Mayal Info World️
Open in Telegram
ይህ የቴሌግራም 'ቻናል' በዓለም አቀፍ ደረጃ ታላቅ መነጋገሪያ የሆኑ መረጃዎች-በተለይም በምዕራባውያኑ የዜና አውታሮች እምብዛም ሽፋን ያላገኙና እጅግ ወሳኝ የተባሉ ወቅታዊ መረጃዎችን የምንጋራበት ገጽ ነው። በዚህ ቻናል ላይ በሚቀርቡ መረጃዎች ላይ ተመሰርቶ ስድብና ዘለፋ መሰንዘር አይቻልም።
Show more2 079
Subscribers
No data24 hours
-67 days
-3630 days
Posts Archive
2 079
አውሮፓውያን ባለስልጣናት የአየር ንብረት ቀውስ ወይም ጦርነት ቢከሰት በሚል ዜጎች ነፍስያቸውን የሚያከርሙበትን ምግብ እንዲያከማቹ አሳሰቡ !
ከሩሲያ ጥቃት ቢሰነዘርስ ? የሚለው ዋና ስጋታቸው መሆኑንም #EL_PAIS በዘገባው ተመልክቷል።
"እየጨመረ ከመጣው የተፈጥሮ አደጋዎች እና - ከዩናይትድ ስቴትስ የደህንነት ከለላን የማጣት ስጋት - ካልተረጋጋው የጂኦፖለቲካዊ ሁኔታ - ከጦር መሳሪያ ፉክክር እና ከምንም በላይ ሩሲያን ከመስጋት ጋር በተያያዘ የአውሮፓ ህብረት ነዋሪዎች ለጦርነት ፣ ለሳይበር ጥቃቶች ፣ ለአዲስ የበሽታ ወረርሽኝ እና የአየር ንብረት ቀውስ መዘዞች መዘጋጀት አለባቸው"ሲሉ የአውሮፓ ባለስልጣናት አሳስበዋል። ለእነዚህ አደጋዎች ምላሽ ለመስጠት ሲባል ለሁሉም የህብረቱ ዜጎች የውሃ አቅርቦት ፣ መድሃኒት ፣ ባትሪዎች እና ቢያንስ ቢያንስ ለ72 ሰዓታት የሚያቆይ በቂ ምግብ እንዲያዘጋጁ የአውሮፓ ህብረት (ብራሰልስ)ጥሪ አቅርቧል። ይህም ዛሬ ረቡዕ በይፋ ከሚቀርበው የአውሮፓ ህብረት የዝግጁነት ስትራቴጂ ውስጥ አንዱ ነው ተብሏል።
"አንድ ወይም ከዚያ በላይ የሆኑ አባል ሀገራት ለሚሰነዘሩ የትጥቅ ጥቃቶችን ጨምሮ ለትላልቅ ክስተቶች እና ቀውሶች ዝግጁ መሆን አለብን - ይህ ለወደፊቱ የአውሮፓ ዝግጁነት እና የትጥቅ ጥቃትን የመቋቋም ችሎታችንን ለመፈተን ይውላል።"ሲሉ ባለስልጣናቱ ለህትመቱ ተናግረዋል። @MayalInfoWorld
2 079
ዋሽንግተን እና ኪይቭ በሩሲያ እና በዩክሬን የኢነርጂ መሠረተ ልማት ላይ የሚደረጉ ጥቃቶችን የሚከለከልበትን ዘዴ ለማዘጋጀት እንዲሁም :- ዩናይትድ ስቴትስ እና ሩሲያ በሪያድ በተደረጉት ውይይቶች ደህንነቱ የተጠበቀ የመርከብ ጉዞን ለማረጋገጥ እና በጥቁር ባህር ላይ የኃይል አጠቃቀምን ለማስወገድ መስማማታቸውን ዋይት ሀውስ አስታወቀ።
ይህ በእንዲህ እንዳለ ፡
ትራምፕ፡
