en
Feedback
Yeneta Courses

Yeneta Courses

Open in Telegram

መቀመጫ | ADDIS ABABA UNVERSITY ©Yeneta Tutorial

Show more
2 787
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
#የመቁረጫ_ነጥብ የአቅም ማሻሻያ (ረሜዲያል) የመቁረጫ ነጥብ፦ - የተፈጥሮ ሳይንስ ወንድ ተማሪዎች ፤ ከ700 በመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች ለመማር የረሜዲያል መቁረጫ ነጥብ 👉 263 - የተፈጥሮ ሳይንስ ሴት ተማሪዎች ፤ ከ700 በመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች ለመማር የረሜዲያል መቁረጫ ነጥብ 👉 227 - የማህበራዊ ሳይንስ ወንድ ተማሪዎች ፤ ከ600 በመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች ለመማር የረሜዲያል መቁረጫ ነጥብ 👉 220 - የማህበራዊ ሳይንስ ሴት ተማሪዎች ፤ ከ600 በመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች ለመማር የረሜዲያል መቁረጫ ነጥብ 👉 190 - የታዳጊ ክልል የተፈጥሮ ሳይንስ ወንድ ተማሪዎች ፤ ከ700 በመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች ለመማር የረሜዲያል መቁረጫ ነጥብ 👉 210 - የታዳጊ ክልል የተፈጥሮ ሳይንስ ሴት ተማሪዎች ፤ ከ700 በመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች ለመማር የረሜዲያል መቁረጫ ነጥብ 👉 210 - የታዳጊ ክልል የማህበራዊ ሳይንስ ወንድ ተማሪዎች ፤ ከ600 በመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች ለመማር የረሜዲያል መቁረጫ ነጥብ 👉 180 - የታዳጊ ክልል የማህበራዊ ሳይንስ ሴት ተማሪዎች ፤ ከ600 በመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች ለመማር የረሜዲያል መቁረጫ ነጥብ 👉 180 (ተጨማሪ ከላይ በተያያዘው ምስል ያንብቡ) 🎖📖🎖 @aplusacademyy @aplusacademyy ▬▬▬▬▬▬▬▬

#Update የሬሚዲያል ፕሮግራም መቁረጫ ነጥብ ዛሬ ይፋ ይደረጋል። በሬሚዲያል ፕሮግራም የሚካተቱ ተማሪዎች የመቁረጫ ነጥብ ዛሬ የካቲት 06/2015 ዓ.ም ይፋ ይደረጋል። በ2014 የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ወስደው የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ውጤት ያላስመዘገቡና የተሻለ ውጤት ካላቸው ተማሪዎች መካከል 100 ሺህ የሚሆኑት ተማሪዎች በሬሚዲያል ፕሮግራም እንደሚካተቱ መገለጹ ይታወቃል። የሬሚዲያል ፕሮግራሙን ለአራት ወራት ከየካቲት 15 እስከ ሰኔ 15/2015 ዓ.ም ለመስጠት ታቅዷል።

📚 የዩኒቨርሲቲ ምደባ ማየት ተጀምሯል። በቀረቡት አማራጮች ገብታችሁ ማየት ትችላላችሁ። https://result.ethernet.edu.et SMS: 9444 Telegram bot: @moestudentbot

#ምደባ የተመደባችሁበትን ተቋም ለማየት የቀረቡ አማራጮች Website: https://result.ethernet.edu.et SMS: 9444 Telegram bot: @moestudentbot ከምደባ ጋር ተያይዞ ላላችሁ ማንኛውም ጥያቄ result.ethernet.edu.et ላይ በመግባት Complaint የሚለውን በመጫን ጥያቄዎቻችሁን ማቅረብ የምትችሉ መሆኑን እየገለጽን ምንም አይነት ጥያቄም ሆነ ማመልከቻ በአካል የማንቀበል መሆኑን እናሳውቃለን። 🎖📖🎖 @aplusacademyy @aplusacademyy ▬▬▬▬▬▬▬▬

