EiABC ቤተ-መጽሐፍት
Closed channel
Show more
The country is not specifiedThe category is not specified
406
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
+730 days
Posts Archive
"ያለፉት ቁስሎች ልብህን የመራራነት ምንጭ እንዲያደርጉት ከቶ አትፍቀድ። ይቅር ለማለት ፈቃደኛ ሳትሆን ስትቀር፣ የደስታህን ቁልፍ በበደሉህ ሰዎች እጅ ላይ እየተውከው ነው።"
🌟ሊቁ አውግስጢኖስ
+1
ነሐሴ 24 በዚህች ቀን የአባታችን የአቡነ ተክለሃይማኖት ዕረፍት እና የቅድስት ክርስቶስ ሠምራ የዕረፍቷ መታሰቢያ ነው።
ተክለ ሃይማኖት ማለት በሃይማኖት መሬት ላይ የበቀለ ተራ ተክል ሳይሆን፣ ሥሩ በሐዋርያት መሠረት የተተከለ፣ ጫፉ በሥላሴ ዙፋን ፊት የደረሰ፣ ፍሬውም ለነፍሳት ድኅነት የሆነ የሕይወት ዛፍ ነው። እርሱ በምድር ሲመላለስ የሰማያውያንን ኑሮ የኖረ፣ በሥጋ ድካም ውስጥ ሳለ የመላእክትን ሱራፌላዊ ክንፍ የተጎናጸፈ፣ በጸሎቱ እሳትነት የዲያብሎስን ደጅ ያፈረሰ የብርሃን ሐዋርያ ነው።
በአንድ እግሩ ለሰባት ዓመታት ቆሞ ሲጸልይ ደሙ እንደ ማይ ሲፈስ፣ አጥንቱ እስኪሰበር እግሩ ተቆርጦ ሲወድቅ፤ ያ የተቆረጠ አካል የምድርን እርኩሰት ያደቀቀ፣ ያ የተቀደሰ ደም ደግሞ ሰማያዊውን ምሕረት ወደ ምድር ያወረደ ታላቅ የመስቀል አብነት ነበር። እርሱ እንደ ዮሐንስ መጥምቅ በበረሃ ፍጹም ምንኩስናን ያከናወነ፣ እንደ ብርሃነ ዓለም ጳውሎስ አሕዛብን ወደ እውነት የጠራ፣ እንደ ጴጥሮስ የሃይማኖት መሠረት ሆኖ የቆመ የእግዚአብሔር ታላቅ አገልጋይ ነው።
✍ዲያቆን ጐሥዓ ቶላ
🌟✨የእናታችን የቅድስት ክርስቶስ ሠምራ እና የአባታችን የአቡነ ተክለሃይማኖት በረከት፤ ምልጃ፣ ጸሎት ቃልኪዳናቸው ከሁላችን ጋር ይሁን፡፡✨🌟
“የምትበላውን ምግብ እንደምትመርጥ ሁሉ፣ የምትናገረውንም ቃል ምረጥ፤ መጥፎ ምግብ ሥጋን እንደሚመርዝ፣ መጥፎ ቃልም ነፍስን ይመርዛል።"
💫አባ ጴሜን
"ሰማይ ታላቅ ነው ቢሉ ከአንቺ ጋር አይስተካከልም፤ ሰማይና ምድርን የሞላው በማሕፀንሽ ሞልቶአልና። ሰዎች ከአንቺ ይልቅ ምድርን ታላቅ ናት ቢሉኝ ምድርማ የእግሩ መረገጫ ብቻ ናት እላቸዋለሁ።
የኖኅ መርከብ ነሽ ይሉሻል፤ የኖኅ መርከብ ግን ያዳነችው ኖኅንና ቤተሰቦቹን ነው። በአንቺ ግን ዓለም ዳነ። ታቦት ነሽ ይሉሻል ታቦቱ የያዘው በእግዚአብሔር ጣቶች የተጻፉ ሁለት ጽላትን ነበር። አንቺ ግን የዓለማትን ጌታ በኃይሉ ቃል ጸነስሽው!"
✨ቅዱስ ዲሜጥሮስ
☀️እኔን ያስደነቀኝ...
