993
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
-3230 days
Posts Archive
#ጃኪ_ቻን በህይወቱ ደስተኛ ስለመሆኑ ከጋዜጠኛ ለቀረበለት
ጥያቄ በሚከተሉት ጥበባዊ ቃላት መልስ ሰጠ።
“#ታውቃለህ፣ በአንድ ወቅት በጣም ጥበብ የተሞላባቸው ቃላትን ሰማሁ፡-
የአንተ ፈታኙ ሥራህ የሁሉም ሥራ እጥ ሰው ህልም ነው።
ሰላም የማይሰጥህ ልጅህ ልጅ ለሌለው ሰው ህልም ነው።
የአንተ ትንሽ ቤት የሁሉም ቤት አልባ ሰው ህልም ናት።
የአንተ ትንሽ ካፒታል የእያንዳንዱ ተበዳሪ ህልም ነው።
የእኛ ቀላል በሽታ በማይድን ሕመም ለተያዙ ሰዎች ህልም ነው።
ሰላምህ፣ ሰላማዊ እንቅልፍህ እና ተደራሽ ምግብህ በጦርነት ውስጥ ባለ አገር ውስጥ ያለ ሰው ሁሉ ህልም ነው።
ስለዚህ ያለህን ሁሉ ማድነቅ አለብህ። ደግሞም ነገ ምን እንደሚመጣ ማንም አያውቅም።
የታክሲ ሰልፍ ላይ ቆሜ..
ረጅም ነው..የሰልፉ ጫፍ ለመድረስ ሌላ ታክሲ መያዝ የሚያስመኝ አይነት ረጅም ሰልፍ
ከሓላዬ የቆመችው 'የሰልፍ አጋሬ' ትቁነጠነጣለች..አንዴ በግራዬ አንዴ በቀኜ ወጣ ገባ እያለች የታክሲ መምጣቱን ሩቅ አሻግራ ታያለች..
"ዛሬ መንገድ ዝግ ነው እንዴ?" ስትል ዞር አልኩ..
"..አላወኩም ይሆናል..' ንግግሬን ባጭሩ ዘጋሁት..
"ረጅም ሰዐት ሆነን እኮ ከሓላ የት እንደደረሰ አየኸው?"
"..ያው በዚ ሰዐት እኮ እንዲ ነው.."አልኳት ይቺን ሰልፍ ብርቁ የሆነች ዜጋ
"..አይ ቢሆንም ቢያንስ አንድ ሁለት ታክሲ እንዴት ይጠፋል.."
ዝም ..አልኩ
"..በነገርህ ላይ ሀምሳ ሀምሳ ብር ብናዋጣ እኮ ራይድ መጠቀም እንችላለን"
"..እ.. አይደል?"ስልችት ብሎኛል ንግግሯ..ቅብጠት አለባት..በአጭር ቀሚስ የተያዙት እግሮቿ ይቁነጠነጣሉ፤ወይ ሰልፍ አለመደባትም..ወይ ቸኩላለች ብዬ አስብኩ..
ከሓላዋም ከፊቷም ብትዞር ማንም ትኩረት አልሰጣትም።
..".. ብራዘር እኔ መቶ ብር ልክፈል አንተ ሀምሳ ብር ክፈልና እንሂድ ቆመን ቀርን እኮ!"
አሳዘነችኝ..እሺ አልኳት አንዱን ባለ ታክሲ አናገርንና ወደ ገርጂ ጉዞ ጀመርን..
ከሓላ ቁጭ ብለን በዝምታ ውስጥ ተውጠናል..
"..አይ ሆፕ አላስቸገርኩህም አደል..?"አለችኝ
..ኖ በፍፁም..ያው ለሁለታችንም እኮ ነው..
ቁጭ ስትል ወደ ታፋዋ የተሰበሰበውን ቀሚሷን ወደታች ሳብ ሳብ ታረጋለች..ነገሩ አልሸሹም ዞር አሉ ቢሆንባትም..
በዝምታ ውስጥ አንገቷን ዘንበል አርጋ ትከሻዬ ላይ ደገፍ አለች..ዝም አልኩ..መልስ አልሰጠሁዋትም..
ተደላድላ ደገፍ ብላ ማንጎራጎር ጀመረች..
የተዘናፈለው ፀጉሯ የሆነ መዐዛ አለው..ጠባቧን ታክሲ የተነሰነሰችው ሽቶ አውዶታል..