📌📌ማስታወቂያ ‼️ ለ 29,909 ተማሪዎች የዩኒቨርስቲ ምደባ ዛሬ ይፋ ይሆናል። ስለዚህ ያለፋችሁ ተማሪዎች ምድባችሁ ስለቀቅ በ Website ገብታችሁ ማየት ትችላላችሁ። የ 100ሺ ተማሪዎች ምልመላ ወይም የመቁረጫ ነጥብ #ነገ ይነገራል። በዚሁም የ #College መግቢያ ውጤትም ይነገራል። (College የምትገቡት ግን የማካካሻ ትምህርት ለመማር ነው።) 🎖📖🎖 @aplusacademyy @aplusacademyy ▬▬▬▬▬▬▬▬

#ትምህርት_ሚኒስቴር የትምህርት ሚኒስቴር የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ወስደው ውጤታቸው ከግማሽ በታች የሆኑትን በቅድመ መደበኛ ዩኒቨርሲቲ ትምህርት ጉድለታቸውን እንዲሞሉ ኮርስ ይወስዳሉ ብሏል። የትምህርት ሚኒስቴር ዴኤታው ዶ/ር ሳሙኤል ክፍሌ ለኤፍ ቢ ሲ በሰጡት ቃል ፤ " እነኚህ ተማሪዎች ያለባቸውን ጉድለት የሚሞላው የሬሜዲያል ፕሮግራም ይከታተላሉ፤  ያ ማለት በ2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የተማሯቸውን ከሞላ ጎደል እነኚህን ኮርሶችን እንዲማሩ እናደርጋለን " ብለዋል። " ዋና ዋና ይዘቶች እና መታወቅ ያለባቸውን እስከ አራት ወር ወስደን ከየካቲት 15 እስከ ሰኔ መጫረሻ አካባቢ እነኚህን ትምህርቶችን እንዲማሩና እንዲከልሱ እናደርጋለን " ሲሉ ዶ/ር ሳሙኤል ተናግረዋል። ዶ/ር ሳሙኤል ክፍሌ ፤ " ተማሪዎች ተከታታይ ምዘና ይመዘኑና ከመቶ ይያዝላቸዋል ፤ እሱን ወደ 30% ቀይረን ከማዕከል ተመሳሳይ ፈተና በግል ተቋማትም ዕጩ ለሆኖ ፍሬሽ ተማሪዎች በመንግስት ተቋማት ላሉ እጩ ፍሬሽ ማን ተማሪዎች ተመሳሳይ ፈተና እንሰጣለን። ይሄንን አድርገን 50 % እና ከዛ በላይ ያመጡትን ወደ መደበኛ ፌሽ ማን ፕሮግራም እንዲገቡ ይደረጋል። መደበኛ ፍሬሽማን ፕሮግራም ተከታትለው የዩኒቨርሲቲ ተማሪ ይሆናሉ " ብለዋል። ተማሪዎች የሚማሩት በ2ኛ ደረጃ ትምህርት ላይ ያሳዩት ጉድለት ሲሆን ፦ - ቋንቋ፣ -  ሂሳብ፣ - የተፈጥሮ ሳይንስ (ኬሚስትሪ፣ ባዮሎጂ፣ ፊዚክስ) አስፈላጊ ከሆነ ዩኒቨርሲቲዎች ተጨማሪ ይዘት ይጨምሩላዋል ተብሏል። በማህበራዊ ሳይንስ ደግሞ ፦ - ጂዮግራፊ፣ - ታሪክ፣ - ቋንቋ እና ሂሳብ የሚማሩ ሲሆን ዩኒቨርሲቲዎች እንደፍላጎታቸው ተጨማሪ ይዘት ሊጨምሩላቸው እንደሚችሉ ተገልጿል። መንግስት ለ100 ሺህ ተማሪዎች የቅድመ ፍሬሽማን ኮርስ እድል የሚያማቻች ሲሆን ለዚህም ቁርጥ ያለ ነጥብ እንደሚያስቀምጥ ይጠበቃል በራሳቸው ወጪ ሸፍነው ኮርስ ለሚወስዱ መንግስት ዝቅተኛ የመቁረጫ ነጥብ እንደሚያስቀምጥ ተነግሯል። ዶ/ር ሳሙኤል ክፍሌ ፦ " ወጪውን ችሎ ወደ መንግስት ተቋማት የሚሄደው የግል ውሳኔ ስለሆነ አነስተኛውን መቁረጫ ነጥብ ብቻ መንገር ነው የኛ ኃላፊነት። በመንግስት የሚሄደውን መለየት ስላለብን በዝርዝር ለሴቶች፣ ለወንዶች፣ ለተፈጥሮ ሳይንስ ፣ ለማህበራዊ ሳይንስ ፣ አካል ጉዳት ላለባቸው፣ ከታዳጊ ክልል ለመጡ፣ ለአርብቶ አደር አካባቢዎች በዝርዝር ማስቀመጥ ስላለብን 100 ሺ ለመቀበል ስንት ተማሪ ምንያክል መቁረጫ ነጥብ አድርገን ነው የምናገኘው የሚለው የመንግስት ውሳኔ ነው የሚሆነው። እኚህ መንግስት ወጪያቸውን ችሎ፣ ዶርም አስገብቶ፣ አብልቶ ፣ አስተኝቶ ሬሚዲያል ፕሮግራም ለሚሰጣቸው ነው። በራስ ለሚወሰን አነስተኛውን ነው መንገር ያለብን በራስ ውሳኔ የሚለው የግድ ወደ ግል ተቋማት ይሄዳሉ ማለት አይደለም በመንግስት ተቋማትም ሊማሩ ይችላሉ ወጪያቸውን ሸፍነው " ብለዋል። ይኸው እድል ለአንድ አመት ብቻ እንደሆነ ተገልጿል። በ2014 ዓ/ም ፈተና ያለፉ #ተማሪዎችን_ምደባ እስከ #እሁድ ለማሳወቅ ፤ የቅድመ ፍሬሽማን ተማሪዎችን መቀበያ ነጥብ እስከ #ሰኞ ይፋ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ትምህርት ሚኒስቴር ለፋና ብሮድካስት ኮርፖሬት ተናግሯል።

