ያሲን ኑሩ️️ YASIN NURU
የ ያሲን ኑሩ ሐዲሶች Yasin Nuru "ወደ መልካም ነገር ያመላከተ ሰው የሰራውን ሰው ያህል አጅር ያገኛል" ረሱል (ﷺ) "የበጎ ስራ ምላሹ በጎ እንጂ ሌላ አይደለም " የብናኝ ክብደት ያክልም መልካምን የሰራ ሰው ያገኘዋል :>> { አል -ዘልዘለህ 7} ለአስተያየት👇👇 @Hasabbbbot ሀዲሶችን ከፈለጋችሁ👇👇 @yasin_nuru_hadis
Show more25 971
Subscribers
+5924 hours
+2027 days
+48730 days
- Subscribers
- Post coverage
- ER - engagement ratio
Data loading in progress...
Subscriber growth rate
Data loading in progress...
«እነዚህን መሰል ሴቶች ለትዳር ከመምረጥ ተጠንቀቅ! ይህ የኢስላም ሳይሆን የኢንስታግራም ዲን ነው። ይህ ኒቃብ ሳይሆን ፋሽናዊ አለባበስ ነው። «ኪዩት ሙስሊም» ይባሉ ዘንድ ሂጃብን ሴክሹዋላይዝድ አድርገውታል።
ይህ ሐራም ነው ሒጃብ አይደለም ፣ወንድ ጋር መቀላቀል አለበት ወዘተ ስትላት ከራሷ ላይ ለመከላከል የማታመጣው ሎጅክ የለም።አንዷንም ማሳመን አትችልም።ፌሚኒዝምን በኢስላም ካባ ማራመድ የምትፈልግ ሆና እንጅ አታገኛትም!
ሸይጣን የፈበረከላቸው አንድ አባባል ደግሞ አለ «ኒቃብ ከምንም አያግድም!» ይሉሃል። ከምንም ላያግድማ አልተደነገገም።የአላህ ህግ አይደለም፡ የሰው ልጅ ህግ እንኳን ያለ አላማ አይደነገግም!
እግር ኳስ ላይ ተቀላቅላ በመዋኛ ገንዳ ውስጥ ተዘፍቃ ኒቃብ ከምንም አያግድም ትላሀለች።
እስኪ በአላህ!? ልብስ ውሃ ሲነካው ሰውነት ላይ ተለጥፎ መቀመጫና ታፋን እንደሚያሳይ ህፃን ልጅ ራሱ የሚስተው ሀቅ ነው ??! ደግሞ በቅርብ ርቀት ነን ሙስሊም ወጣቶች ያዩዋቸዋልኮ! እንደዚህም ሆኖ ኒቃብ ከምንም አያግድም ¡
ይሄንንም ኢስላማዊ ዳሌ ይሉት ይሆናልኮ! ያችኛዋ በታይት ዳሌዋን አሳየች ይችኛዋ በኒቃብ አሳየችው ታዳ ልዩነቱ ምንድን ነው? የልብሱ ድንጋጌ ስም ብቻ ይመስሏችኋል?
እነዚህን አምሳያዎች ካገባህ ቤትህ ውስጥ አቂዳና አኽላቅ እንደሌለ እወቅ ሂጃብ በሚመስል ልብስ ፌሚኒዝም ተጠቅልሎ ቤትህ እንደገባ እወቀው!
አላህ ሀቅና ባጢልን ከለየ በኋላ ምርጫውን ለህሊና ነው የሰጠው። ሂጃብ በእይታ እንኳን ትክክልና ሀሰት መሆኑን ህሊና ይፈርዳል!
ከዚህ ሁሉ በኋላ ትመጣና ፦ አንተ ለምን ታያለህ? አይንህን አትሰብርም?» ትልሀለች ።
ወላሂ በይ? ፎቶ አንስተች የለቀቅሽው እኛ አይናችንን አጨፍነን ስክሮል እንድናደርገው ነው?
ጉዳዩ ወዲህ ነው ፦ ስሜታዊ ዝንባሌን ሸይጣን በዲን ስም ከሽኖ ሲያቀርበው ነው!ውሃና ጥመት ሲወስድ እያሳሳቀ ነው።»
ኢስማዒል ኑሩ
@yasin_nuru @yasin_nuru
👍 33❤ 21👏 3👌 3👎 1🤔 1😭 1
#የ25ቱ_ነቢያት_ስም_ከነአመጣጡ_እና_ሀገራቸውን !!!