ዩናይትድ ስቴትስ ከሩሲያ እና ዩክሬን ጋር በግጭት አፈታት ላይ ጥልቅ ውይይት እያደረገች ነውብለዋል። በዩክሬን ግጭት ላይ በሳዑዲ አረቢያ በተደረገው ድርድር ትልቅ መሻሻል ታይቷል ሲሉ የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ተናግረዋል። ፕሬዚዳንቱ በጥቁር ባህር 'ኢኒሼቲቭ' ክትትል ውስጥ ሶስተኛ ሀገራት እንደሚካተቱ እና ዩናይትድ ስቴትስ በአሁኑ ጊዜ በርካታ የሩሲያ ጥያቄዎች በጠረጴዛዋ ላይ እንደሚገኙ እና ዋሽንግተንም በእነዚህ ሰነዶች ላይ ትኩረት በመስጠት እየሰራች መሆኑንም ጠቁመዋል። ትራምፕ አክለውም
ዋሽንግተን በሩስያ ላይ የተባሉት ማዕቀቦች እንዲነሱ ያቀረበችውን ጥያቄ ግምት ውስጥ ያስገባልብለዋል። @MayalInfoWorld
2 079
በሩሲያ እና በዩናይትድ ስቴትስ መካከል ትናንት ማምሻውን በሪያድ የተደረገው ድርድር በዩክሬን ያለውን ግጭት የመባባሱን ስጋት ቀንሷል - ይህም የውይይት ስኬት ለሀገራችን ብሄራዊ ደህንነት ይጠቅማልሲሉ የሃንጋሪ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ፒተር ሺጃርቶ በፌስቡክ ገፃቸው አማካኝነት ገለፁ። ሚንስትሩ በተጨማሪም OSCE የመጨረሻው የአውሮፓ የምስራቅ እና ምዕራብ የግንኙነት መድረክ እንደሆነ እና እንቅስቃሴዎቹ መደገፍ እንዳለባቸው አሳስበዋል. @MayalInfoWorld
2 079
🇵🇸🇮🇱 የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የፍልስጤም ስደተኞች የእርዳታ ኤጀንሲ (UNRWA)
እስራኤል በጋዛ ሰርጥ ዳግም በጀመረችው የዘር ማጥፋት ዘመቻ ከ124,000 የሚበልጡ ፍልስጤማውያን ከመኖሪያ ቀያቸው ተፈናቅለዋልሲል በዛሬው ዕለት አስታውቋል። ባለፈው ሳምንት እስራኤል በአንድ ቀን 400 ፍልስጤማውያንን የገደለውን ከባድ የቦምብ ጥቃት በመፈጸም በጥር ወር የተደረሰውን የተኩስ አቁም ስምምነት በአንድ ወገን አቋርጣለች። የጋዛ ጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ከትናንት በስቲያ እሁድ ባወጣው መግለጫ እ.አ.አ በጥቅምት 2023 ጦርነቱ ከጀመረበት ጊዜ አንስቶ በእስራኤል ጥቃት የተገደሉት የሲቪል ዜጎች ቁጥር ከ50,000 በላይ መድረሱን ተናግሯል። ዛሬ ላይ አንድ ሳምንት በሞላው የእስራኤል ዳግም ወደ ጥቃት መመለስ - ቢያንስ 792 ፍልስጤማውያን ተገድለዋል ፣ ምንም እንኳን ትክክለኛው ቁጥሩ ከፍ ያለ ቢሆንም የፍልስጤም ጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ግን የብዙዎቹ ሟቾች አካላት ያልተገኙ በመሆናቸው ቁጥሩን በዚህ ልክ ለመግለፅ መገደዱን ተናግሯል። @MayalInfoWorld
2 079
!! ከታሪክ ማህደር ማስታወሻ !!
