en
Feedback
𝐅𝐢𝐧𝐟𝐢𝐧𝐧𝐞𝐞 𝐏𝐫𝐞𝐬𝐬

𝐅𝐢𝐧𝐟𝐢𝐧𝐧𝐞𝐞 𝐏𝐫𝐞𝐬𝐬

Open in Telegram

✅|| 𝐘𝐀𝐀𝐃𝐀 ykn komii yoo qabaattan nuuf barreessaa. ✅|| ማንኛውም አስተያየት ወይም ቅሬታ ካለዎት ይፃፉልን ✅|| write to us if you have any comments or complaints. 👀 @Fastmereja_Bot 👀

Show more

📈 Analytical overview of Telegram channel 𝐅𝐢𝐧𝐟𝐢𝐧𝐧𝐞𝐞 𝐏𝐫𝐞𝐬𝐬

Channel 𝐅𝐢𝐧𝐟𝐢𝐧𝐧𝐞𝐞 𝐏𝐫𝐞𝐬𝐬 (@fastsinfo99) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 10 422 subscribers, ranking 17 917 in the News & Media category and 3 188 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 10 422 subscribers.

According to the latest data from 07 September, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 32 over the last 30 days and by -5 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 7.81%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 5.54% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 814 views. Within the first day, a publication typically gains 577 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 3.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
✅|| 𝐘𝐀𝐀𝐃𝐀 ykn komii yoo qabaattan nuuf barreessaa. ✅|| ማንኛውም አስተያየት ወይም ቅሬታ ካለዎት ይፃፉልን ✅|| write to us if you have any comments or complaints. 👀 @Fastmereja_Bot 👀

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 08 September, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the News & Media category.

10 422
Subscribers
-524 hours
No data7 days
+3230 days
Posts Archive
🚨🇪🇺 Taphoota Shaampiyoonsi Liigii Awurooppaa marsaa 1ffaa har'a galgala gaggeeffaman 01:45 | Atens vs LASK 01:45 | Kilab B
🚨🇪🇺  Taphoota Shaampiyoonsi Liigii Awurooppaa marsaa 1ffaa har'a galgala gaggeeffaman 01:45 | Atens vs LASK 01:45 | Kilab Biruuj vs Astoon Viillaa 04:00 | R*Maadriid vs Intar Miilaan 04:00 | Doortimand vs Viyaariyaal 04:00 | Poortoo vs Maan Siitii 04:00 | Liil  vs  Beetis 𝐎𝐝𝐞𝐞𝐟𝐟𝐚𝐧𝐧𝐨𝐨 𝐃𝐚𝐛𝐚𝐥𝐚𝐭𝐚𝐚𝐟, 𝐂𝐡𝐚𝐚𝐧𝐚𝐚𝐥𝐢𝐢 𝐓𝐞𝐥𝐞𝐠𝐢𝐫𝐚𝐚𝐦𝐢𝐢 𝐊𝐞𝐞𝐧𝐲𝐚𝐚 "𝐉𝐎𝐈𝐍" 𝐆𝐨𝐝𝐡𝐚𝐚 📌 t.me/Fastsinfo99       🌴  🌴  🌴

🚨🇪🇺 ዛሬ ምሽት የሚደረጉ የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ የመጀመሪያው ዙር ጨዋታዎች!⚽️🏆 01:45 | አቴንስ ከ ላስክ 01:45 | ክለብ ብሩጅ ከ አስቶን ቪላ 04:00 | ሪያል ማድሪድ ከ ኢንተ
🚨🇪🇺 ዛሬ ምሽት የሚደረጉ የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ የመጀመሪያው ዙር ጨዋታዎች!⚽️🏆 01:45 | አቴንስ ከ ላስክ 01:45 | ክለብ ብሩጅ ከ አስቶን ቪላ 04:00 | ሪያል ማድሪድ ከ ኢንተር ሚላን 04:00 | ዶርትሙንድ ከ ቪያሪያል 04:00 | ፖርቶ ከ ማንቸስተር ሲቲ 04:00 | ሊል ከ ቤቲስ ለተጨማሪ መረጃዎች የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ 📌 t.me/Fastsinfo99     🌴  🌴  🌴

Haadduu Gabroomfattuu Sibuu  Guutoo Laf Naqamtee Giiftii Qannoo biqilchate Urjii aartii cichoominaa Faajjii Qabsoo Bilisummaa ‘Artist’ Ilfee Ulfinasheen geggeessite… Ilmaa ilmeef laattee qabdoo Dukkan keessa urjii taatee iftee guddoo… Harma muraa Haadha Oromoo Booree baafte booree gadoo… Harka muraa, abbaa qomoo Abbaa biyyaa Dhiira Madoo.. Badaa baafte diina iddoo… Hadhaa wal’aansoo, wareegamaa Umrii kan kee ijoollummaa Itti fixxee bar moosinnaa Harmee Oromoo Ilfee Qannoo Irbuu Oromoof Oromummaa Haadduun diinaa homaa hinbaatu Haadduu Gabroomfattuu doomtee Rifeensa kee mataa gogaa Qaruuraadhaan itti haadamte Qara hinbulle warri cubbuu Daaraa bubbeen fuute taate! Akeekaa kaayoon gomboobdeen Akka haada gubbaa Gaalaa, Dhaloota walitti hiitee booddeen Mul’anni kee inni dheeraan Bulee ga’ee mataa buusee Galma ga’iinsaaf birmadee… Citee’n hafuu bara baraan Lugaamaafi cancala haafaa Ciree kukkute finni Waanjoo diinaa dursee jifaa Har’a ga’ee si baannataa Walabummaa waliibiifaa Galata siif galcha Sabni!! Artis Ilfee Sagaleeshee ‘Tulluu raasu’ Ifa aduuf qara biiftuun Miila miti Miira kaasu,… Ganni Herreg- Dhiiraa Hagayya Haawwonnii Waan ati gumaachiteen Halkan Qaammee kanaan Seenaa kee jireenyaan Yaadata dhaloonni# Fulbaana 7,2026 𝐎𝐝𝐞𝐞𝐟𝐟𝐚𝐧𝐧𝐨𝐨 𝐃𝐚𝐛𝐚𝐥𝐚𝐭𝐚𝐚𝐟, 𝐂𝐡𝐚𝐚𝐧𝐚𝐚𝐥𝐢𝐢 𝐓𝐞𝐥𝐞𝐠𝐢𝐫𝐚𝐚𝐦𝐢𝐢 𝐊𝐞𝐞𝐧𝐲𝐚𝐚 "𝐉𝐎𝐈𝐍" 𝐆𝐨𝐝𝐡𝐚𝐚 📌 t.me/Fastsinfo99       🌴  🌴  🌴

At Elfinesh Qanno’s funeral, the people of Ambo & the larger West Shewa made a bold and historic statement today. It is up to us to get the right interpretation of that statement. ========== Ilfuu Asxaafi faajjii Oromootaa. Urjii qabsoo bilisummaa. Haadha Oromoota maraa. Riqicha ilmaan Oromoo maraa. Ilfuu keenya ati hambaadha. Hambaa jaallan shinnigaa. Hambaa Jen. Taaddee Birruu. Hambaa Jen. Waaqoo Guutuu. Hambaa Elemoo Qilxuu. Hambaa Eebbisaa Addunyaa. Hambaa Dararaa Kafanii. Hambaa Maammoo Mazammir. Hambaa Agarii Tulluu. Hambaa Jaal. Nadhii Gammadaa. Hambaa Hacaaluu Hundeessaa. Hambaa gootota qaqqaalii. Goota waan himaniif qabdu.

