en
Feedback
ALCHEMIST WAY

ALCHEMIST WAY

Open in Telegram

HOW TO TRAIN YOUR MIND 🧠 Talk to me 👁 ... @Roba642 ... @Roba642 For Series magic of life training packages Languages : 👂Amharic 👂English 👂Tigregna ,and 👂oromifa

Show more
993
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
-3230 days
Posts Archive
አሁን አሁን በብዛት እየተስተዋለ ስለሚገኘው የወንድ ብልት የመቆም ችግር (erectile dysfunction) ላጋራቹ መጀመሪያ የሰው ልጅ ወሲባዊ ኡደት(Human Sexual Response Cycle) ምንድን ነው? -ተመራማሪዎች ስለ ጤናማ የወሲብ ባህርያቶች ብዙ ብለዋል ከነዚህም መካከከል ማስተርስ እና ጆንሰን የተባሉት ባለሙያዎች የመጀመሪያውን የምርምር ውጤት በ1966-1970 አካባቢ Human sexual response እና Human sexual inadequacy  የሚል መፅሀፎችን አሳትመው ተቀባይነትን አጊንተዋል። -ይህም የሰው ልጅ ወሲባዊ ኡደት አራት የወሲብ ደረጃዎች ጠብቀው የሚከሰቱ የወሲብ ኡደቶች ናቸው ተብሎ ይታሰባል።እነዚህም መነቃቃት(excitement phase)፣ሁለተኛው ደረጃ  (plateau phase) ሙሉ ለሙሉ  የአካልን እና የመራቢያ ክፍሎችን ዝግጁነት ፣ሶስተኛው እርካታ (orgasm phase)ሲሆን ፣አራተኛው ደግሞ መረጋጊያ (Resolution phase) ይህም ከእርካታ በዃላ ዝግጁ የነበሩ የሰውነት  ክፍሎቻችን ወደ ቀድሞ ይዞታቸው የሚመለሱበት ደረጃ ነው። - እሰቲ ስንቶቻችን ነን የወሲብ ችግር አጋጥሞን የህክምና  እርዳታ የጠየቅነው? ስንቶቻችንስ ከፍቅር አጋራችን ጋር የወሲብ ችግሮቻችን በግልጽ የምንነጋገረው? -የወሲብ ችግር ትዳርን እስከማፋረስ፣ ቤተሰብ እስከመበተን የሚያደርስ ችግር ነው። በአለም አቀፍ ደረጃ ይህ ችግር እንደ የአእምሮ ሀመም ይወሰዳል። እኛ ሀገር ላይ ይህን ችግር መናገር እነደ ነውር፣ ከባህል የወጣ ተብሎ የሚቆጠርበት ሁኔታ ይስተዋላል። -አንድ ማወቅ ያለብን ነገር የወሲብ ቸግር  በወንድም በሴትም ምክንያት ሊሆን ይችላል። -እንደ DSM IV የተባለው የሳይኮሎጂ መጽሀፍ የወሲብ ችግሮችን በአራት ይከፍላቸዋል እነዚህም የወሲብ ፍላጎት ችግር (desire disorders)፣ ለወሲብ መነቃቃት ችግር (arousal disorders)፣ የእርካታ ችግር (orgasm disorders) እንዲሁም በወሲብ ጊዜ ህመም (pain disorders) በማለት ይከፍላቸዋል፡፡ በወንዶች ላይ የሚስተዋለው የብልት መቆም ችግር (Erectile dysfunction) ምንድን ነው? -ይህ ችግር  ወንዱ ወሲብ ለማድረግ እንቅስቃሴ ውስጥ ባለበት ወቅት በተለያዩ ምክንያቶች ብልቱ ዝግጁ አልሆን ሲለው ማለት ነው፡፡ ይህ ችግር እድሜ አየጨመረ ሲሄድ በብዛት ይስተዋላል። ነገር ግን በወጣትነት እድሜ ላይ የሚታይበት ሁኔታ አለ። -ይህ ችግር በአለም አቀፍ ደረጃ በሚሊዮን የሚቆጠር ህዝብን ያጠቃል። ምክንያቶቹስ ምን ሊሆኑ ይችላሉ? -ከምክንያቶቹ መካከል አደንዛዥ ዕፅ መጠቀም፣ ድባቴ፣ ጭንቀት፣ የteseterone hormone ማነስ ፣ የደም ግፊት፣ ስኳር በሽታ፣ የልብ ህመም፣ የደም ስር በሽታ፣ የጉበት እና የኩላሊት በሽታ፣ የአልኮል መጠጥ፣ ሲጋራ ማጨስ፣ የአነጎል እና ህብለሰረሰር ጉዳት፣ የኮሌስሮል መጨመር፣ ከመጠን በላይ ውፍረት፣ ስትሮክ በሽታ፣ የእንቅልፍ ችግር፣ የሆርሞን መዛባት፣ የመድሀኒቶች የጎንዮሽ ጉዳት ለምሳሌ ፀረ-ድባቴ (anti depressants ) ፣ ፀረ-ግፊት (antihypertensives) የሚጠቀሙ ሰዎች፣በትዳር መሀል ስጋት እና ፍራቻ መኖር፣ በፍቅር ግኑኝነት መሀል ችግር መኖር እንደ ምክንያትነት ይጠቀሳሉ። ተያያዥ ጉዳቶቹስ ምንድን ናቸው? -በራስ መተማመን ማጣት ፣የፍቅር ግንኙነት መበላሸት፣ ልጅ ለመውለድ መቸገር፣ በራስ ማዘን እና መሸማቀቅ፣ ጭንቀት ፣ ፍራቻ፣ እንዲሁም እስከ ቤተሰብ መበተን ሊያደርስ ይችላል። እንዴት መከላከል እንችላለን? -ጤናማ የሆነ የአኗኗር ዘይቤን መከተል፣ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ማድረግ እና ሌሎች የጤና እክሎች ካሉ በወቅቱ መታከም ተገቢ ነው። በማህበረሰባችን ያሉ የተሳሳቱ አመለካከቶችስ? -አንዳንድ ጊዜ ማህበረሰብ ውስጥ ይህ ችግር በወንድ ብቻ ወይም በሴቷ ብቻ ችግር ነው ብሎ ማሰብ -የዚህ ችግር መኖር እና በግለፅነት ማውራት አንደ ነውር መቁጠር እና -ህክምና እነደሌለው ተደርጎ ማሰብ የህክምና አማራጮቹስ ምንድን ናቸው? -የመጀመሪያው እና ዋነኛው ነገር እንደዚህ አይነት ችግር ሲከሰት በጥነዶች መሀል በግልፅነት መነጋገር እና መወያየት ከዛም መግባባት ይጠበቅባቸዋል። -ከዛም በግልፅነት የጤና ባለሙያ ማማከር፣አንዳንድ ጊዜም የስነ አእምሮ ጤና ባለሙያ ማማከርም አስፈላጊ ሊሆን ይችላል። -ተያያዥ የጤና እክሎች ካሉ መታከም -የሚዋጡ መድሀኒቶች በሀኪም ትእዛዝ እንደ አስፈላጊነቱ ሊታዘዙ ይችላሉ። -የteseterone hormone የመተካት ህክምና አንዲሁም የቀዶ ጥገና ሌሎች የህክምና አማራጮች ናቸው። ጤና ይብዛላቹ ዶ/ር ኤርሚያስ ማሞ