እመቤቴ ሆይ! እኔን ያስደነቀኝ ከሙታን መካከል ተለይተሽ መነሣትሽ አይደለም፤ ትንሣኤና ሕይወትን በመውለድሽ ነው እንጅ። ሞት በሠለጠነበት ማኅፀን የሕይወት መገኘት እንደምን ይደንቃል?
ድንግል ሆይ! ወደ ሰማይ ከመውጣትሽ ይልቅ የሰማይ ሁለተኛ ተብለሽ መጠራትሽ ይደንቀኛል። ማሕደረ መለኮት በመሆኑ ምድርን ሰማይ ሰማይን ምድር ያደረገ ሰውነትሽ በምድር ተወስኖ ሊኖር እንደምን ይቻላል?
እመብርሃን ሆይ! ልጅሽ የጽድቅ ብርሃን ነው አንች ደግሞ የብርሃኑ መገኛ የፀሐይ ክበብ ነሽ፤ የፀሐይ ክበብ ለጊዜው በተራሮች ራስ ቢጋረድ መልሶ ላይወጣ ኖሯልን? ያንችም ትንሣኤ እንደዚያ ነው።
ለጊዜው ሰውነትሽ በመቃብር ውስጥ አደረ ነገር ግን በምሽት የጠለቀችው ፀሐይ በማለዳ እንድትወጣ ያንችም ሰውነት ከመቃብር ወጣ።...
🌺ሊቀ ሊቃውንት ስምዓኮነ መልአክ!
"ከሐዋርያት ጋር ሆኜ የእመቤታችንን የዕረፍቷንና የክብሯን ነገር በተመለከትኩ ጊዜ፡ ከሰው ህሊና በላይ የሆነ ታላቅ የብርሃንና የመላእክት ምስጋና አየሁ። ሥጋዋም በክብር ወደ ሰማይ ተወሰደ።"
ምንጭ:-ቤተ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
🌺ቅዱስ ዲዮናስዮስ ዘአርዮስፋጎስ
🌼እንኳን ለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ዓመታዊ የትንሳኤና የዕርገት በዓል በሰላም አደረሳችሁ።🌼
"ቢያማችሁ፣ቢርባችሁ፣ቢጠማችሁ፣ብታጡ፣ ጓደኛ ቢያስቀይማችሁ፣ ሮጣችሁ መገኘት ያለባችሁ ከእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ(ቤተክርስቲያን) ነው። ቤተክርስቲያን የሰላም ሀገር ናት።አትባክኑ የትም ቦታ አትሂዱ ያጣችሁትን የምታገኙት ቤተክርስቲያን ውስጥ ነው።"
💫ርዕሰ ሊቃውንት የኔታ አባ ገብረ ኪዳን ግርማ
"እውነተኛ ወዳጅ በማዕበል ጊዜ መጠለያ፣ በጨለማ ወራትም ብርሃን ነው። ለወዳጅ ራስን መስጠት ጣፋጭ ነው፤ ለወዳጅህ ራስህን ስትሰጥ የክርስቶስን ፍቅር እያንጸባረቅክ ነውና። በፀሐይ ጊዜ ብቻ አብሮህ የሚሄድ ሳይሆን፣ ዝናብ ሲዘንብ በአጠገብህ የሚጸና ወዳጅን ፈልግ።"
አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ
ነሐሴ 7 ጽንሰታ ለእግዝትነ ማርያም