👉ካነበባችሁ በኋላ ለሌሎች ማስተላለፍ አትርሱ👈
#1=አደም(ዐለይሂ ሰላም)፡- ይህ ስም በቅዱስ ቁርኣን ውስጥ በ9 ሱራዎች በ25 አንቀጾች ውስጥ 25 ጊዜ ተጠቅሷል፡፡
#2=ኢድሪስ(ዐለይሂ ሰላም)፡- ይህ ስም በቅዱስ ቁርኣን ውስጥ በ2 ሱራዎች በ2 አንቀጾች ውስጥ 2 ጊዜ ተጠቅሷል፡፡
#3=ኑሕ(ዐለይሂ ሰላም)፡- ይህ ስም በቅዱስ ቁርኣን ውስጥ በ30 ሱራዎች በ50 አንቀጾች ውስጥ 50 ጊዜ ተጠቅሷል፡፡
#4=ኢብራሒም(ዐለይሂ ሰላም)፡- ይህ ስም በቅዱስ ቁርኣን ውስጥ በ25 ሱራዎች በ63 አንቀጾች ውስጥ 69 ጊዜ ተጠቅሷል፡፡
#5=ሉጥ(ዐለይሂ ሰላም)፡- ይህ ስም በቅዱስ ቁርኣን ውስጥ በ14 ሱራዎች በ27 አንቀጾች ውስጥ 27 ጊዜ ተጠቅሷል፡፡
#6=ኢስማዒል(ዐለይሂ ሰላም)፡- ይህ ስም በቅዱስ ቁርኣን ውስጥ በ8 ሱራዎች በ12 አንቀጾች ውስጥ 12 ጊዜ ተጠቅሷል፡፡
#7=ኢስሐቅ(ዐለይሂ ሰላም)፡- ይህ ስም በቅዱስ ቁርኣን ውስጥ በ12 ሱራዎች በ16 አንቀጾች ውስጥ 17 ጊዜ ተጠቅሷል፡፡
#8=የዕቁብ(ዐለይሂ ሰላም)፡- ይህ ስም በቅዱስ ቁርኣን ውስጥ በ10 ሱራዎች በ10 አንቀጾች ውስጥ 16 ጊዜ ተጠቅሷል፡፡
#9=ሁድ(ዐለይሂ ሰላም)፡- ይህ ስም በቅዱስ ቁርኣን ውስጥ 3 ሱራዎች በ7 አንቀጾች ውስጥ 7 ጊዜ ተጠቅሷል፡፡
#10=ሷሊሕ(ዐለይሂ ሰላም)፡- ይህ ስም በቅዱስ ቁርኣን ውስጥ በ9 ሱራዎች በ25 አንቀጾች ውስጥ ለ 25 ጊዜ ተጠቅሷል፡፡
#11=ሹዐይብ(ዐለይሂ ሰላም)፡- ይህ ስም በቅዱስ ቁርኣን ውስጥ በ4 ሱራዎች በ10 አንቀጾች ውስጥ 11 ጊዜ ተጠቅሷል፡፡
#12=ሙሳ(ዐለይሂ ሰላም)፡- ይህ ስም በቅዱስ ቁርኣን ውስጥ በ34 ሱራዎች በ131 አንቀጾች ውስጥ 136 ጊዜ ተጠቅሷል፡፡
#13=ሀሩን(ዐለይሂ ሰላም)፡- ስም በቅዱስ ቁርኣን ውስጥ በ13 ሱራዎች በ20 አንቀጾች ውስጥ ለ 20 ጊዜ ተጠቅሷል፡፡
#14=ዳዉድ(ዐለይሂ ሰላም)፡- ይህ ስም በቅዱስ ቁርአን ውስጥ በ9 ሱራዎች 16 አንቀጾች ውስጥ ለ 16 ጊዜ ተጠቅሷል፡፡
#15=ሱለይማን(ዐለይሂ ሰላም)፡- ይህ ስም በቅዱስ ቁርኣን ውስጥ በ7 ሱራዎች 16 አንቀጾች ውስጥ ለ 17 ጊዜ ተጠቅሷል፡፡
#16=ኢልያስ(ዐለይሂ ሰላም)፡- ይህ ስም በቅዱስ ቁርኣን ውስጥ 1 ሱራ በ2 አንቀጾች ውስጥ ለ 2 ጊዜ ተጠቅሷል፡፡
#17=አዩብ( ሰላም)፡- ይህ ስም በቅዱስ ቁርኣን ውስጥ በ4 ሱራዎች በ4 አንቀጾች ውስጥ ለ 4 ጊዜ ተጠቅሷል፡፡
#18=ዩኑስ(ዐለይሂ ሰላም)፡- ስም በቅዱስ ቁርኣን ውስጥ በ4 ሱራዎች በ4 አንቀጾች ውስጥ ለ 4 ጊዜ ተጠቅሷል፡፡
#19=ዩሱፍ(ዐለይሂ ሰላም)፡- ይህይህ ስም በቅዱስ ቁርኣን ውስጥ 3 ሱራዎች በ26 አንቀጾች ውስጥ ለ 27 ጊዜ ተጠቅሷል፡፡
#20=በአል-የሰዕ(ዐለይሂ )፡- ይህ ስም በቅዱስ ቁርኣን ውስጥ በ2 ሱራዎች በ2 አንቀጾች ውስጥ ለ 2 ጊዜ ተጠቅሷል፡፡
#21=ዙል-ኪፍል(ዐለይሂ ሰላም)፡- ይህ በቅዱስ ቁርኣን ውስጥ በ2 ሱራዎች በ2 አንቀጾች ውስጥ ለ ስም2 ጊዜ ተጠቅሷል፡፡
#22=ዘከሪያ(ዐለይሂ ሰላም)፡- ይህ ስም በቅዱስ ቁርኣን ውስጥ በ4 ሱራዎች በ6 ውስጥ ለ 7 ጊዜ ተጠቅሷል፡፡
#23=የሕያ(ዐለይሂ ሰላም)፡- አንቀጾችይህ ስም በቅዱስ ቁርኣን ውስጥ በ4 ሱራዎች በ5 አንቀጾች ውስጥ ለ 5 ጊዜ ተጠቅሷል፡፡
#24=ዒሳ(ዐለይሂ ሰላም)፡- ይህ ስም በቅዱስ ቁርኣን ውስጥ በ11 ሱራዎች በ25 አንቀጾች ውስጥ ለ 25 ጊዜ ተጠቅሷል፡፡
