Digital Library of Educations | ትምህርታዊ ዲጂታል መፅሀፍት
Open in Telegram
አጠቃላይ የአጫጭር ማስታወሻ በቪዲዮ የተዘጋጀ ለብዙ ትምህርታዊ ነክ የሆኑትን ማዘጋጀት ጀምረናል። • 1-12ኛ ክፍል • ጥያቄ እና መልስ መስራት ዩቱብ ላይ ተከታተሉ: https://youtube.com/@Mstv_Kinemaster_Show https://youtube.com/@DigitalLibraryofEducations • ዩኒቨርሲቲ የተጠቃለለ ኮርሶች እና መፅሐፎች • ዩኒቨርሲቲ ጥያቄ እና መልስ መስራት።
Show more1 041
Subscribers
No data24 hours
-77 days
-2030 days
Data loading in progress...
Similar Channels
Tags Cloud
No data
Any problems? Please refresh the page or contact our support manager.
Incoming and Outgoing Mentions
---
---
---
---
---
---
Attracting Subscribers
September '26
September '26
+1
in 0 channels
August '26
+24
in 0 channels
Get PRO
July '26
+24
in 0 channels
Get PRO
June '26
+21
in 0 channels
Get PRO
May '26
+14
in 0 channels
Get PRO
April '26
+12
in 0 channels
Get PRO
March '26
+16
in 0 channels
Get PRO
February '26
+13
in 0 channels
Get PRO
January '26
+19
in 0 channels
Get PRO
December '25
+14
in 0 channels
Get PRO
November '25
+13
in 0 channels
Get PRO
October '25
+28
in 0 channels
Get PRO
September '25
+102
in 0 channels
Get PRO
August '25
+11
in 0 channels
Get PRO
July '25
+14
in 0 channels
Get PRO
June '25
+29
in 0 channels
Get PRO
May '25
+39
in 0 channels
Get PRO
April '25
+29
in 0 channels
Get PRO
March '25
+26
in 0 channels
Get PRO
February '25
+54
in 0 channels
Get PRO
January '25
+45
in 0 channels
Get PRO
December '24
+31
in 0 channels
Get PRO
November '24
+29
in 0 channels
Get PRO
October '24
+35
in 0 channels
Get PRO
September '24
+36
in 0 channels
Get PRO
August '24
+32
in 0 channels
Get PRO
July '24
+25
in 0 channels
Get PRO
June '24
+31
in 1 channels
Get PRO
May '24
+28
in 0 channels
Get PRO
April '24
+29
in 0 channels
Get PRO
March '24
+13
in 0 channels
Get PRO
February '24
+27
in 0 channels
Get PRO
January '24
+21
in 0 channels
Get PRO
December '23
+17
in 0 channels
Get PRO
November '23
+33
in 0 channels
Get PRO
October '23
+79
in 5 channels
Get PRO
September '23
+55
in 0 channels
Get PRO
August '23
+54
in 0 channels
Get PRO
July '23
+110
in 0 channels
Get PRO
June '23
+153
in 0 channels
Get PRO
May '23
+151
in 0 channels
Get PRO
April '23
+58
in 0 channels
Get PRO
March '23
+42
in 0 channels
Get PRO
February '23
+67
in 0 channels
Get PRO
January '23
+183
in 0 channels
Get PRO
December '22
+765
in 0 channels
| Date | Subscriber Growth | Mentions | Channels | |
| 08 September | 0 | |||
| 07 September | 0 | |||
| 06 September | 0 | |||
| 05 September | +1 | |||
| 04 September | 0 | |||
| 03 September | 0 | |||
| 02 September | 0 | |||
| 01 September | 0 |
Channel Posts
ትምህርት ሚኒስቴር በ2019 የትምህርት ዘመን በፌዴራል 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለመማር ለተመዘገቡና ለፈተና ለተመረጡ ተማሪዎች ነሐሴ 29/2018 ዓ.ም ፈተና መስጠቱ ይታወቃል።
ይሁን እንጂ ለፈተና ተመርጣችሁ በተለያየ ምክንያት ፈተና ያልተፈተናችሁ ተማሪዎች፣ ሰኞ ጳጉሜን 02/2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 2:30 ጀምሮ በአቅራቢያችሁ በሚገኝ የፈተና መስጫ ማዕከል በመገኘት መፈተን የምትችሉ መሆኑን ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል።
ነሐሴ 29/2018 ዓ.ም ፈተና የወሰዳችሁ ተማሪዎች በድጋሜ መፈተን የማይቻል መሆኑ ተገልጿል።
| 2 | #University
#Placement
የዩኒቨርሲቲ እና የትምህርት መስክ ምርጫ ያድርጉ!