🔘|| ILFEEn waa shan dhaammatte: uffata gaafa karchallee Amboo baate uffatte faana awwaalamuu, alaabaa ABO dhanna isheetti aa
+5
🔘|| ILFEEn waa shan dhaammatte: uffata gaafa karchallee Amboo baate uffatte faana awwaalamuu, alaabaa ABO dhanna isheetti aanee kafanamuu, Ambootti awwaalamuu, alaabaa ABOtiin gaggeeffamuu fi dhalootaaf ammoo tokkummaa fi jaalala. Dhaammannoo ishee afur guunneerraaf. Tokko ammoo dhaloonni ofitti haa fudhatu. Oromoon saba tokko, hiree tokko waliin qabu ta'uu dhaloonni haa mirkaneessu. ~©Lemmi Begna ✍️

🚨 እልፍነሽ ቀኖ!!💔 በህይውት እያለች ፣ በግጥም፣ በዜማ፣ በጥዑምና ኪሎሌ ድምጽዋ ኦሮሞን በአራቱም አቅጣጫ እኩል ስብስባ አስጨፈረች፣ በደስታ አስለቀስች፣ እልህና ቁጭት ፈንቅሎ ለመብትና ለነጻነት እንዲፋለም ከአንድ በላይ ትውልድ አስከበረች። እነሆ ትንፋሾዋ ቆሞም ኦሮሞን በሽኝቱዋ ሰበሰበች፣ በጀግኖች ምድር ከፊንፊኔ እስክ አምቦ ህዝቡ ግልብጥ ብሎ እየወጣ የጀግና አቀባበል አደረገላት። ዳግም ታሪክ ጻፈች!! የኤቢሳ አዱኛን ሽኝት አስታወሰኝ😭 ያኔ ከፊንፊኔ እስክ ደንቢዶሎ በየመንገዱ እየወጣ አቀባበልና ሽኝት ያደረገው ህዝብ ብዛትና ቁጭት በታሪክ ብዙም ያልተነገረለት ነበር። እልፍዬ ክብርና ሞገስ ይገባሻል። ኦሮሞ ጀግኖቹን ማክበር ይችልበታል። በህይወት እያሉ ቢሆን ደግሞ የበለጠ ያምርብናል። በሰላም እረፊ ጊፍቲኮ💔🙏

ILFINASH QANNOO akkuma dhaammatte AMBOTTI awwaalamuun taateewwan Tokkummaa Qabsoo Oromoof raawwataman gurguddoo sadan keessaa
+9
ILFINASH QANNOO akkuma dhaammatte AMBOTTI awwaalamuun taateewwan Tokkummaa Qabsoo Oromoof raawwataman gurguddoo sadan keessaa tokko ta’eera. 1) DHEERAA: Jeneraal Taaddasaa Birruu fa'aan Islaamaa - Kiristaana foon koma tokkoo nyaachisuu 2) SHINNIGGA: Magarsaa Barii fa'aan amantiin gargar bahuu didanii waliin wareegamuu 3) AMBO: Ilfinash Qannoo qa’ee dhaloota ishii mannaa handhura Qabsoo tan taate Ambotti awwaalamuu filachuu. * Keessattuu shira waggoottan saddeettan dabre ummata keenya Wallaggaafi Shawaa walitti diinomsuuf godhame yoo yaadannu, dhaammannoon Ilfee hiika dacha dachaa qabaata) ~©Jawaar Mohammed ✍

Obbo Jawaar Ilfinesh Ambootti akka awwaalamtu dhaammachuun isheefi akkuma dhaammattettis achitti awwaalamuun ishee tokkummaa Oromoo jabeessuu keessatti ergaa jabduu akka qabu kaasuun ibsan. "ILFINASH QANNOO akkuma dhaammatte AMBOTTI awwaalamuun taateewwan Tokkummaa Qabsoo Oromoof raawwataman gurguddoo sadan keessaa tokko ta'eera. 1) DHEERAA: Jeneraal Taaddasaa Birruu fa'aan Islaamaa - Kiristaana foon koma tokkoo nyaachisuu 2) SHINNIGGA: Magarsaa Barii fa'aan amantiin gargar bahuu didanii waliin wareegamuu 3) AMBO: Ilfinash Qannoo qa'ee dhaloota ishii mannaa handhura Qabsoo tan taate Ambotti awwaalamuu filachuun," Infinesh hiika guddaa akka qabu himan. Du'a Ilfinash irratti waan aanga'oonniifi namoonni beekamoon waan jedhan as keessaa ni argattu. 👇👇 https://bbc.in/3UuPQfX