#25=ሙሐመድ(ዐለይሂ ሶላቱ ወስ-ሰላም)፡- ይህ ስም በቅዱስ ቁርኣን ውስጥ በ4 ሱራዎች በ4 አንቀጾች ውስጥ ለ 4 ጊዜ ተጠቅሷል፡፡
⬇➡➡~የነቢያቶች ሀገር 👇👇
1.. አደም (ዐ.ሰ) = ስሪላንካ (Sirilanka)
2.. ኑህ (ዐ.ሰ) = ጆርዳን (Jordan)
3.. ሹዓይብ (ዐ.ሰ) = ሶሪያ (Soria)
4.. ኢብራሂም (ዐ.ሰ) = ፍልስጤም (Palistain)
5.. ኢስማኤል (ዐ.ሰ) = ሳኡዲ (Saudi)
6.. ያእቆብ (ዐ.ሰ) = ፍልስጤም (Palistain)
7.. ያህያ (ዐ.ሰ) = ፍልስጤም (Palistain)
8.. ዘከሪያ (ዐ.ሰ) = ፍልስጤም (Palistain)
9.. ኢስሃቅ (ዐ.ሰ) = ፍልስጤም (Palistain)
10.. የሱፍ (ዐ.ሰ) = ፍልስጤም (Palistain)
11.. ሉጥ (ዐ.ሰ) = ኢራቅ (Iraq)
12.. ኢዩብ (ዐ.ሰ) = ጆርዳን (Jordan)
13.. ሁድ (ዐ.ሰ) = የመን (Yemen)
14.. ሙሀመድ (ሰ.ዐ.ወ) = ሳኡዲ (Saudi) ( ከሁሉም በተለየ መልኩ የተላኩት ለአለም ህዝቦች ነው )
15.. ሙሳ (ዐ.ሰ) = ግብፅ (Egypt)
16.. ሀሩን(ዐ.ሰ) = ግብፅ (Egypt)
17.. ሷሊህ (ዐ.ሰ) = የመን (Yemen)
18.. ሱለይማን (ዐ.ሰ) = ግብፅ (Egypt)
19.. ኢሊያስ (ዐ.ሰ) = ጀሩሳሌም (ፍልስጤም)
20.. ዳውድ (ዐ.ሰ) = ኢራን (Iran)
21.. ኢሳ (ዐ.ሰ) = ጀሩሳሌም (ፍልስጤም)
22.. ኢድሪስ (ዐ.ሰ) = ኦማን (Oman)
23.. ዩኑስ (ዐ.ሰ) = ኢራን (Iran)
24.. ዙልኪፍል (ዐ.ሰ) = ጆርዳን ( Jordan )
25.. አልየስእ (ዐ.ሰ) = ሶሪያ ( Soria)
የአላህ እዝነት እና ሰላም በሁሉም ላይ ይስፈን
ሳታነብት እንዳታልፉ
@yasin_nuru @yasin_nuru
👍 146❤ 42👌 7🥰 5⚡ 4👎 3
ትንሽ ፈገግ በሉ‼
============
✍ «… ወሎ ውስጥ ነው አሉ። አንድ ቆለኛ ሙስሊምና አንድ ደገኛ ክርስቲያን ጓደኛሞች ይሆናሉ። ክርስቲያኑ ሙስሊሙን ግብዣ ጠራው። የገና በአል ነበር። ሙስሊሙ ሲመጣ ምግቡ፣ መጠጡ፣ ሁሉ ነገር ተትረፍርፏል። ሰዎቹ ፌሽታ በፌሽታ፣ ፈንጠዝያ በፈንጠዝያ ሆነዋል።
* ሙስሊሙ:– "ድግሱ ምንን ምክንያት በማድረግ ነው?" ብሎ ጠየቀ።
"ጌታ ተወልዶ ነው" አሉት።
ለሙስሊሙ ይሄ አስደንጋጭ ነበር። ጌታ ይወለዳል?! ግን ከሰው ቤት ነው ያለው ምን ይላል? "ህምምም" ብሎ የሆዱብ በሆዱ አድርጎ ዝም ይላል። ይህን ጉድ አይቶ ተመለሰ።
ሌላ ጊዜ ተጠራ። ጥምቀት ነበር። ሲመጣ ድግሱ አሁንም እንደባለፈው የደመቀ ነው። ሰዎቹም ደስታ በደስታ ናቸው።
"ይሄስ በአል ምንድን ነው ምክንያቱ?" ብሎ ጠየቀ።
"ጌታ ተጠምቆ ነው" አሉት። ዘንድሮ ጉድ ተአምር እያየ ነው። እንዲያም ነው፤ እንዲህም ነው ሳይል ወደ ቤቱ ተመለሰ።
አሁንም ተጠራ። ስቅለት ነበር። ሲመጣ ከወትሮው የተለየ ነገር አየ። ሰዎቹ የባለፈው አይነት ደስታ አይታይባቸውም። አዝነዋል። በባዶ እግር ይሄዳሉ። የሚበሉት ንፍሮ ነው። ግንባራቸውን በሳር መሳይ ነገር አስረዋል። ምን ጉድ ነው?! ቆለኛው ግራ ገብቶታል።
* "ምንድን ነው የሆናችሁት?" አላቸው።
"ጌታ ሞቶ ነው" አሉት።
* "ያ ባለፈው የተወለደው?" ሲል ጠየቀ።
"አዎ" አሉት።
·
ከዚያ ምን ቢል ጥሩ ነው:–
"እኔኮ ቀድሞም ፌሽታ ስታበዙ እንደማያድግ አውቄያለሁ!"