ጨው እና ስኳር ከአንድ ዓመት በታች ላሉ ህፃናት ምግባቸው ላይ መጠቀም አለብን ወይስ የለብንም❓️ 👉 ከአንድ ዓመት በታች ከሆኑ ህፃናት በቀን የሚያስፈልጋቸው ሶድየም በጣም ዝቅተኛ ነው (0.3 - 0.5 mg) ይሄንን ሶድየም መጠን ደሞ ከእናት ጡት ወተት ወይም ከጣሳ ወተት ወይም ከ ሌሎች ምግቦች ማግኘት ስለሚችሉ በተቻለ መጠን ጨው ምግባቸው ላይ መጨመር አይመከርም❗️ ⚠️⚠️ ምግባቸው ላይ ተጨማሪ ጨው የምንጠቀም ከሆነ ምን ይከሰታል?👇 1. የኩላሊት ስራቸው ሊታወክ ይችላል 2. የምግብ ፍላጎታቸው ሊቀንስ ይችላል 3. እድሜያችው እየጨመረ በሄደ ቁጥር የጨው አጠቃቀማቸው እየጨመረ ስለሚሄድ ጨዋማ ምግቦች በማብዛት ያለ እድሜያቸው ደም ግፊት ሊይዛቸው ይቺላል:: 🔊 ስኳርስ ከአንድ ዓመት በታች መጠቀም አለብን ወይስ የለብንም❓️ 👉 ህፃናት በተፈጥሯቸው ጣፋጭ ነገርን ይወዳሉ ስለዚህ ጣፋጭ ይወዳሉ ብለን ምግባቸው ላይ በተከታታይ ስኳር ወይም ሌላ ጣፋጭ የምንጠቀም ከሆነ 1. የምግብ ፍላጎታቸው ይቀንሳል ጣፋጭ ካልሆነ ሌላ ምግብ አልበላም ሊሉ ይችላሉ 2. ጥርሳቸው ሊበላሽ ወይም ሊቦረቦር ይችላል 3. አላስፈላጊ ውፍረት በማምጣት ገና በወጣትነታቸው ለደም ግፊት እና Type 2 የሚባለው ስኳር ህመም ሊጋለጡ ይቺላሉ 🔊 #ጥያቄ 3 : ከ አንድ ዓመት በታች ያሉ ህፃናት ማር መጠቀም ይቺላሉ ወይስ አይቺሉም❓️ምክንያቱስ ምንድነው ❓️ መልሱን ሰኞ በክፍል 2 ፅሁፋችን ላይ እናቀርባለን ይከታተሉን ❤️ መረጃውን ከወደዱት ሌሎችም ወላጆች forward ወይም share ያድርጉት ❤️ አዘጋጅ: ዶ/ር ፋሲል መንበረ (የህፃናት ስፔሻሊስት ሀኪም እና ረዳት ፕሮፌሰር) ‼️💯