🇪🇹📜 የወሎ ታሪክ — ታሪክን የኋሊት የጁ ኦሮሞ የጦርነት ስልት! ዘመነ መሳፍንት በሚባለው የየጁዎች መንግስት ወቅት እንዲህ ሆነ፤ ራስ አሊ የጁ የተባለ ጀግና ጎፈሬ መስፍን አገሪቱን ይመራ ነበር፤ ከእሱ በታች፤ በነ ራስ አሊ ትዛዝ ደጃች ውቤ የተባለ ባለሹርባ መስፍን፤ ከስሜን እስከ ምፅዋ ያለውን ግዛት ያስገብራል። የሆነ ጊዜ ላይ ውቤ ደጃዝማችነቱ አላረካው አለ፤ መፈንቀለ መንግስት ማድረግ ፈለገ፤ ደጁን ብቻ ሳይሆን ሙሉውን ግቢ ፈለገው፤ ለመንገስ በጣም ሻፈደ። በምፅዋ በኩል ብዙ ጠመንጃ እየሰበሰበ አካማቸ፤ ብዙ ጭፍራ መለመለ፤ የሚቀማውን ስልጣን የተገባ Legitimate ለማድረግ አባ ሰላማ የተባለ የግብፅ ቅጥረኛ ጳጳስ አሰናዳ፤ የሚቀረው ምንድነው? ራስ አሊን ከስልጣን ማባረር። ታሪኩን ላሳጥረውና፤ ራስ አሊና ውቤ ደብረታቦር ላይ ገጥመው ተፈሳፈሱ! በጦርነቱ ላይ የውቤ ባለነፍጥ ሰራዊት የራስ አሊን ፈረሰኛ እንደ ቅጠል ያረግፈው ጀመር፤ የራስ አሊ ፈረሰኛ በጎራዴ ነበረ የምዋጋ፤ የራስ ውቤ በግብፆችና በክሪስትያን ሀገሮች እገዛ የተገኛ መሳርያ ነበረ። ነገሩ ያላማረው ራስ አሊ ብረት-ለበሱን ማለቴ ፈረሱን የኋሊት አዞረና ቆሰቆሰው፤ አብዛኞቹም ወታደሮቹም ተከትለውት ሸሹ፤ የጦርነት ስልት ነው። ውቤ፤ ነገሩ አሸወይና እንደሆነ ሲመለከት ድንኳኑን ጥሎ አስደግሶ ወታደሮቹን የድል ምሳ ጋበዘ። ምሳው እየተበላ፣ ጠጁ እየተጠጣ፣ ወታደሮች እየመጡ ይፎክራሉ፤ ምርኮኞችም ደግሞ መሳርያቸውን እየጣሉ በውቤ ፊት ይንበረከካሉ። በዚህ መሀል፤ የወሎው ጀግና አሊጋዝ ብሩ የተባለ እውቅ፤ የየጁ ጀግና ወደ ደጃች ውቤ ቀረበ። ሌሎች ምርኮኞች እንደሚያደርጉት መሳርያውን የሚያስቀምጥ ይመስል በርከክ እንደማለት አለና፦ “እጅ ወደላይ!” ብሎ ጮኸ! ውቤ ቁጭ ባለበት ደርቆ ቀረ፤ ምንም ማድረግ አልቻለም። እየጋጠ የነበረውን የዶሮ ቅልጥም ማእዱ ላይ አስቀምጦ እጁን ወደ ላይ አነሳ። (የቅልጥሙን ቀደዳ እንኩዋን እኔ ነኝ የጨመርኩት) ራስ አሊ፤ ከሸሸበት ቦታ ሆኖ አንድ መልክት ደረሰው፦ “ውቤ ተማርከዋልና ይመለሱ” ይላል መልእክቱ። ላኪው አሊጋዝ ብሩ የየጁ ጀግና ነው። ይህ በሆነ በማግስቱ አንዲት ባልቴትና እና አንድ ሰውየ መንገድ ላይ ተገናኙ። “እቴዋ! የራስ አሊና የደጃች ውቤ ጦርነት እንዴት አለፈ?” አለ ሰውየው። “ራስ አሊ ሸሹ፤ ደጃች ውቤ አሸንፈው ተማረኩ” አሉ ባልቴቲቱ። “እረ ባክዎ በቅጡ በቅጡ አድርገው ያውጉኝ!” “ተወኝ ባክህ! እነሱ በቅጡ ያልተዋጉትን እኔ እንዴት በቅጡ ላውጋው?” --- 🧠 ከዚህ አጭር የታሪክ ገጠመኝ የምንማረው የዘመናዊ ፖለቲካ ንድፈ ሀሳብ “የሚሸሽ ሁሉ የተሸነፈ አይደለም፤ የሚያሸንፍ ሁሉም አሸናፊ አይደለም።” ይህ የውቤ ታሪክ እንደ ተራ የጦርነት ገጠመኝ ብቻ ከተመለከትነው ብዙ ነገር እናጣለን። ነገር ግን ከፖለቲካ ስልት አንፃር ስናነበው የሚያስተምረን ነገር አለ። ውቤ የጦር ሜዳውን አሸነፈ ብሎ አሰበ። ስለዚህ የድል ምሳ አዘጋጀ። ራስ አሊ ግን ወደኋላ ተመለሰ። ይህ ሽንፈት ይመስል ነበር። ነገር ግን ጨዋታው እዚያ አልተጠናቀቀም። የውቤ ድል ወደ የድል ምሳ ሲቀየር፣ የራስ አሊ ሽንፈት ወደ የፖለቲካ ውጤት ተቀየረ። ይህ ነው የፖለቲካ ስልት። አንድ ኃይል በዛሬው የጦር ሜዳ ሊያሸንፍ ይችላል፤ ሌላው ደግሞ በዛሬው ጦርነት ሊሸሽ ይችላል። ግን የመጨረሻውን ውጤት የሚወስነው የመጀመሪያው ቅጽበት አይደለም። የሚወስነው፦ ማን እስከመጨረሻ አስቦ ነው? ማን የተቃዋሚውን ቀጣይ እርምጃ አይቷል? ማን በድል ስሜት አልተዘናጋም? ማን የሕዝብን ድጋፍ ማቆየት ችሏል? የዛሬ ኢትዮጵያ ፖለቲካም በዚህ መነፅር ሊታይ ይችላል። የዛሬን ድል ብቻ አትመልከት፤ የነገን እርምጃ ተመልከት። የዛሬ ሽንፈትንም የመጨረሻ ሽንፈት አድርገህ አትቁጠር። ምክንያቱም፦ የፖለቲካ ጨዋታ እስካልተጠናቀቀ ድረስ የድል ምሳ ማዘጋጀት አደገኛ ነው። 🔥 ታሪክን የኋሊት ስናየው፣ የዛሬን ፖለቲካ የበለጠ እንረዳለን። ተፃፈ [©Miky Sultan Barento] ✍️ . . ለተጨማሪ መረጃዎች የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ 📌 t.me/Fastsinfo99     🌴  🌴  🌴