በ2018 ዓ.ም የ2ኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ሀገር አቀፍ ፈተና ወስዳችሁ በመደበኛው የትምህርት መርሐግብር የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ውጤት ያስመዘገባችሁ ተማሪዎች በሙሉ የዩኒቨርሲቲ እና የትምህርት መስክ ምርጫ እንድታደርጉ ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል፡፡
የዩኒቨርሲቲ እና የትምህርት መስክ ምርጫ ማድረጊያ ጊዜ 👇
ከነሐሴ 28/2018 ዓ.ም እስከ ጳጉሜን 05/2018 ዓ.ም
የዩኒቨርሲቲ እና የትምህርት መስክ ምርጫ የሚያደርጉበት ሊንክ 👇
https://student.ethernet.edu.et/
የሕክምና፣ የአካል ጉዳተኝነት፣ ተመሳሳይ ጾታ ያላቸው መንትያዎች እና ከስድስት ወር በታች ህጻን የሚያጠቡ እናቶች አስፈላጊውን ሕጋዊ ማስረጃ ማያያዝ ይኖርባችኋል ተብሏል። | 88 |
| 3 | #Remedial
በ2018 ዓ.ም የሪሚዲያል ፕሮግራም ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የቆዩ ተማሪዎች ውጤት ተለቋል።
https://result.ethernet.edu.et ላይ በመግባት Remedial Examination ከሚለው ስር View Results የሚለውን በመጫንና Username በማስገባት ውጤትዎን ይመልከቱ።
ከግንቦት 27 እስከ ሰኔ 03/2018 ዓ.ም የተሰጠውን ሀገር አቀፍ የሪሚዲያል ፕሮግራም ፈተና 53,620 ተፈታኞች መውሰዳቸውን የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት መግለፁ ይታወሳል። | 103 |
| 4 | #Grade12
በማህበራዊ ሳይንስ የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና በሀገር አቀፍ ደረጃ ከሴቶች ከፍተኛውን ውጤት ያመጣችው መቅደላዊት ሱራፌል ስትሆን ያስመዘገበችው 569.17 ነው። መቅደላዊት ሱራፌል በአዲስ አበባ ከተማ የቦሌ ሱፐር ሆሊ ሴቪየር ትምህርት ቤት ተማሪ ናት። | 171 |
| 5 | #Grade12
በማህበራዊ ሳይንስ የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና በሀገር አቀፍ ደረጃ ከወንዶች ከፍተኛውን ውጤት ያመጣው ተማሪ ሳደም አብዱልአዚዝ ሲሆን ያስመዘገበው ከፍተኛ ውጤት 576.25 ነው። ሳደም በኦሮሚያ ክልል፣ የዶዶላ ኢፋቦሩ አዳሪ ትምህርት ቤት ተማሪ ነው። | 171 |
| 6 | #Grade12
በዘንድሮ የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና በሀገር አቀፍ ደረጃ ከመላው ተፈታኞች ከፍተኛውን ሁለተኛ ውጤት ያመጣው በሀዲያ የሚገኘው የሊችጎጎ አዳሪ ትምህርት ቤት ተማሪው ሮቤል ጌታቸው ሲሆን ያስመዘገበው ውጤት 590.08 ነው። | 146 |
| 7 | #Grade12
#EntranceExam
በ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና 2ኛውን ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገበችው ተማሪ - ሕዳሴ ዘመኑ
በአማራ ክልል አዊ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን እንጅባራ ከተማ የሚገኘው የአገው ምድር 2ኛ ከፍተኛ ደረጃ ት/ቤት ተማሪዋ ሕዳሴ ዘመኑ በ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና 583 በማምጣት 2ኛውን ከፍተኛ ውጤት አስመዝግባለች፡፡
