cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

ኢትዮ ጤና

health information especially Covid19, issues, news,datas research findings,will be prsented. ጤና ነክ በተለይም በኮሮና ዙሪያ የተጻፉ ትኩስ ትኩስ ዜናዎች ፣ግኝቶች፣ዳታዎችና ፣መረጃዎች ይቀርቡበታል

Show more
The country is not specifiedThe language is not specifiedThe category is not specified
Advertising posts
157
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

በአማራ ክልል የማህፀን በር ጫፍ ካንሰር ቅድመ መከላከያ ክትባት ለ307 ሺህ ሴቶች ከጥር 17 እስከ ጥር 22/2013 ዓ/ም እንደሚሰጥ የክልሉ ጤና ቢሮ አስታውቋል። የአማራ ክልል ጤና ቢሮ ከሚዲያ ባለሙያዎች፣ የትምህርት ተቋማት፣ የሃይማኖት ተቋማት፣ ከመድሃኒት አቅራቢ ኤጀንሲ ባሕር ዳር ቅርንጫፍና ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በእንጅባራ ከተማ ውይይት አካሂዷል። የማህፀን በር ጫፍ ካንሰር መከላከያ ክትባት እድሜያቸው 14 ዓመት ለሞላቸው ሁሉም ሴቶች ከጥር 17 እስከ ጥር 22/2013 ዓ.ም በመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤቶች፣ በቀበሌ ማዕከላትና በሁሉም ጤና ተቋማት እንደሚሰጥ በአማራ ክልል ጤና ቢሮ የክትባት ባለሙያ አቶ ሙሉጌታ አድማሱ አመላክተዋል፡፡በ2012 ዓ.ም የመጀመሪያ ዙር ክትባት ከወሰዱ በኋላ በኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ምክንያት ትምህርት ቤቶች በመዘጋታቸው ሁለተኛ ዙር ላልወሰዱ እና በ2013 ዓ.ም ዕድሜያቸው ከ9 እስከ 14 ዓመት ለሞላቸው ሴቶች ደግሞ የ1ኛ ዙር ክትባት በትምህርት ቤቶች፣ በአቅራቢያቸው በሚገኙ የክትባት ጣቢያዎችና ጤና ተቋማት እንደሚከተቡ ባለሙያው በውይይቱ ላይ ገልጸዋል፡፡ [AMMA]
Show all...
በጃፓን ሌላ አይነት የኮሮና ቫይረስ ተገኘ‼️ በጃፖን ሌላ አይነት የኮሮና ቫይረስ መገኘቱን የሀገሪቱ ጤና ሚኒስቴር አስታወቀ። በብሪታኒያ እና ደቡብ አፍሪካ ከተገኘው የኮሮና ቫይረስ ጋር በከፊል ተመሳሳይነት ያለው ቫይረስ መሆኑን ሚኒስቴሩ ገልጿል። የጃፓን የጤና ሚኒስቴር ቫይረሱ ከብራዚል ከመጡ አራት ሰዎች ላይ እንደተገኘ ነው ያስታወቀው። ብሄራዊ የተላላፊ በሽታዎች ኢንስቲትዩት እስከ አሁን ቫይረሱ በከፍተኛ ሁኔታ የሚሰራጭ መሆኑን የሚያሳይ ማስረጃ እንደሌለ ገልጿል። እንዲሁም ቫይረሱ ከባድ ምልክቶች እንዳሉት እና የኮሮና ቫይረስ ክትባትን መቋቋም አለመቋቋሙ ለማወቅ የሚያስችል ምርመራ እየተካሄደ መሆኑን ኢንስቲትዩቱ ማስታወቁን የጃፓን ታይምስ ዘገባ ያሳያል። ቫይረሱ ከተገኘባቸው ሰዎች መካከል የ40 ዓመቱ ግለሰብ ከብራዚል ጃፓን በደረሰበት ወቅት ምንም አይነት ምልክት ያልነበረው ቢሆንም ከቆይታ በኋላ የመተንፈስ ችግር አጋጥሞት ሆስፒታል እንደገባ በዘገባው ተጠቅሷል። ሌላኛው የ30 ዓመት እድሜ ያላት ሴት ደግሞ የእራስ ምታት ምልክት ፤ ከ10 እስከ 19 እድሜ ውስጥ የሚገኘው ታዳጊ ትኩሳት እንዲሁም በተመሳሳይ የእድሜ ክልል ውስጥ የምትገኘው ታዳጊ ምንም አይነት ምልክት አለማሳየቷ ተነግሯል። Zehabeshanews
Show all...
በኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ የተያዙ ሰዎች ቁጥር ከ85 ሚሊየን አለፈ ********************* ከአንድ ዓመት በፊት እ.አ.አ 2019 መጨረሻ ላይ በዓለም አቀፍ ደረጃ በተከሰተው የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ የተያዙ ሰዎች ቁጥር 85 ሚሊየን በላይ መድረሱን የወርልዶሜትርስ ኢንፎ መረጃ አመለከተ። በበሽታው ሕይወታቸው ያለፈ ሰዎች ቁጥር አንድ ሚሊየን 850 ሺህ በላይ ሲሆን፣ ከ60 ሚሊየን የሚልቁ ሰዎች ደግሞ ከበሽታው ማገገማቸው ተገልጿል። ከዚህ ቁጥር ውስጥ አሜሪካ ከ21 ሚሊየን በላይ የሚሆኑ በቫይረሱ የሚሆኑ ዜጎች በማስመዝገብ በዓለም በግንባር ቀደምትነት ተቀምጣለች። ከዚህ ቁጥር ውስጥ የ360 ሺህ በላይ ዜጎቿ ሕይወት ሲያልፍ፣ 12 ሚሊየን በላይ የሚሆኑት ዜጎቿ ደግሞ ከበሽታው አገግመዋል። ሕንድ ከ10 ሚሊየን በላይ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች በማስመዝገብ በሁለተኛነት ስትቀመጥ፣ 150 ሺህ ገደማ ዜጎቿ ሕይወት አልፏል። በሦስተኝነት የተቀመጠችው ብራዚል ከሰባት ሚሊየን በላይ ዜጎቿ በቫይረሱ ሲያዙ፣ 200 ሺህ ያህል ዜጎቿ ሕይወት አልፏል። ሩስያ ሦስት ሚሊየን በላይ እንዲሁም ፈረንሳይ፣ ዩናይትድ ኪንግደም፣ ቱርክ፣ ጣልያን እያንዳንዳቸው ከሁለት ሚሊየን ዜጎቻቸው በኮሮናቫይረስ መያዛቸውን መረጃው አመልክቷል።ኢቢሲ
Show all...