©: የታሪኩ ምንጭ አንድ የደሴ ክርስቲያን ነው።
@yasin_nuru @yasin_nuru
😁 110👍 74🤣 51❤ 23👌 9✍ 5🥰 5😢 1😇 1
ትንሽ ፈገግ በሉ‼
============
✍ «… ወሎ ውስጥ ነው አሉ። አንድ ቆለኛ ሙስሊምና አንድ ደገኛ ክርስቲያን ጓደኛሞች ይሆናሉ። ክርስቲያኑ ሙስሊሙን ግብዣ ጠራው። የገና በአል ነበር። ሙስሊሙ ሲመጣ ምግቡ፣ መጠጡ፣ ሁሉ ነገር ተትረፍርፏል። ሰዎቹ ፌሽታ በፌሽታ፣ ፈንጠዝያ በፈንጠዝያ ሆነዋል።
* ሙስሊሙ:– "ድግሱ ምንን ምክንያት በማድረግ ነው?" ብሎ ጠየቀ።
"ጌታ ተወልዶ ነው" አሉት።
ለሙስሊሙ ይሄ አስደንጋጭ ነበር። ጌታ ይወለዳል?! ግን ከሰው ቤት ነው ያለው ምን ይላል? "ህምምም" ብሎ የሆዱብ በሆዱ አድርጎ ዝም ይላል። ይህን ጉድ አይቶ ተመለሰ።
ሌላ ጊዜ ተጠራ። ጥምቀት ነበር። ሲመጣ ድግሱ አሁንም እንደባለፈው የደመቀ ነው። ሰዎቹም ደስታ በደስታ ናቸው።
"ይሄስ በአል ምንድን ነው ምክንያቱ?" ብሎ ጠየቀ።
"ጌታ ተጠምቆ ነው" አሉት። ዘንድሮ ጉድ ተአምር እያየ ነው። እንዲያም ነው፤ እንዲህም ነው ሳይል ወደ ቤቱ ተመለሰ።
አሁንም ተጠራ። ስቅለት ነበር። ሲመጣ ከወትሮው የተለየ ነገር አየ። ሰዎቹ የባለፈው አይነት ደስታ አይታይባቸውም። አዝነዋል። በባዶ እግር ይሄዳሉ። የሚበሉት ንፍሮ ነው። ግንባራቸውን በሳር መሳይ ነገር አስረዋል። ምን ጉድ ነው?! ቆለኛው ግራ ገብቶታል።
* "ምንድን ነው የሆናችሁት?" አላቸው።
"ጌታ ሞቶ ነው" አሉት።
* "ያ ባለፈው የተወለደው?" ሲል ጠየቀ።
"አዎ" አሉት።
·
ከዚያ ምን ቢል ጥሩ ነው:–
"እኔኮ ቀድሞም ፌሽታ ስታበዙ እንደማያድግ አውቄያለሁ!"
©: የታሪኩ ምንጭ አንድ የደሴ ክርስቲያን ነው።
ጁሙዓን የት ሃገር፣ የት መስጅድ ሰገዳችሁ? ኹጥባው ስለምን ነበር? ለሌሎችም እንዲጠቅም ከሰማችሁት ውስጥ የኹጥባውን ጭብጥ በአጭር አስፍሩት።
@yasin_nuru
👍 85❤ 29🥰 7🔥 4😍 4😁 3
«አንዱ አረብ ሒሳብ አዋቂ ተጠየቀ ....
.
... ስለ ሴት ምን ታስባለህ?
.
ፈከረ
.
'ሴት' አለ ...
... እምነት ካላት 1 ነጥብ አላት
... ውበት ካላት 0 ከጎኑ ጨምር
...ዘሯ ካማረ ሌላ 0 አሁንም ጨምር
... ሀብትም ካላት 0 ጨምር ከኋላ
.
ሁሉም ካላት 1000 ነጥብ አላት ... የመጀመሪያው ከጎደለ ግን ምንም ናት!
.
ምገርም ነው!
ምደንቅ ነው!
ሐዲሱም እንዲያ ነው!»