በዚህች ዕለት እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ተጸነሰች። የእመቤታችን ወላጆችዋ ኢያቄምና ሃና ይባላሉ። እነዚህ ቅዱሳን ኢያቄም እና ሃና በአንድነት ተጋብተው ሲኖሩ ልጅ አጡ፤ ከእለታት አንድ ቀን ወደ ቤተ እግዚአብሄር ሂደው ሲፀልዩ ሲያዝኑዋሉ፡፡ ሃዘናቸው እንዴትስ ነው ቢሉ፡- ኢያቄም:- "አቤቱ ጌታዬ ያባቶቼ የእስራኤል አምላክ እኔ ባርያህ እለምንሃለሁ አትጣለኝ አትናቀኝ ፀሎቴን ስማኝ ፈቃዴን ፈጽምልኝ፤ ለአይኔ ማረፊያ ለልቤ ተስፋ የሚሆን የተባረከ ወንድ ልጅ ስጠኝ" ብሎ ሲለምን ዋለ፤ ሃናም በበኩሏ "አቤቱ ጌታዬ የአባቶቼ የእስራኤል አምላክ እኔ ባርያህ እለምንሃለሁ ስማኝ ለአይኔ ማረፊያ ለልቤ ተስፋ የምትሆነኝ የተባረከች ሴት ልጅ የማህፀኔን ፍሬ ስጠኝ" ብላ ስትለምን ዋለች። እንዲህ ብለው ሲያዝኑ ሲጸልዩ ውለው ርግብ ከልጆቿ ጋር ስትጫወት አይታ ሃናም አቤቱ ጌታዬ ለዚች ግእዛን ለሌላት እንስሳ ልጅ የሰጠህ አምላክ ምነው ለኔ ልጅ ነሳኸኝ ብላ ምርር ብላ አለቀሰች፡፡ እንዲህ ብለው ሲያዝኑ ሲፀልዩ ውለው ከዘካርያስ ከሊቀ ካህናቱ ሄደው አቤቱ ጌታችን ሆይ ወንድ ልጅ ብንወልድ ተምሮ ቤተ እግዚአብሄርን አገልግሎ እንዲኖር እንሰጣለን፤ ሴት ልጅም ብንወልድ ማይ (ውሃ) ቀድታ መሶብ ወርቅ ሰፍታ መጋረጃ ፈትላ ካህናትን አገልግላ እንድትኖር እንሰጣለን ብለው ስዕለት ገቡ። ዘካርያስም እግዚአብሄር ጸሎታችሁን ይስማችሁ ስእለታችሁን ይቀበልላችሁ ጻህቀ ልቦናችሁን ይፈጽምላችሁ ብሎ አሳረገላቸው። ከዚያም በኋላ ቅድስት ሃና እና ቅዱስ እያቄም ዕለቱን ራእይ አይተው ነገር አግኝተው አደሩ፤ ራእዩም እንዴት ነው ቢሉ ኢያቄም "7ቱ ሰማያት እንደ መጋረጃ ተገልጠው ከላይኛው ሰማይ ነጭ ወፍ ወርዶ በራሴ ላይ ሲቀመጥ" አየሁ አላት፤ ሃናም እኔም አየሁ አለችው ምን አየሽ ቢላት "ነጭ ርግብ መጥታ በራሴ ላይ ወርዳ በጆሮዬ ገብታ በማህጸኔ ስትተኛ አየሁ" አለች። ይህንን ራእይ ያዩት ሐምሌ 30 ዕለት ነው፡፡ እነሱም እንዲህ ያለ ራዕይ ካየን ነገር ካገኘን ብለው ዕለቱን በሩካቤ ሥጋ አልተገናኙም፤ ፈቃደ እግዚአብሄር ቢሆን ብለው አዳምንና ሄዋንን ብዙ ተባዙ ምድርንም ምሉአት ብሎ ያበሰረ አምላክ ለኛስ ይልክልን የለምን? ብለው ዕለቱን አልጋ ምንጣፍ ለይተው እስከ 7ቀን ድረስ ለየብቻቸው ሰነበቱ፡፡ ነሃሴ በባተ በሰባተኛው ቀን ከሰው የበለጠች ከመላእክት የከበረች ደግ ፍጥረት ትወልዳላቹህና ዛሬ በሩካቤ ስጋ ተገናኙ ብሎአቹሃል ጌታ ብሎ መልአኩ ለሃና ነገራት በፈቃደ እግዚአብሄር በብስራተ መልአክ እመቤታችን እግዝእትነ ማርያም እሁድ እለት ነሐሴ 7 ቀን ተፀነሰች፡፡
ምልጃዋ በረከቷ በሁላችን ላይ ይደርብን፡፡
ምንጭ:-ቤተ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
“ወደ ቤተ ክርስቲያን መጥተህ እግዚአብሔርን ለአምላክነቱ እንደሚገባ አምልከህ ከዚያ በኋላ ወደ ሥራህ ብትሔድ የምትሠራው ሥራ የተባረከና የሰመረ እንደሚሆንልህ አታውቅምን?"