🙏ነፃ መረጃ ስለ አባይ በአባይ ጉዳይ ዜና፣ሀተታ ፣ቃለ መጠይቅ እና ትንታኔ ያገኛሉ https://t.me/nileabay
Show all...
The Niles ናይል

news,article ,interview and analysis on nile issues . በአባይ ጉዳይ ዜና፣ሀተታ ፣ቃለ መጠይቅ እና ትንታኔ ያገኛሉ

ወይም ከመጣበት ለየት ያለ ያደርገዋል፡፡ ይህ ለየት ያለው ቫይረስ ነው እንግዲህ አዲስ ዝርያ ተብሎ የሚጠራው፡፡ አሁን አዲስ የተከሰተው ቫይረስ፣ በውስጡ ባሉ ፕሮቲኖች መጠነኛው ወይም ስፋት ያለው ለውጥ ካለው ምን ይሆናል የሚል ጥያቄም አለ፡፡ ባይገርማችሁ፣ እንዲህ ለወጥ ያለ ፕሮቲን ያለው ቫይረስ፣ ሰንካላ በመሆኑ መቀጠልና መራባት ሳይችል ሲቀር በዛው ይከስማል፡፡ ሰለዚህ የፕሮቲን ለውጥ ማድረጉ ለቫይረሱም የማይበጅበት ሁኔታ አለ ማለት ነው፡፡ ነገር ግን ይህ ለወጥ ያለው ቫይረስ፣ ከሁኔታው ጋር ተስማሚ ከሆነ፣ ያደረገው ለውጥ ደግሞ እንዲቀጥልና እንዲባዛ የሚያስችለው ከሆነ፣ እንደምትገምቱት፣ መራባቱን ይቀጥላል፣ እንዳውም አዲስ የፈጠረው ፕሮቲን ጠንከር የሚያደርገው ከሆነ፣ ከመጀሪያው ቫይረስ በበለጠ ይራባል ይባዛል፣ አንደዛ ሲሆን፣ ርስቱን የሚይዘው አዲሱ ዝርያ ይሆንና የቀድሞው እየከሰመ ይሄዳል ማለት ነው፡፡ በቫይረስ አለምም ቢሆን ጉልበተኛው ያሸንፋል፡፡ ለዚህ ነው እንግዲህ፣ በታሕሣሥ የተከሰተው አባት ቫይረስ እየከሰመ ሲሄድ አዳዲሶቹ ሥርጭቱን እየተቆጣጠሩት የሚሄዱት፡፡ አስተውላችሁ ከሆነ፣ ለአዳዲስ ጉልበተኛ ቫይረሶች መከሰት ምክንያቱ ቫይረሱ መራባት ወይም መባዛት ሲቀጥል ነው፡፡ መዋለድ ካልጀመረ አዲስ ልጅ ከየት ይመጣል? ይህ ደግሞ የሚሆነው፣ ሰዎች፣ ቫይረሱን ከአንዱ ሰው ወደሌላው በማወቅም ሆነ ባለማወቅ ሲያሻግሩት ነው፡፡ የለንደንም ሆነ የደቡብ አፍሪካው ቫይረስ በዚህ መንገድ ነው የተከሰቱት፡፡ ለምን አሁን ጉልህ ሆነ ብትሉ፤ በሥርጭት ላይ ያሉ ቫይረሶችን የዝርያ ጥናት በስፋትና በጥልቀት ሰለሚመመረምሩ ነው፡፡ ኢንግላንድ፣ ንብረቷን ወጣ አድርጋ ብዙ ቫይረሶችን በመመርመሯ ምክንያት በህብረተሰቡ ውስጥ እየተሠራጨ ያለውን ቫይረስ ቶሎ ማወቅ ችላለች፡፡ በአንፃሩ፣ አሜሪካ ይህንን ነገር የጀመረችው በቅርብ ጊዜ ሲሆን፣ ይሀ ፅሁፍ እስከወጣበት ጊዜ 57ሺ ቫይረሶችን ብቻ ነው የመመረመረችው፡፡ ሰለዚህ አሜሪካ ውስጥ ምን አይነት የቫይረስ ዝርያ እንደሚሠራጭ በውል ማወቅም አይቻልም፡፡ ኢትዮጵያም ቢሆን፣ እኔ እሰከ አሁን እሰከማውቀው ድረስ ምን አይነት የቫይረስ ዝርያ ነው ለሚለው የቀረበ ጥናት አልሰማሁም፡፡ ወደ አሳሳቢው ክፍል እንሂድ ከዚህ ቀደም ይህን ጉዳይ፣ ወደፊት ሊከሰቱ ከሚችሉ አደጋዎች አንዱ ነው በማለት ምክር ስንሠጥ ሰንብተናል፡፡ ትልቁ ጥያቄ፣ አዲሱ ቫይረስ ወይም ዝርያ፣ በውስጡ በተደረገው የፕሮቲን ለውጥ ምክንያት የባህሪ ለውጥ አሳይቷል ወይ ነው፡፡ ከፕሮቲኖቹስ የትኞቹ ናቸው ለውጥ እየታየባቸው ያለው የሚለው ቀደም ያለውን ጥያቄ ያጠናክረዋል፡፡ ባህሪን በሚመለከት አንድ ሁለት ልበል፡፡ አንደኛ፡ የመራባት ችሎታ፡፡ ይህ ሳኮ ቁ 2፣ ከጠዋቱም ቢሆን፣ ከዘመዶቹ ከመጀመሪያው ሳርስና (SARS) ከሚድል ኢስት ኮሮና ቫይረስ (MERS Co virus) በበለጠ መራባት ይችላል፣ ለዚህም ጥናቶች አሉ፡፡ የጎሽ ድረ ገፅም ላይ ቢሆን ተቀምጧል፡፡ መራባት ሲባል፣ ቫይረሱ ወደ ሰውነት ሲዘልቅ በሰውነት ውስጠ ከሚገኝ ACE 2 ከሚባል ሞሎኪል ጋር በመጣበቅ ነው ወደሌላ የሚስፋፋው፡፡ ሰለዚህ ከዚህ ሞሎኪል ጋር በቀላሉና በፍጥነት ከዛም ጠንከር ያለ የመጣበቅ ሁኔታ ካለው ወደ ሰውነት ወስጥ ቶሎ የመዝለቅ ባህሪ ይኖረዋል ማለት ነው፡፡ በዚህ ምክንያት ደግሞ፣ ከሰው ወደ ሰው ለመሻገር አስፈላጊ የሚሆነው የቫይረስ መጠን ያንሳል ማለት ነው፡፡ ማለት ለመጠነኛ የቫይረስ መጠን መጋለጥ ወደ ኢንፌክሽን ይቀየራል ማለት ነው፡፡ ሌላው ከዚህ ጋር በተያያዘ፣ አዲስ ባገኘው