# ማስታወቂያ በ 2014 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ አገር አቀፍ ፈተና ወስዳችሁ 50 ከመቶ እና ከዚያ በላይ ያመጣችሁ እና በመንግስት ተቋማት ገብታችሁ መማር የምትፈልጉ ተማሪዎች የተቋም ምርጫችሁን  በየትምህርት ቤታችሁ በተወከሉ መምህራን በኩል እስከ የካቲት 02/2015 ዓ.ም ድረስ #ማስተካከል የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን። ማሳሰቢያ:- በ 2015 የትምህርት ዘመን በልዩ ሁኔታ በአዳማ እና አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዪኒቨርሲቲዎች መማር የምትፈልጉ የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች የመግቢያ ፈተና የማይሰጥ መሆኑን አውቃችሁ መርጣችሁ መመደብ የምትችሉ  መሆኑን እንገልጻለን። በምደባ ወቅት አዎንታዊ ድጋፍ የምትሹ (ተመሳሳይ ጾታ ያላችሁ መንትያዎች፣ እመጫቶች(በቅርቡ የወለዳችሁ እናቶች) ፣ ነፍሰጡር ተማሪዎች፣ በመንግስት ሆስፒታሎች ህክምና ቦርድ የተረጋገጠ ልዩ ክትትል የሚሻ ህመም ታማሚዎች … ወዘተ)  ተማሪዎች ማመልከቻችሁን እና ደጋፊ ሰነዶቻችሁን  በቀጣዩ ሊንክ  https://student.ethernet.edu.et በኩል ብቻ እንድትልኩ እየገለጽን ምንም አይነት ማመልከቻ በአካል የማንቀበል መሆኑን እናሳውቃለን። 🎖📖🎖 @aplusacademyy @aplusacademyy ▬▬▬▬▬▬▬▬

የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚንስቴር ዴኤታው ዶክተር ሳምኡል ክፍሌ ከፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ጋር በነበራቸው ቆይታ ከተናገሩት የተወሰደ 👇 ፨ከ50% በላይ ያመጡ ተማሪዎች በሙሉ በባቻቸው ፍ
የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚንስቴር ዴኤታው ዶክተር ሳምኡል ክፍሌ ከፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ጋር በነበራቸው ቆይታ ከተናገሩት የተወሰደ 👇 ፨ከ50% በላይ ያመጡ ተማሪዎች በሙሉ በባቻቸው ፍሬሽማን ኮርስ ይጀምራል። ፨ከ50% በታች ያመጡ ተማሪዎች ሶስት አማራጭ አላቸው 1) *መንግስት የሚሰጠውን ሁለተኛ ዕድል በመጠቀም የማካካሻ ትምህርት መውሰድ እና አንድ ባች ዝቅ ብሎ ፍሬሽማን መጀመር።(መቁረጫ ነጥብ ለሚያሟሉ) *ከመንግስት ዩንቨርሲቲ ውጭ በግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የማካካሻ ትምህርት ተምረው በድጋሚ የወደቁባቸውን ትምህርት በመከታተል ቀጣይ ዓመት በግል ፍሬሽማን ኮርስ መጀመር 2) ከቀጣይ ተፈታኞች ጋር በግል ድጋሚ መፈተን 3)ቴክኒክና ሙያ መሰልጠን በመንግስት ስፖንሰርነት ማካካሻ የሚወስዱ የ#100ሺህ ተማሪዎች የመቁረጫ ነጥብ ከ10-15 ቀን ጊዜ ውስጥ ይፋ ይደረጋል። ━━━━━━━━━━━━━━━━━━━ #Share #Share #Share https://t.me/+yq35UmSRvF42MjA0 https://t.me/+yq35UmSRvF42MjA0 ━━━━━━━━━━━━━━━━━━━

#ተጨማሪ_ማብራሪያ ‼️ 29,909 ተማሪዎች ምደባ ተደርጎላቸው ቀጣይ ወደ ዩኒቨርስቲ ገብተው Freshman ይማራሉ። ከዚሁ ውስጥ Astu, Aastu እና Phaulos መወዳደር የፈለጉም ተወዳድረው ይገባሉ። 100ሺ ተማሪዎችም ተመልምለው ዩኒቨርስቲ ገብተው የማካካሻ ትምህርት ይወስዳሉ። የማካካሻ ትምህርቱ በወደቁበት/በደከሙበት / Subject ብቻ ይሆናል። ከዛም ፈተና ወስደው ካለፉ እዛው ዩኒቨርስቲ ቀጣይ አመት Freshman ይጀምራሉ። College ትምህርት ዘንድሮ የለም። ነገር ግን በግል ኮሌጅ ገብቼ የማካካሻ ትምህርት እማራለሁ የሚሉ ካሉም ትምህርት ሚኒስቴር ፈቅዷል። ስለዚህ የ College መግቢያ ቀጣይ ይነገራል። ሌላው ደግሞ ቴክኒክ እና ሙያ መማር ነው።  ይሄንን የማይፈልግ ደግሞ ከ 2015 ተፈታኞች ጋር በ Private መፈተን ይችላል ። https://t.me/+yq35UmSRvF42MjA0 https://t.me/+yq35UmSRvF42MjA0

🎤በአማራ ክልላዊ መንግስት የደሴ ከተማ ልዩ አዳሪ ት/ቤት ተማሪ የሆነውና በሀገር አቀፍ ደረጃ ከፍተኛውን ውጤት ማለትም #666/700 ያስመዘገበው ተማሪ ሚኪያስ አዳነ ከፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ጋር ያደረገው የስልክ ቃለምልልስ https://t.me/+yq35UmSRvF42MjA0 https://t.me/+yq35UmSRvF42MjA0

ምን ያህል ተማሪዎች በማጠናከሪያ ፕሮግራም ወደ ዩኒቨርሲቲ ይገባሉ? በ2014 የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከወሰዱ 896,520 ተማሪዎች መካከል 29,909 ተማሪዎች ብቻ በቀጥታ ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት እንደሚገቡ የትምህርት ሚኒስቴር መግለጹ ይታወቃል። የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ውጤት ያላስመዘገቡና የተሻለ ውጤት ካመጡ ተማሪዎች መካከል 100 ሺህ የሚሆኑት ተማሪዎች በደከሙባቸው የትምህርት አይነቶች በልዩ ክትትል እንዲማሩ ከተደረገ በኋላ ድጋሜ እንዲፈተኑ በማድረግ ሁለተኛ ዙር ዕድል እንደሚሰጣቸው የትምህርት ሚኒስቴር ገልጿል፡፡ ይህም እንደ ዩኒቨርሲቲዎቹ የመቀበለ አቅምና የተማሪዎቹን ውጤት መሠረት አድርጎ በሚፈጸም የምልመላ መስፈርት የሚከናወን ነው። ውጤት ያላመጡ ተማሪዎቹ በደከሙባቸው የትምህርት ዓይነቶች የማጠናከሪያ ድጋፍ ተደርጎላቸው በድጋሜ ፈተና እንዲወስዱ ተደርጎ የሚያልፉ ብቻ የዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸውን እንዲቀጥሉ ይደረጋል፡፡ በፈተናው ወቅት ለሴቶች እና በተለያዩ ችግሮች ውስጥ ለሚገኙ ተማሪዎች የመግቢያ ነጥብ ላይ áŠĽáŒˆá‹› ይደረግላቸዋል ተብሏል፡፡ 