የውሸት እርግዝና (pseudocyesis) ምንድነው? 👍Pseudocyesis/ሲውዶሲሲስ (የውሸት እርግዝና) ለብዙ መቶ ዘመናት የህክምና ባለሙያወችን እና ሌሎች የህብረተሰብ ክፍሎችን ትኩረት የሳበ የበሽታ አይነት እኝደሆነ በብዙ መጽሃፎች, ፊልሞች እና የቴሌቪዥን ትርዒቶች ውስጥ ታይቷል። 👍ይህ ህመም ብዙም ያልተለመደ ሲሆን አንዲት ነፍሰ ጡር ያልሆነች ሴት ነፍሰጡር መሆኗን በጥብቅ የምታምንበት  እና እንዴ ማቅለሽለሽ ፣ የሆድ እብጠት መጨመር፣ የወር አበባ መቅረት እና የፅንስ እንቅስቃሴ ሳይቀር የመሳሰሉ የእርግዝና ምልክቶችን የምታሳይበት ክስተት ነው። 👍ይህ በሽታ በአብዛኛው የአዕምሮ ህመም ተጠቂ በሆኑ፣ በተደጋጋሚ ልጅ በሞተባቸው ወይም በጠፋባቸው እና የመካንነት ችግር ባለባቸው ሴቶች ላይ ይስተዋላል። በብዛት ከ 20 እስከ 39 ዓመት የዕድሜ ክልል ውስጥ ባሉ ሴቶች ላይ በጣም የተለመደ ቢሆንም አልፎ አልፎ በቅድመ-ወር አበባ (premenarchal) እና በድህረ ማረጥ (post menopausal) ሴቶች ላይም ሊከሰት ይችላል። በሽታው ያለባቸው ሴቶች ምን ምን ዓይነት ምልክቶችን ያሳያሉ? 👍በሽታው  ሥነ ልቦናዊ እና ፊዚዮሎጂያዊ ገጽታዎች ያሉት ሲሆን የዚህ ችግር ሰለባ የሆኑ ሴቶች ነፍሰጡር አለመሆናቸው በህክምና ምርመራ ተረጋግጦ ቢነገራቸውም አያምኑም፤ በግትርነት ነፍሰ ጡር እንደሆኑ ያምናሉ። 👍ነፍሰ ጡር ናቸው ተብለው በስህተት ቀዶ ጥገና (cesarean section) ሳይቀር የተሰራላቸው እናቶች ሳይቀር እንዳሉ በጥናት ተረጋግጧል። 👍 በተጨማሪም ከሚከተሉት ምልክቶች ወይም ምልክቶች አንዱ ወይም ከዚያ በላይ ሊኖራቸው ይችላል። እነርሱም፡ ●የሆድ መጨመር /ማበጥ ● የወር አበባ መዛባት ወይም መቅረት ●የፅንስ እንቅስቃሴ ስሜት ● ማቅለሽለሽ እና ማስመለስ ●የጡት ለውጦች ●የሆድ ህመም ● የሽንት ቶሎ ቶሎ መምጣት ... ወዘተ ናቸው ። በሽታው እንዴት ይታከማል? 🙏 ነፍሰ ጡር ነኝ ብላ ማሰቧ በራሱ ስህተት እንዳልሆነ ነገር ግን በተደረጉ አካላዊ፣ የላቦራቶሪ እና አልትራሳውንድ ምርመራወች እርግዝና እንደሌላት በጥንቃቄ ማስረዳት 🙏የምክር አገልግሎት መስጠት 🙏ተጓዳኝ የስነ አእምሮ  ወይም ሌላ የታወቀ ህመም ካለ ማከም 🙏የወር አበባ ሊያመጡ የሚችሉ መድሀኒቶችን መስጠት ... ወዘተ ናቸው ። ዶ/ር ሀብታሙ አውለው (የማህፀን እና ፅንስ ሬዝዳንት ሀኪም) የማጣቀሻ መጽሀፍት፡ - william gynecology, 4th edition