አይኔን የማሳርፍበት ነገር እያሰብኩ በመስኮት አሻግሬ ማየት ጀመርኩ፣
"መልካም ሰው እኮ ጠፍቷል.. አሁን አንተ እሺ ባትለኝ እዛ ፀሀይ ላይ ተገትሬ ነበር.."
ኧረ ቀለል አርገሽ እይው አታካብጂው.. አልኳት..
የታክሲው ሹፌር በሓላ መስታወት ሰረቅ እያረገ ያየናል..
መድረሻችን..ገርጂ ኮንዶሚኒየም ስንደርስ ሂሳብ ከፍለን ወረድን..
"..ፕሊዝ እምቢ እንዳትለኝ..ቀዝቃዛ ጁስ ጠጥተህ ትሄዳለህ.."
ድንገተኛ ቢሆንብኝም አልተግደረደርኩም "..ይሻላል..ብለሽ ነው እሺ..የት እንቀመጥ..?"
"..ኧረ ቤቴ እዚ ሁለተኛ ፍሎር ነው፤ ገባ ብለህ ትወጣለህ.."
..እያንገራገርኩ ተከተልኳት ደረጃውን ቀደም እያለች..ስትወጣ <ምን እያረኩ ነው?> እያልኩ ነበር .. ትንሽ ጥርጣሬ ውስጤ ቢሰማኝም ምን እንዳታረገኝ በሚል ትቢትና በመመካት ተከተልኳት..
የምትኖረው ብቻዋን እንደሆነ ነገረችኝ የቤቷን በር ከፍታ ስንገባ ህልም ነበር የመሰለኝ..የማላውቃትን ሰልፍ ላይ ያገኘሓትን ሴት ተከትዬ ቤቷ ገባው..እሺ ከዛስ..
የሚያምር ፅድት ያለ ቤት ነው ያላት ጠንካራ ሴት አልያም ከባድ ቢዝነስ የምትሰራ ሴት መሆን አለባት፥ሶፋ ላይ ቁጭ አልኩ..ዙሪያውን ለመቃኘት፥መረጃ ለመሰብሰብ ፎቶዎችን ለማየት ሞከርኩ
"..እንደቤትህ ቁጥረው..ፈታ በል" ብላ ወደመኝታ ቤት ገባች ስሟን እንኳ ያላወኳት ሴት...እንዴት አንድ የማታውቀውን ወጣት ወንድ ቤቷ ድረስ ትጋብዛለች?
ለክፉም ለደጉም ጁስ ያለችውን ስትሰራው ማየት አለብኝ ማን ያውቃል..አደንዝዛ ይቺን ኩላሊቴን ዘክዝካ ብትወስድስ...ሀሳቡ ብቻውን ፍርሃትም ሳቅም ፈጠረብኝ።
ከላይ የለበሰችውን ቀይራ ቀለል ያለ የቤት ልብስ ለብሳ ተመለሰች..አለባበሷ በትኩረት እንዳያት የማይጋብዝ ነው ሰውነቷን ያጋላጠ ለብዙ ነገር የሚጋብዝ አይነት..
"..ኡፍ ሙቀቱ ግን ብሶበታል አይደል..ተቃጠልን እኮ..."
'ሰው በረደኝ ይላል አንቺ ስለሙቀት ታወሪያለሽ..ይልቅ እንዳንቺ የምታሞቅ ሚስት ፈልጊልኝ.."
ምን አንቀልቅሎኝ አፌን እንደከፈትኩ
..ከጣራ በላይ ድምጿን ከፍ አድርጋ ሳቀች..
"ፀባይ ይኑርህ ጠንካራ ሰራተኛ ሁን እንጂ የምታሞቅ ሚስት ብቻ ሳይሆን ልጆችም ይሰጡሀል..!"
እሱማ ልክ ነሽ..ንግግሬን ሳታስጨርስ በንፅህና ወደ ተያዘው ኪችን ገባች..
"..እንዳይደብርህ ጆይን ልታረገኝ ትችላለህ.."..
<ጥሩ ሀሳብ ነው..በዛውም ሙያሽን ልይ እስኪ> ብዬ ተክትያት ገባው..ያረገችው ቁምጣና ቦዲ ላይ አይኔን ተክዬ አብሪያት ጉድ ጉድ አልኩ ለእኔ አቦካዶ ጁስ ለራሷ የብርቱኳን ጭማቂ በጣም በሚያማምሩ ብርጭቆዎች አቀረበች..
