en
Feedback
ዜና ማኅበረ ካህናት ዘሰሜን አሜሪካ

ዜና ማኅበረ ካህናት ዘሰሜን አሜሪካ

Open in Telegram

Under EOTC USA clergy association. Mahibere Kahinat zeSemen America

Show more
958
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
😢 አንተ ካህኑ ለእግዚአብሔር!
+2
😢 አንተ ካህኑ ለእግዚአብሔር!

#ሰበር_ዜና ብፁዕ አቡነ አረጋዊ (ዶ/ር) አረፉ። ሐምሌ 9 ቀን 2009 ዓ.ም በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃ
#ሰበር_ዜና  ብፁዕ አቡነ አረጋዊ (ዶ/ር) አረፉ። ሐምሌ 9 ቀን 2009 ዓ.ም በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት አንብሮተ ዕድ ከተሾሙት 14 ኤጲስ ቆጶሳት መካከል አንዱ የሆኑት በቀድሞ ስማቸው አባ ኃይለማርያም መለሰ (ዶ/ር) በጵጵስና ስማቸው ብፁዕ አቡነ አረጋዊ (ዶ/ር) የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ጽ/ቤት እና የውጪ ግንኙነት መምሪያ የበላይ ኃላፊ የድሬዳዋና የጅቡቲ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ከዚህ ዓለም ድካም አርፈዋል። ብፁዕነታቸው ለረጅም ጊዜ ከሀገር ውጪ እና በሀገር ውስጥ በህክምና ሲረዱ ቆይተው ሊሻላቸው ሳይችል ቀርቶ ከዚህ ዓለም በሞተ ሥጋ  ተለይተዋል። በረከታቸው ይደርብን!!