ነገረ #ልደቱ አቶ ልደቱ አያሌው ከርዕዮት ሚዲያ ጋር ያደረጉትን ቃለ ምልልስ ዘግይቼም ቢሆን ሰማሁት። ቴዲ ባለፈው ጀዋርን እንደዛ ሲያፈጥጠው ከልደቱም ጋር ተመሳሳይ ቆይታ ያደርጋል ብዬ ጠብቄ ነበር። ነገር ግን አልሆነም። ልደቱ አብዛኛውን ጊዜ ጀዋርን በማማት ነው ያሳለፈው ማለት ይቻላል። በእውነቱ፣ ልደቱ በዚህ መልኩ ቅንነትና ሐሳብ ነጥፎበት፣ character assassination ላይ ተሰማርቶ አይቼ አላውቅም። ጀዋርን በብዙ ነገሩ መተቸት እየቻለ ተራ ሀሜት ውስጥ መግባቱ አስገርሞኛል። #ጀዋር በመንግሥት ጭምር ጥበቃ እንደሚደረግለትና ወደ እሱ ቤት የሚያቀና ማንኛውም ሰው እንደሚፈተሽ ብዙዎቻችን እናውቃለን። ይህ ከደህንነት አንጻር እንደሆነና ከክብር ጋር እንደማይገናኝ ልደቱ ቢስተው፣ ቴዲ እንዴት ዝም ሊለው ቻለ? በዚሁ አጋጣሚ፣ ወደ ጀዋር ቤት የሄዱ ሰዎች ነርቫቸው ለምን በዚህ ደረጃ እንደሚነካ የሆነ ጥናት ቢጤ ቢደረግ ባይ ነኝ😏 በነገራችን ላይ፣ ጀዋር በፖለቲካ ሕይወቱ ሁለት ግዙፍ ስህተቶችን ሠርቷል ብዬ አስባለሁ፤ በተለይም ከመታሰሩ በፊት። አንደኛው፣ ኦፌኮን ተቀላቅሎ የአክቲቪስትነት ዘመን ነፃነቱን መገበሩ ሲሆን፤ ሁለተኛው፣ ልደቱን በኦኤምኤን ላይ ጋብዞ፣ ከመስከረም በኋላ “መንግሥት የለም” የሚል ዘመቻ ማስተጋባቱ ነበር። የሁለተኛው ጦስ፣ ከኮሮና ጋር ተዳምሮ፣ ለሐጫሉ መገደልና ለነጀዋር መታሰር አስተዋጽኦ እንደነበረው መካድ አይቻልም። ልደቱ በዚህ ቃለ ምልልስ የራሱን ፖለቲካዊ ዋጋ ከፍ ለማድረግ የሞከረው አንዳንዴ አስቂኝ፣ ሌላ ጊዜ ደግሞ አደገኛ የሆኑ ፍረጃዎችን በመጠቀም ጭምር ነው። የኦሮሞ ሕዝብ በጀዋር ላይ የሚነሳው ልደቱ ስለተናገረ ብቻ አይመስለኝም። የሕዝቡን intelligence መናቅም ይሆናል። የኦሮሞ ነፃነት ሠራዊት ጀዋር ላይ እንዲነሳ መቀስቀስም በራሴ ላይ ተደረገብኝ ከሚለው የግድያ አዋጅ የሚተናነስ አይደለም። ጀዋር ፖለቲከኛ ነው። ፖለቲከኛ ዋነኛ ግቡ፣ በተገኘው አጋጣሚ ሥልጣን መያዝ ነው። በዚህ ስሌት፣ ጀዋር መፈንቅለ መንግሥት ቢያስብ ችግሩ ምንድነው? የኔ ለሚለው constituency ማለትም የኦሮሞ ሕዝብ ፍላጎት እንዲጠበቅ ቢታገልና ጽምዶ የዚህ ተቃራኒ ነው ብሎ ቢያስብ፣ መብቱ አይደለም ወይ? አቶ ልደቱ ሆይ፣ እርሶ መንግሥተ ሰማያት ሊገቡበት ነው ፖለቲካ የሚሠሩት? እኔ ፖለቲከኛን በሚናገረው ሳይሆን፣ በሚፈጽማቸው ተግባራትና በድርጊቱ የምመዝን ሰው ነኝ። ጀዋር ይህን ሥርዓት እንዳይወድቅ ቢከላከልና ኦሮሞ በቀጣይ ቦታውን ያጣል ብሎ ቢሰጋ፣ ኃላፊነት የሚሰማውና pragmatist የሆነ ፖለቲከኛ የሚያደርገው ነገር ነው ብዬ አስባለሁ። ለዚህ ስሜት ማረጋገጫ መስጠትና በመተማመን አብሮ መሥራት ሲገባ፣ በአደባባይ “ራቁቱን ቀርቷል” ብሎ መፎከር አግባብ አይደለም። በዚህ ሁኔታ ከአቶ ልደቱ ጋርስ ማን አምኖ ይሠራል? እኔ የታየኝ የጀዋር ራቁቱን መቅረት ሳይሆን፣ የአቶ ልደቱ ስጋትና ለሽንፈት የቀረበ አነጋገር ነው። አንድ ነገር ግን ግልጽ ነው። ልደቱ በዚህ ንግግሩ ጽምዶ ገና በጠዋቱ መክሸፉን አውጇል። ከሌሎች ልሂቃን በተሻለ መልኩ የሰከኑና አማካይ መንገድ ሊጠቁሙ የሚችሉት እንደ ልደቱ ያሉ ሰዎች፣ በዚህ ደረጃ አንድን ትብብር፣ ለዚያውም ገና ፍሬው ያልታወቀውን፣ “ካልደገፍክ ትቀሰፋለህ” ካሉ እውነትም ችግር አለ ማለት ነው። ይህም ሀገርን ወደ ልማት ሳይሆን፣ ወደ ጥፋት የሚያመራ ነው የሚሆነው። ብቻ ሀገራችንን ሰላም ያድርግልን😊 VIA, [Hussein Tulu] 🙏🙏 . .

📌 የብልጽግና ሥራት- መንግሥት ፣ የሚከተለው = "ደርግ" ስራት ነው 🙆‍♂️🤦‍♀️ 📍 "ጽምዶ" የሚባለው ሰብሰብ የሚያራምደው -ስራት -መንግስት = "አዳዊ " ነው 👥 እኛ የማልቲ ፌደራሊስት ደጋፊዎች፣ ሁለቱም ከላይ የጠቀስኩት ስራት መቶ በመቶ ለኛ ስለመሆኑ ፣ ተደራጅተን ካልታገልን ትልቅ የፖለቲካ ክራይስስ ውስጥ እንገባለን!!🤘🙏 . . . #ብልግናና #ጽምዶ #ማልቲ_ፌዴረሊስት #ኢትዮጵያ

