Hawaasi Quchumi Gashshooti Rosu Biddishsha/ሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ትምህርት መምሪያ/Hawassa City Administration Education Department
Open in Telegram
5 669
Subscribers
-124 hours
-17 days
+3630 days
Posts Archive
የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር የ2019 ዓ.ም የመንግስት ትምህርት ቤቶች የተማሪ ምዝገባ አጀማመር ግምገማ አደረገ።
የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ትምህርት መምሪያ የ2019 ዓ.ም የተማሪዎች ምዝገባ በተያዘለት ጊዜ ገደብ ለማጠናቀቅ የመጀመሪያ ቀን የምዝገባ አጀማመር እና ምዝገባውን በበይነ መረብ ከማከናወን አንጻር የሚያጋጥመውን የክህሎት ክፍተት መሙላት የሚያስችን ስልጠና ሰጥቷል፡፡
በውይይቱ መድረክ የትምህርት መምሪያ ኃላፊ ዶ/ር ብርሃኑ ደሳለኝ የተገኙ ሲሆን ኃላፊውም በመልዕክታቸው የተማሪ ምዝገባ በወቅቱ አለማጠናቀቅ ለትምህርት ብክነት የሚዳርግ በመሆኑ ሁሉም ትምህርት ቤቶች ምዝገባውን በተያዘው ጊዜ ውስጥ በማጠናቀቅ የመማር ማስተማር ስራ በካላንደሩ መሰረት ለመጀመር መዘጋጀት እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡
የ6ኛ፣8ኛ እና 12ኛ ክፍል ለሚያስፈትኑ ትምህርት ቤቶች ክልል አቀፍ ሞዴል ፈተናን አስመልክቶ ኦሬንተሽን ተሰጠ።
ሐዋሳ ከተማ አስተዳደር ትም/መምሪያ
ሚያዝያ 28/2018
********
በ2018 ዓ.ም በሐዋሳ ከተማ አስተዳደር ስር ለሚገኙ የ6ኛ፣ 8ኛና 12ኛ ክፍል አስፈታኝ የመንግስትና የግል/መያድ ትምህርት ቤቶች ከግንቦት 5-7/2018 ዓ.ም ለሚሰጠው ክልል አቀፍ ሞዴል ፈተና የቅድመ ዝግጅት ስራው ተጠናቆ በዛሬው ዕለት የመንግስትና የግል/መያድ ትምህርት ቤቶች ርዕሰ መምህራን፣ ሱፐርቫይዘሮች እንዲሁም የትምህርት መምሪያ ማኔጅመንትን በተገኙበት የፈተና ማስፈጸሚያ ዕቅድ ቀርቦ ውይይት የተደረገ ሲሆን ትምህርት ቤቶችም በተቀመጠው አቅጣጫ መሰረት በጥብቅ ዲሲፕሊን እንዲያስፈጽሙ አቅጣጫ ተቀምጧል።
ከመድረኩ እንደተገለፀው የዚህ ፈተና ዋና ዓላማ ተማሪዎች ለዋናው ፈተና በአእምሮና በስነልቦና በቂ ዝግጅት ለማድረግ እገዛ የሚያደርግ በመሆኑ ትኩረት ሊሰጡትና መምህራንም ከሞዴል ፈተናው በኋላ ከተማሪዎች ውጤት መነሻ ጥያቄዎችን በመስራት ተማሪዎችን ሊደግፋ እንደሚገባ በውይይቱ የተገለጸ ሲሆን ተማሪዎችም ይህንን ከግንዛቤ በማስገባት አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት ሊያደርጉ እንደሚገባና ለዚህ ተግባር የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ሁሉ አስፈላጊውን እገዛ እንዲያደርጉ በመግለጽና የጋራ መግባባት ላይ በመድረስ የዕለቱ ውይይት ተጠናቅቋል።
student_registration_template - Hawassa final.xlsx0.87 KB
For grade 6 and 8 registration
student_registration_template - sidama final.xlsx0.11 KB
For grade 6 and 8 registration
student_registration_template - program.xlsx0.12 KB