እንኳን ለብርሀነ መስቀሉ በሰላም አደረሳቹ ❤ መልካም በዓል..
እንኳን ለብርሀነ መስቀሉ በሰላም አደረሳቹ ❤ መልካም በዓል..

ድንቅ ሃሳብ "እየጨፈርን #የናድነውን ቤት እያለቀስን አንሠራውም!" ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ "ሁላችንም ዘር አለን ፡፡ ዘሩ ግን እኛ #አይደለንም! እኛ #ሰዎች ነን ፡፡ ሰውነት #ከመፈጠር እንጂ #ከመወለድ አይጀምርምና ፈጣሪ ዘራችንን ኢትዮጲያ በምትባል ምድር ላይ ዘራው ፡፡ ሲዘራው ኢትዮጲያ ማለት ሰዎች መሆኗን አወቅን ። መነጣጠል እስከማንችል ተዋሃድን ፡፡ ትናንት የሆነ የሰው ዲስኩር አንዳችንን ካንዳችን ካልለየሁ እያለ ሥያሜ አበጀልን ፡፡ ፈጣሪን ለማረም ይመስል እኛም ሆሆሆ ብለን ተቀበልን ፡፡ በሕንድ 2032 ብሔረሰብ በሠላም እየኖረ በቻይና 499 ብሔረሰብ በሠላም እየኖረ ምነው እኛ (ሰማኒያዋን) መሸከም አቃተን ? ተራ በተራ መግዛታችንን ለበላይነት ተጠቀምንበት ? ማንም ከማንም ጋር የሰውነት ጥል ሊኖረው አይችልም የዕውቀት ጥል እንጂ ፡፡ ገና ስንወለድ ዘር ምን ይሁን ቋንቋ ምን ይሁን የምናውቀው ነገር አልነበረም ፡፡ #የዕውቀት ጥል ደግሞ በጠረጴዛ ዙሪያ እንጂ በጦር ሜዳ አይፈታም ፡፡ ምክንያቱም #ይቅርታ እንጂ #በቀል ታሪክን አያርምምና፡፡ ቋንቋ የሚባልን ነገር ከመካከላችን አውጥተን ማሰብ ብንጀምር ዘረኝነት ሃሳብ ላይ እንጂ ደም ላይ እንደሌለ እንረዳለን፡፡ #እየጨፈርን የናድነውን ቤት #እያለቀስን አንሠራውም ፡፡ ሁልጊዜ ጥፋት ካደረስን በኋላ እንዳጠፋን ምንረዳ ከሆነ ዞሮ መልሶ አለማወቅ ይሆንብናል ፡፡ በመቻቻል ሳይሆን በፍቅር እንኑር መቻቻል አንድ ቀን ያሰለቸናል ፡፡ ታገስኩህ ቻልኩህን ያመጣል ፡፡ ፍቅር ግን እስከዖሜጋ ይሸከማል ፡፡ ከሰውነት በላይ ምን ማንነት ኖሮ ፤ የሁሉም መገኛ ያው አዳም ነው ዞሮ ፤ የማይሻር ሽረን አይሆኑሽ ሆነናል ፤ የማይድን ስናክም የማይሞት ገለናል ፡፡ አትዮጵያዊነት ከዘር በላይ ነው ፡፡ ኢትዮጵያ ለሁላችንም በቂ ናት! እንወዳድ በፍቅር እንኑር ፡፡" ፕ/ር በየነ ጴጥሮስ ═════════❁✿❁ ═════════ 💪💯