ለረጅም አመታት የማውቃት ሰው ትመስላለች..ቀለል አርጋ ነው የምታወራው..አላገባችም፥ ብዙ የእድሜዋን ክፍል ትምህርት ላይ ነው ያሳለፈችው..ውበት የሴትነት ገላ ብቻ ሳይሆን ጭንቅላትም የተሰጣት ትመስላለች..
የእኔ አዕምሮ አሻግሮ መኝታ ቤቱን ቢያስመለክተኝም እሷ ግን ከመሳቅ ከመጫወት ያለፈ ነገር አይታይባትም..እራሴን ለመቆጣጠር ከብዶኛል ፥ይሄ ወንድነት እኮ ድካም ነው፤መቆየት አልፈለኩም.."ይቅርታ የምሄድበት ጉዳይ አለ..ባይሆን ስልክሽን ስጪኝና ሌላ ግዜ በሰፊው እንገናኝ"..ብያት ከተቀመጥኩበት ተነሳሁ..ስንለያይ እንደ ብዙ ግዜ ወዳጆች ጉንጬን ሳም አድርጋኝ ተመለሰች...
እንዴትም አርጌ እኔ ቤት እንድትመጣ ባደርጋትም በፍፁም ጨዋነት አስተናግጄ እንደምለያት እያሰብኩ ነበር..
ከትቂት ቀናት በሓላ እዛው ሰልፍ ላይ ለመቆም እየተራመድኩ አንዲት መኪና አጠገቤ መጥታ ስትቆም እሷ መሆኗን ያወኩት ዘግይቼ ነበር፥
.."..ዛሬ እኔ ነኝ ራይድ የምሰጥህ.. ግባ!" አለችኝ የመኪናዋን መስታወት ዝቅ አድርጋ..
፨፨፨፨፨፨፨፨
እንዴትም ቢቀርቡህ እንዴትም ቢለብሱ፥ እንዴትም ቢስሙህ፥ እንዴትም ቢያቅፉህ ፥ ስላንተ ሌላ ምንም የማያስቡ ብዙ አስደማሚ ሴቶች አሉ!
የተለያዩ ጥያቄዎችን መጠየቅ ይቻላል።
ለመቀላቀል
👇👇👇👇👇
https://t.me/albotube
"ልቡ ጠቢብ የሆነ አስተዋይ ይባላል፥ በከንፈሩም ጣፋጭ የሆነ ትምህርትን ያበዛል። ገንዘብ ላደረገው ሰው እውቀት የሕይወት ምንጭ ነው፤ ስንፍና ግን የሰነፎች ቅጣት ነው። የጠቢብ ልብ አፉን ያስተምራል፥ ለከንፈሩም ትምህርትን ይጨምራል። ያማረ ቃል የማር ወለላ ነው፤ ለነፍስ ጣፋጭ ለአጥንትም ጤና ነው።"
📜(መጽሐፈ ምሳሌ፡ 16፥21-24)📜
#ይሄን_ጋብቻ ስታይ እግዚኦ መሀረነ ክርስቶስ ወይ ስምንተኛው ሺህ 🤣🤣 የመጨረሻው ዘመንማ ደርሷል አበስኩ ገበርኩ ቱቱቱ ልትል ትችላለህ በጌታ ስም ወጋሁት አኡዝቢላሂም ብለህ ይሆናል
ግን ተረጋጋ ወገን ይሄ እምቦቃቅላ አንድ ፍሬ ጨቅላ መሳይ ልጅ ከሙሽሪቷ የሚያንሰው በ 1 አመት ብቻ ነው ደቡብ አፍሪካ በፊልም ስራዎቹ የምታውቀው ህጻን መሳይ ሼባ የ 27 አመት ሶዬ ነው... ሙሽሪት ልጅም ባልም አገኘች ማለት ነው
የጥሪው ወረቀት ላይ ሳይሆን ሰርጉ ላይ እንዲታደም የተጠራ ሰው ሁሉ ምን ይላል "የርሱ ፍቃድ ይሁን ብለን ዝም አልን"
ታክሲ ላይ ልጄ ገና ህጻን ስለሆነ አይከፍልም ብሎ ሲከራከር ረዳቱ እሱ ይከፍላል ግድ ነው ባይሆን አንተነህ የማትከፍለው እንደተባለው አይነት አባት መሆኑ ነው
Themba Ntuli መልካም የምትተዛዘሉበት የምትተሳሰቡት የትዳር ዘመን ይሁንላችሁ።
በውስጥ በጣም ብዙ ጥያቄዎች ይመጣሉ ?