❄️ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
እመቤታችንን ንጽሕት፣ ጽንዕት፣ ክብርት፣ ልዩ ትባላለች። ይህም፡-
"ንጽሕት" ስንል፡-
ሌሎች ሰዎች (ቅዱሳን) ቢነጹ ከገቢር፣ ከነቢብ ኃጢአት ነው እንጂ ከኃልዮ ኃጢአት አይደለም፡፡ እርሷ ግን ከነቢብ፣ ከገቢር፣ ከኃልዮ ንጽሕት ናት፡፡ "ለመኑ ተውኅቦ ተደንግሎ ኅሊና ለመላእክትሂ ኢተክህሎሙ" ኃጢአትን ከማሰብ መጠበቅ ከሰው ልጆች ለማን ተሰጠው ይህስ ለመላእክትም አልተቻላቸውም" እንዲል፡፡ (ተአምረ ማርያም)
"ጽንዕት" ስንል:-
ሴቶች ቢጸኑ ለጊዜው ነው እንጂ በኋላ በጊዜው ተፈትሆ አለባቸው:: እመቤታችን ግን ቅድመ ጸኒስ ጊዜ ጸኒስ ድኅረ ጸኒስ ቅድመ ወሊድ ጊዜ ወሊድ ድኅረ ወሊድ ድንግል ናትና:: "ጽንዕት በድንግልና አልባቲ ሙስና" እንዳላት ቅዱስ ያሬድ "ወትረ ድንግል ማርያም" ማርያም ዘለዓለማዊት ድንግል ናት" እንዳለ፡፡ (መጽሐፈ ቅዳሴ)
"ክብርት" ስንል፡-
ሌሎች ሴቶች ቢከብሩ ጻድቃን ሰማዕታትን ነቢያት ሐዋርያትን ወልደው ነው እመቤታችንን ግን የምናከብራት "የአምላክ እናቱ" ብለን ነውና፡፡
"ልዩ" ስንል፡-
ከእርሷ በቀር እናት ሆና ድንግል እመቤት ሆና አገልጋይ የሆነች በድንግልና ወልዳ ወተትን (ሐሊበ ድንግልናዌን) ያስገኘች ሌላ ሴት የለችምና፡፡
በዚህም እመቤታችንን ንጽሕት፣ ጽንዕት፣ ክብርት፣ ልዩ እንላታለን፡፡
ምንጭ:-ቤተ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
"ከንስሐ አባትህ ጋር ስትሆን ጥያቄህን እንጂ ውሳኔህን አታቅርብላቸው፤ በልብህ ካሰብከው ጋር እንዲስማሙ ሳይሆን በሐሳብህ ላይ ሐሳባቸውንና ምክራቸውን እንዲሰጡህ አድርግ።"
💫ብፁዕ አቡነ ሺኖዳ ሣልሣዊ
ወደ ቤተ ክርስቲያን የምንመጣው ፍጹም ስለሆንን ሳይሆን ፍጹም ለመሆን ነው፤ ጤነኛ ስለሆንን ሳይሆን በኃጢአት የቆሰለውን ነፍሳችንን በእግዚአብሔር ቃልና በምስጢራት እንድንፈውስ ነው። ስለዚህ በደካሞች ወይም በኃጢአተኞች ላይ ከመፍረድ ይልቅ፥ ቤተ ክርስቲያን የሁሉም አባት የእግዚአብሔር የይቅርታ ደጅ መሆኗን አምነን በደስታ ልንመላለስባት ይገባል።
🌟ዲያቆን ጐሥዓ ቶላ
🌟✨ሐምሌ 21🌟✨