በዚህ ረገድ ሰዎች የፖለቲካ አቋማቸውን ለመቀየር የተራዘመና በጣም አስቸጋሪ የሆነ የእስር ዓመታት ማሳለፍ የሚጠበቅባቸው ለምንድነው? የሚለውን የmorality ጥያቄ ግን ላንባቢያን መተው የሚገባ ነው። የሆነው ሆኖ፣ እዚ ላይ አንድ ትዝብት አንስተን እንለፍ፥ ጸሃፊው ቀድሞ ይደግፈው የነበረውን የኦሮምያ መገንጠል ሃሳቡን የተወው፣ “ኦሮምያ ከኢትዮጵያ ቢገነጠል ሰላም አያገኝም” ከሚለው የቆየ መከሪያከሪያ ነጥብ ተነስቶ ነው። በኔ እይታ ይሄ ምክንያት ከኦሮምያ ነጻነት ተቃዋሚች (ለምሳሌ የታወቁቱ ጸረ ኦሮምያ አቋም የሚያራምዱ የፖለቲካ ቡድኖች) ሲመጣ የሚጠበቀው የተቃራኒ ወገን negativist tactic ይሆናል። ልክ ልጆችን ለማስፈራራት “ይሄን ካደረክ ጆሮ ቆራጩ ይመጣብሃል” እንደሚባለው ዓይነት መሆኑ ነው። ይሄው ምክንያት ከነ ኦቦ ጋዲስ ዓይነት ካሉት የቀድሞ የኦነግ ታጋዮች ዘንድ ሲመጣ ደግሞ defeatist argument ይሆናል። ይልቅ ኦሮምያ የኢትዮጵያ ፌዴሬሽን ውስጥ ቢቆይ፣ እንዴት ሁለንተናዊ ጥቅሞቹ በላቀ ደረጀ ሊከበሩ እንደሚችሉ ተንትኖ በማሳየት መገንጠል ብዙ ፋይዳ ያለው ነገር አለመሆኑን በመቂ መንገድ ማሳየት አይቻልም ወይ? ፋ) ጸሃፊው ኦቦ ጋዲሳ፣ እስከ አስረኛው ምራፍ የኦሮሞ ብሄተኝነት ቆቡን ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ ያወልቅና በቀጣዮቹ ምራፎች በሌላ መልኩ ይከሰታል። በታሪክ ውስጥ በነበረ ቤተሰባዊ መስዋዕትነት ላይ ጭምር የቆመ የድሮ Ethiopian Nationalist፣ የግብጽን ታሪካዊ ጸረ—ኢትዮጵያ ተንኮሎች የሚያጋልጥ geopolitical analyst፣ የመጪው ዓለም የስነህዝብ እድገትና የአየር ንብረት ለውጥ እንዲሁም የተፈጥሮ ሃብት መመናመን ላይ science alarmist ብሎም የጠቅላይ ምንስትር አብይ አህመድ ደጋፊ optimist (not to say propagandist) ወዘተ ሆኖ ይታያል። ይመቸው። እውነት ለመናገር በተለይም የኋላኛው ነጥብ ግን ትኩረቴን ሳይስበው አልቀረም። ያው “ብልጽጌ ብልጽጌ እየተጫወተ ስለሆነ በደንብ እርገጠው” የምትል ማሳሰቢያ ደርሶኝም የለ? ጸሃፊው በተለይም በአስራ ዘጠነኛውና በሃያኛው ምራፎች ለጠቅላይ ምንስትሩ ያለውን ትልቅ ድጋፍ በግልጽ ያሳያል። በውነቱ ያወድሳል ወይም ያሸበሽባል ሊባልም ይችላል። ይህ በንዲህ እንዳለ፣ ሃያ አንደኛው ምራፍ ውስጥ “የኢትዮጵያን አንድነት የሚፈታተኑ” ያላቸውንና ጠቅላይ ምንስትሩ ላይ የሚስተዋሉ “አስደንጋጭ ውስንነቶች” በሚል የቀረቡት ትንተናዎች ግን ጸሃፊው some sense of balanced view ያለው ስለመሆኑም የሚያሳዩ ናቸው ብዬ ገምታለው። ለምሳሌ ኢትዮጵያ ውስጥ የከፋ ድህነት አሁን ያለው መንግስት ሲመጣ ከነበረበት 25 በመቶ አካባቢ ዛሬ ላይ ወደ 43 በመቶ ከፍ እንዲል ያደረገውን የአይኤምኤፍ ፖሊሲ ፕሪስክሪፕሽን ተቀብሎ ስራ ላይ ማዋል፣ እንዲሁም በኢትዮጵያ ታሪክ ታይቶ በማይታወቅ ሁናቴ እጅግ የከፋ ደረጃ ላይ ደርሷል ያለውን የሙስና ችግር ባሳማኝ ትንተናዎች አስደግፎ ያቀረበበት ሂደት ይሄንኑ ነጥቤን የሚያጠናክር ነው። እነዚህን ጨምሮ ሌሎች እጅግ አስከፊ ችግሮች እጫንቃው ላይ ስለተጫነበት ህዝቡ መኖር አቅቶታል፤ አስቸኳይ መፍትሄ ይሻል ባይ ነው ደራሲው። ጋ) ከላይ በተጠቀሰው የመጽሃፉ ሃያ አንደኛው ምራፍ ውስጥ አንድ ወሳኝና እንደ አንባቢ ትኩረቴን የሳበ ጥያቄ ያነሳል ደራሲው። “እነዚህ አስደንጋጭ ችግሮች እያሉ፣ ህዝቡ ለምን ከሁከት ተቆጥቦ ሸክሙን በትዕግስት ይሸከማል?” …. ጸሃፊው ለዚህ ወሳኝ ጥያቄ ምላሽ ይሆናሉ ያላቸውን አምስት ምክንያቶች አስቀምጧል። ትኩረቴን የሳበው ግን ሁለተኛው ሲሆን፣ ይኻውም “ከተቋሟዊ አፈጻጻም ይልቅ ህዝቡ በመሪው ላይ ያለው እምነት” የሚለው ነው። እዚ ላይ ህዝቡ ምንም’ንኳ እጅግ አስከፊ ሁናቴ ውስጥ ያለ ቢሆንም ቅሉ፣ ስርዓቱ ላይ እስካሁን ያላመጸው “በመሪው ዓላማና በተቋሟዊ ብልሽት መካከል ያለውን ልዩነት ስለሚገነዘብ ነው” ባይ ነው ኦቦ ጋዲሳ። ይሄ ነጥብ “እኔ የምደግፈው ጠቅላይ ምንስትር አብይን እንጂ የብልጽግና ፓርቲ መንግስትን አይደለም” ያለንችንን አንዲት ወዳጃችንን የሚያስታውሰኝ ነው። እዚህ ላይ አንድ የመጽሁፉ አንባቢ ሊያነሳ የሚችለውን የpolitical morality ጥያቄ አንስተን እንለፍ፥ አንድ ለፖለቲካ አቅመ አዳም የደረሰ ሰው (ህዝብ ላለማለት) በህግ ተቋቁመው በህግ ከሚሰሩ ሃገራዊ ተቋማት ይልቅ ባንድ ግለሰብ መሪ ላይ እምነት የሚያሳድር ከሆነ፣ ያ ሃገር በርግጥም ሃገር ሊባል ይችላል ወይ? ወይም እንደሃገር ሊቀጥል ይችላል ወይ? በነገራችን ላይ ይሄን ኢትዮጵያ እንደሃገር የገባችበትን አደገኛ ቅርቃር ጠቅላይ ሚንስትሩም በደንብ የተረዳው ይመስላል። ለዚህ ማሳያ የሚሆን አንድ ምሳሌ እናንሳ። ስድስተኛው ምርጫ ተደርጎ፣ ብልጽግና ፓርቲ ሙሉ በሙሉ አሸነፍኩ አለ። ኋላ ጠቅላይ ምንስትሩ ፓርላማ ላይ ካቢኔውን ሲያቋቁም፣ ምርጫ ተወዳድሮ የወደቀው ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ የትምህርት ምንስትር ሆኖ መሾሙን አንዲት የፓርላማ አባል በግልጽ ወጥታ ተቃወመች።  “ህዝብ መርጦኝ ነው እዚ ያለውት” የሚል ነጥብ አስገብታ ነበር በንግግሯ። የፓርላማ አባሏ የፕሮፌሰሩን ሹመት የተቃወመችበት ምክንያት አሳማኝ ሊባል የሚችል ነበር። የፓርላማ አባሏ ራሷ በትምህርት አስተዳደር መስክ PhD ያላት ነበረች። ብርሃኑ ነጋ ግን በትምህርት አስተዳደር ምንም ዓይነት መደበኛ ስልጠና የሌለው ብቻም ሳይሆን፣ የኮሌጅ ዲን ሆኖ ስለመስራቱ እንኳ ምንም ማስረጃ የለም። እንዲያውም አሜሪካ ኢኮኖሚክስ ኮርሶችን ከሚያስተምርበት ኮሌጅ ለቆ ኤርትራ በርሃ በመውረድ የታጠቀ አማጺ ቡድን መሪ ሆኖ የነበረ ስለሆነ፣ ሹመቱ ልክ አይደለም የሚል ነበር የፓርላማ አባሏ ነጥብ። ከተቋማዊ የሙያ አሰራርና እሳቤ አንጻር ሲታይ የፓርላማ አባሏ ትክክል ነበረች። ጠቅላይ ምንስትሩ በዛ የፓርላማ ስብሰባ ላይ የሰጣት መልስ ግን በዚህ ረገድ revealing ሊባል የሚችል ነበር። “ህዝብ አንቺን የት አውቆ ይመርጥሻል? እኛን አይቶ እንጂ” ነበር ያላት ጠሚው። በዚ ምላሽ የፓርላማ አባሏ ደንግጣ አማተበች። ያቺ የፓርላማ አባል አሁን ያለችው የት ይሆን? ባለችበት ሰላሟ ይብዛ! ሃ) በመጨረሻም፣ መጽሃፉ ምንም’ንኳ አንባቢዎች ሊማሩባቸው የሚችሏቸውን በርካታ ጠቃሚ ጭብጦች (substantive points) አጭቆ ያቀረበልን ቢሆንም ቅሉ፣ የአርታዊ (editor) ዓይን ያላየው መሆኑ ግን በግልጽ የሚታይ ነው። መጽሃፉ እንደመጽሃፍ ሳይሆን ዝም ብሎ እንደ ተራ ጥራዝ ነገር ስለታተመ፣ የመጽሃፉ አዲስ ምዕራፍ ባሮጌው ምዕራፍ የመጨረሻ ገጽ አጋማሹ ላይ ታትሞ ልታገኙት ትችላላቹ። ብዙ ጊዜ የፖለቲካ ሰዎች መጽሃፍ ሲያሳትሙ፣ ለይዘቱ የሚጨነቁትን ያህል መጽሃፉ ስታንዳርድ ፎርማት ይዞ እንዲታተም በማድረግ ረገድ የሚያሳዩት ስንፍና ሁሌም የሚገርመኝ ነገር ነው በውነቱ። ደራሲው ኦቦ ጋዲሳ በመጽሃፉ ቀጣይ ህትመት ይሄን ነገር ያስብበታል በሚል ተስፋ አስተያየቴን በዚሁ እቋጫለው። ኢ) መጽሃፉን እንድታነቡት እጋብዛለው። አመሰግናለው።  ~ ተጻፈ በ ግርማ ጉተማ 👀🙏✌️! ይሄን መጸሐፍ በ "PDF" በዚህ የቴሌግራም ቻናላችን ላይ በቅርብ ቀን ....!!📖📚🤘 እስከዛ ድረስ ቻናሉን "JOIN" እያደረጋችሁ ጠብቁን!!👌 . . . 📌 t.me/Fastsinfo99     🌴  🌴  🌴