ቢን ዓሊ
@yasin_nuru @yasin_nuru
👏 96👍 69❤ 30👌 14😁 11🥰 7
በዚህ ታሪክ ውስጥ አላህ ምን ያህል ለባሮቹ ሩህሩህ፣ ያሻውን የሚያደርግ ኃያል ጌታ እንደሆነ እንረዳ ዘንድ እናስታውስ ላመኑት ይጠቅማልና ማስታወስ
Mahi Mahisho
ውልደታቸው በፓኪስታን ዋና ከተማ ነው። በዘመናችን አንቱታን ያተረፉ ከኒውሮሎጂ የህክምና ዘርፍ ጠበብቶች ውስጥ በግንባር ቀደምትነት የሚጠቀሱ ስመ-ጥር ስፔሻሊስት ናቸው። ሕክምና ለመስጠት ከሀገር ወደ ሀገር ከከተማ ወደ ገጠር ስለሚዘዋወሩ በስራቸው ባህሪ ከባድነትና እረፍት አልባነት ጋር ተደማምሮ ህመምተኞች እሳቸውን በቀላሉ ለማግኘት ይቸግራቸዋል። ከስድስት ወራቶች እስከ ዓመት ቀጠሮ መጠበቅ ግድ ይላል።
እነሆ ዛሬ እዛው ፓኪስታን ውስጥ በሽተኞችን ለማከም ቀጠሮ ይዘዋል። ካሉበት ከተማ ወደ ሌላ ከተማ ለመሄድ በአውሮፕላን ጉዞ ጀምረዋል። ብዙም ሳይርቁ የተሳፈሩበት አውሮፕላን በገጠመው ጭጋጋማና መጥፎ የአየር ሁኔታ በአንድ ትንሽ ከተማ አየር ማረፊያ ለማረፍ ተገደዱ። ከአውሮፕላኑ ወርደው የአየር ሁኔታው እስኪሻሻል ቢጠብቁም እንዳሰቡት ሳይሆንላቸው ቢቀር የአውሮፕላኑን ፓይለት የጉዟቸው መዳረሻ ወደሆነችው ከተማ ለመድረስ ምን ያህል ጊዜ እንደሚፈጅ ጠየቁት። ፓይለቱም ሶስት ስዓት እና ከዛ በላይ እንደሚሆን ነገራቸው። ዶክተሩ አንድ የሚያስጨንቃቸው ነገር አለ። ብዙ ህመምተኞች የእሳቸውን እርዳታ በመፈለግ በቀጠሯቸው መሰረት የሳቸውን መምጣት በመጠባበቅ ላይ መሆናቸው አሳስቧቸዋልና በዚህ ሁኔታ ለማደር አእሞሯቸው አልፈቀደም። መኪና ይዘው ጉዟቸውን ለመቀጠል ይወስናሉ። ግና ትንሽ ከተጓዙ በኋላ ከባድ ዝናብ መንገዳቸውን ገታው። መንገዱ ጭቃማ ስለሆነ መኪናቸውን መንቀሳቀስ ባለመቻሏ አሁንም በድጋሚ ባሉበት ስፍራ ለመቆየት ተገደዱ። አሁን ያሉበት መንደር ደግሞ በጣም ሩቅ የሆነ ገጠራማ መንደር ሲሆን ዝናቡ እስኪያባራ ከመኪናቸው ወርደው ሰላት ለመስገድ አሰቡ። ውሃ እና መስገጃ ፍለጋ ወደ አንድ ቤት አቀኑ።
በሩን በዝግታ አንኳኩ። እድሜያቸው ገፋ ያለ አንዲት አዛውንት በሩን ከፈቱ። ምን ልርዳችሁ በማለት ጠየቁ። ዶክተሩም ሰላምታ ካቀረቡ በኋላ ሰላት ለመስገድ ስለፈለኩኝ ጥቂት ውሃ እና መስገጃ ፈልጌ ነው በማለት ጠየቁ። መርሃባ ግቡ በማለት ውሃ እና መስገጃ አቀረበችላቸው። ሰግደው እንደጨረሱ ሙስልሟን ሴት አመስግነው ሊወጡ በመራመድ ላይ ሳሉ አልጋ ላይ የተኛ ሰው ተመለከቱ “ምነው?.. ምን ገጥሞት ነው?” ብለው ጠየቁ። ሴትዮዋም ታሪኩን ታወጋ ጀመር “እዚህ ቤት ውስጥ የምንኖረው እኔና ይህ የምትመለከቱት ልጄ ነው። ለረጅም ጊዜ በያዘው ህመም በመሰቃየት ላይ ነው። በተደጋጋሚ የተለያዩ ሐኪሞች ጋር በመሄድ ሕክምና እንዲያገኝ ብሞክርም ሳይሳካ ቀረ። ዶክተሮች ወደ ታዋቂ ስፔሻሊስት ዶክተር እንድሄድ በሰጡኝ ጥቆማ መሠረት ወደተባለው ዶክተር ዘንድ ሄጄ ነበር። ነገር ግን ዶክተሩ ብዙ በሽተኞች ስለሚያስተናግዱ እሳቸውን ማግኘት እንደማይቻልና ከ6 ወር በሃላ እንድንመለስ ቀጠሮ ተሰጥቶን ወደ ቤት ተመለስን” አሉ አዛውንቷ ትክዝ ብለው መሬት እንዳቀረቀሩ ንግግራቸውን ቀጠሉ “እኔ አቅመ ደካማ አዛውንት ነኝና ልጄን ይዤ ወደ ቤት ተመለስኩ። አላህን ቀንና ማታ እየለመንኩት ነው። አልሀምዱሊላህ እስካሁን ነብሱ አለች...” አሉ አዛውንቷ እምባ እየተናነቃቸው።