ባህሪ ምክንያት ቫይረሱ በመተንፈሻ አካላት ላይ ከመጠን በላይ የሚራባ ከሆነ፣ በተለይም የላይኛው የመተንፈሻ ክፍሎች፣ ሰዎች በሚያስሉበት፣ በሚያስነጥሱበት፣ ጮክ ብለው በሚናገሩበት፣ በሚዘምሩበት፣ ከባድ ትንፋሽ በሚተነፍሱበት ጊዜ ብቻ ሳይሆን፣ በመደበኛ ንግግር በሚወጣው ትንፈሻቸው ክምር ክምር ቫይረስ ያዘልቃሉ ማለት ነው፡፡ ይህ ነው አንግዲህ በፐርስንት እየተጠቀስ፣ እነዚህ አዳዲስ ዝርያዎች ቀድሞ ከተከሰቱት ቫይረሶች በዚህ መጠን ከፍ ባለ ሁኔታ ይታላለፋሉ የሚባለው፡፡ ለቫይረሶች የከፋ ጉዳት ለማስከተል አንዱ ባህሪ ይህ በፍጥነትና በብዛት መሸጋገር መቻል ነው፡፡ ለምሳሌ ለመጥቀስ፣ መተላለፍን በተመለከተ፣ አንደኛ ደረጃነቱን የያዘው ቫይረሰ ሚዝልስ ወይም ኩፍኝ ነው፡፡ በኩፍኝ ቫይረስ ከተጋለጡ አስር ሰዎች፣ ዘጠኙ ይያዛሉ (ዘጠና ፐርስንት መተላለፍ)፡፡ መግቢያ ላይ የጠቀስኩት ትልቅ ሰው የነገሩንን ነገር እዚህ ላስገባ፡፡ ስውየው የተናገሩት የሰሙትን ነው፡፡ እናም ቫይረሱ በአይን ይተላለፋል ሰለዚህ ትክ ብለህ አትየኝ እሰከማለተ ተደርሷል ነው፡፡ ይህ አባባል ትክክለኛ ክፍልም አለው፣ የተሳሳተ ክፍልም አለው፡፡ ቫይረሱ በአፍ፣ በአፍንጫ በአይን ላይ ካረፈ እንደሚተላለፍ ይታወቃል፡፡ ይህ የሚሆነው፣ እነዚህ ክፈሎች፣ የአፍንጫ ውስጥ፣ የአፍ ውስጥና አይን በመደኛው የውጭ ቆዳ ሳልተሸፈኑ መከላከል አይችሉም፡፡ እናም አውነት ነው በአይን ይተላለፋል፤ ለዚህም ነው ህክምና ቦታ ላይ ተደራቢ የፊት መሸፈኛ ፕላሰቲክ የሚለበሰው ወይም የአይን መሸፈኛ መነፀርም የሚደረገው፡፡ ትክክል ያልሆነው በአይን በኩል መግቢያ እንጂ መውጫ አይደለም፣ አፍና አፍንጫ ግን የተለየ ታሪክ ነው፡፡ በውስጥ የተከመረው ቫይረስ፣ በተነፈስንና በተናገርን ቁጥር ወደ ውጭ ይወጣል፣ በአይናችን በኩል ግን ቫይረስ አይወጣም፡፡ ትክ ብሎ ማየቱ ሳይሆን፣ አፍና አፍንጫውን ካልሸፈነ፣ ምን ለማድረግ እንጠጋለን፡፡ የሚፈጠሩ የባህሪ ለውጦችን በሚመለከት ተጨማሪ ሁለተኛ፡፡ በባህሪ ለውጥ ምክንያት ሀይል ከጨመረ፣ ከፍተኛ ደረጃ ህመም ወይም የመግደል ችሎታው ይጨምር ይሆን የሚል ትልቅ ፍራቻ አለ፡፡ ይህ ደግሞ መላ ምት ብቻ አይደለም፣ ከዚህ ቀደም በሌሎች ቫይረስ ለምሳሌ የ1918 የስፓኒሽ ፍሉ፣ በአገር ቤት ደግሞ የህዳር በሽታን ያስከተለው ቫይረስ፣ ሲለዋወጥ ከርሞ ነው መግደል የጀመረው፡፡ አሁን ታዩ በተባሉት አዲስ ቫይረሶች፣ የበሽታ መክፋትና ተጨማሪ ሞት አልታየም ተብሏል፡፡ ነገር ግን ጥናት ያስፈልገዋል፡፡ ለምን? በሰውነት ውስጥ የቫይረሱ መጠን በጣም ከፍ ባለ ቁጥር ህመም እንደሚከብድ የሚታወቅ ነገር ስላለ ነው፡፡ ሶሰተኛ፡፡ አሁን በሥራ ላይ ያሉት ክትባቶች ላይሠሩ የሚችሉበት ሁኔታ ይኖር ይሆን የሚል አሳሳቢ ጥያቄ አለ፡፡ እንግዲህ ከላይ ሳብራራ፣ በኮድ ለውጥ ምክንያት የቫይረሶች ፕሮቲኖች የሚቀየሩ ከሆነ፣ የትኛው ፕሮቲን ነው ይህን ለውጥ ያሳያው፣ ካሳየስ የባህሪ ለውጥ አለ ወይ ነው፡፡ በዚህ ቫይረስ ወሳኝ ፕሮቲን ሆኖ የተገኘው ሰፓይክ ፕሮቲን ነው፡፡ በርግጥ በዚህ ፕሮቲን ላይ፣ 23 ቦታዎች የአሚኖ አሲድ ለውጦች ታይተዋል፡፡ ለውጡም ቫይረሱ ከሞሎኪል ጋር የሚገናኝበት ቦታን ነካክቷል፡፡ ነገር ግን እሰካሁን በመጠኑ ነው፣ እናም በፕሮቲኑ ላይ የተያው የኮድ ለውጥ ክትባቱን እንደማይሠራ አያደርገውም ነው፡፡ ያ ግን አስከመቼ እንደሆነ አይታወቅም፡፡ እናም ከዚህ ቫይረስ ጋር የግድ መሽቀዳደም ይኖርብናል፡፡ ሌላ ዝርያ ከመፍጠሩ በፊት፣ በቁጥጥር ሥር ማድረግ፣ ያ ደግሞ ሥርጭቱን ለመግታት የሚደረጉ ተግባራትን መከተል ነው፡፡ አለዚያ ሁሉም በሚገባ ቢከተብ ግን ክትባቱን ማምለጥ የሚችል ፕሮቲን ያለው ቫይረሰ በቀላሉ እንደገና ይሠራጫል ማለት ነው፡፡ እዚህ ላይ የሰውነት መከላከያ አቅም፣ የቫይረሱ መታወቂያ አድርጎ ዘግቦ የያዘው ይህንን የስፓይክ ፕሮቲን ከሆነ፣ ቫይረሱ ደግሞ የሰፓይክ ፕሮቲኑን
Show all...