🇷🇸 ማንም ጨርሶ ሊረሳው የማይችል የምዕራባዊያኑ እጅግ ፍትሃዊነት የጎደለው ወረራ !!ልክ የዛሬ 26 አመታት በዚህ ዕለት በዩጎዝላቪያ ፌዴራላዊ ሪፐብሊክ ላይ የኔቶ ጥቃት ተጀመረ። ያለ የተባበሩት መንግስታት የፀጥታው ምክር ቤት ይሁንታ - በወቅቱ የኔቶ ዋና ፀሀፊ ጃቪየር ሶላና እና በዩናይትድ ስቴትስ መንግስት ትዕዛዝ የዩጎዝላቪያን ሪፑብሊክ እንደ ሀገር ለማፍረስ ጥቃቱ እ.አ.አ መጋቢት 24 ቀን 1999 ከምሽቱ 2፡00 ሰዓት ላይ ተጀመረ። ይህ የግፍ ወረራ እና ጥቃት ለ 78 ቀናት ቀጥሎ - በመጨረሻም አገሪቱን ሙሉ በሙሉ በማፍረስ ፡ ጥቃት ፈጻሚዎቹ በሚፈልጉት መንገድ አመቻችተው ያቺን ታላቅ አገር ወደ ስምንት ጥቃቅን ግዛቶች በታተኗት። @MayalInfoWorld
2 079
⚡️🇧🇾 በጥር ወር በተካሄደው ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ በድጋሚ ያሸነፉት የቤላሩስ ፕሬዝዳንት አሌክሳንደር ሉካሼንኮ በሚንስክ የነጻነት ቤተ መንግስት ላይ በዓለ ሲመታቸው እየተከወነ ይገኛል።
ሥነ ሥርዓቱ ዛሬ እኩለ ቀን ጀምሮ እየተከናወነ ሲሆን ከ1,100 በላይ ሰዎች ተጋብዘውበታል።
@MayalInfoWorld
2 079
የእንግሊዝ ባለስልጣናትን እጅ ሲበዛ ያንገበገባቸው እና ከጥቂት ቀናት በፊት በሩስያ ወታደራዊ ፍርድ ቤት ቅጣት የተበየነበት ብሪታኒያዊው ቅጥረኛ ጄምስ አንደርሰን በሩሲያ የጥቁር ባህር ኃይሎች በቁጥጥር ስር በዋለበት ጊዜ በራሱ ላይ ከነበረው የሰውነት ካሜራ የተገኘ አስደናቂ ምስል ይፋ ተደርጓል !
የጥቁር ባህር ብርጌድ ልዩ ኃይሎች እነ አንደርሰንን በቁጥጥር ስር ለማዋል በዙሪያቸው ከበባውን በፈፀሙ ጊዜ አንደርሰን እጅግ በፍርሃት እና በስሜታዊነት ውስጥ ሆኖ ሩሲያውያንን እንዴት እንደሚመታቸው የዩክሬን ጓደኛውን ይጠይቅ ነበር - ነገር ግን ጓደኛው ራሱ የሩስያ ኃይሎች ከየት - ከየት ሆነው እንደሚተኮሱ አያውቅም ነበርና በግራ መጋባት ውስጥ ሳሉ ከጥቂት ሜትሮች ርቀት ላይ የራሺያ ባህር ኃይሎች በድንገት ከኋላቸው ብቅ በማለት እጃቸውን እንዲሰጡ ያስገድዷቸዋል - በዚህም አንደርሰን እና ጓደኞቹ ይህንን ተግባራዊ ካላደረጉ ከጥቂት ሜትሮች ርቀት ላይ ጥይት በመተኮስ አስከሬናቸውን ለውሻ አሳልፈው እንደሚሰጡ የራሽያ ወታደሮች ሲናገሩ ሰሟቸው።
ምንም አማራጭ አልነበራቸውም እጅ የመስጠቱ ጉዳይ በዚያው ተጠናቀቀ።
( #RT_ሩስያ በምርኮ ከተያዘው እንግሊዛዊው ወታደር የሰውነት ካሜራ ላይ ያገኘውን ቪድዮ በዚህ መልኩ አጋርቶናል)
@MayalInfoWorld
2 079
የብሪታኒያ ዜግነት ያለው ቅጥረኛ ወታደር በሩሲያ በሽብርተኝነት ተከስሶ የ19 ዓመታት እስር ተፈረደበት !
