en
Feedback
Asham TV | አሻም ቲቪ

Asham TV | አሻም ቲቪ

Open in Telegram

እንኳን ወደ ይፋዊው የአሻም ቲቪ የቴሌግራም ገጽ በደህና መጡ:: የተለያዩ ትኩስ መረጃዎች እና ታማኝ ዜናዎችን ለማግኝት ገጻችንን ይከታተሉ ። አሻም ለሁላችን !

Show more

📈 Analytical overview of Telegram channel Asham TV | አሻም ቲቪ

Channel Asham TV | አሻም ቲቪ (@asham_tv) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 19 819 subscribers, ranking 11 746 in the News & Media category and 1 703 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 19 819 subscribers.

According to the latest data from 09 June, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by -286 over the last 30 days and by 0 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 0%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects N/A% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 0 views. Within the first day, a publication typically gains 0 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 0.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
እንኳን ወደ ይፋዊው የአሻም ቲቪ የቴሌግራም ገጽ በደህና መጡ:: የተለያዩ ትኩስ መረጃዎች እና ታማኝ ዜናዎችን ለማግኝት ገጻችንን ይከታተሉ ። አሻም ለሁላችን !

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 10 June, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the News & Media category.

19 819
Subscribers
No data24 hours
-247 days
-28630 days
Posts Archive
🔵ከአሻም ሚዲያ ትሬዲንግ አክሲዮን ማህበር የቦርድ አባላት የተሰጠ ይፋዊ መግለጫ አሻም ሚዲያ ትሬዲንግ አክሲዮን ማህበር ከተመሰረተችበት ባለፉት 8 ዓመታት ጀምሮ በማህበራዊ ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ
🔵ከአሻም ሚዲያ ትሬዲንግ አክሲዮን ማህበር የቦርድ አባላት የተሰጠ ይፋዊ መግለጫ አሻም ሚዲያ ትሬዲንግ አክሲዮን ማህበር ከተመሰረተችበት ባለፉት 8 ዓመታት ጀምሮ በማህበራዊ ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ጉዳዮች ዙሪያ በዜናና ወቅታዊ እንዲሁም በመዝናኛ ዝግጅቶች መረጃዎችን በቴሌቪዥን እና በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮቿ ስታደርስ ቆይታለች፡፡ ይሁን እንጂ አሻም ሚዲያ ትሬዲንግ አክሲዮን ማህበር ስራዋን ለመቀጠል አቅም ስለሌላት በቴሌቪዥንም ሆነ በየትኛውም የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮቿ ከዛሬ ታህሳስ 01 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ሙሉ በሙሉ በይፋ ስርጭት ማቆሟን ለማሳወቅ እንወዳለን፡፡ ስለሆነም ከተጠቀሰው ጊዜ ጀምሮ የአሻም ሚዲያ መታወቂያ በመያዝ ወይም የሚዲያዋን ሎጎ በመጠቀም በየትኛውም ሁነት (Event) ፣ በእቅድ ዜና ወይም ፕሮግራም ፣ በስልጠና መድረክ ፣ ቃለ-መጠይቅ እና በመሰል ጉዳዮች ላይ የሚገኙ (የሚሳተፉ) ባለሞያዎች የሚዲያ ተቋሙን እንደማይወክሉ ለሁሉም የግልና መንግስታዊ ተቋማት እንዲሁም ግለሰቦች ጭምር በትህትና ለማሳወቅ እንወዳለን፡፡ ባለፉት 8 ዓመታት ከአሻም ሚዲያ ትሬዲንግ አክሲዮን ማህበር ጋር አብራችሁ ለዘለቃችሁ ለውድ ተመልካቶቻችንና ተከታታዮቻችን ልባዊ ምስጋናችን ላቅ ያለ ነው፡፡ አሻም ለሁላችን!