ለምንድነው ስራውን የምትወደው ለምትሉኝ
🏆ለምንድነው ስራዬን የምወደው (direct selling industry ) መርጬ የምሰራበት 8 ምክንያቶች
1ኛ👉 አለቃ የሌለው ስራ ስለሆነ
አለቃዬ ህልሜ ነው
2ኛ👉በየትኛው ቦታ መሰራት ስለሚቻል ማለትም በቤት፣በቢሮ፣በትራንስፓርት፣በየትኛውም ቦታ መሰራት ስለሚችል።
3ኛ👉ሀገር ውስጥም ከ ሀገር ውጪም ሆኖ መሰራት ስለሚቻል።
4ኛ👉በሙሉ ግዜ እና በትርፍ ሰዓት መሰራት ስለሚቻል።
5ኛ👉በማንኛውም ግዜ እና ሰዓት መሰራት ስለሚቻል።
6ኛ👉ስለ ቢዝነስ በጥልቅ እንድንረዳ ስለሚያደርገን
7ኛ👉አብረውን በቲም የሚሰሩ ብዙ ሚሊየነሮች ስለሚፈጠሩ።
8ኛ👉 የግዜ እና የገንዘብ ነፃነት ስለሚሰጠኝ።
በውስጥ በጣም ብዙ ጥያቄዎች ይመጣሉ ?
ለምንድነው ስራውን የምትወደው ለምትሉኝ
🏆ለምንድነው ስራዬን የምወደው (direct selling industry ) መርጬ የምሰራበት 8 ምክንያቶች
1ኛ👉 አለቃ የሌለው ስራ ስለሆነ
አለቃዬ ህልሜ ነው
2ኛ👉በየትኛው ቦታ መሰራት ስለሚቻል ማለትም በቤት፣በቢሮ፣በትራንስፓርት፣በየትኛውም ቦታ መሰራት ስለሚችል።
3ኛ👉ሀገር ውስጥም ከ ሀገር ውጪም ሆኖ መሰራት ስለሚቻል።
4ኛ👉በሙሉ ግዜ እና በትርፍ ሰዓት መሰራት ስለሚቻል።
5ኛ👉በማንኛውም ግዜ እና ሰዓት መሰራት ስለሚቻል።
6ኛ👉ስለ ቢዝነስ በጥልቅ እንድንረዳ ስለሚያደርገን
7ኛ👉አብረውን በቲም የሚሰሩ ብዙ ሚሊየነሮች ስለሚፈጠሩ።
8ኛ👉 የግዜ እና የገንዘብ ነፃነት ስለሚሰጠኝ።
📎 የአልፋ ጥቅል ስልጠና በቅርብ ቀን
📍በድሬዳዋ፣ በጅማ እና በበደሌ - የኃያል ሂደት ስልጠና በቅርቡ ይሰጣል!
°•°አልፋ ለስኬትዎ ጉልህ ድርሻ! °•°
📍አዲስ አበባ፣ ቦሌ ክፍለ-ከተማ፣ ወረዳ 3 አለምነሽ ፕላዛ 6ተኛ ፎቅ
🌐 www.alphagenuine.com
☎️ +251930020395 ቦሌ ቅርንጫፍ
+251988010611 መገናኛ ቅርንጫፍ
+251903441155 አዳማ ቅርንጫፍ
የብሬክስሩ ትሬዲንግ አ.ማ የማኔጅመንት አካላት ለ2024GC batch ተጓዦች የሽኝት መርሃ-ግብር በብሬክስሩ ትሬዲንግ አ.ማ ዋና ቢሮ ውስጥ አከናውኗል።
ማነው ቀጣይ ተጓዥ!?