🔘|በ|  “የኦሮሞ ትግልና ታላቋ ኢትዮጵያ” ላይ አጭር የመጽሃፍ ዳሰሳ “የአሸባሪው ማስታወሻ” በሚለው የቀደመ መጽሃፉ የምናስታውሰው ኦቦ ጋዲሳ አበራ፣ በቅርቡ ያሳተመውን አዲስ መጽሃፍ “የኦሮሞ ትግልና ታላቋ ኢትዮጵያ) አነበብኩት። ከመጽሃፉ አንዳንድ ነጥቦች አንስቼ እይታዬን ከማካፈሌ በፊት ደራሲውን ኦቦ ጋዲሳን መጽሃፉን ስለላከለኝ እጅግ አድርጌ ላመሰግነው እወዳለው።👀🙏 * ይሄን ካልኩ ዘንዳ፣ መጽሃፉ ውስጥ ወደ ተነሱት አንዳንድ ነጥቦች ላምራና በስምምም ሆነ በሂሳዊ አካሄድ እየቀላቀልኩ ጥቂት አስተያየቶኦቼን ላስቀምጥ። . ኣ) የመጽሃፉ የይዘት ሽፋን አድማስ ከኦሮሞ ፖለቲካዊ ትግል ስረ መሰረት ተነስቶ፣ እስከታላቋ ኢትዮጵያ እውን መሆን ጽንሰ ሃሳብዊ ትንተና ድረስ የሚዘልቅ ነው። ደራሲው “ታላቋ ኢትዮጵያ” ሲል necessarily አሁን የምናውቃትን ኢትዮጵያ ሳይሆን፣ ተመሳሳይ/ተቀራራቢ የባህል፣ የታሪክና የፖለቲካል ኢኮኖሚ ፍላጎት ያላቸውን የምስራቅና የአፍሪካው ቀንድ አካባቢ ሃገሮችን ጭምር አስተሳስራ (integrate አድርጋ) የምትፈጠረውን ባለሰፊ ቁመትና ወርድ ባለቤት የምትሆነውን አዲስ ሃገር ይመስላል። ከዚህ አንጻር የቀረቡት ትንተናዎች መጽሃፉ ለአንባቢያን ያለውን ጠቀሜታ ከፍ ያደረጉ ሆነው ይታያሉ። ባ) ደራሲው የኦሮሞን ትግል ስረ መሰረቶችና ስኬቶች እንዲሁም ተግዳሮቶችን ባቀረበባቸው የመጀመሪያዎቹ ዘጠኝ ምራፎች (መጽሃፉ ውስጥ ከተካተቱት ሃያ ሁለት ምራፎች አብዛኞቹ አጫጭሮች ናቸው)፣ በርካታ ውይይት የሚያጭሩ ጉዳዮችን ያነሳል። ለምሳሌ፣ የቀደሙት የኦሮሞ የትግል አባቶችና ያሁኖቹ ፖለቲከኞች ወይም አክቲቪስቶች የፖለቲካ ስልጣንን በተመለከተ ስላላቸው ከፍተኛ የእይታ ልዩነት በሚያቀርብበት ሶስተኛውና አራተኛ የመጽሃፉ ምራፎች ውስጥ የተነሱት ነጥቦች መሬት ጠብ የማይሉ ናቸው። ጉዳዮ በኦሮሞ ትግል ውስጥ በተለይም ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እየታየ የመጣው ህዝባዊ ጥቅሞችን ሳይሆን የፖለቲካ ስልጣንን ማዕከል አድርጎ የማየት አባዜን (syndrom of political-power-centerism) በጥልቀት እንድናስተውል የሚጋዝብ ነው። ቀደምቶቹ የኦሮሞ ትግል አባቶች የነበራቸውን ስልጣን እንኳን ትተው ህዝባዊ ወገንተኝነታቸውን በማሳየትና ህዝቡንም በማታገል ከፍተኛ የሞራል ልዕልናቸውን ያሳዩ ናቸው። በዚ ረገድ ከጀነራል ታደሰ ብሩ እስከ ጀነራል ዋቆ ጉቱ፣ ከኤሌሞ ቂልጡ እስከ ቄስ ጉዲና ቱምሳ እንዲሁም ከማሞ መዘምር እስከ ሃይሌ ፊዳ ያሉት ቀደምት የኦሮሞ ትግል አባቶች ያሳዩት ህዝባዊ ወገንተኝነትና ተምሳሌታዊ የሞራል ልዕልናቸው ተዳሷል። በተቃራኒው ደግሞ ያሁኑ ፖለቲከኞች የኢትዮጵያ የፖለቲካ ስልጣን ተምሳሌታዊ ትዕምርት (symbolism for political power) መሆኑ የሚታወቀውን “አራት ኪሎ”ን ደረታቸውን ነፍተው “አታስለቅቁንም” ሲሉ ስንሰማ፣ በዚ ረገግ የጸሃፊውን የሰላ ትዝብት አግባብነት እንረዳለን።  በተቃዋሚ ጎራ ያሉትም ሆነ የገለልተኝነት ካባ ለብሰው “ ሴሌብሪቲ ሴሌብሪቲ“ የሚጫወቱት የፖለቲካ አክቲቪስቶችም የዚሁ ችግር ዋነኛ ሰለባ የመሆናቸው እውነታ ሊያከራክር አይችልም። ጽሃፊው በዚህ ላይም ብዙ ብሎበታል። ጫ) ጸሃፊው “የኦሮሞ ትግል” በሚል ለበየነው የኦነግ የፖለቲካ ትግል እንቅስቃሴ ተገቢ እውቅናና ክብር በመስጠት ረገድ ፍትሃዊ እይታውን ካስቀመጠ በኋላ፣ ለኦነግ መዳከምና መከፋፈል ተጠያቀውን አካል በሚያፈላልግበት ስድስተኛው ምራፍ፣ የኦሮሞ ዲያስፖራን ለዚህ ተጠያቂ ያደርጋል። በኔ እይታ የዚህ ዓይነቱ ድምዳሜ ላይ ለመድረስ ጠለቅ ያሉ ጥናቶችን ማካሄድ የሚፈልግ ቢሆንም፣ ኦቦ ጋዲሳ ከኦነግ ትግል ጋር ተያይዞ የኦሮሞ ዳያስፖራ ሚና ከሌሎች ሃገሮች የዳያስፖራ ማህበረሰቦች ጋር በታሪክ እያነጻጸረ የሚያቀርበው ሂስ ትኩረት የሚስብ ነው። እርሱ እንደሚለው በተለይም ከቻርተሩ ዘመን ማለትም ከ1991 በኋላ፣ በተለያዩ የምዕራብ ሃገሮች ያሉ የኦሮሞ ዳያስፖራ ማህበረሰቦች በተለይም በስነምግባር የለሽ ተግባራት (የኦሮሞ ትግል ውስጥ እንደተሳተፉ አስመስሎ በማጭበርበር በየሃገራቱ ወረቀት ማግኘትን ጨምሮ)፣ በሰርጎ ገብነት፣ መንደርተኝነትንና ጎሰኝነት (tribalism) ዓይነት ረብ የለሽ አስተሳሰቦችን በማስፋፋት፣ የመሪዎችን ስም አላግባብ በማጥፋትና ያልተገባ ተጽኖ በመፍጠር ወዘተ… በድርጅት ውስጥ እምነትን ቀስ በቀስ ሽርሽረው፣ የአመራር መዋቅሩ እንዳይረጋጋ ብቻም ሳይሆን እንዲፈርስ ጭምር አድርገውታል። የኦነግ የፖለቲካ ትግል ላይ ለዶክትሬት ዲግሪ ጥናት እያካሄዱ ያሉ የቁቤው ትውልድ አባላት የሆኑ ምሁራን እንዳሉ አውቃለውና፣ ይሄ ኦቦ ጋዲሳ የሚያነሳው የዳያስፖራ ሚና ጉዳይም ወሳኝ ትኩረት የሚሻ መሆኑ በዚሁ አጋጣሚ መጠቆም ተገቢ ይመስለኛል። ለነገሩ ርዕሰ ጉዳይ ሰፋ ተሰርጎ፣ የአጠቃላይ ኢትዮጵያ የዳያስፖራ ማህበረሰቦች ሚና በፓርቲ ፖለቲካ እንዲሁም በሰላምና በሃገር ግንባታ ጋር ተያይዞ ጥናት ቢደረግ ጠቀሜታ ያለው ውጤት ሊገኝ እንደሚችል ጥርጥር የለውም። ዳ) ጸሃፊው “የኦነግ ትግል: ተገቢው እውቅና የተነፈገው መስዋዕትነት” በሚለው ምራፍ ስር interesting የሆኑ ነጥቦችን ያነሳል። “በምስራቅ አፍሪካ ረጅሙ የፖለቲካ ትግል” የተባለው የኦነግ ትግል፣ መንግስታዊ ስልጣን ለመያዝ እድል ሳያገኝ ሃሳቦቹ ግን የኢትዮጵያን ሃገረ መንግስት ፖለቲካዊ ገጽታ መሰረታዊ በሆነ መልኩ እንደለወጠው ይከራከራል። እንደ ብሄራዊ እውቅና፣ ፌዴራሊዝም፣ የቋንቋ መብቶችና የባህል እኩልነት ያሉትን የፖለቲካ ትሩፋቶችን በመጠቃቀስ፣ እነዚህ ፍትሃዊ ትሩፋቶች ከኦነግ በፊት በነገረችው ኢትዮጵያ ፍጹም ሊታሰቡ የማይችሉ ስለመሆናቸው ይሞግታል። እነዚ የዛሬይቱን ኢትዮጵያ በመሰረተዊነት የበየኑ ፖለቲካዊ እሳቤዎች መጪም ሆኑ ሂያጅ መንግስታት ሊጥሏቸው የማይችሉ መሆናቸውን በማስረገጥ፣ ኦነግ በዚ ረገድ ላደረገው ታሪካዊ አስተዋጾ በቂ እውቅናና ክብር አላገኘም ባይ ነው ነጻፊው። ነጥብ ያለው ይመስለኛል። ኤ) ደራሲው ኦቦ ጋዲስ አበራ፣ ከአስራ አንድ ዓመታት የፖለቲካ እስረኝነት ተለቆ ወደ ቄሮ ትግል የተቀላቀለበትን ሂደት የሚተርክበት ምራፍም የአንባቢን ትኩረት ሰቅዞ የሚይዝ ነው። ታሪኩ የኦሮሞን ትግል ስትራቴጂካዊ እድገትና ህዝባዊ አቅም (grassroots power) የሚያሳይም ነው ማለት ይቻላል። እዚህ ላይ Hidhaan qoraasuma dhiiraati የሚለው የቆየ የኦሮሞ ታጋዮች አባባል ሊነሳ የሚገባው ነው። ሃሳቡ የተራዘመ ፖለቲካዊ የእስር ጊዜን ለንባብ፣ ለማሰላሰል እንዲሁም እንደጥሞና ጊዜ በመጠቀም፣ አስቸጋሪውን የእስር ቤት ኑሮ ለበጎ ነገር የማዋል አካሄድን የሚጠቁም ነው። ፈረንጆቹ a blessing in disguise እንደሚሉት ወይም አስከፊ በሆነ ነገር ውስጥም’ንኳ አንዳች በጎ ነገር ሊገኝ የመቻሉን እውነታ የሚገልጽ ጽንሰ ሃሳብ መሆኑ ነው። ጸሃፊው ኦቦ ጋዲሳ፣ የቀድሞ ፖለቲካዊ አቋሞቹን የቀየረበትን ሂደት (ኦሮምያን ከኢትዮጵያ መገንጠል የሚለውን የበፊት አቋሙን ጨምሮ)፣ ከተራዘመ የእስር ቆይታው ከወጣ በኋላ በቄሮ ትግል ውስጥ በምን መልኩ መሳተፍ እንዳለበት የወሰነበት አካሄድ፣ እሱ በግልጽ ባያስቀምጠውም የዚሁ ህሳብ ተጋሪ መሆኑን አመላካች ሆኖ ይታያል።