በስሟ ቤተ መጽሐፍት የተሰየመላት ጀግናዋ ተማሪ ሕዳሴ ዘመኑ በተፈጥሮ ሳይንስ በሀገር አቀፍ ደረጃ 2ኛውን ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገበች ሲሆን÷ በሴቶች ደግሞ 1ኛ ደረጃን ይዛ አጠናቅቃለች፡፡
ተማሪ ሕዳሴ በ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና በሀገር አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ ውጤት በማስመዝገቧ መደሰቷን ለፋና ዲጂታል ገልጻለች፡፡
ለፈተናው ልዩ ትኩረት በመስጠት ቀድማ አስፈላጊውን ዝግጅት አድርጋ እንደነበርና በዚህም የድካሟን ፍሬ እንዳገኘች ጠቅሳለች፡፡
በቀጣይ በኮምፒውተር ሳይንስ ሶፍት ዌር ኢንጂነሪንግ ዘርፍ ትምህርቷን በመከታተል ለሀገሯ የበኩሏን ማበርከት እንደምትፈልግ ገልጻለች፡፡
የተማሪ ሕዳሴ ዘመኑ ወላጅ አባት መምህር ዘመኑ ምህረት (ዶ/ር)÷ ልጃቸው ባስመዘገበችው ከፍተኛ ውጤት መደሰታቸውን ተናግረዋል፡፡
ዘንድሮ ፈተናውን ከወሰዱ ተማሪዎች መካከል 12 ነጥብ 8 በመቶ ወይም 70 ሺህ 544 ተማሪዎች የማለፊያ ወጤት አምጥተዋል፡፡ | 166 |
| 8 | #NGAT
#Grade12
የ2018 ዓ.ም የድኅረ-ምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (NGAT) ከነገ ነሐሴ 20/2018 ዓ.ም ጀምሮ ለሁለት ተከታታይ ቀናት በጠዋት እና በከሰዓት ፈረቃ ይሰጣል።
ተፈታኞች ፈተናው ከሚጀመርበት 3ዐ ደቂቃ ቀድመው በመፈተኛ ማዕከል መገኘት ይኖርባቸዋል፡፡
ፕሪንት ያደረጉትን የመፈተኛ መግቢያ ትኬትዎን (Entrance Ticket) መያዝ አይዘንጉ።
ተፈታኞች ከተመደቡበት ማዕከል ውጪ መፈተን አይችሉም።
የብሔራዊ ፋይዳ መታወቂያ የግድ መያዝ ይኖርብዎታል፡፡
የሞባይል ስልክ፣ ሚሞሪ ያለው የእጅ ሰዓት፣ ... የመሳሰሉ ኤሌክትሮኒክ መሳሪያዎች ይዞ ወደ ፈተና ማዕከል መሔድ አይቻልም። | 128 |
| 9 | #Update
#Grade12
#Result
#EntranceExam
የ12ኛ ክፍል ፈተና ውጤት ይፋ ሆነ።
የ2018 ዓ/ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ውጤት ይፋ ተደርጓል። ተፈታኞችም ውጤታቸው ማየት ጀምረዋል።
ውጤት ለማየት ፦
👉 በድረ ገጽ ፡ https://result.eaes.et
👉 ቴሌግራም፡ https://result.eaes.et/telegram
👉 አጭር የጽሑፍ መልዕክት፡ https://result.eaes.et/sms
በአንድ ጊዜ በርካታ ተማሪዎች ውጤታቸውን ለማየት ስለሚሞክሩ የኔትዎርክ መጨናነቅ ሊያጋጥም ስለሚችል ደጋግሞ መሞከር ይገባል።
የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ተፈታኞች ቅሬታ ሲኖራቸው በአካል መምጣት ሳያስፈልጋቸው https://result.eaes.et/complaint የሚለውን ማስፈንጠሪያ በመጠቀም ቅሬታቸውን ከነሐሴ 19 እስከ 26/2018 ዓ/ም ከቀኑ 10፡00 ሰዓት ድረስ ማቅረብና ምላሹንም በዛው ማስፈንጠሪያ መከታተል እንደሚችሉ ገልጿል። | 126 |
| 10 | #Grade12
#Update
#EntranceExam