የታላቁ አባት ዬኔታ ሐረገ ወይን የሕይወት ታሪክ። ++++++++++++++++++++++++++ የታላቁ አባት ዬኔታ ሐረገ ወይን ምህረቱ በወሎ ክፍለ ሐገር ሰገራት (ኩታበር ወደ ግሸን መሔጃ) ከወላጅ አባታቸው ከአለቃ ምህረቱ ካሣ ከእናታቸወ ወይዘሮ አበቡ ወልደ ጻድቅ በየካቲት 16 ቀን 1921 ዓ.ም ተወለዱ። ከፊደል እስከ ንባብ ትምህርት የጀመሩት በእናታቸው ሀገር በቦሩ ሥላሴ ነው። ግብረ ዲቁና በ1935 ዓ.ም ከግብጻዊው አቡነ ቄርሎስ በአዲስ አበባ ቅድስት ማርያም ተቀበሉ። ጸዋትወ ዜማ ዳውንት ምዕራፍ ጾመ ድጓ የኔታ ሐረገወይን ቦሩ በድጋሚ ተመልሰው ተማሩ እርሳቸው እንደተናገሩት "ቦሩ እያለን አንድ ጓደኛችን ቅኔ ተቃኝቶ መጣ እኛም በቅንዓት ወደ ቅኔ ገባን:: ቅኔ ቤት ወቄጣ ማርያም ሸደሆ ገረገራ አጠገብ ከአባ ገብረ ሕይወት ዘንድ አባ ነብሮ (በልጅኘታቸው ተማሪ እያሉ ውሻ ቢመጣባቸው ዘለው ጣሪያ ላይ ስለ ወጡ አባ ነብሮ ቅጽል ስም ነው ያላቸው) አንድ ጊዜ ተቀኘሁ።" ሲሉ ተናግረዋል። መምህራቸው ወደ ግሸን ሲሄዱ ተነስተው ደላንታ ጉርባ ጊዮርጊስ የኔታ ብሩ ድጋሚ ሙሉ ቅኔ ከነአገባቡ ተምረዋል። አቋቋም ቤት አንሳሳ ጊዮርጊስ ጋይንት የኔታ የማነ ብርሃን ክብረ በዓል እስከ አስተርእዮ ተማሩ። መምህሩ ወደ አማራ ሳይንት ሲሄዱ እርሳቸው በዚያው ቀሩ። የኔታ ቆይታቸውን "አለቃ ታደሰ የሚባሉ መምህር መጡልን ሙሉ ክብረ በዓል አዘለቁን" ሲሉ ገልጸዋል። ጋይንት ልዳ ጊዮርጊስ የኔታ ዓለሙ መዝሙሩን ዝማሜና ማንሻውን በጌ ምድር መድኃኔዓለም የኔታ አለልኝ መዝሙር የመንና መረግዱን ጽፋቱን ተምረዋል። የኔታ ስለ አብነት ትምሕርታቸው ሲተርኩ "ወገራ ቅ/ሚካኤል ሄድን ረሀብ ነበረ ተማሪ ተበትኖ አገኘነው ወደ በለሳ ላኩን:: በለሳ መድኃኔዓለም የኔታ አፈወርቅ የጎንደሮች ማርያም አለቃ ናቸው ከእኚህ ሊቅ መዝሙርና ክብረ በዓል ከለስን ዞዝ አምባ ቅ/ጊዮርጊስ ከየኔታ ዕፁብ (ዐይነ ሥውር ናቸው) (የነየኔታ ቤተ ማርያም ጓደኛ ናቸው) ክብረ በዓል ወርሃ በዓል መዝሙር ከነ ዓመሉ የወሰንነው እዛው ነው። (አንድ ደቀ መዝሙር ወደ ምስክር ከመሔዱ በፊት የወሰነ ከሆነ "አድራሽ" ይባላል:: አድራሽ የሆንነው እዛው ነው)" በማለት ይናገሩ ነበር። የኔታ ትምሕርታቸውን ቀጥለው ድምጫ ላይቤት ታች ቤት ሳንኳ ፊት ሚካኤል/አደባባይ ኢየሱስ /በዓታ/ ቂርቆስ እስከ ሦስት ዓመት አጠናክረዋል። ስለ መምህርነት ህይወታቸው ሲናገሩ "የኔታ ዕፁብ መረቁን አስተምር ብለው ፈቀዱልኝ 1ኛ የማስተማር ጊዜ በጎንደር ክፍለ ሀገር በበለሳ በታች አባሽካ ጊዮርጊስ ከ1940 ማስተማር ጀመርኩ። ሰባት ዓመት አስተማርኩ 2ኛ የማስተማር ጊዜ የጣራሽ ማርያም ስምንት ዓመት አስተምሬ ቤተሰብ ለመጠየቅ ወደ አዲስ አበባ መጣሁ። "እዚሁ ተቀመጥ" አሉኝ አክስቴ:: 'ባይሆን ተማሪዎቼን አሰናብቼ እኔም ተሰናብቼ ልምጣ' ብዬ ተመልሰው ሂጀ ተማሪዎቼን ሸኝቼ ተመለስኩ" በማለት ወደ አዲስ አበባ የመጡበትን አጋጣሚ ይተርካሉ። ሲቀጥሉም "እንደ መጣሁ ዮሐንስ ወልደ ነጎድጓድ በአሥር ብር ተቀጠርኩ የዛን ጊዜ ኮተረና ሱሪ ይገዛል ሰበካ ጉባኤ የለም በኋላ ነው አቡነ ቴዎፍሎስ ያቋቋሙት; ከዛ ወደ ኮልፌ ትምህርት ቤት ገባሁ ሰባት ዓመት ሐዲስ ኪዳን ተማርን ዘመናዊ እስከ ዘጠነኛ ክፍል ተማርኩ እነ አቡነ ገብርኤል ወደ ቅድስት ሥላሴ ገቡ እኔ ወላጆቼ ስለነበሩ 'እረዳለሁ' ብዬ ወደ ቅድሥት ሥላሴ አልገባሁም:: አቡነ ቄርሎስ የትግሬው ደብረ ሲና አሥመራ ነው የመነኮሱት እዛው ነው የተቀበሩት ትልቅ አባት ናቸው:: እኔም በውስጤ ወድያው የመጣልኝ 'የትልቅነት መለኪያው ምንድነው?' የሚል ነው:: የኔታ ቀጠሉና አስታራቂ የተጣላን የሚያስታርቁ ባለ ብዙ ጸጋ አባት ናቸው። ቀደም ያሉ ናቸው:: እኚህ አባት ወደ ኤልባቡር ወሰዱኝ" በማለት በኤሊባቡር (በኢሉአባቦራ) የነበራቸውን የአገልግሎት ሕይወት ይተርካሉ። ታላቁ አባት ዬኔታ ሐረገ ወይን ምህረቱ በኤሊባቡር የሀገረ ስብከቱ ስብከተ ወንጌል ሓላፊ; አቡነ ቀሲስ (የሊቀ ጳጳሱ እንደራሴ) ሆነው ለሁለት ዓመት አገልግሎት ተሰጥተዋል። ቤተ ክህነቱ ጋሞ ጎፋ ጅንካ መድቧቸው ወደ ጋሞ ጎፋ በመሄድ አቡነ ሰላማ ዘንድ የሀገረ ስብከቱ ትምህርት ክፍል ሰባኬ ወንጌል ሆነው 10 ዓመት አገልግለዋል። "አርባ ምንጭ እያለሁ አቡነ ሰላማ ወደ ደብረ ሊባኖስ ልከዋቸው በደብረ ሊባኖስ ገዳም መንኩሰዋል። የታላቁ አባት የኔታ ሐረገ ወይን ምህረቱ በአዲስ አበባ የጠቅላይ ቤተ ክህነት የመጋቤ ካህናት ለቄ ብርሃኑ ጸሐፊ ሆነው አንድ ዓመት ሠርተዋል። የመንበረ ፓትርያርክ የጊቢ ሓላፊ በመሆን በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ተክለሃይማኖት ጊዜ አራት ዓመት አገልግሎት ተሰጥተዋል። ወደ ኬንያ ናይሮቢ በማቅናት በመድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን የስብከተ ወንጌል ኃላፊ ሆነው ከብፁዕ አቡነ ኤልያስ ጋር ሠርተዋል። ብፁዕ አቡነ ኤልያስ ወደ ጅቡቲ ሲሄዱ የቤተ ክርስቲያኑ አስተዳዳሪ ሆነው አንድ ዓመት አገልግለዋል። ከዚያም ወደ አዲስ አበባ መጡ ወደ ዝዋይ ያቀኑበትን አጋጣሚ ሲገልጹ "አቡነ ጎርጎርዮስ አገኙኝ ሹመት ይፈልጋሉ ወይ? አሉኝ አረ እኔ አልፈልግም መምህራችን ሹመት የሚባል ነገር እንዳትፈልጉ ብለውኛል አልኳቸው:: ማስተማር የሚፈልጉ ከሆነ ዝዋይ እንሂድ አሉኝ:: እሺ ብዬ ወረድኩ ሲያመጡኝ በ1980 ዓ/ም ነበር። አዲስ አበባ 200 ብር ይከፈለኝ ነበረ:: 100 ብር እከፍለዎታለሁ አሉኝ። ከዛ ወረድኩኝ የምን ደሞዝ ነው ልጆችን ከዛም ከዚህም ሰብስበው እያሳደጉ ይቅርብኝ ብዬ ማስተማር ጀመርኩ ወደ 26 ዓመት አሰተማርኩ" ሲሉ ይገልጻሉ። የኔታ ወደ ዝዋይ ገዳም ከመጡ ጀምሮ ወዴትም አልሔዱም:: የገዳሙ በረከት ናቸው። በዝዋይ ገዳም ብቻ በዓት አጽንተው 35 ዓመት አስተምረዋል። ታላቁ አባት ዬኔታ ሐረገ ወይን ምህረቱ በእርግና መጋቢት 1 ቀን 2015 ዓ.ም ከዚህ ዓለም ድካም አርፈዋል። በረከታቸው ይደርብን። የሕይወት ታሪካቸውን የከተቡት (አባ አትናቴዎስ ወልደ ጎርጎርዮስ) ናቸው።

