cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

ቢቢሲ አማርኛ

@desalegntemesgen.com

Show more
Ethiopia6 193Amharic5 824The category is not specified
Advertising posts
786
Subscribers
No data24 hours
-37 days
-2430 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

የመንግሥት ሚስጥራዊ መረጃዎችን ለመጠበቅ የሚያስችል ረቂቅ ደንብ በሥራ ላይ እንዲውል ተወሰነ‼️ የመንግሥት ሚስጥራዊ መረጃዎች በሕገወጥ መንገድ ይፋ እንዳይሆኑ፣ እንዳይጠፉ፣ እንዳይለወጡ እና እንዳይተላለፉ ለመጠበቅ የሚያስችል ረቂቅ ደንብ በሥራ ላይ እንዲውል መወሰኑን የሚኒስትሮች ምክር ቤት አስታወቀ፡፡ የሚኒስትሮች ምክር ቤት በዛሬው ዕለት ባካሄደው 22ኛ መደበኛ ስብሰባ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳልፏል፡፡ የመንግሥት ሚስጥራዊ መረጃዎችን በማስተዳደር እና ጥቅም ላይ በማዋል ረገድ የተለያዩ የመንግሥት ተቋማት፣ የመንግሥት ኃላፊዎችና ሠራተኞች እንዲሁም በተለያየ መልኩ መረጃው ተደራሽ የሆነላቸው አካላት መብትና ግዴታዎች በግልፅ መደንገግ በማስፈለጉ፤ ሚስጥራዊ መረጃዎችን በኤሌክትሮኒክስ ዘዴዎች ለመለዋወጥ የተዘረጋ ስርዓት ባለመኖሩ በየደረጃ ያሉት የመንግሥት አመራሮች እና ሰራተኞች እራሳቸው በመረጡትና ደህንነታቸው ባልተረጋገጠ መረጃ መለዋወጫ ቴክኖሎጂዎች የሚጠቀሙ በመሆኑ የአገሪቱን ደህንነትና ሉዓላዊነት ለአደጋ የሚያጋልጥ እንዳይሆን መከላከል በማስፈለጉ፤ የመንግሥት ሚስጥራዊ መረጃዎችን ለመመደብ የሚያስችል ግልፅ እና ተጠያቂነት የሰፈነበት የአሠራር ስርዓት መዘርጋት እንዲሁም መረጃዎቹ በህገወጥ መንገድ ይፋ እንዳይሆኑ፣ እንዳይጠፉ፣ እንዳይለወጡ እና እንዳይተላለፉ ተገቢውን ጥበቃ ለማድረግ የሚያስችል ረቂቅ ደንብ ተዘጋጅቶ ለምክር ቤቱ ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም በረቂቅ ደንቡ ላይ በሰፊው ከተወያየ በኋላ ግብዓቶችን በማከል በነጋሪት ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በሥራ ላይ እንዲውል በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡ ---ፀደይ ኒውስ - Tsedey News--       "T.me/tsedeynews"
Show all...
ለልዩ ኃይል ፖሊስ አባላት የተላከን ዱቄት ሸጠው ለግላቸው ጥቅም ያዋሉ የጎንደር ከተማ የሥራ ሃላፊዎች በጽኑ እሰራት ተቀጡ ለአማራ ብሔራዊ ክልልላዊ መንግሥት ፖሊስ ኮሚሽን የልዩ ኃይል ፓሊስ አባላት የተላከን ዱቄት ሸጠው ለግላቸው ጥቅማቸው ያዋሉ የጎንደር ከተማ የሥራ ሃላፊዎች በጽኑ እሰራት መቀጣታቸው ተገለጸ፡፡ የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን የልዩ ሀይል ፓሊስ መምርያ የሚኒሊክ ክፍለጦር የሎጀስቲክ ኃላፊ የሆነው 1ኛ/ተከሳሽ ኮማንደር ኡስማን መሐመድ፤ ለልዩ ኃይል ፓሊስ አባላት አገልግሎት የሚውል 199 ኩንታል  “የፊኖ ዱቄት” ከፓሊስ ኮሚሽን ከልዩ ሀይል መምርያ ዘርፍ ይረከባል፡፡ ከዚህም ውስጥ 129 ኩንታል ዱቄት በሲኖትራክ የጭነት መኪና በመጫን፤ ጭልጋ ሰራባ ልዩ ኃይል ካንፕ ማድረስ ሲገባው፤ መስከረም 25/2015 ከረፋዱ 4:00 ሰዓት ላይ ከተጫነው ዱቄት ውስጥ 80 ኩንታል ለአንዱ ኩንታል 4 ሺሕ አምስት መቶ ብር በመተመን፤ 80 ኩንታሉን በጎንደር ከተማ ለሚገኘው ለሐሮን ዳቦ ቤት በ360 ሺሕ ብር መሸጡ ተገልጿል። ከኮማንደሩ በተጨማሪም፤ የጎንደር ከተማ አስተዳደር ፓሊስ መምርያ የ3ኛ ፓሊስ ጣቢያ ትራፊክ ፓሊስ ሆኖ የሚሰራ ዋና ሳጅን እንድሪስ ሐሰን ወንጀልን የመከላከል ኃላፊነት እያለበት ከሕዝብና ከመንግሥት የተሰጠውን ኃላፊነት ወደ ጎን በመተው የዳቦ ቤቱን ባለሀብት ሻጭ እና ገዥን በስልክ ያገናኘ እና ያስማማ በመሆኑ ወንጀለኛ ተደርጓል። በዚህም የመንግሥት ንብረት የሆነው የዳቦ ዱቄት እየተራግፉ ባሉበት በአካባቢው በነበሩ የጸጥታ ሃይሎች እጅ ከፈንጅ መያዛቸው የተገለጸ ሲሆን፤ የጎንደር ከተማ አስተዳደር ፓሊስ መምርያ የሙስና ነክ ወንጀሎች ምርመራ ዋና ክፍል እና የማዕከላዊ ጎንደር ዞን ፍትህ መምርያ የሙስና ወንጀል ጉዳዮች የሥራ ሒደት በጋራ በተቋቋመ የምርመራ ቡድን ምርመራው ተጣርቶ ለዞኑ ፍትህ መምርያ መላኩ ተገልጿል። የዞን ዐቃቤ ሕግ መዝገቡን መርምሮ በ10 የሰው እና የሰነድ ማስረጃ አስደግፎ የኢ.ፌ.ድ.ሪ የወንጀል ሕግ አንቀፅ 32/1/ለ/33 እና የሙስና ወንጀሎችን ለመደንገግ የወጣውን አዋጅ ቁጥር 881/2007 አንቀፅ 31/2/ስር የተመለከተውን የመሰረተ ሲሆን፤ ክሱንም ለማዓከላዊ ጎንደር ዞን ከፍተኛ ፍ/ቤት አቅርቧል። ጉዳዩ በክርክር ቆይቶ ሰኔ 15 /2015 በዋለው የወንጀል ችሎት ተከሳሾች ጥፋተኛ ሆነው በመገኘታቸው፤ አንደኛ ተከሳሽ ኮማንደር ኡስማን መሐመድ በአምስት ዓመት ጽኑ እሰራትና በ3 ሺሕ ብር፤ ዋና ሳጅን እንድሪስ ሐሰን በሦስት ዓመት ከሦስት ወር ጽኑ እስራትና በኹለት ሺሕ ብር እንዲቀጡ መወሰኑን ገልጿል። t.me/TsedeyNews t.me/TsedeyNews
Show all...
👍 1
ሰላም የፀደይ ኒውስ ቤተሰቦች✋ ፀደይ ኒውስ የተለያዩ ወቅታዊ መረጃዎችን ከተለያዩ ምንጮች በማጠናቀር ወደ እናንተ ወድ ቤተሰቦቹ የሚያቀርብ ምርጥ እና አማራጭ የዜና ቻናል ነው። በቻናላችን:- 1. የሀገር ውስጥ ዜናዎች 2. የውጪ ዜናዎች 3. ትምህርት ነክ መረጃዎች 4. የጤና መረጃዎች 5. የስራ ማስታዎቂያዎች 6. አስተማሪ፣ አዝናኝ እና ቁምነገር ያላቸው ዝግጅቶችን የምናቀርብ ይሆናል። እናንተም ውድ የቻናላችን ቤተሰቦች፣ በተለያዩ መድረኮች በመሳተፍ፣ ኮሜንት ላይ ሀሳብ አስተያየት በመስጠት፣ ዜናዎቻችንን ሼር በማድረግ እና ሌሎችን በመጋበዝ በንቁ እንድትሳተፉ እንጠይቃለን። ---ፀደይ ኒውስ - Tsedey News--- "ተመራጭና ተአማኒ የመረጃ ምንጭ"       "T.me/tsedeynews"
Show all...