ዶክተሩ የሴትዮዋን ንግግር በጥሞና አድምጠው ሲጨርሱ ”ማን የሚባል ዶክተር ጋር ነው ዶክተሮች እንድትሄዱ የነገሯችሁ?” አሉ። “አንድ ታዋቂ የሆነ ስሙ ዶ/ር ኢሻም የሚባል ሀኪም ዘንድ እንድሄድ ነበር የተነገረኝ” በማለት ለዶክተሩ ምላሽ ሰጡ። የሰሙትን ነገር ለማመን የከበዳቸው ዶክተር እራሳቸውን መቆጣጠር ተስኖዋቸው እምባቸውን ማፍሰስ ጅመሩ። አስከተሉና "አላህ ዱአዎትን ሰምቶ ምላሽ ሰጥቷል” አሉና ንግግራቸውን አስከተሉ “ህመምተኞችን ለመርዳት ወደሌላ ከተማ ቀጠሮ ነበረኝ። በአውሮፕላን ጉዞዬን ጀመርኩ ግን በመጥፎ የአየር እክል ምክንያት ሳይሳካ ቀረ እንደገና በመኪና ጉዞዬን ለመቀጠል ሞከርኩ። በከባድ ዝናብ እና ጭቃ እዚህ መንደር ለመቆየት ተገደድኩ ...” በማለት ተናገሩ። ለመጀመሪያ ጊዜ ታሪኩን ስሰማ እንባዬን መቆጣጠር አልቻልኩም ነበር ይላሉ ታሪኩን የተረኩልን ሙፍቲ ሜንክ።
አላህ ይህን ውድ ዶክተር የዚህችን አቅም አልባ እና ልጇን ምታስታምም አዛውንት ቤት ድረስ አምጥቶ በራቸውን እንዲያንኳኩ ሲያስደርግ፣ ሩቅ እና ገጠራማውን መንደር አቆራርጦ አላህ በችሎታው ቤት ድረስ ሲያመጣው ከማየት በላይ ሚያስደንቅ ነገር አለመኖሩን እናስታውስ ላመኑት ይጠቅማልና ማስታወስ።
አላህን የያዘ ምን አጣ
አላህንስ ያጣ ምን አገኘ
@yasin_nuru @yasin_nuru
❤ 137👍 79🥰 9🤗 4🤓 1
በዚህ ታሪክ ውስጥ አላህ ምን ያህል ለባሮቹ ሩህሩህ፣ ያሻውን የሚያደርግ ኃያል ጌታ እንደሆነ እንረዳ ዘንድ እናስታውስ ላመኑት ይጠቅማልና ማስታወስ
Mahi Mahisho
ውልደታቸው በፓኪስታን ዋና ከተማ ነው። በዘመናችን አንቱታን ያተረፉ ከኒውሮሎጂ የህክምና ዘርፍ ጠበብቶች ውስጥ በግንባር ቀደምትነት የሚጠቀሱ ስመ-ጥር ስፔሻሊስት ናቸው። ሕክምና ለመስጠት ከሀገር ወደ ሀገር ከከተማ ወደ ገጠር ስለሚዘዋወሩ በስራቸው ባህሪ ከባድነትና እረፍት አልባነት ጋር ተደማምሮ ህመምተኞች እሳቸውን በቀላሉ ለማግኘት ይቸግራቸዋል። ከስድስት ወራቶች እስከ ዓመት ቀጠሮ መጠበቅ ግድ ይላል።
እነሆ ዛሬ እዛው ፓኪስታን ውስጥ በሽተኞችን ለማከም ቀጠሮ ይዘዋል። ካሉበት ከተማ ወደ ሌላ ከተማ ለመሄድ በአውሮፕላን ጉዞ ጀምረዋል። ብዙም ሳይርቁ የተሳፈሩበት አውሮፕላን በገጠመው ጭጋጋማና መጥፎ የአየር ሁኔታ በአንድ ትንሽ ከተማ አየር ማረፊያ ለማረፍ ተገደዱ። ከአውሮፕላኑ ወርደው የአየር ሁኔታው እስኪሻሻል ቢጠብቁም እንዳሰቡት ሳይሆንላቸው ቢቀር የአውሮፕላኑን ፓይለት የጉዟቸው መዳረሻ ወደሆነችው ከተማ ለመድረስ ምን ያህል ጊዜ እንደሚፈጅ ጠየቁት። ፓይለቱም ሶስት ስዓት እና ከዛ በላይ እንደሚሆን ነገራቸው። ዶክተሩ አንድ የሚያስጨንቃቸው ነገር አለ። ብዙ ህመምተኞች የእሳቸውን እርዳታ በመፈለግ በቀጠሯቸው መሰረት የሳቸውን መምጣት በመጠባበቅ ላይ መሆናቸው አሳስቧቸዋልና በዚህ ሁኔታ ለማደር አእሞሯቸው አልፈቀደም። መኪና ይዘው ጉዟቸውን ለመቀጠል ይወስናሉ። ግና ትንሽ ከተጓዙ በኋላ ከባድ ዝናብ መንገዳቸውን ገታው። መንገዱ ጭቃማ ስለሆነ መኪናቸውን መንቀሳቀስ ባለመቻሏ አሁንም በድጋሚ ባሉበት ስፍራ ለመቆየት ተገደዱ። አሁን ያሉበት መንደር ደግሞ በጣም ሩቅ የሆነ ገጠራማ መንደር ሲሆን ዝናቡ እስኪያባራ ከመኪናቸው ወርደው ሰላት ለመስገድ አሰቡ። ውሃ እና መስገጃ ፍለጋ ወደ አንድ ቤት አቀኑ።