"የብፁዕ አቡነ ባስልዮስ ሣልሳይ ሥርዓተ ቀብር በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ይፈጸማል! ቅዱስ ሲኖዶስ ጽ/ቤት ብፁዕ አቡነ ባስልዮስ ሣልሳይ መጋቢት ፩/፳፻፲፭ ዓ/ም በኢትዮጵያ ሰዓት አቆ
+1
"የብፁዕ አቡነ ባስልዮስ ሣልሳይ ሥርዓተ ቀብር በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ይፈጸማል! ቅዱስ ሲኖዶስ ጽ/ቤት ብፁዕ አቡነ ባስልዮስ ሣልሳይ መጋቢት ፩/፳፻፲፭ ዓ/ም በኢትዮጵያ ሰዓት አቆጣጠር ምሽት ከዚህ ዓለም ድካም ማረፋቸውን የቅድስ ሲኖዶስ ጽ/ቤት በላከው መረጃ ገልጿል። ብፁዕ አቡነ ባስልዮስ ሣልሳይ ከ፲፯ ዓመታት በፊት በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ ፓትርያርክ ርእረ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ አንብሮተ ዕድ የተሾሙ ናቸው። ብፁዕነታቸው አስኬማ መላእክት ከሚለበስበት የኤጲስ ቆጶስነት በፊት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በተለያዩ አካባቢዎች ሲያገለግሉ እንደነበር ታሪካቸው ያስረዳል። በተለይ አገልግሎታቸውን ከጀመሩበት ከአገው ምድር አዊ ጀምሮ በባሕርዳር ፈለገ ገነት ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን በተለያዩ የአገልግሎት ዘርፎች አገልግለዋል። ከዚህ በተጨማሪ ብፁዕነታቸው በድሬዳዋ ብሎም በቤተ ክርስቲያናችን ፈቃድ ጀርመን ሀገር ተልከው የሚገባውን ትምህርት የተከታተሉ ሲሆን ከዚያም በሰሜን አሜሪካ በኒውዮርክ ሀገረ ስብከት በሚገኘው በመንበረ ጵጵስና ቅድስት ሥላሴ ቤተክርስቲያን ከአገልጋይነት እስከ የበላይ ጠባቂነት በአባትነት አገልግለዋል። ብፁዕ አቡነ ባስልዮስ ሣልሳይ የኒውዮርክ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እንደነበሩ የአገልግሎት ፍሬ ታሪካቸው ያስረዳል። የብፁዕ አቡነ ባስልዮስ ሣልሳይ ዕረፍትን ተከትሎ የቅዱስ ሲኖዶስ ጽ/ቤት ያደረሰን መረጃ እንደሚያመለክተው ክቡር አስከሬናቸው በሚቀጥለው ሳምንት ቅዳሜ መጋቢት ፱/፳፻፲፭ ዓ/ም ወደ አዲስ አበባ እንደሚመጣ የገለጸ ሲሆን የቀብር ሥነ ሥርዓቱም በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል እንደሚፈጸም አስታውቋል።

ሰበር ዜና ዕረፍት ወላዴ አእላፍ መምህር የኔታ ሐረገ ወይን በተወለዱ በ፺፱ ዓመታቸው ከዚህ ዓለም ድካም አረፉ። የታላቁ የዝዋይ ሐመረ ብርሃን ቅዱስ ገብርኤል ገዳም አበ ምኔት የኔታ መምህር ሐረገ ወ
+2
ሰበር ዜና ዕረፍት ወላዴ አእላፍ መምህር የኔታ ሐረገ ወይን በተወለዱ በ፺፱ ዓመታቸው ከዚህ ዓለም ድካም አረፉ። የታላቁ የዝዋይ ሐመረ ብርሃን ቅዱስ ገብርኤል ገዳም አበ ምኔት የኔታ መምህር ሐረገ ወይን ከ40 ዓመት በላይ ወንበር ዘርግተው በማስተማር በርካታ ሊቃነ ጳጳሳትንና ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያንን አፍርተዋል። የኔታ ሐረገ ወይን ከብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ተክለሃይማኖት ጊዜ ጀምሮ ከአንዴም ሁለቴ ጳጳስ እንዲሆኑ ቢጠየቁም "ምንኩስና ይበቃኛል" ብለው በዓታቸውን ያፀኑ አባት ናቸው። ከሀገር ውስጥ እስከ ሀገር ውጭ፡ ከጋሞ ጎፋ አርባምንጭ - ኬንያ፡ከመንበረ ፓትርያርክ የግቢ ኃላፊነት እስከ ዝዋይ ሐመረ ብርሃን ቅዱስ ገብርኤል ገዳም አበምኔትነት ቤተክርስቲያን ባሠማራቻቸው ቦታ ሁሉ በቅንነትና በጽናት ያገለገሉ ብዙዎችን በጸሎት የጠበቁ የብዙኃን ጥላና ዋርካ ነበሩ፡፡ የዓለም ነገር የማያጓጓቸው፡ ለቤተክርስቲያን ራሳቸውን ሰጥተው በትኅትና ያገለገሉ ፡ በርካታ የከተማው አቅም የሌላቸው ሕጻናትን ደብተር፡ ልብስ፡ እስክርቢቶ እየገዙ ለትልቅ ቁም ነገር ያበቁ የገዳሙ ምልክትና ሕያው ባለታሪክ ነበሩ፡፡ ዓርብ መጋቢት ፩ ቀን ፳፻፲፭ ዓ.ም ከሌሊቱ 5:00 ሰዓት ላይ በተወለዱ በዘጠና ዘጠኝ ዓመታቸው ከዚህ ዓለም ድካም ዐርፈዋል። ሥርዓተ ቀብራቸውም መጋቢት ፫ ቀን ፳፻፲፭ ዓ.ም ከቅዳሴ በኋላ በዝዋይ ገዳም እንደሆነ ታውቋል። ለመላው የእምነቱ ተከታይ እና ለመንፈስ ቅዱስ ልጆቻቸው እግዚአብሔር መጽናናትን ያድልልንን። በረከታቸው ይደርብን!!