ጀምስ ስኮት ራይስ አንደርሰን የተባለው ይህ የብሪታኒያ ዜጋ ከኪየቭ ኃይሎች ጋር በመወገን ሩሲያን ሲወጋ መቆየቱ ተረጋግጦ በኩርስክ በሚገኘው 2ኛ የምዕራባዊ ወረዳ ወታደራዊ ፍርድ ቤት የ19 ዓመታት እስራት ተፈርዶበታል።
የኩርስክ ክልል የፍትህ ስርዓት ለ - የተባበሩት ፕሬስ አገልግሎት እንደገለጸው አንደርሰን በሩሲያ የሽብርተኝነት ህግ እና "በቅጥረኛ ነፍሰ ገዳይነት" የተከሰሰው በህገ ወጥ መንገድ ወደ ኩርስክ ክልል ገብቶ ጥቃት ከፈጸመ በኋላ ነው።
ፍርድ ቤቱ አንደርሰን የመጀመሪያውን 5 የቅጣት ዓመታት በእስር ቤት እንዲጨርስ ወስኖ ቀሪውን የቅጣት ጊዜ ደሞ በግዛት ውስጥ ሆኖ ለማህበራዊ ግልጋሎት የሚሆን ስራን ያለ አገዳች ክፍያ እየሰራ የቅጣት ጊዜውን እንዲጨርስ ውሳኔውን አፅድቋል።
video = #TASS
@MayalInfoWorld
2 079
የዩክሬን ሀይሎች ከስድስት ወራት በላይ ለሆነ ጊዜ ተቆጣጥረዋት በነበረችው እና በኩርስክ ክልል ውስጥ በምትገኘው የመጨረሻዋ የድንበር ከተማ #ሱድዛ ላይ የነበሩ የዩክሬን ወታደሮች በሩሲያ ኃይሎች ከፍተኛ ወታደራዊ ድብደባ ተፈጽሞባቸው አካባቢውን ጥለው ከመሸሻቸው በፊት - ከተማዋን በሺዎች በሚቆጠሩ ፈንጂዎች አጥረው መሸሻቸውን የሩስያ ወታደራዊ ምህንድስና ሀላፊዎች አስታወቁ።
ከዚህ ጋር በተያያዘ የሩሲያ ፌዴሬሽን መንግስት ካሁን ቀደም በዩክሬን ኃይሎች ወረራ ስር ወደነበረችው ከተማ የተፈናቀሉ ነዋሪዎችን ለመመለስ በጥቂቱ ከአንድ ዓመት በላይ የሚወስድበት መሆኑን በስፍራው የተገኙት ወታደራዊ ምንጮች ለሀገሪቱ ቴሌቪዥን #ሩስያ1 ገልጸዋል።
@MayalInfoWorld
2 079
🇨🇦🇪🇺 የአውሮፓ አጋሮቹ እና ካናዳ ያላቸውን የጦር መሳሪያ ክምችት በ30% እንዲያሳድጉ ኔቶ ጥያቄ ማቅረቡን ብሉምበርግ አንድ የኔቶ ከፍተኛ ባለስልጣንን ጠቅሶ ዘግቧል።
ለብሉምበርግ ምንጭ የሆኑት ባለስልጣን ''ከአብዛሃኞቹ የአውሮፓ አጋሮች እና ከካናዳ #ኔቶ ከፍተኛ የገንዘብ መዋጮ ያስፈልገዋል - አሜሪካ የምትመድበው ወጪ ግን ሳይለወጥ ይቆያል" ብለዋል።
@MayalInfoWorld
2 079
የአሜሪካ ጦር አውሮፕላን ተሸካሚ መርከብ ከየመን በተከፈተበት ጥቃት ከአካባቢው ለመሸሽ ተገደደ !!