በሰሜን ምዕራብ ናይጄሪያ፣ “ነብዩ መሐመድን ተሳድቧል” የተባለ ግለሰብ፣ በድንጋይ ተወግሮ እንደተገደለ፣ ባለሥልጣናት እና የመብት ተሟጋች ቡድኖች አስታወቁ። ድርጊቱ፥ በአካባቢው የሃይማኖት ነፃነትን አደጋ ላይ የሚጥል ነው፤ ያሉት የመብት ተሟጋቾቹ፣ ጉዳዩ አሳሳቢ እንደሆነ ገልጸዋል። ኡስማን ቡዳ የተባለው ሟቹ ሉካንዳ ነጋዴ፣ ከትላንት በስቲያ እሑድ፣ በሶኮቶ ግዛት ጉዋንዱ ወረዳ የተገደለው፣ በገበያ ሥፍራ ከሌላ ነጋዴ ጋራ ሲከራከሩ፣ “ነብዩ መሐመድን ተሳድቧል፤” በሚል እንደሆነ፣ የፖሊስ ቃል አቀባይ አሕመድ ሩፋ፣ በአወጡት መግለጫ አስታውቀዋል። ከግድያው ስፍራ የተወሰዱና ነዋሪዎች ያጋሯቸው የቪዲዮ ምስሎች፣ ሕፃናትን ጨምሮ በርካታ ሰዎች ተሰብስበው፣ መሬት ላይ የወደቀውን ኡስማን ቡዳን ሲራገሙ እና ድንጋይ ሲወረውሩበት ያሳያሉ። የፖሊስ ቃል አቀባዩ ስለጉዳዩ ሲያብራሩ፣ በሥፍራው የፖሊስ ኃይል ሲደርስ፣ “ሕዝቡ ተበትኖ፣ ጉዳት የደረሰበት ግለሰብ ራሱን ስቶ” እንዳገኘው ገልጸው፣ ወደ ሆስፒታል ከተወሰደ በኋላ ሕይወቱ እንዳለፈ አብራርተዋል። በአብዛኛው የእስልምና ሃይማኖት ተከታዮች በሚበዙበት ሰሜናዊ ናይጄሪያ የተፈጸመው ይኸው የደቦ ግድያ፣ የእምነት ነፃነትን አደጋ ላይ ይጥላል፤ በማለት፣ የመብት ተሟጋቾች ድምፃቸው እያሰሙ ነው። ናይጄሪያ የሚገኘው አምነስቲ ኢንተርናሽናል፣ “መንግሥት ለጉዳዩ በቂ ትኩረት አልሰጠም፤” ብሎ በመክሠሥ ባወጣው መግለጫ፣ እንደዚኽ ዐይነት ግድያዎች፣ ፍትሕ ሳያገኙ ከቀሩ፣ ሕግ ፊት ሳይቀርቡ በመንጋ የሚፈጸሙ ግድያዎችን ያበረታታል፤ ብሏል።
Show all...
  • File unavailable
  • File unavailable
  • File unavailable
  • File unavailable
  • File unavailable
ሰመመን - ክፍል 1 ❤️‍🔥❤️‍🔥❤️‍🔥 ━━━━━━━━ ከ ጸጋዬ አብራር ━━━━━━━━ ⇲⇲⇲⇲ ሼር ያድርጉ!! ⇲⇲⇲⇲ አዘጋጅ፦⇨ @Ethio_Tereka@Ethio_Tereka ━━━━✦✗✦━━━━
Show all...