" ተማሪዎች ከምሽቱ 1፡00 ሰዓት ጀምረው ውጤታቸው ማየት ይችላሉ " - የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት
የ2018 ትምህርት ዘመን የኢትዮጵያ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ፈተና ውጤት የሚገለጽባቸው አድራሻዎች ይፋ ሆነዋል።
በ2018 ትምህርት ዘመን የኢትዮጵያ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ፈተና ውጤትን ተፈታኞች ዛሬ ነሐሴ 19 ቀን 2018 ዓ/ም ከምሽቱ 1፡00 ሰዓት ጀምረው የሚከተሉትን አማራጭ ማስፈንጠሪያዎችን (Link) በመጠቀም ማየት የሚችሉ መሆኑን የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቋል።
በተያያዘም ተፈታኞች ቅሬታ ሲኖራቸው በአካል መምጣት ሳያስፈልግ https://result.eaes.et/complaint የሚለውን ማስፈንጠሪያ በመጠቀም ቅሬታቸውን ከነሐሴ 19 እስከ 26/2018 ዓ/ም ከቀኑ 10፡00 ሰዓት ድረስ በማቅረብ ምላሹንም በተመሳሳይ ማስፈንጠሪያ በኩል መከታተል የሚችሉ መሆኑን አገልግሎቱ ገልጿል።
ውጤት የሚገለጽባቸው ማስፈንጠሪያዎች፡-
- በድረ ገጽ ፡ https://result.eaes.et
- ቴሌግራም፡ https://result.eaes.et/telegram
- አጭር የጽሑፍ መልዕክት፡ https://result.eaes.et/sms | 127 |
| 11 | #EntranceExam
#Grade12
ተማሪዎች ውጤት ማየት የሚችሉበት ቀን የተገለፀ ቢሆንም ብዙ ጊዜ ከተጠቀሰው ቀን ቀደም ብሎ ዌብሳይቱ Active ሊሆን ይችላል። ዌብሳይቱ እንዲሁም የቴሌግራም ቦቱ Active በሆነበት ቅጽበት ተከታትለን የምናሳውቃቹህ ይሆናል። | 120 |
| 12 | #Grade12
የ12ኛ ክፍል ፈተና ውጤት ይፋ አልተደረገም።
የተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ውጤት መለቀቁን በመግለጽ ተማሪዎችና ወላጀችን የሚያደናግር ሀሰተኛ መረጃ እያሰራጩ ይገኛሉ።
እስካሁን የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት፣ የፈተናው ውጤት ይፋ ስለመደረጉ በይፋ አላሳወቀም።
ትክክለኛ የተረጋገጡ መረጃዎች ከትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ብቻ የሚገኙ በመሆኑ ተማሪዎች እና ወላጆች ሀሰተኛ መረጃዎችን ከሚያሰራጩ የተለያዩ አካላትና ገጾች ትጠነቀቁ ዘንድ መልዕክት ያስተላልፋል።
የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) በ2018 ዓ/ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ውጤት ዙሪያ መግለጫ በሰጡበት ወቅት የፈተናው ውጤት ሰኞ ወይም እስከ ማክሰኞ ከሰዓት ይፋ ይደረጋል ማለታቸው ይታወሳል።
ውጤት ሰኞ ዕለት ይፋ ያልተደረገ ሲሆን እስከ ማክሰኞ ከሰዓት ይፋ ይደረጋል ተብሎ ይጠበቃል።
የፈተናው ውጤት ይፋ ሲደረግ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ብቻ በይፋ የሚያሳውቅ ሲሆን እንዴት ማየት እንደሚቻልም ተቋሙ ገለጻ ያወጣል። እኛም ተከታትለን የምናቀርብ ይሆናል። | 134 |
| 13 | #Grade12
ውጤት እስካሁን አልተለቀቀም!!
የ12ኛ ክፍል ውጤት ጋር ተያይዞ ብዙዎች ጥያቄ እየጠየቁ ስለሆነ ዉጤት እስካሁን አለመለቀቁን እናሳዉቃለን::
ከጥቂት ደቂቃዎች በፊት ወደ [ፖርታሉ] ገብተን ስንመለከት፣ "The 2018 result is not released" (የ2018 ውጤት አልተለቀቀም) የሚል መልእክት አለ።
አዲስ መረጃ ወይም ለውጥ ካለ በቅርቡ በትክክለኛው ሰዓት እናደርሳችኋለን።
በትዕግሥት እንድትጠብቁን እንጠይቃለን። | 120 |
| 14 | #Grade12
#EntranceExam
የ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ተማሪ ጃላል ግርማ በሀገር አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ ውጤት አስመዘገበ
የኦሮሚያ ልማት ማህበር አዳማ ልዩ ቦርዲንግ ትምህርት ቤት ተማሪ የሆነው ጃላል ግርማ በ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና 591.6 ከፍተኛ ውጤት አምጥቷል።
ጃላል ግርማ በተፈጥሮ ሳይንስ ዘርፍ 591.6 በማስመዝገብ በሀገር አቀፍ ደረጃ 1ኛ ደረጃን ይዟል።
በማህበራዊ ሳይንስ ዘርፍ ደግሞ ከኢፋ ቦሩ ዶዶላ ልዩ ቦርዲንግ ትምህርት ቤት ተማሪ ሳዳም አብዱላዚዝ ኡመር 576.25 ውጤት በማስመዝገብ በ1ኛ ደረጃ ላይ ይገኛል። | 122 |
| 15 | እንኳን ለ1501ኛው የነቢዩ ሙሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) የመውሊድ በዓል በሰላም አደረሳችሁ። | 124 |
| 16 | የ2019 ትምህርት ዘመን የነባር እና አዲስ ገቢ ተማሪዎች ምዝገባ ከዛሬ ነሐሴ 18/2018 ዓ.ም ጀምሮ በሁሉም ክልሎች ይከናወናል።
ምዝገባው እስከ ጳጉሜን 05/2018 ዓ.ም ድረስ የሚቆይ መሆኑ ተገልጿል።
ዕድሜአቸው ለትምህርት የደረሱ ነባር እና አዲስ ገቢ ተማሪዎችን በማስመዝገብ ኃላፊነትዎን ይወጡ!!
መስከረም 05/2019 ዓ.ም የመጀመሪያ ቀን የመጀመሪያ መደበኛ ትምህርት ክፍለ ጊዜ የሚጀምርበት እንደሆነ መገለፁ ይታወቃል። | 140 |
| 17 | #Update
#Grade12
#EntranceExam
የ12 ኛ ክፍል ውጤት ከዛሬ ምሽት 5 :30 ጀምሮ ይለቀቃል ተብሏል
በእነዚህ አማራጮች
https://eaes.edu.et/
https://t.me/eaesbot
ቅሬታ ለማቅረብ በአካል ሳይመጡ
https://t.me/eaesbot (complaint tab) | 127 |
| 18 | #Grade12
#EntranceExam
የትምህርት ሚኒስትር ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) ምን አሉ ?