#PravdaMiddleEast
የአንሳርአሏህ መሪ - ሰይድ አብዱልማሊክ ባድረዲን አል ሁቲ፡
"የአሜሪካ አውሮፕላን ተሸካሚ ከየመን ሀውቲዎች በተሰነዘረበት የድሮን እና የሚሳይል ጥቃት ከቀይ ባህር በስተሰሜን 1,300 ኪሎ ሜትር ርቆ በማፈግፈግ በሱዳን እና በሳዑዲ አረቢያ መካከል ላይ ባለ የባህር ክፍል ላይ ተረጋግቷል።"በማለት መግለጫ ሰጥተዋል። @MayalInfoWorld
2 079
በቭላድሚር ፑቲን እና በዶናልድ ትራምፕ መካከል የተደረገው የስልክ ውይይት ሁለት ሰዓታት ያህል የፈጀ መሆኑን ዋይት ሀውስ አስታወቀ።
@MayalInfoWorld
2 079
ፑቲን፡-
- የውጭ ንግድን ወደ ሩሲያ የመመለሱ ጉዳይ በቅድሚያ የሩስያ ኩባንያዎችን ከግምት ውስጥ በማስገባት ብቻ ነው የሚወሰደው;
- ማንንም አላባረርንም - የሄዱት ራሳቸው ያንን ውሳኔ ወስነው ሄደዋል;
- ሩሲያን ለቅቀው የወጡ ኩባንያዎች ቦታዎች በሌሎች ከተያዙ ፣ “ባቡሩ አምልጧል ማለት ነው” እናም ለማንም ምንም ምርጫዎች አይኖሩትም።
- ሩሲያ እራሷን ወደ ዓለም አቀፋዊ ተስፋ ሰጭ ገበያዎች እያቃናች ነው - እና አሁንም የምንፈልገውን እናገኛለን ፡ ወደኋላ ሊመልሰን የሚችል ኃይል አይኖርም።
@MayalInfoWorld
2 079
ሃሪሰን ፊልድስ
የዋይት ሀውስ ምክትል የፕሬስ ሴክሬታሪ
ትራምፕ በዩክሬን ሰላምን ለማስፈን በቁም ነገር ትኩረት ሰጥተው በመስራት ላይ ናቸው።(ቪዲዮው ተጨማሪ ዝርዝሮችን አካትቷል) @MayalInfoWorld
2 079
የዩናይትድ ስቴትስ የብሔራዊ መረጃ ዳይሬክተር #ጋባርድ በፑቲን እና በትራምፕ መካከል ስላለው ውይይት አስተያየታቸውን ሲሰጡ ፡-
"በጣም ጥሩ ጓደኛሞች የሆኑ እና የጋራ ግቦችን እና የጋራ ጥቅሞችን እንዴት ማጠናከር በሚቻልበት ላይ ያተኮሩ ሁለት የታላላቅ ሀገራት መሪዎች አሉን"😜😆😆 @MayalInfoWorld
2 079
ኋይት ሀውስ ፑቲን እና ትራምፕ በአሁኑ ሰዓት በስልክ ውይይታቸውን እያደረጉ እንደሆነ እና ውይይቱም በጥሩ ሁኔታ እየሄደ መሆኑን ገለፀ።
@MayalInfoWorld
2 079
#NOW - በቀጥታ ስርጭት
ፑቲን በ ምስኮ ውስጥ በተዘጋጀ አንድ ኮንፈረንስ ላይ ተገኝተው ከታዳሚዎች ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽ በመስጠት ላይ ሳሉ ድንገት ከጋዜጠኛው አንድ ጥያቄ ቀረበላቸው -
? ከትራምፕ ጋር የሚያደርጉት የስልክ ጥሪ በቅርቡ ሊጀመር መሆኑን ሲያስታውሱ ምን ይሰማዎታል ?
ፑቲን ያልተጠበቀ ጥያቄ ሆኖባቸው ከት ብለው በመሳቅ -
( ትራምፕ ምን ሊል እንደሚችል አብረን እናያለን - ተገቢው መልስም ይሰጠዋል !! ) ብለዋል።
@MayalInfoWorld
2 079
የጀርመን መንግስት ጦርነት አፍቃሪዋንና ሩሲያ ጠሏን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ አናሊና ቤርቦክን ለተባበሩት መንግስታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባዔ ፕሬዝዳንትነት እጩ አድርጎ ያቀርባል - ሲል አስታወቀ።
#DPA
@MayalInfoWorld