ከ1000 በላይ ሰዎችን አሳፍራ በሁለተኛው የዓለም ጦርነት የሰመጠች አንዲት የጃፓን መርከብ በፊሊፒንስ የባህር ዳርቻ ተገኘች። ፍለጋውን ያካሄዱ የጥልቅ ባህር ተመራማሪዎች እንደገለፁት የመርከቧ ፍርስራሽን ከ4000 ሜትር ጥልቀት በኋላ በደቡብ ቻይና ባህር ውስጥ ለማየት ችለዋል። ፍለጋው በዘመናዊ ቴክኖሎጂ ታግዞ ከተጀመረ 12 ቀናት በኋላ መርከቢቱ መገኘቷን በተልዕኮው የተሳተፈ «ሳይለንት ወርልድ ፋውንዴሽን» የተባለ የአውስትራሊያ ድርጅት ዛሬ አስታውቋል። «ሞንቴቪዲዮ ማሩ» የሚል መጠሪያ የነበራት መርከብ እጎአ ሀምሌ 1 ቀን 1942 ዓ.ም የሰመጠችው በዩናይትድ ስቴትስ ሰርጓጅ መርከብ ጥቃት ከደረሰባት በኋላ ነው። 1060 ገደማ ሰዎችን አሳፍራ እንደነበር የሚነገረው ይህቺው መርከብ ከዚያን ጊዜ በኋላ የደረሰችበት አይታወቅም ነበር። አብዛኛዎቹ ሰዎች በጃፓን ቁጥጥር ስር የዋሉ የአውስትራሊያ የጦር እስረኞች የነበሩ ሲሆን በጠቅላላው የ 14 ሀገራት ዜጎች በመርከቧ ላይ ይገኙ እንደነበር እና እድሜያቸውም ከ 15 እስከ 60 እንደሚደርስ ተዘግቧል። ለሟች ቤተሰቦች ክብር በሚል መርከቢቱ ሰምጣ ከተገኘችበት ቦታ በስተቀር ከሰው ቅሪት ምንም የተወሰደም ይሁን በቪዲዮ የተቀረፀ ነገር እንደሌለ የጀርመን ዜና አገልግሎት አክሎ ዘግቧል።
Show all...
የዎላይታ ሕዝቦች ነፃነት ንቅናቄ በአጭሩ (ዎሕነን) የተሰኘ አዲስ የፖለቲካ ፓርቲ ዛሬ ወላይታ ሶዶ ውስጥ ተመሠረተ። ንቅናቄው በፓርቲ ደረጃ እንዲመሰረት ከኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ ባገኘው ጊዜያዊ የምስረታ ፍቃድ መሠረት ላለፉት ሶስት ወራት ሲሰራ እንደነበር ዛሬ በምስረታ ጉባኤው ላይ ተገልጿል። ከንቅናቄው ስራ አስፈፃሚዎች አንዱ የሆኑት አቶ አማኑኤል በላቸው ለዶይቸ ቬለ እንደተናገሩት የንቅናቄው ዋንኛ አጀንዳ የወላይታን ሕዝብ መብት እና እኩልነት በኢትዮጵያ ማስከበር ነው። የዎላይታ ሕዝብ የራስ በራስ አስተዳደር ለመመሥረት ያነሳው ጥያቄ ምላሽ እስኪያገኝ ፓርቲው በሰላማዊ መንገድ እንደሚታገል አክለው የገለፁት አቶ አማኑኤል የፖርቲው ስያሜ ብሔር ተኮር መሆኑ እና በሀገራዊ ፓርቲነት መሰየሙ «ምንም ግጭት አይፈጥርም» ሲሉ ለሐዋሳው የዶይቸ ቬለ ወኪል ሸዋንግዛው ወጋየሁ ገልፀዋል።
Show all...
ጃፓን ወታደሮቿ የሰሜን ኮሪያን የባልስቲክ ሚሳይልን መትተው ለመጣል ዝግጁ እንዲሆኑ አዘዘች። ጃፓን ይህን ያዘዘችው ሰሜን ኮሪያ ወታደራዊ የስለላ ሳተላይት ለማምጠቅ ዝግጁ መሆኗን ከገለጸች በኋላ ነው ተብሏል። የጃፓን የመከላከያ ሚኒስትር ዛሬ ባስተላለፉት ትዕዛዝ የሰሜን ኮሪያ የባልስቲክ ሚሳኤል አደጋን ለመቀነስና ለማክሸፍ አስፈላጊውን እርምጃ ለመውሰድ ወታደሮቻቸው እንዲዘጋጁ አስጠንቅቀዋል ሲል አዣንስ ፍራንስ ፕረስ ዘግቧል። ባለፈው ሳምንት ሰሜን ኮርያ የመጀመሪያዋን አህጉር አቋራጭ የባሊስቲክ ሚሳኤል ሙከራ አከናውናለች። በዚህ ሳምንት መጀመሪያ ላይ ደግሞ የሰሜን ኮሪያው መሪ ኪም ጆንግ ኡን ቀኑን ሳይጠቅሱ የመጀመሪያው ወታደራዊ ሰላይ ሳተላይት በታቀደበት ጊዜ ወደ ህዋ እንደሚልኩ ተናግረዋል። እያደገ የመጣውን የሰሜን ኮሪያ የሚሳይል ስጋት በተሻለ ብቃት ለመከላከል በሚል ዩናይትድ ስቴትስ፣ ጃፓንና ደቡብ ኮሪያ የሚሳይል ጥቃት የመከላከል ልምምድ እንዲሁ በሳምንቱ መጀመሪያ ላይ ማካሄዳቸው ይታወሳል። የሦስቱ ሃገራት ወታደራዊ ትብብር የሚቀጥለው ሳምንትም መቀጠሉን ተንተርሶ ሰሜን ኮርያ በበኩሏ ቀጣይ ሙከራዎችን እንደምታካሄድ ይጠበቃል።
Show all...