ድሃ ሆነህ የደሃ ልጅ ካስረገዝክ ትክዳለህ ። ድሃ ሆነህ የሀብታም ልጅ ብታስረግዝ ቤተሰቦቿ ይክዱሃል 😂😂 ከንቱ ዓለም 😭
Anonymous voting

አንዳንድ ጊዜ መገፋታችን ሳይሆን የተገፋንበት ቦታ እና ሁኔታ የሕመማችን መሠረት ይሆናል።

በዚህ በምንኖርበት አለም ያሉ ሴቶች💃 ፣ሕፃናት... ፣ ውሻ አና ድመት😸 ሳናስበው ልንወዳቸው እና ቀልባችንን ሊገዙት ይችላሉ።*** ነገር ግን በሚሠራው ስራ : ባለው ነገር ተመዝኖ የምንወደው ፍጡር ወንድን👨‍💻👨‍🔧👨‍🎨 ብቻ ነው።😂😂😂💪

በማንኛውም ጥረት ውስጥ በተወሰነ ደረጃ ስኬትን የሚያረጋግጡ ሁለቱ በጣም አስፈላጊ ንጥረ ነገሮች ድፍረት እና በራስ መተማመን ናቸው። እነዚህ ሁለት ንጥረ ነገሮች ከሌሉ የመጀመሪያውን እርምጃ ወደ ማን
በማንኛውም ጥረት ውስጥ በተወሰነ ደረጃ ስኬትን የሚያረጋግጡ ሁለቱ በጣም አስፈላጊ ንጥረ ነገሮች ድፍረት እና በራስ መተማመን ናቸው። እነዚህ ሁለት ንጥረ ነገሮች ከሌሉ የመጀመሪያውን እርምጃ ወደ ማንኛውም ነገር ለማድረግ እና በችግር ጊዜ ለመቀጠል የበለጠ ከባድ ይሆናል ። ስለዚህ ችግሮችህ ተጋፈጣቸው እና ቀጥል  በዚያ ጊዜ አንተነትህ ይስራል ።

ሰው በህሊናው እንዳሰበው እንደዚሁ ደግሞ ነው፡፡ ተብለናል፡፡ መቼም ትዕዛዝን ያለምክንያት መቀበል ታላቅነት ነው፡፡ ካልሆነ እንኳ ትዕዛዝን በምክንያት መርምሮ መቀበል ያባት ነው፡፡ ከሁለቱ ያልሆነ ደግሞ በብልጭልጭ የጨለማ እውነት ውስጥ መኖሩ አይቀርም፡፡ የጠየቅነውን፣ ያሰብነውን፣ ያንኳኳነውን እንድንቀበልም የፈጣሪ ድርሻ እና የእኛ ድርሻ በግልጥ ተቀምጦልናል፡፡ ይህም እግዚአብሔር ያከናውናል፣ እኛም ባሪያዎቹ ተነስተን እንሰራለን፡፡ ይህንን የተገነዘበ ታላቅ የእረፍት ህይወትን ይኖራል፡፡ ትግልን ያቆማል፡፡ መቀበልን ይረዳል፡፡ ስለዚህም አንዳች ክንውን እኛ እንደማናደርግ ነገር ግን ክንውን ሁሉ በእርሱ እንደሆነ ያስረዳናል፡፡ የእኛ ድርሻ ተነስቶ መስራት ነው፡፡ እኛ ተነስተን ስንሰራ እርሱ የሚከውንልን የሰራነውን ሳይኖን በመጀመሪያ የጠየቅነውን፣ ያንኳኳነውን፣ የሻነውን፣ ያሰብነውን ነው፡፡ ለዚህም ነው ሰዎች አንድ አይነት ሥራ ሰርተው የተለያየ ውጤት የሚያገኙት፡፡ ነገር ግን በመደናገር ዓለም ውስጥ የሚኖሩ ሰዎች ይህንን ዕድሌ፣ ወይንም ዕድል ነው ብለው የሚጠሩት፡

You can exchange 10,000 coin = 1 dollar ...