እኔ ጀዋር ላይ ያቀረብኳቸው ክሶች አራት ነበሩ :- 1ኛ. የታጣቂ ሃይሎችን ትብብር ተቃውመሃል የሚል ነው። እሱ ግን "አልተቃወምኩም ÷አልደገፍኩም" ብሎ ነበር። አንተ ጋር መጥቶ ግን 99.9% ሲቃወ
እኔ ጀዋር ላይ ያቀረብኳቸው ክሶች አራት ነበሩ :- 1ኛ. የታጣቂ ሃይሎችን ትብብር ተቃውመሃል የሚል ነው። እሱ ግን "አልተቃወምኩም ÷አልደገፍኩም" ብሎ ነበር። አንተ ጋር መጥቶ ግን 99.9% ሲቃወም ነበር። 2ኛ. የመሪ እንጂ የመንግስት ለውጥ እንዲመጣ አትፈልግም ብዬዋለሁ። እሱንም መጥቶ በይፋ አረጋገጠ። እንኳንስ መንግስት እንዲወርድ ÷ እንዲዳከም አይፈልግም። የኦህዴድ ብልጽግና ወደ ድርድር እንዲመጣ አልያም መፈንቅለ-መንግስት እንዲካሄድ የሚፈልገው። 3ኛ. በተቋም (institution) አታምንም ነው ያልኩት። መጥቶ "እኔ .. እኔ" እያለ ሲያወራ የነበረው። አሁን ላይ ጀዋር ከማንም ጋር እየሰራ አይደለም። ያቺ ምኞቱ እንድትሳካና እድሉን ለመሞከር ብቻውን እየተንቀሳቀሰ ነው። 4ኛ. ሌላው ነገር ጀዋር የኢትዮጵያ ሕዝብ የህልውና ችግር የለበትም ብሎ ያምናል። ታጣቂዎቹ የህልውና ችግር እንዳለባቸው አያምንም። ይሄን አሳንሶ "የሰላም ጥያቄና የኢኮኖሚ መበላለጥ" አድርጎ ያስቀምጠዋል። አሁን ላይ የህልውና ጥያቄ አለበት ብሎ የሚያምነው "የኦህዴድ ብልጽግናን" ነው። የህልውና ችግር አለበት አናፍርሰው ÷ ካፈርስነው እንጎዳለን እያለ ነው። ጀዋር already ያቀረብኳቸውን ክሶች መልስ ሰጥቷል። አረጋግጦልኛል። 🗣️ልደቱ አያሌው🤘