ኦ እግዚአብሔር አዕርፍ ነፍሰ ብጹዕ አቡነ አባ ባስልዮስ!!! የጸሎት፣ የበረከት አባት፣ ምክራቸው አጥንትን ዘልቆ የሚገባ፣ ሁሉን በእኩል የሚያዩበት አባታዊ ፍቅራቸውና ትህትናቸው አቻ የማይገኝለት፣
ኦ እግዚአብሔር አዕርፍ ነፍሰ ብጹዕ አቡነ አባ ባስልዮስ!!! የጸሎት፣ የበረከት አባት፣ ምክራቸው አጥንትን ዘልቆ የሚገባ፣ ሁሉን በእኩል የሚያዩበት አባታዊ ፍቅራቸውና ትህትናቸው አቻ የማይገኝለት፣ በዕርግና ዘመናቸው ማኅሌት ሲቆሙና ሲቀድሱ ከሰማያዊ ዓለም ጋር የሚያገናኙ ፍጹም መንፈሳዊ አባታችን ብጹዕ አቡነ ባስልዮስ ከዚህ ዓለም ድካም አርፈዋል። መላ ዘምንዎትን ያገለገሉት አምላክ በክብር ይቀበልዎ፣ ለእኛም ቅድስት በረከትዎ ትደርብን!

በምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት በጊንብቹ ወረዳ መጋቢት 1ቀን 2011 ዓ.ም የቦይንግ 737 አውሮፕላን አደጋ በደረሰበት ቦታ ላይ ቤተክርስቲያን ለመሥራት በብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ መልካም ፈቃድ የመሠረት ድንጋይ ተቀመጠ ፡፡ ++++++++++++++++++++++++++ የዛሬ አራት ዓመት መጋቢት 1ቀን 2011 ዓ.ም የኢትዮጵያ አየር መንገድ ንብረት የሆነው ቦይንግ 737 አውሮፕላን ከአዲስ አበባ ወደ ኬንያ ጉዞ እንደ ጀመረ በምሥራቅ ሸዋ ጊንብቹ ወረዳ ልዩ ስማ ሐማ ቁንጡሽሌ በተባለ ቦታ ላይ በደረሰበት አደጋ የአውሮፕላኑ ሠራተኞች ጨምሮ 157 የተለያዩ ሀገራት ዜጎች ሕይወታቸው ማለፉ ይታወሳል። በዚሁ ዕለት ሕይወታቸውን ያጡት 17 ኢትዮጵያውያን ሲሆኑ የእነዚሁ ኢትዮጵያውያን ቤተሰቦች በየዓመቱ አደጋው በተፈፀመበትና አስከሬናቸው ባረፈበት ቦታ መታሰቢያ እያደረጉ ቆይተዋል፡፡ እነዚሁ የአደጋው ሰለባ የሆኑ ቤተሰቦች በቦታው ላይ ለመታሰቢያ የሚሆን ቤተ ክርስቲያን ለመሥራት ከ7000 ካሬ ሜትር በላይ ቦታ ገዝተው ባቀረቡት ጥያቄ የምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ መልካም ፈቃድ ዛሬ የ4ኛ ዓመት መታሰቢያ በሚከበርበት ቀን መጋቤ ጥበብ ቀሲስ ጌቱ ሞቲ የሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ልዩ ፀሐፊ ፣ መ/ሐ/ቆሞስ አባ ገ/ፃድቅ መኮንን የሀገረ ስብከቱ ስብከተ ወንጌል ክፍል ኃላፊ፣ ሊቀ ትጉኃን መንክር አቤ፣ መ/ኃ/ቀሲስ ኃ/መስቀል የጊንቢቹ ወረዳ ቤተ ክህነት ሥራ አስኪያጅ እንዲሁም ከአዲስ አበባ መ/ር ዘላለም ወንድሙ ና ዘማሪያን እንዲሁም ሕይወታቸውን ያጡ ቤተሰቦች በተገኙበት የመሠረት ድንጋይ ተቀምጧል። በመርሐ ግብሩ ላይ በዘማሪ ፈቃዱ አማረና በዘማሪ ይትባረክ ተገኘ የማጽናኛ ዝማሬ የቀረበ ሲሆን በመምህር ዘለዓለም ወንድሙ የሚያጽናና ትምህርተ ወንጌል ተሰጥቷል፡፡ በመቀጠልም መጋቤ ጥበብ ቀሲስ ጌቱ ሞቲ ይህን ቅዱስ ዓላማ ወገኖቻቸውን ለማሰብ ቤተክርስቲያንን ለማነጽ መነሳሳታቸው እጅግ የሚበረታታ መሆኑና ዘመን የማይሽረው ታሪክን በወገኖቻቸው ስም እያስቀመጡ መሆኑን ገልጸው የብፁዕነታቸውን አባታዊ መልእክት አስተላልፈዋል፡፡ © ሐመረ ተዋሕዶ ሚዲያ