Great app to earn FREE gift cards, PayPal cash, or mobile recharge. Enter code VMG3HU to receive 500 coins instantly! https://play.google.com/store/apps/details?id=com.gettocash.app

#የወር_አበባ_እያየሽ_እርግዝና_ይፈጠራል? ስለ እርግዝና ሲነሳ የተለመደው እና ብዙ ጊዜም የሚነገረው በወር አበባ ወቅት እርግዝና አይፈጠርም የሚለው ሚት (myth) ነው። ምንም እንኳን በወር አበባ ወቅት የእርግዝና የመፈጠር እድል እጅግ ያነሰ ቢሆንም ዜሮ በሚባል ደረጃ ግን አስተማማኝ አይደለም። በወር አበባ ወቅት ስለሚደረግ ወሲባዊ ግንኙነት እና ስለ እርግዝና ጉዳይ የሚከተለውን ማወቅ ለግንዛቤ ይረዳል እና እነሆ…. ☑️ ለመሆኑ እርግዝና እንዴት ነው የሚከሰተው? እርግዝና የሚፈጠርበት ሂደት እና እድል አስገራሚ ነገር አለው። እርግዝና ለመፈጠር የሴቷን እንቁላል እና የወንዱን የዘር ፍሬ መገናኘት የሚፈልግ ሲሆን የሴቷ እንቁላል ከኦቫሪ ከተለቀቀ በኋላ ያለው እድሜ ከ12-24 ሰዓት ብቻ ነው። የወንዱ የዘር ፍሬ ግን እስከ ሶስት ቀን የመቆየት አቅም አለው። ስለዚህ እርግዝና ሊከሰት የሚችለው የሴቷ እንቁላል ተለቆ በህይወት በሚቆይበት እድሜ የወንዱን የዘር ፍሬ የሚያገኝበት እድል ሲፈጠር ነው ማለት ነው። በነገራችን ላይ መደበኛው የሴት ልጅ የወር አበባ ኡደት 28 ቀን ሲሆን የሴቷ እንቁላል የሚለቀቀው (ovulation) በ14ኛው ቀን ገደማ ነው። ይህም ማለት በ12,13 ወይም በ14ኛው ቀን ሊሆን ይችላል። ይሁንና ሁሉም ሴቶች በተመሳሳይ የ28 ቀን የወር አበባ ዑደት የላቸውም። አንዳንድ ሴቶች እስከ 35 ቀን የሚደርስ ረዘም ያለ ዑደት ሲኖራቸው፤ አንዳንዶቹ ደግሞ 21 ቀን ብቻ ሊኖራቸው ይችላል። ይህ የወር አበባ ዑደት ልዩነት ደግሞ ኦቩሌሽን የሚፈጠርበትንም ቀን የተለያየ እንዲሆን ያደርገዋል። በዚህም መሰረት ባለ 21 ቀኖቹ በ7ኛው ቀን ገደማ፤ ባለ35 ቀኖቹ ደግሞ በ21ኛው ቀን ገደማ ኦቩሌሽን (የእንቁላል መለቀቅ) ይኖራቸዋል። ☑️ ታዲያ አንዲት ሴት በወር አበባዋ ወቅት እንዴት ልታረግዝ ትችላለች? አንዳንዴ ከሴት የመራቢያ አካል የሚወጣን ደም ከወር አበባ ጋር የማሳሳት ነገር ይፈጠራል። ይህም ማለት አንዲት ሴት ለእርግዝና ዝግጁ ሆና ሳለ የወር አበባዋ እንደመጣ ልታስብ ትችላለች። ይህ አንዱ ምክንያት ሊሆን ቢችልም ዋነኛው ግን ከወንድ ልጅ የዘር ፍሬ እድሜ ጋር የሚያያዝ ነው። የወንድ ልጅ የዘር ፍሬ እስከ 72 ሰዓታት በሴቷ አካል ውስጥ የመቆየት አቅም ስላለው አንዲት ሴት በወር አበባ መገባደጃ አከባቢ ወሲብ ብትፈጽም የማርገዝ እድል ይኖራታል። የአብዛኞቹ ሴቶች የኦቩሌሽን ሳይክል ከ28-30 ቀን ነው። ይህም ማለት በወር አበባ ጊዜ ወሲብ ቢፈጸም ለብዙ ቀናት እርግዝና ላይከሰት ይችላል። ይሁንና አጭር የኦቩሌሽን ሳይክል ያላቸው ሴቶች በኦቩሌሽን እና በወር አበባ መካከል በቂ ቀን ላይኖራቸው ይችላል። ☑️ በወር አበባ ወቅት የእርግዝና መከሰት እድሉ ምን ያህል ነው? አንዲት ሴት የወር አበባ ማየት በጀመረችበት ሁለት ተከታታይ ቀናት ወሲብ ብትፈጽም የማርገዝ እድሏ ዜሮ ነው ማለት ይቻላል። ይሁንና ከሶስተኛው ቀን ጀምሮ የማርገዝ እድሏ ቀስ በቀስ እያደገ ይሄድና ልክ 13ኛው ቀን ላይ 9% ይደርሳል። ይህ ቁጥር ቢቀንስ እንኳን መቶ ፐርሰንት እርግዝና እንደማይከሰት እርግጠኛ ሆኖ መናገር አይቻልም። 🦋 ሲጠቃለል የሴቶች የኦቩሌሽን ሳይክል የተለያየ ነው። ስለዚህ በስታቲስቲክስ አንዲት ሴት የወር አበባ ላይ ሆና የምታረግዝበት እድል ሊፈጠር ይችላል። ምንም እንኳን በወር አበባ የመጀመሪያዎቹ ቀናት እርግዝና የመከሰት እድሉ እጅግ ያነሰ ቢሆንም ቀን እየገፋ በሄደ ቁጥር ግን እርግዝና የመፈጠር ዕድሉ እያደገ ይሄዳል።