ቀይሮ አዲስ ካደረገው፣ የመከላከያ አቅሙ ዘግቦ ከያዘው ፕሮቲን የተለየ ከሆነ፣ የተሠራው የተፈጥሮ አንቲቦዲ አግልጎሎት ላይ አይውልም፡፡ በቀላል አማርኛ፣ ፖሊስ ክትትል የሚያደርገው በፀጉር ቀለም፣ በመታወቂያ ከሆነ፣ ይህንን መቀየር የቻለ ተፈላጊ ያመልጣል ማለት ነው፡፡ ይህም እንዱ አደጋ ነው፡፡ በነገራችን ላይ፣ ይህን የፕሮቲን መሥሪያ ኮድ መቀየርና ፕሮቲኖችን (የቫይረሶች) ማለቴ ነው ባህሪያቸውን መቀየር መቻል፣ ለተላላፊ ባለሙያኞች የእለት ከእለት ክትትል የሚያደርጉበት ነገር ነው፡፡ ያም እንደ ኤች አይ ቪ፣ ሄፓታይትስ ሲ ና ቢ የተባሉ ቫይረሶችን የምናክም ሰዎች፡፡ Mutation and mutation codes የሚባሉ ነገሮች በሥራ ላይ የምንጠቅምባቸው ነገሮች ናቸው፡፡ ይህ ደግሞ የሚሆነው፣ የተሠሩት መድሃኒቶች የቫይረሱን አንድ ክፍል ፕሮቲን (ኤንዛይም) ኢላማ ሰለሚያደርጉ ነው፡፡ ቫይረሱ ያንን ፕሮቲን ሲቀይር መድሐኒቱ አይሠራም ሰለዚህ አስቀድመን ማወቅና መቀየር አለብን፡፡ እናም በቀላሉ ጂኖታይፕ የሚባሉ የላቦራቶር ምርመራ በማድርግ ቫይረሱ መድሐኒቱ ኢላማ ያደረገውን ፕሮቲን መቀየርና አለመቀየሩን ለማወቅ እንሞክራለን፡፡ መድሐኒቱ በቫይረሱ ላይ የማይሠራበትን ቫይረስ (Resistance virus) እንለዋለን፡፡ እናም በዚህ ቫይረስም፣ ለህክምና የሚውሉት መድሐኒቶችም አደጋ ላይ ሊወድቁ እንደሚችሉ ነው፡፡ አራተኛ፡ እምብዛም የማይነገረው አደጋ ደግሞ፣ የላቦራቶር ምርመራ ነው፡፡ ቫይረሶችን ለይቶ ለማወቅ የተለዩ የቫይረሱን አካላት በምርመራ ተለይተው እንዲታወቁ ይደረጋል፡፡ እናም ለቫይረሱ እንደመለያ የሆኑት የቫይረሱ አካሎች (ፕሮቲኖች) ከተቀየሩ፣ መመርመሪያው መንገድ ሳያውቃቸው ይቀርና፣ ቫይረሱ እያለ፣ የላቦራቶሪው ውጤት ቫይረሱ የለም የሚል ይሆናል፡፡ (False negative)፡፡ እሰካሁን ድረስ በሳርስ ኮ ቫይረሰ ቁ2 በኩል ይህ ሥጋት የለም፡፡ ምክንያቱም ቫይረሱን ለመለየት እንደመታወቂያ ተጠንተው በላቦራቶሪ በኩል የሚፈለጉት የቫይረሱ የፕሮቲን መጠኖች ብዛት ያላቸው ናቸው፡፡ በተወሰኑ ብቻ አየደለም፡፡ ሰለዚህ ቫይረሱ ከላቦራቶሪ ምርመራ ለማምለጥ ብዙ ፕሮቲኖችን መቀየር ወይም ብዛት ያላቸው mutation ማደረግ አለበት፡፡ አስካሁን አልሆነም፡፡ ያም ሆኖ ሥጋቱ ሰላለ፣ የዚህን ቫይረስ ሥርጭት በፍጥነት ማድከምና ማስቆም ይኖርብናል፡፡ እዚህ ላይ ግን ሁሉም ተባባሪ መሆን አለበት፡፡ ሰለዚህ ቫይረሰ፣ መከላከያ፣ መመርመሪያ መንገዶች አዲስ አይደሉም፡፡ አዲስ የሆነው ቫይረሱና ባህሪው ነው፡፡ ሰለዚህ ትንሽም ቢሆን ማብራራቱን ጉዳዩን ለሚያውቁ ሰዎች ማድረግ ጥሩ ነው፡፡ የጓደኛና የጎረቤት ኤክስፐርቶቸን፣ አንድ ላይ እናንብብ ብሎ መልካም ምክር መለገስ ጥሩ ነው፡፡ ከመዝጋቴ በፊት፣ ሰለ አዲሶቹ ክትባቶች አንድ ልበል፡፡ ከላይ እንደጠቀስኩላችሁ፣ ፕሮቲን ሲመረት፣ ከጀርባው ትዛዙን የያዘውን ኮድ ይዞ የሚመጣው mRNA መልክተኛው ነው፡፡ መልክተኛው፣ የተወሰኑ ኮዶች ለተወሰነ የፕሮቲን አይነት ይዞ ነው የሚመጣው፡፡ ይህ እንግዲህ ሰውነታቸን በህይወት ዘመኑ በየቀኑ የሚያደርገው የተፈጥሮ ሂደት ነው፡፡ ሂደቱ እንግዳ አይደለም፡፡ ሀኪሞቹና ሳይንቲሰቶቹ እየጣሩ ያሉት በተፈጥሮ የሚታዩትን የመከላከያ መንገዶች በመኮረጅ ለመጠቀም ነው፡፡ እንጂ አንዳንዶቸ በስፋት እንደሚያወሩት የተለየ ፀረ- ሰው ባሕሪ ያለው ነገር ለመሥራትም አይደለም፡፡ እንግዲህ ክትባቶቹ፣ ከውጭ የሚዘጋጁት ሰውነት ውስጥ ከገቡ በኋላ፣ ሰፓይክ የተባለውን ፕሮቲን ብቻ እንዲመረት የሚያደርግ ትዛዙን የያዘ mRNA መሥጠት ነው፡፡ በሴሎች በተለይም በጡንቻ ሴሎች ውስጥ፣ ይህ ከውጭ የተዘጋጀው mRNA በሴሉ ውስጥ ይሆንና ስፓይክ ፕሮቲን እንዲሠራ ያደርጋል፡፡ ልብ ብሉ፣ ያ የሚሠራው ስፓይክ ፕሮቲን አሁን በመዘዋወር ላይ ያሉ ቫይረሶች ወደ ሰውነት ለመግባት የሚጠቀሙበት ስፓይክ ፕሮቲን ቅጅ ወይም