(የ2018 ዓ/ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ውጤት መግለጫ)
- የዘንድሮው ውጤት ከአምናው በጥሩ ደረጃ ተሻሽሏል።
- ተማሪዎችን ወደ ዩኒቨርስቲ አስገብቶ ማስፈተን በተጀመረበት የመጀመሪያ አመት ያለፉ 3.2% ፣ በሁለተኛው 2.9% ፣ በሶስተኛው 5.2% ፣ በአምናው አራተኛው ዓመት 8.9% ደረሰ አሁን በአምስተኛው ዓመት 12.8% ነው ያለፉት።
- ዘንድሮ በ2018 ብሔራዊ ፈተና የተመዘገበው ተማሪ ቁጥር 563,960 ሲሆን 550,210 ተማሪ ነው የተፈተነው።
- ፈተናውን ያለፈው ተማሪ ብዛት 70,544 ነው።
- ከተፈጥሮ ሳይንስ 16.6% አልፈዋል። ከማህበራዊ ሳንይስ 8.3% አልፈዋል።
በፐርሰንት - ክልሎች ካስፈተኗቸው ተማሪዎች ምን ያህል ተማሪ አሳለፉ ? (ያሰፈተኗቸው ተማሪዎች ቁጥር ይለያያል)
1. አዲስ አበባ 32.3%
2. ሀረሪ 22.67%
3. አፋር 15.6%
4. አማራ 15.56%
5. ድሬዳዋ 11.29%
6. ትግራይ 11.2%
7. ኦሮሚያ 10.53%
8. ማዕከላዊ ኢትዮጵያ 9.23%
9. ሶማሌ 9.2%
10. ሲዳማ 6.95%
11. ቤኒሻንጉል ጉሙዝ 6.12%
12. ደቡብ ኢትዮጵያ 5.82%
13. ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ 4.92%
14. ጋምቤላ 3.74%
በቁጥር ምን ያህል ተማሪ ከየክልሉ አለፉ ? (ያስፈተኑት ቁጥር ይለያያል)
1. ኦሮሚያ ➡ 20,807 ተማሪዎች
2. አዲስ አበባ ➡ 18,646 ተማሪዎች
3. አማራ ➡ 15,225 ተማሪዎች
4. ትግራይ ➡ 3,146 ተማሪዎች
5. ደቡብ ኢትዮጵያ ➡ 3,011 ተማሪዎች
6. ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ➡ 2,800 ተማሪዎች
7. ሲዳማ ➡ 1,827 ተማሪዎች
8. ሶማሌ ➡ 1,616 ተማሪዎች
9. ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ➡ 835 ተማሪዎች
10. አፋር ➡ 705 ተማሪዎች
11. ሀረሪ ➡ 599 ተማሪዎች
12. ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ➡ 457 ተማሪዎች
13. ድሬዳዋ ➡ 410 ተማሪዎች
14. ጋምቤላ ➡ 280 ተማሪዎች
- ባለፈው ዓመት ምንም ተማሪ ያላሳለፉ ትምህርት ቤቶች 1,232 ነበሩ ዘንድሮ ምንም ተማሪ ያላሳለፉ 565 ናቸው።
- ከዚህ ቀደም ምንም ተማሪ ካላሳለፉ ትምህርት ቤቶች ውስጥ በኮፒዩተር ፈተና ወደ 4,500 ተማሪዎች አልፈዋል።
ምንም ተማሪ ያላሳለፉ ትምህርት ቤቶች በክልል ምን ያህል ናቸው ?
• ኦሮሚያ 156
• አማራ 98
• ደቡብ ኢትዮጵያ 86
• ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ 69
• ትግራይ 48
• ቤኒሻንጉል ጉሙዝ 29
• ማዕከላዊ ኢትዮጵያ 22
• አፋር 21
• ሲዳማ 16
• ሶማሌ 9
• ድሬዳዋ 5
• ሀረሪ 3
• ጋምቤላ 2
• አዲስ አበባ 1
- ሁሉንም ያስፈተኑትን ተማሪዎች ያሳለፉ 100% ያሳለፉ ትምህርት ቤቶች ባለፈው አመት 62 ነበሩ ዘንድሮ 88 ሆነዋል።
በክልሎች ምንም ያህል ትምህርት ቤቶች 100% አሳለፉ ?