photo content

ከ50 በመቶ በታች ያመጡ ተማሪዎች ወደ ዩኒቨርሲቲ እንደማይቀላቀሉ የተገለጸ ሲሆን ነገር ግን የዩኒቨርሲቲዎችን የመቀበል አቅም ከግምት ውስጥ በማስገባት በውጤታቸው መሰረት ተጨማሪ ተማሪዎችን በመቀበል
ከ50 በመቶ በታች ያመጡ ተማሪዎች ወደ ዩኒቨርሲቲ እንደማይቀላቀሉ የተገለጸ ሲሆን ነገር ግን የዩኒቨርሲቲዎችን የመቀበል አቅም ከግምት ውስጥ በማስገባት በውጤታቸው መሰረት ተጨማሪ ተማሪዎችን በመቀበል ለቀጣይ ዓመት ዩኒቨርሲቲ መግባት የሚያስችላቸውን ውጤት እንዲያገኙ ይሰራል ተብሏል። እስከ 100 ሺሕ የሚደርሱ ከ50 ከመቶ በታች ያስመዘገቡ ተማሪዎች፣ በውጤት ተለይተው ማካካሻ ትምህርት ወስደው በቀጣይ ዓመት የፈተና ዕድል ያገኛሉ ተብሏል። ማካካሻውን የሚወሰዱ ተማሪዎች ዩኒቨርስቲ ገብተው ማካካሻውን ከወሰዱ በኋላ ማለፊያ ውጤት ካስመገቡ በዚያው የዩኒቨርስቲ ትምህርታቸውን እንደሚቀጥሉም ተገልጿል። ፨ለጥቆማ 👇 @atc_newsbot 🔔ቻናላችንን ይቀላቀሉ👇 @atc_news @atc_news @atc_news @atc_news

ትምህርት ሚኒስቴር ፦ - በሀገር ደረጃ የተመዘገበው ከፍተኛ ውጤት በተፈጥሮ ሳይንስ ከ700 ፤ 666 ሲሆን በማህበራዊ ሳንይንስ ከ600 ፤ 524 ሆኖ ተመዝግቧል። - በፆታ በተፈጥሮ ሳይንስ ከ700 ፤ ወንድ 666 ሴት 650  ፤ በማህበራዊ ሳይንስ ከ600 ወንድ 516 ፤ ሴት  524 - በአጠቃላይ ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገቡ በማህበራዊ ሳይንስ ከ500 እና በላይ ያስመዘገቡ 10 ተማሪዎች፤ - በአጠቃላይ በተፈጥሮ ሳይንስ ከ600 እና በላይ ያስመዘገቡ 263 ተማሪዎች ናቸው።

የትምህርት ሚኒስትሩ ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ በሰጡት መግለጫ ምን ምን ጉዳዮችን አነሱ ? - በ2014 የትምህርት ዘመን ለፈተና የተመዘገቡ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች በጠቅላላ 985 ሺህ 354 ተማሪዎች ሲሆኑ ለፈተና የቀረቡት 92 ነጥብ 2 % 908 ሺህ 256 ተማሪዎቹ ሲሆኑ 77 ሺህ 98 ተማሪዎች ፈተና አልወሰዱም። - በደንብ  ጥሰት ፣ለመኮራረጅ በመፈለግ እና በሌሎች ምክንያቶች 50 ሺህ 170 ተማሪዎች ሳይፈተኑ ቀርተዋል። - በ2014 የትምህርት ዘመን 899 ሺህ 520 ተማሪዎች ተፈትነዋል ። - በፆታ ማዕከልነት የአማካይ ውጤት በወንዶች 30 ነጥብ 2 እንዲሁም ሴቶች 28 ነጥብ 09 % አማካይ ውጤት አስመዝግበዋል። - በትምህርት ዘርፍ የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች ከማህበራዊ ሳይንስ በተሻለ ውጤት ያስመዘገቡ ሲሆን  የተፈጥሮ ሳይንስ 31 ነጥብ 63 ከመቶ እንዲሁም የማህበራዊ ሳይንስ 27 ነጥብ 79 ከመቶ በአማካኝ አስመዝግበዋል። - በክልል ደረጃ ይህየ ነው የሚባል የውጤት ልዩነት የሌለ ሲሆን አዲስ አበባ ፣ ሐረሪ እና ድሬደዋ የተሻለ ውጤት አስመዝግበዋል። - ከተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች ወንድ ከ 700፤  666 ያስመዘገበ ሲሆን 650 ሴት ተማሪ አስመዝግባለች ። - በማህበራዊ ሳይንስ ከ600 ወንድ 524 አስመዝግቧል። - ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎች በትምህርት ሚኒስቴር እውቅና እና ሽልማት ይሰጣቸዋል።