አምሳያ ነው፡፡ ፕሮቲኑ ከተሠራ በኋላ፣ ከውጭ በክትባት በኩል የተሠጠው mRNA ወዲያውኑ ከሴሉ ይወገዳል፡፡ ሴሎቹ ራሳቸውን የማፅዳት ችሎታ አላቸው፡፡ ሰለዚህ የሚቀር ነገር የለም፡፡ ሌላው ጠቀሜታ፣ ሰውነት የራሱን መከላከይ ለማበጀት ስፓይክ ፕሮቲኑን ኢላማ ለማድረግ አንድ ሰው በቫይረሱ መያዝ አለበት፣ ነገር ግን በዚህ የክትባት መንገድ ያ አስፈላጊ አይደለም፣ ፕሮቲኑን ብቻ ማዘጋጀት ነው፡፡ ፕሮቲኑ ብቻውን ደግሞ መራባት የሚችል ቫይረስ ቀርቶ ቫይረስም አይሆነም፣ ሰለዚህ ለቫይረሱ ሳይጋለጡ በአቋራጭ የቫይረሱን መታወቂያ ማግኘት ነው፡፡ ሌላው ነገር ደግሞ፣ mRNA ወደ ሴሉ አስኳል አይገባም፡፡ የሴል አስኳል፣ የተከበረ ቦታ ነው፣ ለምን የዘር ሀረጋችን የሚተረጉመው DNA የሚባለው የዘር ስንሰለት እዛ ውስጥ ነው ያለው፡፡ ሰለዚህ በክትባት በኩል የተሠጠው mRNA በጣም ውሱን ሥር ብቻ የሚሠራ ከመሆኑ ባሻገር ወደ አስኳሉ ሰለማይገባ ከዘር ሀረጋችን ጋር ንክኪ የለውም፡፡ ሰፓይክ ፕሮቲኑ ከተሠራ በኋላ ገና ከጡንቻ ሴሎች ብቅ ከማለቱ፣ የሰውነታችን የስለላ ክፍልና መከላከያ ክፍሉ ይህንን አዲስ ፀጉረ-ልውጥ ፕሮቲን ይመዘግብና መደመስሻ አንቲቦዲ ያዘጋጅለታል፡፡ ያ ብቻ ሳይሆን፣ በደንብ በጠላትነት ፈርጆ ሰለመዘገበው፣ በሚቀጥለው ይህንን ፕሮቲን የያዘው ውነተኛው ቫይረስ ብቅ ሲል፣ ለዚህ ጉዳይ የተመደቡ ሴሎችና አንቲቦዲዎች በፍጥነት ተንቀሳቀሰው ፐሮቲኑን ከነቫይረሱ ያመክኑታል፡፡ በዚሀ መንገድ በቫይረሱ ከመያዝ ከዛም አስተላለፊ ከመሆን እንድናለን ማለት ነው፡፡ አንግዲህ ክትባት ማለት ሚስጥሩ ይሀ ነው፡፡ የተፈጥሮ መከላከያን ማንቃትና ማዘጋጀት ነው፡፡ ዘዴው ነው ዋናው፡፡ ይህ ዘዴ ወይም የክትባት አሠጣጥ አሁን ተሳክቶ ሥራ ላይ ዋለ እንጂ ከ1990 ጀምሮ ጥናት ላይ የነበረ ነው፡፡ ለማንኛውም በዚህ ላቁም አካፍሉ ከምሰጋና ጋር
Show all...
አዲስ የኮሮና ቫይረሶች መከሰት ምን አደጋ አለው? ከ Gosh Health የተወሰደ ------ በቅርቡ በብዙሀን መገናኛ የኮሮና ቫይረስ ቁጥር 2 አዲስ ዝርያዎች በኢንግላንድና በደቡብ አፍሪካ መከሰታቸው እየተገለፀ፣ ከመልስ ይልቅ ብዙ ጥያቄ ያስነሳ ጉዳይ ሆኗል፡፡ በባለሙያተኞቹ በኩል፣ ርዕሱ ወይም ጉዳዩ በብዙሀን መገናኛ መገለፁን የወደድነው ቢሆንም ለብዙ ትርጉም መጋለጡን ስናይ ደግሞ አሳሳቢነቱ የሚጨምር ነገር አድርጎታል፡፡ ሰለዚህ፣ ትክክለኛውን ማብራሪያ መሥጠት የግድ ነው፡፡ የብዙ ሰዎች ጥያቄም ነው፡፡ አንድ ትልቅ ሰውም፣ ይህ ነገር ማለትም፣ በሥርጭት በኩል አዳዲሶቹ ቫይረሶች ከድሮዎች ከሰባ ከመቶ በላይ ነው ማለት ምንድን ነው ብለው ጠየቁ፡፡ አስከትለው የተናገሩት ነገር ደግሞ ፈገግ እንድንል ቢያደርገንም ማብራራት እንዳለብን ግዴታውን ጨምሮታል፡፡ ምን እንዳሉ በኋላ ልመለስበት፡፡ በቃላት እንጀምር፣ አዲስ እንበላቸው፣ የተከሰቱት መጠሪያ በአንግሊዝኛ በተለያዩ ቃላት ሰለሚጠቀሱ እነሱንም መጥቀስ አለብን በእንግሊዝኛው አጠራር variants, strains or lineage ተብለው ይጠራሉ፡፡ በአማርኛ ዝርያ በማለት ለመጥራት እንስማማ፡፡ ከዚህ ቀደምም ቢሆን ይህ ቫይረስ (ሳርስ ኮሮና ቁ 2) ሳኮ-2፣ ዝርያውን እየቀየረ እንደሚሄድ ለማስገንዘብም ለማስጠንቀቅም ሞክረናል፡፡ በታህሣስ መጨረሻ የተከሰተው አባት ቫይረስ መሠራጨት ከጀመረ በኋላ ብዙም ሳይቆይ በተለያዩ የአለም ክፍሎች የተለያዩ ከዚሁ አባት ቫይረስ የሆኑ ግን በዝርያ በመጠኑም ለየት ያሉ ቫይረሶች ተከስተዋል፡፡ ለምንድን ነው አዲስ ዝርያ የሚከሰተው ለሚለው ጥያቄ መልስ ለመስጠት፣ ወደኋላ ወደ ፕሮቲን አሠራር መመለስ የግድ ነው፡፡ ፕሮቲኖች ባጠቃላይ የአንድ አካል፣ የሰውም ይሁን የእንሰሳ፣ የቫይረስም ይሁን የባክቴርያ መሠረታዊ የግንባታ አካል ናቸው፡፡ ፕሮቲኖች ሲሰሩ ግን፣ እያንዳንዱን ፕሮቲን የተለየ አድርጎ እንዲወጣ የሚያደርጉት የዘር ስንሰለት ኮዶች