በሱዳን ተፋላሚ ኃይሎች መካከል የ 72 ሰዓታት የተኩስ አቁም ዓርብ ዕለት ቢታወጅም በሱዳን ጦር ኃይሎች እና በፈጥኖ ደራሽ ኃይሎች መካከል የሚካሄደው ውጊያ ቀጥሏል። እንደ የዓይን እማኞች ገለጻ ጦርነቱ ለተወሰነ ጊዜ በዒድ አልፈጥር ምክንያት ጋብ ካለ በኋላ ዛሬ ጧት እንደገና ቀጥሏል። በዋና ከተማዋ ካርቱም በርካታ አካባቢዎች ከባድ የተኩስ ድምጽ፣ከፍተኛ ፍንዳታ እና ተዋጊ ጄቶች ይሰሙ እንደነበር እማኞች ገልጸዋል። የዓለም ጤና ድርጅትን ጠቅሶ የጀርመን የዜና አገልግሎት እንደዘገበው ጦርነቱ ከጀመረ ካለፈው ቅዳሜ አንስቶ ቢያንስ 413 ሰዎች ሲገደሉ ከ3,500 በላይ ቆስለዋል። ቀደም ሲል የታወጁ ሁለት የተኩስ አቁም ስምምነቶችም በተፋላሚ ወገኖች ችላ ተብለዋል። በሌላ ዜና ብርቱ ጦርነት ውስጥ ከምትገኘው ሱዳን የውጭ ሀገር ባለስልጣናትን እና ዜጎችን ማስወጣት ተጀመረ። የሱዳን ጦር ቃል አቀባይ ዛሬ እንደገለፀው የጦሩ አዛዥ ጄኔራል አብደል ፋታህ አል-ቡርሃን ከተለያዩ ሀገራት መሪዎች ጋር ተወያይተው ዜጎቻቸው ደህንነታቸው ተጠብቆ ከሱዳን የሚወጡበትን መንገድ ለመተባበር ተስማምተዋል። በዚህም መሠረት የዩናይትድ ስቴትስ፤ ብሪታንያ፣ ፈረንሳይ እና ቻይና ዜጎች በወታደራዊ የጭነት አይሮፕላኞች ከመዲናይቱ ካርቱም እንደሚወጡ የሱዳን ጦር ገልጿል። የቡርሀን ተቀናቃኝ እና የፈጥኖ ደራሽ ኃይሎች አዛዥ ጄነራል ሃምዳን ዳጋሎ በበኩላቸው የውጭ ዜጎችን ለማስወጣት እንዲቻል ሁሉንም የአይሮፕላን ማረፊያዎች በከፊል ክፍት ለማድረግ ተስማምተዋል። ይሁንና በመዲናዋ ካርቱም የሚገኘው አለም አቀፍ አይሮፕላን ማረፊያ በተደጋጋሚ የጦር ፍልሚያ እንደተካሄደበት መሆኑን የጀርመን ዜና አገልግሎት ዘግቧል። እንደ ሱዳን ጦር ገለፃ ከሳውዲ አረቢያ ኤምባሲ ዜጎችን የማስወጣት ርምጃው ተጠናቋል። በቅርቡ ደግሞ የዮርዳኖስ ኤምባሲ ይከተላል ብሏል። ቆየት ብሎ የሳዑዲ አረቢያ ቴሌቪዥን ሱዳንን ለቀው የወጡ የሳዑዲ እና የሌላ ሀገራት ዜጎች በጀልባ ጅዳ መድረሳቸውን ዘግቧል። የጀርመን ፌደራል መንግስት በርካታ አማራጮችን እያዘጋጀ እንደሆነ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አናሌና ቤርቦክ ትናንት አስታውቀዋል።
Show all...