ሕክምና🙏 https://t.me/NRSINGPDF

ለማታውቁት ዶ/ር አለማየሁ ዋሴ ይባላል ። እኔ በግሌ በጣም የምወዳቸውን መፃህፍት የእመጓ ፣ የዝጎራ ፣ የመርበብት እና የሰበዝ መፃሕፍት ደራሲ ነው ። የሚኖረውን የሚያስተምር ብርቱ ሰው ነው ። ስለ
ለማታውቁት ዶ/ር አለማየሁ ዋሴ ይባላል ። እኔ በግሌ በጣም የምወዳቸውን መፃህፍት የእመጓ ፣ የዝጎራ ፣ የመርበብት እና የሰበዝ መፃሕፍት ደራሲ ነው ። የሚኖረውን የሚያስተምር ብርቱ ሰው ነው ። ስለሱ የሰማሁትን እውነታዎች ልንገራችሁ ፤ በሚሰራበት መስሪያቤት <<ጠንካራ ስራአስኪያጅ ስለሆንክ ደመወዝህን በእጥፍ አሳድገንልሀል>> ተብሎ በቦርድ የተወሰነለትን ደመወዝ አልቀበልም ብሎ በደብዳቤ መልሷል ። ከአንድ መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት ውስጥ ለስራ ተወዳድሮ ካለፈ በኋላ ፣ ደመወዙ ስለበዛ ቅጥሩን ሰርዞ ያውቃል ። ከወር የቤትና የራሱ ወጪ ውጪ ያለውን የባንክ ገንዘቡን በየወሩ ለነዳያንና ለገዳማት ይሰጣል ። የዶክተር አለማየሁ መርህ ምን መሰላችሁ ? የራሱንና የቤተሰቡን ኑሮ ስታንዳርድ አበጅቷል ። "ቤት አለኝ" ይልህና ፤ "የቤቴን አይነት ግን አትጠይቁኝ"ይልሀል ። "መኪና አለኝ" ይልህና፣ "የመኪናዬን አይነት ግን አትጠይቁኝ" ይልሃል ። "የምኖረው ከተማ ነው" ይልህና ፣"የት ከተማ ግን እንዳትለኝ" ይልሀል ። ምክንያቱም ይላል "ከቤት በላይ ቤት ፣ ከመኪና በላይ መኪና ፣ ከከተማ በላይ ከተማ አለ ፤ ከቀበቶ በላይ እንኳን ቀበቶ አለ ፣ የቀበቶ ስራው ግን ሱሪ እንዳይወልቅ ማድረግ ነው ።" ይላል ። በአጠቃላይ ዶክተር አለማየሁ ምኞትን በጥልቅ ጉድጓድ ቆፍሮ የቀበረ ፣ የገንዘብን አቅም ያሳነሰ ምርጥ ሰው ነው ። ሲናገር እና ሲያስተምር ደግሞ አዝናኝ ነው ። የፃፋቸው አስደማሚ መፃሕፍት የሱን ህይወት ቁልጭ አድርገው ያሳያሉ ። የኔ የሁልጊዜም ምርጥ ሰው ነው ። ረጅም እድሜ ከጤና ጋር ተመኘሁልህ❤🙏# ════════❁✿❁ ════════ 💪💯 አንብባችሁ #ሼር #ሼር አድርጉልን የቴሌግራም ቻናላችንንም ግቡና Join አድርጉ ። https://t.me/joinchat/AAAAAFAtO5kL7-YczXxg_Q