🚨 የቱርክ ፕሬዚዳንት ረሰፕ ጣይይፕ ኤርዶጋን እስራኤል የመካከለኛው ምስራቅን ጦርነት በመቀስቀስ እና የኢራን-አሜሪካ ግጭትን ለማብቃት የተደረሰውን የኢስላማባድ ስምምነት በማኮላሸት ከሰሱ። አክራሪ
🚨 የቱርክ ፕሬዚዳንት ረሰፕ ጣይይፕ ኤርዶጋን እስራኤል የመካከለኛው ምስራቅን ጦርነት በመቀስቀስ እና የኢራን-አሜሪካ ግጭትን ለማብቃት የተደረሰውን የኢስላማባድ ስምምነት በማኮላሸት ከሰሱ። አክራሪ አስተሳሰብ እስካለ ድረስም የክልሉ አለመረጋጋት እንደሚቀጥል አስጠንቅቀዋል" ስል ሮይተርስ ዘግቧል . . ቴሌግራም፦             📌t.me/Brics4ethiopia

🚨🇮🇱 የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ናታንያሁ የኢራን አገዛዝ ማብቂያው መቃረቡን ገልጸው፣ ውድቀቱ የመካከለኛው ምስራቅን እና የአይሁድን ህዝብ ዕጣ ፈንታ እንደሚለውጥ ተናግረዋል። ከአሜሪ
🚨🇮🇱 የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ናታንያሁ የኢራን አገዛዝ ማብቂያው መቃረቡን ገልጸው፣ ውድቀቱ የመካከለኛው ምስራቅን እና የአይሁድን ህዝብ ዕጣ ፈንታ እንደሚለውጥ ተናግረዋል። ከአሜሪካ ጋር በመተባበር የኢራንን የኑክሌር እና የሚሳይል አደጋዎች ማስወገዳቸውን ያነሱት ናታንያሁ፣ እስራኤል ራሷን ለመከላከል እና ጠላቶቿን ለመመከት ሙሉ በሙሉ ቁርጠኛ መሆኗን አስጠንቅቀዋል።🙄😫 ቴሌግራም፦             📌t.me/Brics4ethiopia