አሉ፡፡ ለምሳሌ በሰዎች ላይ ብንመለከት፣ የሰው የዘር ሀረግ (ዲ ኤን ኤ DNA) የሚቀመጠው በሴሎች አስኳል ውስጥ ነው፡፡ (Nucleus) ማለት ነው፡፡ ይህ የዘር ሀረግ ኮድ፣ እንደ አንገት ሀብል ሰንሰለቶች የተቀጣጠሉ ወይም የተያያዙ ንጥሮች በድርብ መስመር ተጠቅለውይገኙበታል፡፡ ሁሉም የሰውነት ክፍላችን ከሴሎች ጀምሮ ሌሎቹም ምን መመስል እንዳለባቸው ትዕዛዙ የሚመነጨው ከዚህ የዘር ሀረግ ነው፡፡ እንግዲህ እንድን ፕሮቲን መስራት ሲያስፈልግ፣ ከዘር ሀረጉ የተወሰነ ክፍል፣ የሚሠራውን ፕሮቲን አይነት ትዛዝ የሚሠጥ ኮድ ይመረጣል፡፡ ነገር ግን ይህ የዘር ሀረግ ከአስኳሉ ሰለማይወጣ፣ ሌላ መልክተኛ ኮድ ተሸካሚ ነገር ያስፈልጋል፡፡ ያ መልክተኛ ከዘር ሀረጉ የሚያስፈልጉትን ኮዶች ብቻ ይገለብጥና ወደ ሴሎች ዋና አካል ለመሄድ ከአስኳሉ ይዘልቃል፡፡ ገምታችሁ ከሆነ፣ ያ የኮዱን መልክት ይዞ የወጣው ነገር መልክተኛው አር ኤን ኤ messanger RNA(mRNA) ይባላል፡፡ ክትባቶችንም ለማብራራ እንዲመች ጠለቅ ማለት ነበረብኝ፡፡ እንግዲህ የኮዱን መልክት የያዘው መልክተኛው፣ ነጠላ ሰንሰለት ነው፣ በሴሎቹ ክፍል፣ ከአስኳሉ ውጭ፣ ኮዱን በመተርጎም የተባለውን ፕሮቲን እንዲሠራ ያደርጋል ማለት ነው፡፡ እንግዲህ ፕሮቲኖቸ ሲሰሩ ደግሞ በውስጣቸው እንደ ግንባታ መሠረት የሚሆኑት በኋላም ተቀጣጥለው የፕሮቲኑን ምንነት የሚወስኑት አሚኖ አሲድ የሚባሉ ነገሮች አሉ፡፡ እነዚህ አሚኖ አሲዶች በአይነትና በተራ ቁጥር በሥነ ሠርአት ተቀጣጥለው መቀመጥ አለባቸው፡፡ አንዱ አሚኖ አሲድ በተራ ቁጥሩ ላይ በሌላ አሚኖ አሲድ ሲተካ፣ ፕሮቲኑን ከመሠረታዊ ግንባታው ባያናጋውም የተለየ ባህሪ ሊፈጥርበት ይችላል፡፡ ይህ በተራ ቁጥር የተቀመጡ አሚኖ አሲዶች አንዱ በሌላው ሲተኩ በእንግሊዝኛ mutation ይባላል፡፡ ወደ ፕሮቲኖች ስንመለስ፣ እያንዳንዱ ፕሮቲን ሲሠራ የራሱ የሆነ የተለየ ተልዕኮ ወይም መገለጫ አለው፡፡ መገለጫም ብቻ ሳይሆን አገልግሎት ወይም ሥራው ለራሱ የብቻ ነው የሚሆነው፡፡ አንግዲህ ቫይረሶችም ቢሆን ከተለያየ ፕሮቲኖች የተገነቡ ናቸው፡፡ እያንዳንዱ የቫይረሱ አካልም የተለያዩ ፕሮቲኖች ውጤት ነው፡፡ ለምሳሌ የሳኮ ቁ 2 ቫይረስ፣ በምስሎች ላይ የምታዩት በአካሉ ላይ ቁጭ ቁጭ ብለው የሚታዩት ነገሮች ስፓይክ ፕሮቲን Spike protein ተብለው ነው የሚጠሩት፡፡ እነዚህ የቫይረሱ ክፍሎች ላይ የምናተኩረው፣ ቫይረሱ ወደ ሰውነት ለመግባት የሚጠቀምባቸው ፕሮቲኖች ሰለሆኑ ነው፡፡ በርግጥ ቫይረሱ በዙ ሌሎች ፕሮቲኖች አሉት፡፡ አሁን ክትባትም ሆነ፣ የሰውነት የውስጥ መከላከያ ኢላማ ያደረጉት የቫይረሱ አካል ይህ የተጠቀሰውን ሰፓይክ ፕሮቲን ነው፡፡ ለምን ከተባለ፣ ቫይረሱ አንደ መግቢያ ቁልፍ አድርጎ የሚጠቀምበት አካሉ ከሆነ፣ ይህንን ቁልፍ ማሰናከል ወይም ማምከን፣ ቫይረሱ ወደ ሰውነት ሴሎች እንዳይዘልቅና እንዳይራባ ያደርገዋል፡፡ አንደዛ ከሆነ ደግሞ በሽታ መያዝ ቀርቶ፣ ተራብቶ መልሶ ሌላ ሰው መያዝ የሚችል ቫይረስ ሰለማይኖር ሥርጭት ይቆማል ነው፡፡ ይህ ነው ትልቁ የክትባትም ሆነ የተፈጥሮ መከላከያ ሚስጥር፡፡ ከዚህ ቀደም ሳኮ ቁ 2 ቫይረስ የተለያዩ ዝርያዎችን እየፈጠረና አዲስ የተፈጠሩት ቫይረሶችም እየተባዙና እየተሠራጩ እየሄዱ እንደሆን እየገለፅንም ነበር፡፡ አዲስ ዝርያ ቫይረስ የሚፈጠረው፣ ፕሮቲኖች እንዲሠሩ የሚያዘው ኮድ በመጠኑ ለወጥ ካለ፣ ቀደም ተብሎ የተጠቀሱት የፕሮቲኑ መሠረታዊ የግንባታ አካላት የሆኑት አሚኖ አሲዶች አንዱ በሌላው ሲተካ፣ የተሠራው ፕሮቲን ከመጀመሪያው ቫይረስ ፕሮቲን እየተለወጠ ይሄዳል ማለት ነው፡፡ ይህ በመሠረቱ የዝርያ ለውጥ እንደሆነ ነው የሚያሳየው፡፡ አንግዲህ በዘር ወይም በኮድ ለየት ያለ ፕሮቲን ያለው ቫይረስ አዲስ ዝርያ ነው የሚሆነው፡፡ አዲስ ዝርያዎችም የየራሳቸው ስም ይሠጣቸዋል፡፡ ሌላው ወሳኝ ጥያቄ፣ አዲሱ ቫይረስ ላይ በመጠኑም ይሁኑ በስፋት የተለወጠው የቫይረሱ የትኛው ፕሮቲን ነው የሚለው ነው፡፡ ቫይረሱ ወደ ሰውነት ለመግባት፣ ከዛም በሰውነት ውስጥ በሰዎች ውስጥ ካለው የተለየ ሞሎኪል ጋር የሚገናኝበት ፕሮቲን፣ ለቫይረሱ ወሳኝ ነው፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ፣ የሰው የሰውነት መከላከያ ይህን ሳኮ ቫይረሰ ቁ 2ን የሚያውቀውና ዘግቦ የሚያስቀምጠው፣ ከዛም ወደ ማጥቃት የሚሄደው ይህንኑ የመግቢያ ፕሮቲኑን (ስፓይክ ፕሮቲን) ነው፡፡ ከዚህ በተጨማሪ፣ በውጭ የተሠራው ክትባት ደግሞ ኢላማ አድርጎ የተሠራው፣ ይህንን ስፓይክ ፕሮቲን ለሰው ሰውነት ተለይቶ እንዲታወቅ በማድርግ ሰውነት የራሱን መከላከያ እንዲያበጅ ነው፡፡ ቫይረሶች ከአንድ ሰው ዘለው ወደሌላ ሰው ከተሻገሩ በኋላ፣ መጀመሪያ የሚያደርጉት ነገር መራባት ነው፡፡ የሚራቡትም በሰው ሰውነት ሴሎች ኪሳራ ነው፡፡ ይህ ባጠቃላይ RNA Virus ተብለው የሚጠሩ ቫይረሶች ባህሪ ነው፡፡ በቀላሉ ሲነገር፣ በሰው ጎጆ ሌጣውን ወይም ብቻውን ገብቶ ልጆቹን እንደመውለድ ማለት ነው፡፡ አዚህ ላይ ቫይረሶቹ፣ mRNA በመጠቀም ኮዱን እያሰተረጎሙ የተለያዩ የቫይሱን ፕሮቲኖች ሲገነቡ፣ ከብዛት የተነሳ፣ ኮድ ግልበጣው ላይ ስህተት ይፈጠራል፡፡ ሰህተቱ ትርጉሙ ላይ፣ ወይም የሚሠራው ፕሮቲን ላይ ነው፡፡ የፕሮቲኑ ለውጥ ከመጀመሪያው ፕሮቲን ምን ያህል በጥልቀት ወይም በርቀት መቀየሩ ወሳኝ ነገር ነው፡፡ እንግዲህ ልብ ማለት ያለብን፣ የተለያዬ የቫይረሱ ፕሮቲኖች በመጠኑ መቀየር ቫይረሱን እንዳለ በትልቅ ዝርያ ወደ ሌላ ቫይረስ አይቀይረውም ግን ከተነሳበት
Show all...
በደቡብ ክልል ጭንብል የማድረግ ግዴታ ተጣለ! በደቡብ ክልል የኮሮና ስጋትን ለመከላከል የክልሉ ነዋሪዎች የአፍና አፍንጫ መሸፈኛ ጭንብል የማድረግ ግዴታ እንዳለባቸው የደቡብ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ርስቱ ይርዳው አስታውቀዋል።ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ ማምሻውን ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ የክልሉ ህዝብ ኮሮናን በመከላከል በኩል እያሳየ ያለው ከልክ ያለፈ ቸልተኝነት አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረሱን ገልጸው ቀደም ሲል የቫይረሱን ስርጭት ለመከላከል ይደረግ የነበረው ጥንቃቄ አሁን ላይ ሊደረግ እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡የበሽታው ባህሪ እየተቀየረና የሚያደርሰው ጉዳት መጠን እየጨመረ በመምጣቱ "ጥንቃቄያችንን የምናጠናክርበት እንጂ የምንዘናጋበት አይደለም" ብለዋል። የበሽታው ሥርጭት እየጨመረና አሳሳቢ ደረጃ ላይ ከመድረሱ ጋር ተያይዞ የክልሉ ህዝብ ተገቢውን ጥንቃቄ እንዲያደርግ አሳስበዋል።ተገልጋዩ ህብረተሰብ ወደ ማንኛውም የመንግስትና አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ሲሄድ የአፍና አፍንጫ መሸፈኛ ጭንብል የመጠቀም ግዴታ እንዳለበትም አስታውቀዋል።የክልሉ ጤና ቢሮ ኃላፊ አቶ አቅናው ካውዛ በበኩላቸው በክልሉ የኮሮና ወረርሽኝ ስርጭት አሳሰቢ ደረጃ ላይ መድረሱን ገልጸዋል። እስካሁን በክልሉ ከ150 ሺህ በላይ ምርመራ ከተደረገላቸው ሰዎች መካከል ከ4 ሺህ 300 በላይ ቫይረሱ እንደተገኘባቸው አመልክተው፤ 46 ሰዎች ደግሞ በበሽታው ሳቢያ ህይወታቸው ማለፉን አውስተዋል።በተለይ የመተንፈሻ መሳሪያዎች እጥረት እያጋጠመ በመሆኑ አሁን ያለንበት ሁኔታ አሳሳቢ ነው ብለዋል።የ"መካኒካል ቬንትሌተር" አቅርቦትም በቂ አለመሆኑን ያነሱት አቶ አቅናው አስከፊ ሁኔታ ከመፈጠሩ በፊት በህብረተሰቡ ዘንድ የሚታየው መዘናጋት እንዲቆም መልዕክት ማስተላፋቸውን ኢዜአ ዘግቧል። @ETHIOPIATENA
Show all...