#Update የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተናን ከ50 % በላይ ያመጡት ከተፈታኞች ውስጥ 3.3 በመቶ መሆናቸውን ትምህርት ሚኒስቴር አስታውቋል። ፈተናውን በትክክል ከወሰዱት 896,520 ተማሪዎች ውስጥ ከግማሽ በላይ ያመጡት፤ 29,909 መሆኑን ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ተናግረዋል። ሚኒስትሩ ይህን ያሉት በትላንትናው ዕለት ይፋ የተደረገውን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ውጤትን አስመልክቶ ዛሬ በሰጡት መግለጫ ላይ መሆኑን ኢትዮጵያ ኢንሳይደር ዘግቧል።

#Update " ብዙም አይርቅም " የትምህርት ሚኒስቴር በ12ኛ ክፍል የብሔራዊ ፈተና ውጤት ዙሪያ ዛሬ መግለጫ ይሰጣል። የ2014 ዓ.ም 12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ውጤት ትላንት ለሊት ይፋ መደረጉ ይታወቃል። ከውጤቱ ጋር በተያያዘ አጠቃላይ መግለጫ ዛሬ ከሰዓት 8:00 በትምህርት ሚኒስትሩ ብርሀኑ ነጋ (ፕ/ር) እንደሚሰጥ ቲክቫህ ኢትዮጵያ አረጋግጧል። " የመልቀቂያ ፈተና ከወሰዱ ተማሪዎች መካከል ውጤታቸው ከ50 በመቶ በላይ የሆኑ ተማሪዎች ከ28 ሺህ እንደማይበልጥ" በተለያዩ የመገናኛ ብዙሃን እየተዘገበ ይገኛል ፤ ይህን በተመለከተ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ለአንድ የትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራር ጥያቄ አቅርቦ ነበር። ከ50 በመቶ በላይ ያመጡ ተማሪዎች አሐዝ ከ28 ሺህ " #ብዙም_እንደማይርቅ " ቲክቫህ ከትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራር አረጋግጧል። እስካሁን የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የመግቢያ መቁረጫ ነጥብ ይፋ ያልተደረገ መሆኑ ይታወቃል።

8:00 መግለጫ ይሰጣል‼️ የ2014 ዓ.ም 12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ውጤት ትላንት ለሊት ይፋ መደረጉ ይታወቃል። ከውጤቱ ጋር በተያያዘ አጠቃላይ መግለጫ ዛሬ ከሰዓት 8:00 በትምህርት ሚኒስትሩ ብርሀኑ ነጋ (ፕ/ር) እንደሚሰጥ ቲክቫህ አረጋግጧል። የቻናላችን ሊንክ👇 #Share #Share #Share https://t.me/+yq35UmSRvF42MjA0 https://t.me/+yq35UmSRvF42MjA0

ኮኔክሽን አልሰራ ያላቹህ ይህን VPN አውርዳቹህ ሞክሩት። ይሰራል👍 #Share #Share #Share https://t.me/+yq35UmSRvF42MjA0 https://t.me/+yq35UmSRvF42MjA0

ልድገምላችሁ🫶 • ማንኛውም ቅሬታ ያላቸው ተፈታኞች በአካል መምጣት ሳያስፈልግ እስከ ጥር 26/2015 ዓ.ም ድረስ በትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ዌብ ሳይት https://eaes.edu.et/ ላይ Compliant የሚለውን ማስፈንጠሪያ በመጫን ማቅረብ ይችላሉ፡፡ https://t.me/+yq35UmSRvF42MjA0 https://t.me/+yq35UmSRvF42MjA0