጥ የማታረጅ የማትለወጥ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ሀገር ናት /2/ የሰጠች ክብር ነፃነት /2/ አዝ________________ ተዋህዶ ያለች በቅድምና ለኢትዮጵያ ሞገሷ ናት እና ያለ እርሷ ኢትዮጵያ አትኖርም መለያየት ከቶ አይቻልም ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ሀገር ናት /2/ የሰጠች ክብር ነፃነት /2/ መዝሙር ዘማሪት ሰብለወንጌል እሸቴ

# ኪዳነ ምሕረት የ ረፍቴ እናት ኪድነ ምሕረት የእ ረፍቴ እናት ሠላም ሆነ በ አንቺ አማላጅነት ንጽሕት ድንኳን በ ዕምነት የአጌጥሁብሽ ሠላም ሆነ በ አማኑኤል ልጅሽ ሠላም ሆነ በ አማኑኤል ልጅሽ/፪/ /አዝማች/ የ ብርሐን ዝናር በአይኖረኝም በ ንጉሥ ፊት ተሸልሜ ብቆም በ ልጅሽ ነው ውበቴ ማማሩ በ ምልጃሽ ነው ሥሜ መቀየሩ በ ልቤ ላይ ተነበበ ልጅሽ አዎ ሥሜ ተጠርቷል በ ልጅሽ ከ ታች በ ምድር እስከ ሠማያት ድረስ ድርሻዬ ነው ሥምሽን ማወደስ ድርሻዬ ነው ሥምሽን ማወደስ /አዝማች/ የ ከበረ ሆነሽ ንግግሬ ቅኔ አነሳሁ ለ ክብርሽ ዘምሬ እንደ ዝግባ ከፍ ብዬ ብታይ ወጥቶልኝ ነው በ ሠማይ ጸሐይ ሥለ ምልጃሽ ዘይቱ ፈሠሠ አንቺን ይዤ ሙሽራው ደረሠ ቀንዲሌ ነሽ ድንግል አዛኝቱ በ ልጅሽ ነው የ ነፍሴ ጽናቱ በ ልጅሽ ነው የ ነፍሴ ጽናቱ /አዝማች/ ከ ኤልያብ ቢደምቅ ደም ግባቴ ማን ሊመርጠኝ ያለ አንቺ እናቴ ተዋብሁብሽ ነፍሴ በ አንቺ አበራ አንደበቴ ሥምሽን ሲጠራ እንደ ሙሴ እንደ አሮን በትር ማምለጫዬ ከ ፈርዖን ቀንበር ከ እንግዲኽማ እኔ እንዴት አዝናለሁ አማላጄ አንቺን ይዤሻለሁ አማላጄ አንቺን ይዤሻለሁ /አዝማች/ ኪዳነ ምሕረት የ ረፍቴ እናት ሠላም ሆነ በ አንቺ አማላጅነት ንጽሕት ድንኳን በ ዕምነት ያጌጥሁብሽ ሠላም ሆነ በ አማኑኤል ልጅሽ ሠላም ሆነ በ አማኑኤል ልጅሽ። በዘማሪ አቤል መክብብ

#ድንግል_ስልሽ #በዘማሪት_መራሽ_ታዬ @Tewodros_yosef_mezmurs @mezmurs_mezmurs @mezmurs_mezmurs_group

#የሰላም_አምላክ_ግባ #በዘማሪት_መራሽ_ታዬ @Tewodros_yosef_mezmurs @mezmurs_mezmurs @mezmurs_mezmurs_group

#እንክርዳድ_ኑፋቄን #በዘማሪት_ፋሲካ_ፍስሃ @Tewodros_yosef_mezmurs @mezmurs_mezmurs @mezmurs_mezmurs_group

#የማያልፍ_የለም #በዘማሪ_ዲያቆን_ዳኛቸው_ደምሴ @Tewodros_yosef_mezmurs @mezmurs_mezmurs @mezmurs_mezmurs_group