አዲሱ የኮሮና ቫይረስ ዝርያ ኢትዮጵያንም እንደሚያሰጋ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት አስታወቀ። በእንግሊዝና ደቡብ አፍሪካ የተገኘው አዲሱ የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ኢትዮጵያን ያሰጋታል ተብሏል። የህብረተሰብ ጤና ኢንስትቲዩት የአስቸኳይ ማስተባበሪያ ማዕከል የኮቪድ 19 ምላሽ ምክትል አስተባባሪ አቶ ዘውዱ አሰፋ ለኢትዮ ኤፍ ኤም እንደተናገሩት የኮሮና ቫይረስ ራሱን ቀይሮ ሊመጣ እንደሚችል ይጠበቅ ነበር ብለዋል፡፡ ሆኖም ግን አሁን የተገኘው ቫይረስም እንደሌሎች የአለም ሀገራት ሁሉ ኢትዮጵያንም ያሰጋታል ሲሉ ተናግረዋል፡፡ ቫይረሱ እስካሁን ወደ ኢትዮጵያ ስለመግባቱ የሚያመላክት መረጃ የለም ያሉት አቶ ዘውዱ ህብረተሰቡ እራሱን ከቫይረሱ መከላከል የሚያስችሉ የመከላከል እርምጃዎችን ማድረጉን እንዲቀጥል አሳስበዋል። ለዚህም የቫይረሱ አሁንም ያልታወቁ ባህሪያት መኖርን እንደምክንያት ጠቅሰዋል፡፡ ሆኖም አስቀድሞ ለመከላከል ጤና ሚኒስቴርና ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት እያደረጉ እንዳለ ነግረውናል። አዲሱ የኮሮና ቫይረስ ዝርያ ለመጀመርያ ጊዜ በእንግሊዝ የተከሰተ ሲሆን አገሪቱ የቫይረሱ ስርጭት ከአቅሟ በላይ መሆኑን ተከትሎ በርካታ አገራት የጉዞ እገዳ መጣላቸውን ቀጥለዋል። ይህ አዲስ የቫይረስ ዝርያ እስካሁን ከእንግሊዝ ውጭ በዴንማርክ፣ ደቡብ አፍሪካ ፣ አሜሪካ ፣ አውስትራሊያ እና ሌሎች አገራት መከሰቱን የአለም ጤና ድርጅት መረጃ ያስረዳል። አዲሱ የኮሮና ቫይረስ ዝርያ ከቀድሞው በ70 በመቶ የመሰራጨት እድል እንዳለውም ድርጅቱ ገልጿል። ምንጭ - ኢትዮ ኤፍ ኤም
Show all...
ከፍተኛ ስጋትን የደቀነው አዲሱ የኮቪድ ዝርያ ! በርካታ የአውሮፓ አገራት ብሪታኒያ ላይ የጉዞ እቀባ እያደረጉ ነው። ለዚህ ምክንያቱ በብሪታኒያ አዲስ ዓይነት የኮቪድ ዝርያ መገኘቱ ነው። አዲሱ ዝርያ ገና በስፋት ያልተጠና ቢሆንም ከቁጥጥር ውጭ በሆነ መንገድ ከሰው ወደ ሰው ይዛመታል የሚለው ፍርሃት በርካታ አገራትን ድንጋጤ ውስጥ ከቷቸዋል። እስከ አሁን ጀርመን ፣ አየርላንድ፣ ፈረንሳይ፣ ጣሊያንና ኔዘርላንድስ እና ቤልጂየም ሁሉም ወደ ብሪታኒያ የአየር በረራን አቋርጠዋል። ዛሬ የአውሮፓ ኅብረት መሪዎች ስብሰባ ስለሚቀመጡ ከዚህ የባሰ የእቀባ ውሳኔ ሊኖር እንደሚችል እየተጠበቀ ነው። አዲሱ ኮቪድ-19 ዝርያ በለንደንና በደቡብ ምሥራቅ ኢንግላንድ በአጭር ጊዜ ውስጥ ነው በስፋት የተሰራጨው። ጠቅላይ ሚኒስትር ቦሪስ ጆንሰን ቅዳሜ በሰጡት አስቸኳይ ትእዛዝ ደረጃ 4 የጥንቃቄ ደንቦች እንዲከበሩ አዘዋል። ለፈረንጆች ገና እና አዲስ ዓመት የእንቅስቃሴ ገደቦች ይላላሉ ተብሎ ታስቦ የነበረውን ሐሳብ ሰርዘዋል። የጤና ባለሙያዎች አዲሱ የተህዋሲው ዝርያ ይበልጥ ገዳይ ስለመሆኑ ሆነ ለክትባት እጅ የማይሰጥ ስለመሆኑ ገና እርግጠኛ አልሆኑም። ሆኖም ግን ከለመድነው የኮሮና ቫይረስ በ70 በመቶ በይበልጥ የመሰራጨት አቅም አለው መባሉ ማን ይተርፋል ? እንዲባል አድርጓል። የብሪታኒያ የጤና ጥበቃ ሚኒስትር ይህ አዲስ ዝርያ ቫይረስ ከቁጥጥር ውጭ ሆኖብናል ፤ በቁጥጥራችን ልናውለው ይገባል ብለዋል። የዓለም ጤና ድርጅት አዲሱን የኮሮና ቫይረስ ዝርያ በተመለከተ ከዩኬ (UK) ባለሥልጣናት ጋር በቅርበት እየተነጋገረ እንደሆነ አስታውቋል። ምንጭ፦ ቢቢሲ
Show all...
Choose a Different Plan

Your current plan allows analytics for only 5 channels. To get more, please choose a different plan.