• ኦሮሚያ 37
• አዲስ አበባ 24
• አማራ 8
• ደቡብ ኢትዮጵያ 4
• ትግራይ 4
• ማዕከላዊ ኢትዮጵያ 3
• ሲዳማ 2
• አፋር 1
• ድሬዳዋ 1
• ሀረሪ 1
• ሶማሌ 1
• ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ 1
- በኮምፕዩተር እና በወረቀት በተፈተኑ ተማሪዎች መካከል ያለው የማለፍ ምጣኔ ትልቅ ልዩነት አለው። ኦንላይ የተፈተኑ 18.3% አልፈዋል። በወረቀት የወሰዱ 4.2% ናቸው ያለፉት። አንዱ ቶሎ በወረቀት ከመፈተን መውጥቶ ኦላይን ለመስጠት እቅድ አለው 60% ነው ዘንድሮ ቀጣይ አመት 100% ኦንላይን ሁሉንም።
- የዘንድሮው ከፍተኛ ውጤት ስንት ነው ?
• በተፈጥሮ ሳይንስ
ከወንድ 👉 591/600 ኦዳ ስፔሻል ቦርንዲግ ትምህርት ቤት አዳማ
ከሴት 👉 583/600 ከአገው ምድር ትምህርት ቤት እንጅባራ
• በማህበራዊ ሳይንስ
ከወንድ 👉 576/600 ዶዶላ ኢፋ ቦሩ ትምህርት ቤት
ከሴት 👉 569/600 አዲስ አበባ ቦሌ ሱፐር ሆሊሴቪየር ትምህርት ቤት
- ስልክ ይዘው የገቡ 265 ተማሪዎች ከፈተናው ተሰርዘዋል።
- ኮምፒዩተር ላይ ባለ " ኢሬጉላተሪ " ተብለው ጉዳያቸው እየተጣራ ያለ አለ።
- ከዚህ በፊት ከነበረው መሻሻል እየታየ ስለሆነ በጣም ደስተኞች ነን።
- ዘንድሮም ወደ ሬሜዲያል የሚገቡ ተማሪዎች ይኖራሉ።
- ሬሜዲያል ሁሌ የሚኖር አይደለም። በሚያልፈው ተማሪ ብዛት ነው የሚወሰነው። ዘንድሮ 70 ሺህ ተማሪ ስላለፈ ዘንድሮ ሬሜዲያል የሚገባው ይቀንሳል።
- ተማሪዎች ውጤታቸውን ከነገ ሰኞ ወይም ከነገ ወዲያ ማክሰኞ ጀምሮ ውጤታቸው ማየት ይችላሉ። ተማሪዎች ውጤት የሚመለከቱባቸውን አማራጮች ተከታትሎ ያቀርባል። | 137 |
| 19 | #Remedial
ለ2019 የትምህርት ዘመን የሪሚዲያል ተማሪዎች ቅበላ እንደሚኖር የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) አረጋግጠዋል።
ይሁን እንጂ በ2019 ዓ.ም ወደ ሪሚዲያል ፕሮግራም የሚገቡ ተማሪዎች እንደቀደሙት ዓመታት ብዙ እንደማይሆን ገልፀዋል።
"ዘንድሮ ካለፉት ዓመታት ውጤት ጋር ሲነጻጸር የተሻለ ተማሪ ቁጥር ወደ ዩኒቨርሲቲ ያለፈ በመሆኑ የምንቀበለው የሪሚዲያል ተማሪ ቁጥር ይቀንሳል" ሲሉ ለጋዜጠኞች ተናግረዋል።
ምን ያህል ተማሪ ወደ ፕሮግራሙ ይገባል የሚለው ግን አጠቃላይ የውጤቱ ሥራ ከተጠናቀቀ በኋላ የመቁረጫ ነጥቡ ወደፊት የሚገለፅ ይሆናል ብለዋል። | 136 |
| 20 | #Grade12
#EntranceExam
የ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ውጤት ሰኞ ወይም ማክሰኞ ለተማሪዎች ይላካል።
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ፣ እና የሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲዎች ምልመላ እና ቅበላ ካደረጉ በኋላ ሌሎቹም ዩኒቨርሲቲዎች ቶሎ ጥሪ እንዲያደርጉ እየሠራን ነው። መስከረም 05/2019 ዓ.ም ትምህርት ይጀመር የሚለውን ለመጠበቅ እንፈልጋለን። | 130 |