* አልፋ ለስኬትዎ ጉልህ ድርሻ!*
ወላጆቾችህ አስበውም ተሳስተው አልወለዱህም።
ስለ መወለድ ስናወራ በአካል መወለድ አለ። በመንፈሳዊው አለም ዳግም መወለድ አለ። ደግሞም ወደዚህች ምድር የመጣንበት አላማ አውቆ በአላማ መኖር በመጀመር መወለድ አለ። ለዛሬ ርእሴ ሶስተኛው ነው። በአላማ የመኖር የመጀመሪያ ቀን።
ብዙ ጊዜ ስልጠና ላይ የህይወት/የስራ/የኑሮ ተሞክሮዬን ሳካፍል ከመወለዴ በፊት እና ከመወለዴ በኋላ ብዬ እከፍለዋለሁ። ከመወለዴ በፊት የምለው ዘመን ተማር ስለተባልኩ ዝም ብዬ የተማርኩበትን፣ ወጪ መሸፈን ስላለብኝ ዝም ብዬ ስራ ያገኘሁበትን፣ ዝም ብዬ የሚያበላ ስራ ስሰራ ውዬ ስሰራ ደክሞኝ ቤት የገባሁትን፣ ደግሞም ጠዋት ወደ ስራ ልሄድ ስል የደከመኝን፣ ጠዋት የነጋብኝ እንጂ ያልነጉልኝ ቀኖችን፣ ዝም ብዬ ስበላ ስለብስ እንዲሁም የሆነ ጣርያ ስር ስጠለል የነበርኩበትን ጊዜያት፣ በቃ ዝም ብዬ ያለ አላማ ወጥቼ የገባሁባቸውን አመታት ነው።
እዚህ ምድር ላይ ያለነው ሶስቱን የሰው መሰረታዊ ፍላጎቶች ለማሟሟላት ከሆነ እናሳዝናለን። በሶስቱ መሰረታዊ ነገሮች ወፍ ትበልጠናለች። ዛሬ ማታ ምን እበላ ይሆን ብላ እጇን አገጯ ላይ አስደግፋ ስትተክዝ ያየናት ወፍ የለችም። የሰው ልጅ ግን ምሳ እየበላ እራት ያስባል። ብዙ ዘናጭ ሴቶች እና ወንዶች ከተማ ውስጥ አሉ። ከወፍ አለባበስ ግን ልብሳቸው አይበልጥም። እንደምናውቀው ጠንቃቃ የሆነው የሰፈራችን ወጣት በ28 አመቱ ኮንዶምንየም ተመዝግቦ ኮንደሚኒየም ሳይደርሰው ይሄው 48 አመቱ ሆኗል። ወፊቱ ግን የሚገርም ጎጆ አላት ያውም ዛፍ ላይ። ከፍታ ላይ። እና ማን ይበልጣል? ወፊቱ አይደለችምን። እና ብልጫችን በማሰባችን ሳይሆን አላማን አውቆ በአላማ የመኖር ምርጫችን ነው።
የዛሬ 5 አመት አንድ ወዳጄ እና አሰልጣኜ "አንተ ማን ነህ?" ሲለኝ። ተንደርድሬ የተናገርኩት ስሜን ነበር። "አንተ ማን ነህ?" እና "ስምህ ማነው?" የተለያዩ ሃሳቦች ናቸው። እንተ እጆችህ፣ እግሮችህ፣ መልክህ፣ ብልቶችህ ነህ? አይደለሁም አይደለህም። ወደዚህ ምድር ለምን አላማ መጣህ? ምን ልታገለግል? እንደሰው ምታገልግለው ይኖራል። ግን በግልህ ምን ልታገለግል? ምክንያቱም አንተ ልዩ ሆነህ ተፈጥረሃል። አንተ ያልተደገምክ Limited Edition ነህ። በቃ ሰዎች እኛ ሰዎች ብለው ሲደፈጥጡህ አትደፍጠጥ። እኛ ነህ ግን አንተም ነህ። እኔ እኛን ሊዘነጋ አይገባውም እኛም እኔን ሊሸፍነው አይገባም። እኔን በአግባቡ ስትኖረው እኛን ታገግላለህ። እጅ እጅ ሆኖ ሲኖር መላው አካልን (እኛን) ያገልግላል። እጅ ሆኖ እንደ እግር ስላልኖረ ደስታው ልዩ ነው። እራሱን ሆኗላና።
አባቴ ያወጣልኝ ስም በሃይሉ ነው። ለምን በሃይሉ እንዳለኝ ሲያስረዳኝ። ወጣት እያለ ወላጆቹን የመርዳት ከፍተኛ ፍላጎት እንደነበረው እና እኔ ሳልታሰብ እንደተረገዝኩ እና በ " ሃይሌ" ወደዚህ ምድር እንደመጣሁ በጠይም ቋንቋ ይገልጽልኛል። ያው ስህተት ነህ ለማለት ነው። ግን እኔ ስህተት ነኝ እንዴ? አንተስ ስህተት ነህ? አንቺስ? በነገራችን ላይ ወላጆቹ ይሄን ልጅ እንውለድ ብለው የተወለደስ አለ? ማለትም ዳዲ ማሚን ዛሬ ያንን እንቁላል ይዘሽው ነይ እንስበረው ተባብለው የተወለደ ሰው አለ? ያው ወላጆች Fun ወይም ተመሳሳዩ ነበራቸው፣ ተረገዝክ ተወለድክ። አንተን ግን አስቀድሞ ያሰበህ ፈጣሪ ነበር። እሱ በአጋጣሚ አልፈጠረህም! ታናሽህን ለመፍጠር አንተ ላይ አልተለማመደም። የሆነ መላክ ግዴለሽ ስለሆነ እንጂ ሌላ ሃገር መወለድ እያለብህም ኢትዮጵያ ውስጥ በስህተት አልተገኘህም።
በቃ ፈጣሪ በዚህ ዘመን፣ በዚህ ቤተሰብ፣ በዚህ ገጽ እና መልክ፣ በዚህ ሁኔታ ለአላማ ፈጥሮሃል። ወላጆችችህ አስበውም ተሳስተው አልወለዱህም። በአላማ ለአላማ የፈጠረህ አለ። እሱን ፈልገህ አግኘው፣ አሁን ላይ ኑረው፣ ብትሸሽውም በውስጥህ የሚጮህ የእርካታህ ድምጽ ያለው በአገልግሎትህ ነውና።
በአላማ በመኖር የማፍራት ሳምንት ይሁንል።
"እራሴን ማወቅ ስችል ብዙ ነገር ማድረግ ቻልኩ"