''አንዲህ በፍቅር ያዝሁሽ በጣቶቼ አይደለም።በሃይማኖት ያዝሁሽ በመዳሰስ አይደለም።በእደ ሕሊና ያዝሁሽ በእደ ሥጋ አይደለም።እደ ሕሊናዬን ግን የሰው ኃይለኝነት ሊያስተወው አይችልምና የሰይፍ ስለትም ሊቆርጠው አይችልምና።ልትደግፊኝ ያዝሁሽ ልትጥይኝ ግን አይደለም።ወደ ላይ ከፍ ከፍ ልታደርጊኝ ያዝሁሽ ወደ ታች ልታወርጂኝ ግን አይደለም።ለዘለዓለሙ ያዝሁሽ ለዕድሜ ልክ ብቻ አይደለም።እናቴ ሆይ ነፍሴ ባንቺ ዘንድ ትክበር ስለ ቸርነትሽም እመቤቴ ነሽ።ስለ ፍቅርሽ የታመንሽ ስለ ልጅሽም የመድኃኒት ቀንድ ሆይ አስቢኝ እንደወደቅሁም እቀር ዘንድ አትርሺኝ።ምንም እናት ልጇን ምንም የሆዷን ፍሬ ባታስብ አንቺ ግን አስቢኝ አትርሺኝ።በአፍሽ የተጠራሁ በፊትሽም የተቀረጽሁ ልሁን።''
ምንጭ:-አርጋኖን ዘሠሉስ(ማግሰኞ)
"ጌታ ሆይ እርሻውን አቃጥለህ ሰብሉን ብትባርክ ምን ይጠቅማል? ዛፉንስ ቆርጠህ ቅርንጫፉን ብትባርክ ምን ይረባል? እናቴ እርሻ ናት እኔ ሰብል ነኝ:: እናቴ ዛፍ ናት እኔ ቅርንጫፍ ነኝ:: እባክህን እናቴ ብትክድ እኔ ባምን ምን ይጠቅማል:: ጌታ ሆይ የእናቴን ልብ በሃይማኖት አጽናልኝ"
(ሕፃኑ ቅዱስ ቂርቆስ ስለ እናቱ ቅድስት ኢየሉጣ የጸለየው ጸሎት)
ቅዱስ ቂርቆስ ሆይ አንተ ሕፃን ሆነህ ትልቅ ነበርክ:: ትልቅ ሆነን ሕፃን የሆንን እኛን በምልጃህ አስበን!
"የእግዚአብሔር ምስክር የታመነ ነው፤ ሕፃናትን ጠቢባን ያደርጋል" መዝ 19፥7
ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
ምንጭ:-ቤተ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
🌹አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ - አርጋኖን🌹
"የምድር ኃጥአን ሁላችሁ ወደ ቅድስት ድንግል ኑ፡ በእርሷ ስጦታ ጻድቃን ትሆኑ ዘንድ፤ ልብሳችሁም ያደፈ ሁላችሁ ወደዚህች ቅድስት ምንጭ ኑ፡ የይቅርታ ዉሃ ወደ ምታፈስ፤ ልብሳችሁንም በልጇ ደም እጠቡ፡ ለሰማያዊ ሙሽርነት ዝግጁ ትሆኑ ዘንድ፡፡ ድውያነ ሥጋ ሁላችሁ ወደ ድንግል ኑ፡ በጸሎቷ ኃይል እንድትፈወሱ፡፡ የእውቀት ድሆች ሁላችሁ ኑ፡ የእውቀት ምንጭን ከእሷ ትቀዱ ዘንድ፡ ያማረ የተወደደውን የጥበብ ምክር ታገኙ ዘንድ”
"ንስሓ ማለት አንድን ምኞት በሌላ መለወጥ ነው። የኃጢአትንና ሥጋዊ ምኞትን ትቶ ከእግዚአብሔር ጋር ለመኖር መመኘት ነው!"
🌟ብፁዕ አቡነ ሽኖዳ ሣልሳዊ
🌾አባቶቻችን እንዲህ አሉ🌾 +
“ እኔ ክርስቲያን ነኝ፡፡ለሚጠይቁት እንደዚህ ብሎ የሚመልስ ሰው በአንድ ጊዜ በኹሉም ነገሮቹ ላይ ማወጁ ነው፡፡ ሀገሩ የት እንደ ኾነ፣ ሥራው ምን እንደ ኾነ፣ ቤተሰቡ እነማን እንደ ኾኑ መመስከሩ ነው፡፡ ክርስቲያን የሰማያዊት ኢየሩሳሌም ነዋሪ እንጂ በምድር ላይ ካሉት ከተሞች የአንዲቱም አይደለምና፡፡”
🌸ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