ፍርድ ቤቱ የሕገወጥ ቡድኑን መቃወሚያዎች ሙሉ በሙሉ ውድቅ በማድረግ ቤተ ክርስቲያን ከጠየቀችው ዘጠና ቀናት ውስጥ የ፵፭ ቀናት የእግድ ትዕዛዝ ወሰነ። (©ኢኦተቤ ቴቪ የካቲት ፴/፳፻፲፭ አዲስ አበባ ኢትዮጵያ) በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በተፈጸመው ሕገወጥና ኢቀኖናዊ ድርጊት ምክንያት በሕግ አግባብ የሚፈቱ ችግሮችን ለመቅረፍ፣ የቤተ ክርስቲያን ሕጋዊ መብት እና የአማኞችን ሁለንተናዊ መብት እንደከበር ያስችል ዘንድ በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት የሕግ ባለሙያዎች የጠበቆች ኮሚቴ በማቋቋም ጉዳዮችን በሕግ አግባብ እንዲፈቱ እየጠየቀችና እየተከታተለች እንደሆነ ይታወቃል። በዚህ መሠረት የጠበቆች ቡድኑ ዛሬ የካቲት ፴/፳፻፲፭ ዓ/ም በዋለ የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ችሎት ሁለተኛ መሠረታዊ መብቶችና ነጻነቶች ችሎት የሰጠውን የተለያዩ ውሳኔዎችን በጥልቅ ማብራሪ መግለጫ ሰጥቷል። በመግለጫውም ፍርድቤቱ የቤተ ክርስቲያኗን ሕጋዊ ጥያቄ በሕግ አግባብ መልካም ውሳኔ የሰጠበት መሆኑን ግልጽና ጥልቅ በሆነው ገለጻው ተጠቁሟል። የጠበቆች ቡድኑ በመግጫው ሕገወጦቹ ያቀረቦቻው የመቃወሚያ ጉዳዮች እንደነበሩ አብራርቶ ፍርድቤቱ በውሳኔ ውድ አድርጓቸዋል ብሏል። ፍርድቤቱ ውድቅ ካደረጋቸው መቃወሚያ መከራከሪያ ነጥቦች መካከል ፩. ቤተ ክርስቲያን ሕጋዊ ሰውነት ያላት በመሆኑ የመክሰስና የመከሰስ መብት የለት መሆኑንና በጉዳዩ ላይ ክስ መመስረት እንደምትችል። ፪. ጉዳዩ ሃይማኖታዊ ብቻ ሳይሆን የመብት ጥሰት የንብረት ባለቤትነት ያለው በመሆኑ ፍርድ ቤቱ ጉዳዩን ማየት የሚችል መሆኑ በመጥቀስ የሕገወጡ ቡን መከራከሪያ ነጥቦችን ውድ አድርጓል። በአጠቃላይ በሕገወጡ ቡድን የቀረቡ መቃወሚያዎች ሙሉ በሙሉ ውድቅ ማድረግ ቤተ ክርስቲያን በሕገ ወጡ ሹመት ላይ በተሳተፉ ፳፮ቱ ግለሰቦች ላይ ክስ እንድትመሠርት ውሳኔ ሰጥቷል። ከዚህ በተጨማሪም ቤተክርስቲያኗ በጠየቀችው የሦስት ወር እግድ ጊዜ ውስጥ ፍርድ ቤቱ ፵፭ ቀናት ከሦስቱ "አባቶች" በስተቀር ፳፮ (26)ቱም ግለሰቦች ከዚህ ቀደም የገቡበትን መንበረ ጵጵስና እና አብያተ ክርስቲያናትን ጨምሮ "የኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በኢትዮጵያ ውስጥ ያሏትን ይዞታዎች፣ አህጉረ ስብከት፣ገዳማት እና አድባራት፤ አብያተ ክርስቲያናት ንብረቶቿን፤ ታሪካዊ ቅርሶች፣ መንፈሳዊ እና ቁሳዊ መገልገያ እንዳይጠቀሙ፣ ወደ ቅጥሯ እንዳይገቡ፤ ንብረቶቿን እንዳይወስዱ፣ እንዳይገለገሉ፣ ዓርማዋንና ስሟን እንዳይጠቀሙ ይህ ጊዜያዊ የዕግድ ትዕዛዝ ለአንድ ወር ከአስራ አምስት ቀናት ብቻ (ከየካቲት ፫/፳፻፲፭ ዓ/ም ጀምሮ እስከ መጋቢት ፲፰ ቀን ፳፻፲፭ ዓ.ም ድረስ ብቻ ተሰጥቷል"። መባሉን የጠበቆች ቡድን በመግጫው አሳውቋል። ከዚሁ ጋር የኦርዶክሳውያን የእስር ሁኔታ የተነሳ ሲሆን በአብዛኛው እየተፈቱ መሆናቸውን ጠቅሶ በሻሸመኔና በአርሲ ነገሌ አካባቢ ያሉ ኦርቶዶክሳውያን እስረኞ ለመጋቢት ፯፳፻፲፭ ዓ/ም ፍርድ ቤት እንደተቀጠሩም ተጠቅሷል። በዚህ ረገድ የሕግ ተርጓሚ አካላት ላይ የሚታየው ፍትሕን የማስፈን ተጠቃሽ ሥራዎችን በመመዘርዘር በፍርድ ቤቶች የሚስተዋለው ፍትሕን የማስፈን መንገድ የሚበረታታና የሚያስመሰግን መሆኑን የጠቀሰው የጠበቆች ቡድኑ በአስፈጻሚ አካላት በተለይ በአዲስ አበባ ከተማ የታየው የፍረድ ቤቶችን ውሳኔ ያለማስፈጸም ሁኔታዎች በእጅጉ ሊታረሙ እንደሚገባም ገልጿል። በሌላ በኩል "በፓስተር ዮናታን" እና "በፓስተር ኢዩ ጩፋ" የቀረበው ክስ ምን ላይ ደረስ? ለሚለውም በምላሹ ከዚሁ ጋር ጎን ለጎን እያስኬደው እንደሆነ ተጠቁሟል። በመጨረሻም የጠበቆች ቡድኑ የሕጉን መንገድ ተከትሎ የቤተ ክርስቲያን መብትና ማስጠበቅ ሁነኛ ግቡ መሆኑን የጠቀሰ ሲሆን ይሁን እንጂ የትኛውም መንገድ ይሁን ድርጊት ከቅዱስ ሲኖዶስ ትዕዛዝ ከአባቶች ቃል የማይቀድምና የማይበጥል በመሆኑ ቤተ ክርስቲያናችን የምትከተላቸውን የይቅርታና የስምምነት አቅጣጫዎችን በማክበረ እንደሚቀጥል ገልጿል። ኃይሉ በላይ

በመሆኑም መንግሥት ለዘመናት የኖረች እና ከግማሽ የሀገሪቱ ህዝብ በላይ የያዘችን ቤተ ክርስቲያን ክብርና ልዕልና በሚዳፈር መልኩ በተፈጸመው ሕገ ወጥ ተግባር ላይ የተሳተፉ እና ይህን ድርጊት የፈጸሙ የጸጥታ አካላትና እንዲፈፀም ያዘዙ የመንግሥት ኃላፊዎችን በ፲፭ ቀናት ጊዜ ውስጥ ለይቶ በሕግ እንዲጠየቁ እንዲያደርግ እና ይህንንም ለቤተ ክርስቲያኒቱም ሆነ ለሕዝበ ክርስቲያኑ በግልጽ እንዲያሳውቅ እንዲሁም በተለመደው የሀሰት ውንጀላ በዓላችንን በማክበር ላይ እያሉ የመንግሥት የፀጥታ አካላት በፈፀሙት ሕገ ወጥ ተግባር ምክንያት በተፈጠረው ግርግር መነሻት የታሰሩ ምእመናንን ያለምንም ቅድመ ሁኔታ እንዲፈቱ እየጠየቅን ይህ የማይሆን ከሆነ ግን ቤተ ክርስቲያን መብቷን ለማስከበር ወደ ቀጣይ እርምጃዎች የምትገባ መሆኑን በአክብሮት እያሳወቅን ይህንንም ድርጊት ተከታትሎ የሚያሳውቅ እና የሚያስፈጽም የሕግ ባለሙያዎች ኮሚቴ ተዋቅሮ ወደሥራ እንዲገባ የሚደረግም መሆኑን ጭምር እናሳስባለን፡፡ በዚህ ሕገ ወጥ ድርጊት የሊቀ ሰማዕቱን የቅዱስ ጊዮርጊስ ክብረ በዓል ለማክበር በመምጣት ህይወቱን ላጣው ልጃችን እግዚአብሔር ነፍሱን በአብርሃም፣ በያዕቆብና በይስሐቅ እቅፍ ያኑር፣ ለቤተሰቦቹም መጽናናትን ያድልልን እያልን ቀላልም ሆነ ከባድ የአካል ጉዳት የደረሰባችሁ የቤተ ክርስቲን የጭንቅ ቀን ልጆች ደማችሁን እና መከራችሁን እንደ ሰማእታት ዋጋ ይቆጥርላችሁ ዘንድ ጸሎታችን ነው፡፡ እግዚአብሔር ኢትዮጵያን ይባርክ የካቲት ፳፬ ቀን ፳፻፲፭ ዓ.ም አዲስ አበባ፣ኢትዮጵያ