ወ/ሮ ድንቋ አዲስ ሰው ስልጠናችንን ከወሰደች በኋላ በህይወትዋ ብዙ ነገሮችን መቀየር እንደቻለች፣ ብዙ ነገር ማወቅ እንደቻለች እንደዚሁም ማንነቷን ማወቅ እንደቻለች ተናግራለች።
በተጨማሪም፤ አላማዋን፣ ለምን መኖር እንዳለባት፣ እቅዶችዋን ወይም ተግባሮችዋን ማወቅ እንድትችል ከስልጠናችን ማትረፍ የቻለች እንደሆነ አሳውቃለች።
ሙሉ ቪድዮ በዩትዩብ ገጻችን መመልከት ይችላሉ፦ https://youtu.be/x5pKjb3aq04?si=8XOyIXRaZXQdtF6B
Some common programming techniques include:
1. Affirmations: Repeating positive statements or affirmations to yourself regularly can help reprogram your subconscious mind with new empowering beliefs.
2. Visualization: Creating vivid mental images of your desired outcomes can help program your subconscious mind to work towards achieving those goals.
3. Hypnosis: Hypnosis is a state of focused attention and relaxation that allows access to the subconscious mind. It can be used to reframe beliefs, overcome fears, and make positive changes.
4. Neuro-Linguistic Programming (NLP): NLP techniques involve using language patterns and techniques to reprogram the mind and change behaviors.
5. Emotional Freedom Techniques (EFT): EFT combines elements of acupuncture and psychology to release emotional blockages and reprogram the mind.
It's important to note that while programming techniques can be helpful, they are most effective when combined with consistent action, self-reflection, and a commitment to personal growth. It's also important to consult with a qualified professional when using these techniques, especially if you have any underlying mental health concerns.
2. Subconscious mind: The subconscious mind, also known as the unconscious mind, is the part of our mind that operates below the level of conscious awareness. It is responsible for storing and processing vast amounts of information, beliefs, memories, emotions, habits, and automatic behaviors. It influences our thoughts, feelings, and actions, often without us being consciously aware of it.
Programming techniques, also known as reprogramming or reconditioning techniques, are methods used to influence and reprogram the subconscious mind to change beliefs, thoughts, and behaviors. These techniques are often used to overcome limiting beliefs, develop positive habits, and achieve personal growth.