ለማታውቁት ዶ/ር አለማየሁ ዋሴ ይባላል ። እኔ በግሌ በጣም የምወዳቸውን መፃህፍት የእመጓ ፣ የዝጎራ ፣ የመርበብት እና የሰበዝ መፃሕፍት ደራሲ ነው ። የሚኖረውን የሚያስተምር ብርቱ ሰው ነው ። ስለ
ለማታውቁት ዶ/ር አለማየሁ ዋሴ ይባላል ። እኔ በግሌ በጣም የምወዳቸውን መፃህፍት የእመጓ ፣ የዝጎራ ፣ የመርበብት እና የሰበዝ መፃሕፍት ደራሲ ነው ። የሚኖረውን የሚያስተምር ብርቱ ሰው ነው ። ስለሱ የሰማሁትን እውነታዎች ልንገራችሁ ፤ በሚሰራበት መስሪያቤት <<ጠንካራ ስራአስኪያጅ ስለሆንክ ደመወዝህን በእጥፍ አሳድገንልሀል>> ተብሎ በቦርድ የተወሰነለትን ደመወዝ አልቀበልም ብሎ በደብዳቤ መልሷል ። ከአንድ መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት ውስጥ ለስራ ተወዳድሮ ካለፈ በኋላ ፣ ደመወዙ ስለበዛ ቅጥሩን ሰርዞ ያውቃል ። ከወር የቤትና የራሱ ወጪ ውጪ ያለውን የባንክ ገንዘቡን በየወሩ ለነዳያንና ለገዳማት ይሰጣል ። የዶክተር አለማየሁ መርህ ምን መሰላችሁ ? የራሱንና የቤተሰቡን ኑሮ ስታንዳርድ አበጅቷል ። "ቤት አለኝ" ይልህና ፤ "የቤቴን አይነት ግን አትጠይቁኝ"ይልሀል ። "መኪና አለኝ" ይልህና፣ "የመኪናዬን አይነት ግን አትጠይቁኝ" ይልሃል ። "የምኖረው ከተማ ነው" ይልህና ፣"የት ከተማ ግን እንዳትለኝ" ይልሀል ። ምክንያቱም ይላል "ከቤት በላይ ቤት ፣ ከመኪና በላይ መኪና ፣ ከከተማ በላይ ከተማ አለ ፤ ከቀበቶ በላይ እንኳን ቀበቶ አለ ፣ የቀበቶ ስራው ግን ሱሪ እንዳይወልቅ ማድረግ ነው ።" ይላል ። በአጠቃላይ ዶክተር አለማየሁ ምኞትን በጥልቅ ጉድጓድ ቆፍሮ የቀበረ ፣ የገንዘብን አቅም ያሳነሰ ምርጥ ሰው ነው ። ሲናገር እና ሲያስተምር ደግሞ አዝናኝ ነው ። የፃፋቸው አስደማሚ መፃሕፍት የሱን ህይወት ቁልጭ አድርገው ያሳያሉ ። የኔ የሁልጊዜም ምርጥ ሰው ነው ። ረጅም እድሜ ከጤና ጋር ተመኘሁልህ❤🙏# ════════❁✿❁ ════════ 💪💯 አንብባችሁ #ሼር #ሼር አድርጉልን የቴሌግራም ቻናላችንንም ግቡና Join አድርጉ ። https://t.me/joinchat/AAAAAFAtO5kL7-YczXxg_Q