"የካቲት 23 ቀን 2015 ዓ.ም በተከበረው የቅዱስ ጊዮርጊስ ክብረ በዓል በቤተ ክርስቲያን ላይ የአድዋ የድል በዓልን አስታኮ በመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች የተፈፀመው እጅግ አሳዛኝ ድርጊት ቤተክርስቲያን ሰምታና አይታ በዝምታና በሀዘን ብቻ የምታልፈው ጉዳይ አልሆነም" ... ብፁዕ አቡነ ሄኖክ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ሙሉ መግለጫው እንደሚከተለው ቀርቧል፦ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን በየካቲት ፳፫ ቀን ፳፻፲፭ ዓ.ም በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን በመናገሻ ገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን ላይ በመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች አማካኝነት የተፈጸመውን ሕገ ወጥ ድርጊት አስመልክቶ ከአዲስ አበባ ሀገረ ሰብከት የተሰጠ መግለጫ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ከሀገራችን ኢትዮጵያ ሀገረ መንግሥት ምሥረታ ጀምሮ ያለችና መንግሥትን ያጸናች፣ የራሳቸው የጽሑፍ ቋንቋ ካላቸው ጥቂት ሀገራት መካከል ኢትዮጵያ አንዷ እንድትሆን ፊደል ቀርፃ ያስተማረች፣ መንግሥት የአረንጓዴ አሻራን መርሐግብር ከማስጀመሩ ከሺህ ዓመታት በፊት የአካባቢ ጥበቃን ስትሠራ የኖረችና አሁንም በየአጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት፣ ገዳማትና አድባራት የአካባቢ ጥበቃ ሥራን የምትሠራ፣ ዘመናዊ ትምህርት ከመጀመሩ ከሺህ ዓመታት በፊት ሥርዓተ ትምህርት ቀርፃ ያስተማረችና የሀገር መሪዎችን፣ የስነ ህንፃ ባለሙያዎችን፣ የመድኃኒት አዋቂዎችንና ተመራማሪዎችን ያፈራች ቤተ ክርስቲያን ከመሆኗም በላይ ተቋም መሥርታ ለዘመናት የተቋምን ምንነት ያስተማረች ራሷ ሀገር የሆነች ናት፡፡ በተለይም ደግሞ መላው የአፍሪካ ሀገራት በቅኝ ግዛት በተያዙበት፣ አውሮፓውያን ኢትዮጵያንም ለመቀራመት ተስማምተው በፋሺስቱ የኢጣልያ መንግሥት አማካኝነት ሀገራችንን በወረረበት ጊዜ የንጉሱን የክተት አዋጅ ተከትሎ ሕዝቡ ለነፃነቱ እንዲዋደቅ የሀገር ፍቅር ለምእመኗ ያስተማረች በመሆኑ እና የንጉሱም ጥሪ ሀገራዊ ብቻ ሳይሆን ሃይማኖትን የመጠበቅ ጥሪም የነበረ በመሆኑ ሕዝቡ በነቂስ ወጥቶ ንጉሱን እንዲከተል ከማድረጓም በላይ ታቦተ ቅዱስ ጊዮርጊስን በካህናቱ አጅባ የጦር ግንባር ድረስ በመዝመት፣ ምእመኑን እና ህዝቡን በማጽናናትና ፀሎተ ፍትሀት በማድረግ በዓድዋ ጦርነት ኢትዮጵያ ሀገራችን ድል እንድትቀዳጅና ለሌሎች የአፍሪካ ሀገራትም የነፃነት አርማ እንድትሆን በማድረግ ትልቁን የታሪክ ድርሻ እንደምትወስድ የታወቀ ሀቅ ነው፡፡ ከዚህ የድል በዓል በኋላም ኢትዮጵያ በነፃነት በቆየችባቸው ዓመታት ሁሉ ይህን የአድዋ የድል በዓል ቤተ ክርስቲያን የሰማእቱን ቅዱስ ጊዮርጊስ ታቦተ ሕግ ከመንበረ ክብሩ ወጥቶ ህዝቡን በመባረክ፣ ካህናቱና ምእመናኑ በታላቅ ምሥጋና እና መዝሙር በመላ ሀገሪቱ ስታከብረው የኖረች፤ ወደፊትም እየፈጸመች የምትጸናበት አኩሪ ታሪኳ ነው፡፡ ይሁን እንጂ ይህ በዓል ላለፉት ጥቂት ዓመታት የድል በዓል መሆኑ ቀርቶ የጠብና የጥላቻ በዓል እየሆነ መምጣቱ ቤተ ክርስቲያንን በእጅጉ ያሳዘነ ተግባር ሆኗል፡፡ በተለይም ትላንት የካቲት ፳፫ ቀን ፳፻፲፭ ዓ.ም በተከበረው የቅዱስ ጊዮርጊስ ክብረ በዓል በቤተ ክርስቲያን ላይ የአድዋ የድል በዓልን አስታኮ በመንግሥት የፀጥታ ኃይሎች የተፈፀመው እጅግ አሳዛኝ ድርጊትን ግን ቤተ ክርስቲያን ሰምታና አይታ በዝምታና በሀዘን ብቻ የምታልፈው ጉዳይ አልሆነም፡፡ በየካቲት ፳፫ ቀን ፳፻፲፭ ዓ.ም የቅዱስ ጊዮርጊስ ክብረ በዓል ለማክበር ሕዝቡ ከየቤቱ ተሰባስቦ ከጠዋቱ ፫፡፲፭ ላይ ታቦተ ሕጉ ብፁዕ አቡነ ያዕቆብ የጆርጅያ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በተገኙበት ከመንበረ ክብሩ ወጥቶ ዑደት ካደረገና ሕዝቡን ባርኮ በዐውደ ምህረቱ ላይ ከቆመ በኋላ ሊቃውንቱ ያሬዳዊ ወረብ በማቅረብ ላይ እንዳሉ ከመንግሥት የጸጥታ መዋቅር የቤተ ክርስቲያኒቱን ተቋማዊ ልዕልናን ተላልፈው በሰሜን በኩል ወደ ቤተ ክርስቲያኑ ቅጥር ግቢ ፪ ጊዜ በተኮሱት አስለቃሽ ጭስ ምክንያት የንግሥ በዓሉ በመረበሹ በዓሉ ተቋርጦ ከጠዋቱ ፬ ሰዓት ላይ ታቦተ ሕጉ ወደ መንበሩ ተመልሷል፡፡ በዚህም ምክንያት እስከአሁን በደረሰን መረጃ መሠረት በቤተ ክርስቲያን ቅጥር ከፍተኛ ረብሻ በመፈጠሩ ምክንያት ፩ ምእመን በተተኮሰው አስለቃሽ ጭስ ታፍነው ሕይወታቸውን ማጣታቸውን፣ አገልጋይ ካህናት አባቶች፣ ምእመናን እና ምእመናት ከፍተኛ የሆነ አካላዊ እና ሥነ ልቡናዊ ጉዳት ደርሶባቸዋል፤ ከ፲፭ ያላነሱ የሰንበት ትምህርት ቤት አገልጋይ ተማሪዎች በደረሰባቸው ጉዳት ምክንያት ወደ ሆስፒታል ተወስደዋል፡፡ ይህ ድርጊት ከተፈፀመ በኋላም መንግሥት የቤተ ክርስቲያኒቱን ክብርና ልዕልና በመዳፈር በቤተ ክርስቲያን ላይ ይህን በደል የፈፀሙ የጸጥታ መዋቅር አካላትን ለሕግ ያቀርባል፣ እንደ መንግሥት ኃላፊነቱን ይወጣል ብለን ብንጠብቅም የመንግሥት ኮሚኒኬሽን ቢሮ በዓሉን አስመልክቶ በዕለቱ ባወጣው መግለጫ ችግሩን የፈጠሩት አካላት ‹‹የአደባባይ በዓሉን ለመረበሽ ሲያቅታቸው በቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን የሚደረገውን ኃይማኖታዊ በዓል ለመረበሽ ሞክረዋል፡፡ የጸጥታ መዋቅሩ ችግሩን ለመቆጣጠር በወሰደው እርምጃ ጉዳቱን ለመቀነስ ችሏል›› ሲል የችግሩን ሁኔታ ገልጧል፡፡ በዚህ መግለጫውም ላይ አሁንም ችግሩ የሌሎች ቡድኖች እንደሆነና የቤተ ክርስቲያኒቱን በዓል የረበሸው የእነዚህ አካላት እንቅስቃሴ ነው በማለት የሰጠው መግለጫ በቦታው ላይ ከነበረው እውነታ በእጅጉ የራቀ እና ድርጊቱ የተወሰኑ ግለሰቦች ሳይሆን የመንግሥት እውቅና ያለው መሆኑን እንዲሁም መንግሥት ችግሩን ለማረም እና መፍታት ፍላጎት የሌለው መሆኑን እንድንረዳ አድርጎናል፡፡ የቤተ ክርስቲያን በዓል እንዲረበሽ እና ምእመናን ህይወታቸውን እንዲያጡ እንዲሁም እንዲጎዱ ያደረገው ከመንግሥት የጸጥታ መዋቅር የተተኮሰው አስለቃሽ ጭስ እና ጥይት መሆኑ ለሁሉም የታወቀ ሆኖ እያለ ጉዳዩን ወደ ሌላ አካል ለማላከክ የተሄደበትን ርቀት ቤተ ክርስቲያን በፍፁም የምትቀበለው አይሆንም፡፡ የመንግሥት የፀጥታ አካል በቤተ ክርስቲያን ቅጥር ግቢ አስለቃሽ ጭስ በመተኮስ ምእመናን ላይ ጉዳት ሲያደርስ እና የቤተ ክርስቲያንን ክብር ሲያጎድፍ ይህ የመጀመሪያው አይደለም፡፡ በጥር ፩ ቀን ፳፻፲፬ ዓ.ም በቅዱስ እስጢፋኖስ ቤተ ክርስቲያን በተሰበሰቡ ምእመናን ላይ በቤተክርስቲያን ቅጥር ግቢ ውስጥ አስለቃሽ ጭስ በመተኮስ ብዙምእመናን እንዲጎዱ የተደረገ ሲሆን በጊዜው መንግሥት ይህን ድርጊት በፈጸሙ አካላት ላይ እርምጃ ከመውሰድ ይልቅ ልክ እንደአሁኑ ችግሩ የሕገ ወጦች ነው በማለት ለድርጊቱ እውቅና ሰጥቶት አልፏል፡፡ በዚህ ድርጊት መንግሥት በጸጥታ መዋቅሩ ውስጥ ያሉ እና መንግሥትንና ሕዝብን እንዲሁም ተገቢ ያልሆነ ያለመግባባት የሚያባብሱትን ግለሰቦች እና አመራሮች ለይቶ እርምት ከመውሰድ ይልቅ ሕዝብና መንግሥትን ሆድና ጀርባ የሚያደርግ ተግባሩን አስፋፍቶ ቀጥሏል፡፡

የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት ፲ኛ ዓመት በዓለ ሢመት ተከበረ። ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳ
+4
የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት ፲ኛ ዓመት በዓለ ሢመት ተከበረ። ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ስድስተኛው የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ ሆነው የዛሬ አሥር ዓመት በቅዱስ ሲኖዶስ ተመርጠው ቤተ ክርስቲያኒቱን በፍፁም ትጋት እያገለገሉ ይገኛሉ። በዓለ ሢመቱ የቤተ ክርስቲያኒቱ በየዘመኑ የሚሾሙ ፓትርያርኮች አገልግሎት ለማዘከር የቤተ ክርስቲያን በዓል ተደርጎ የሚከበር ነው። የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ በዓለ ሢመት በቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ብፁዐን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን፣ ካህናትና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት በስብሐተ እግዚአብሔር ተከብሯል። የቅዱሰነታቸው በረከት ይድረሰን!

የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ፲ኛ ዓመት በዓለ ሲመትን በማስመልከት "ዜና መዋዕል ዘብፁዕ ወቅ
+4
የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ፲ኛ ዓመት በዓለ ሲመትን በማስመልከት "ዜና መዋዕል ዘብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ" እና "ቃለ በረከት ዘብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ " የተሰኙ መጽሐፍት በጠቅላይ ቤተ ክህነት ተመርቋል። ( የካቲት 23 ቀን 2015 ዓ/ም )