በሩን በዝግታ አንኳኩ። እድሜያቸው ገፋ ያለ አንዲት አዛውንት በሩን ከፈቱ። ምን ልርዳችሁ በማለት ጠየቁ። ዶክተሩም ሰላምታ ካቀረቡ በኋላ ሰላት ለመስገድ ስለፈለኩኝ ጥቂት ውሃ እና መስገጃ ፈልጌ ነው በማለት ጠየቁ። መርሃባ ግቡ በማለት ውሃ እና መስገጃ አቀረበችላቸው። ሰግደው እንደጨረሱ ሙስልሟን ሴት አመስግነው ሊወጡ በመራመድ ላይ ሳሉ አልጋ ላይ የተኛ ሰው ተመለከቱ “ምነው?.. ምን ገጥሞት ነው?” ብለው ጠየቁ። ሴትዮዋም ታሪኩን ታወጋ ጀመር “እዚህ ቤት ውስጥ የምንኖረው እኔና ይህ የምትመለከቱት ልጄ ነው። ለረጅም ጊዜ በያዘው ህመም በመሰቃየት ላይ ነው። በተደጋጋሚ የተለያዩ ሐኪሞች ጋር በመሄድ ሕክምና እንዲያገኝ ብሞክርም ሳይሳካ ቀረ። ዶክተሮች ወደ ታዋቂ ስፔሻሊስት ዶክተር እንድሄድ በሰጡኝ ጥቆማ መሠረት ወደተባለው ዶክተር ዘንድ ሄጄ ነበር። ነገር ግን ዶክተሩ ብዙ በሽተኞች ስለሚያስተናግዱ እሳቸውን ማግኘት እንደማይቻልና ከ6 ወር በሃላ እንድንመለስ ቀጠሮ ተሰጥቶን ወደ ቤት ተመለስን” አሉ አዛውንቷ ትክዝ ብለው መሬት እንዳቀረቀሩ ንግግራቸውን ቀጠሉ “እኔ አቅመ ደካማ አዛውንት ነኝና ልጄን ይዤ ወደ ቤት ተመለስኩ። አላህን ቀንና ማታ እየለመንኩት ነው። አልሀምዱሊላህ እስካሁን ነብሱ አለች...” አሉ አዛውንቷ እምባ እየተናነቃቸው።
ዶክተሩ የሴትዮዋን ንግግር በጥሞና አድምጠው ሲጨርሱ ”ማን የሚባል ዶክተር ጋር ነው ዶክተሮች እንድትሄዱ የነገሯችሁ?” አሉ። “አንድ ታዋቂ የሆነ ስሙ ዶ/ር ኢሻም የሚባል ሀኪም ዘንድ እንድሄድ ነበር የተነገረኝ” በማለት ለዶክተሩ ምላሽ ሰጡ። የሰሙትን ነገር ለማመን የከበዳቸው ዶክተር እራሳቸውን መቆጣጠር ተስኖዋቸው እምባቸውን ማፍሰስ ጅመሩ። አስከተሉና "አላህ ዱአዎትን ሰምቶ ምላሽ ሰጥቷል” አሉና ንግግራቸውን አስከተሉ “ህመምተኞችን ለመርዳት ወደሌላ ከተማ ቀጠሮ ነበረኝ። በአውሮፕላን ጉዞዬን ጀመርኩ ግን በመጥፎ የአየር እክል ምክንያት ሳይሳካ ቀረ እንደገና በመኪና ጉዞዬን ለመቀጠል ሞከርኩ። በከባድ ዝናብ እና ጭቃ እዚህ መንደር ለመቆየት ተገደድኩ ...” በማለት ተናገሩ። ለመጀመሪያ ጊዜ ታሪኩን ስሰማ እንባዬን መቆጣጠር አልቻልኩም ነበር ይላሉ ታሪኩን የተረኩልን ሙፍቲ ሜንክ።
አላህ ይህን ውድ ዶክተር የዚህችን አቅም አልባ እና ልጇን ምታስታምም አዛውንት ቤት ድረስ አምጥቶ በራቸውን እንዲያንኳኩ ሲያስደርግ፣ ሩቅ እና ገጠራማውን መንደር አቆራርጦ አላህ በችሎታው ቤት ድረስ ሲያመጣው ከማየት በላይ ሚያስደንቅ ነገር አለመኖሩን እናስታውስ ላመኑት ይጠቅማልና ማስታወስ።
አላህን የያዘ ምን አጣ
አላህንስ ያጣ ምን አገኘ
ለአስተያየትዎ @Strong_iman_bot ይጠቀሙ
@yasin_nuru
ቢስሚላሂ ረሕማኒ ረሒም - መልካም ምክሮች
1- ቀንህን ከምትጀምርባቸው ነገሮች ሁሉ ዚክር እና ሶላት ምርጦቹ ናቸው!!
2- ወንጀል ብትሰራም ባትሰራም ምላስህ ሌት ተቀን አላህን እስቲግፋር ከመጠየቅ አይቦዝን!
3- በዱዐ አትዘናጋ ለመዳን ወሳኙ መሳሪያ እሱ ነውና!!
4- ከመናገርህ በፊት ቃላቶችህን የሚፅፉ መላኢካዎች አጠገብህ እንዳሉ አትዘንጋ!!
5- ትልቅ ማእበል ቢያጋጥምህ እንኳ አሁንም መውጫ እንዳለህ አስብ!!
6- አለንጋ ጣቶችህ የበለጠ የሚያምሩት ዚክር ላይ ሲሳተፉ ነው!!
7- ለዱዐ ምላሽ የምታገኝበትን እድል ሐራም በመብላት አትዝጋው!!
8- የመጥፎ ጥርጣሬ አባዜ ከሌለብህ ደስተኛ ሁነህ ትኖራለህ!!
9- በጋዜጣና በሞባይል ፍቅር ከመውደቅህ በፊት በቁርአን ፍቅር ውደቅ!!
10- የሰው ልጅ ነፍሱ አመፀኛ ናትና በአላህ ትዛዝ ላይ አስገድዳት!!
11- ያንተ አሮጌ ልብሶች ለድሃ አዳድሶች ናቸው!!
12- ምድርን ስትሰናበት ካንተ ጋራ መቃብር የሚገባ ስራ ይኑርህ!!
13- ሀሜተኛ ሰው ካጋጠመህ 'አላህን ፍራ' ለማለት አትፍራ!!
14- ህይወት በተፈጥሮ ውብ ናት፣ ከኢማንና ከተስፋ ጋር ደግሞ እጅግ ውብ ናት!!
15- የምትቸኩልለት ነገር ሁሉ ከሶላት የሚበልጥ አይደለምና ተረጋግተህ ስገድ!!
16- ህይወት እኛ ከምንገምተው በላይ በጣም አጭር ናትና ከዚህም ከዚያም ጋር አትጋጭ!!
17- የጭንቀት ሁሉ መንስኤው ከአላህ ﷻ መራቅ ነውና በተቻለህ አቅም ከአላህ ላለመራቅ ሞክር!!
@yasin_nuru @yasin_nuru
👍 133❤ 65😁 2👏 1😭 1
የቁርአን ቻናሎች በቃሪኦቻቸው ስም የሚያገኙበት!!
1 @mishary_rashid_al_afasi
2 @Yassen_Al_Jazairi
3 @Sheikh_Abu_Bakr_Al_Shatri
4 @Sheikh_Muhammad_Al_Luhaidan
5 @Abdulbasit_Abdussamed1
6 @Sheikh_Abdul_Rahman_Al_Sudais
7 @Ali_Al_Huzaifi
8 @Khalifah_At_Tonaeijy
9 @Ahmad_Al_Ajmy
10 @Sheikh_Saad_Al_Gamidi
11 @Emad_Al_Mansary
12 @Abdullah_ibn_Al_Basfar
13 @Sheikh_Nasser_Al_Qatami
14 @Abdulhadi_Kanakeri
15 @Sheikh_Maher_Al_Muaiqly
16 @Sheikh_Adel_Rayan
17 @Khalil_Al_Hussary
18 @Sheikh_Muhammad_Ayyub
19 @Abdullah_Awad_Al_Juhany
20 @Abdul_Rashid_Ali_Sufi
21 @Mohamed_Siddiq_El_Minshawi
22 @Abdul_Rahman_Al_Ossi
23 @Sheikh_Saud_Al_Shuraim
24 @Yasser_Al_Dosarii
25 @Muhammad_Al_Kurdi1
26 @Fares_Abbad1
27 @Sheikh_Salah_Bukhatir
28 @Imad_Zuhair_Hafez
29 @Muhammad_AbdulKareem
30 @Ahmad_Misbahi
31 @Abdulaziz_Az_Zahrani
32 @Ibrahim_Al_Asirii
33 @Abdulbosit_Qobilov1
34 @Abdullah_al_Matrood1
35 @Afzal_Rafiqov1
36 @Hani_Ar_Rifai
37 @Abdullah_Ali_Jaber
38 @Sheikh_Muhammad_Jibril
39 @Jazza_Alswaileh
40 @Bandar_Balila
41 @Mohammad_Al_Tablawi
42 @Wadee_Al_Yamani
43 @Ghassan_Al_Shorbajyi
44 @Zaki_Dagistan
45 @Ahmad_Al_Lahdan
46 @Abdullah_Xalif
47 @Yasser_Al_Qureshi
48 @Nabil_Al_Rifai
49 @Salah_Al_Hashem
50 @Shirazad_Taher
51 @Tawfeeq_As_Sayeghh
52 @Rashid_Al_Arkani
53 @Sheikh_Mustafa_Ismail
54 @Ali_Yakupovv
55 @Abdullah_Kamel
56 @Mahmud_Ali_Albanna
57 @Sheikh_Idris_Abkar
58 @Hassen_Saleh
59 @Moeedh_Al_Harthi
60 @Ahmed_Naina
61 @Waleed_Al_Naehi
62 @Saber_AbdulHakam
63 @Mohammad_Saleh_Shah
64 @AbdulMuhsin_Qasim
65 @Salah_Al_Budair
66 @Akram_Alalaqimy
67 @Jamaan_Alosaimii
68 @Abdulmohsen_Harty
69 @Abdul_Wadood_Haneef
70 @Mohammad_Al_Abdullah
71 @Yahya_Hawwa
© @Quran_Mp3_Collection
@yasin_nuru @yasin_nuru
👍 104❤ 47🥰 9💯 8🔥 7🤗 7👌 4👎 2👏 2😁 1