🟡ለውድ ተመልካቾቻችን እና ተከታታዮቻችን፡- 🏷ከአሻም ሚዲያ ትሬዲንግ አክሲዮን ማህበር በወቅታዊ ጉዳይ ላይ የተሰጠ  መግለጫ ድርጅታችን አሻም ሚዲያ ትሬዲንግ አክሲዮን ማህበር ጋዜጠኛ ሶፎንያስ ዋሲሁን በኮንትራት ውል በዜና አቅራቢነት እንዲሁም በቅርቡ በጣቢያችን ‹‹ሶፊ ሾው›› ሲል በሰየመው የመዝናኛ ዝግጅቱ  በአሻም የቴሌቪዥን እና በዩትዩብ ገፅ እያዘጋጀ ሲያቀርብ እንደነበረ ይታወቃል፡፡ ይህ በሆነበት ከትላንት ሕዳር 29 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በተለያዩ የማህበራዊ ሚድያ አማራጮች ስለ ጋዜጠኛው ከኢትዮጵያዊነት ባሕል፣ ወግ እንዲሁም ሃይማኖት ያፈነገጠ ተግባር ሲፈጽም የሚያሣይ መረጃ በድምጽ፣ በጽሁፍና በተንቀሳቃሽ ምስል ጭምር ሲዘዋወር ተመልክተናል፡፡ አሻም ይህንኑ በማህበራዊ ሚዲያ ስለ ጋዜጠኛው የተሰራጨውን መረጃ ተከትላ ስለ ተሰራጨበት መረጃ ሶፎኒያስን ማብራሪያ እንዲሰጥበት ጠይቃለች፡፡ በዚህም ሶፎኒያስ <<አሁን ራሴን ለማስተካከል፤ለማከም ፀበል ገብቻለሁ>> የሚል አጭር ምላሽ ከመስጠት ውጭ ተጨማሪ ያለው ነገር የለም። ስለሆነም አሻም ሚድያ ትሬዲንግ አ.ማ. የኢትዮጵያን ባህል እና ወግ እንዲሁም የህብረተሰቡን እሴት እና ሃይማኖት ያከበረ የምትመራበት ኤዲቶሪያል አላት፡፡ ይሁን እንጂ ጋዜጠኛው የሚዲያውን ኤዲቶሪያልም ሆነ የማህበረሰቡን እምነት ፣ እሴት፣ ወግ፣ ባህልና ሃይማኖት የሚጻረር ተግባር ተሰራጭቶበት በመመልከቷ እጅጉን እያዘነች ድርጊቱ የሚዲያ ተቋሟን የማይወክል ይልቁንም በጽኑ የምታወግዘው መሆኑን ለውድ ተመልካቾቻችን እና ተከታታዮቻችን ለመግለጽ እንወዳለን፡፡ ከዚህም በተጨማሪ አሻም ሚዲያ ትሬዲን አክሲዮን ማህበር ጋዜጠኛ ሶፎኒያስ ዋሲሁን በፈጸመው ከባድ የማህበረሰባዊ እሴት እና ኤዲቶሪያል ጥሰት ጭምር የነበራትን የስራ ውል ከዛሬ ሕዳር 30 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ማቋረጡዋን ለመግለጽ ትወዳለች፡፡ አሻም ለሁላችን!

ህዳር 28/2018 የአሻም የምሽት ዜና የኢትዮጵያ እና የደቡብ ኮሪያ የኢንቨስትመንት ትስስር እያደገ መምጣቱ ተገለፀ። ቲጂ ግርማ ትሬዲንግ ኃ/የተ/የግል ማኅበር (TG Girma Trading P.L.C
+2
ህዳር 28/2018 የአሻም የምሽት ዜና የኢትዮጵያ እና የደቡብ ኮሪያ የኢንቨስትመንት ትስስር እያደገ መምጣቱ ተገለፀ። ቲጂ ግርማ ትሬዲንግ ኃ/የተ/የግል ማኅበር (TG Girma Trading P.L.C) የኮሪያ የውበት መጠበቂያ ምርት የሆነውን “ስቴሽን ቢ” (Station B) የተሰኘውን ምርት በኢትዮጵያ ገበያ ላይ በይፋ ማስጀመሩን አስታወቀ። ምርቱ ከኮሪያ የመጡ የንግድ ባለቤቶችና ባለሙያዎች ስለ ምርቱ ልዩ ተፈጥሮ፣ ጥራት እና ለቆዳ ጤንነት ስላለው ጠቀሜታ ሙያዊ ማብራሪያ ሰጥተዋል። በዝግጅቱ ላይ የውበትን ጉዳይ ከጤና ጋር አስተሳስረው ለማቅረብ ስፔሻሊስት የቆዳ ሐኪሞች (Dermatologists) ተገኝተው ሙያዊ አስተያየታቸውን እና ንግግር አቅርበዋል። በተጨማሪም፣ ታዋቂ ግለሰቦችና ጥሪ የተደረገላቸው የክብር እንግዶች በተገኙበት ስለ ምርቱ ሰፊ ገለጻ ተደርጓል። የፊርማ ስነስርዓትም ተካሂዷል። ኩባንያው “ስቴሽን ቢ” የተሰኘውን የኮሪያ ውበት መጠበቂያ ምርት ከሚዲያ ተቋማት ጋር በጋራ በመተባበር ወደ ማኅበረሰቡ ለማስተዋወቅ መስራቱን ይቀጥላል ተብሏል። በብርሀን እሸቴ አሻም ለሁላችን !

ህዳር 28/2018 የአሻም የምሽት ዜና ናሽናል አቪየሽን ኮሌጅ በተለያዩ መርሃግብሮች ያስተማራቸውን 1628 ተማሪዎች አስመረቀ። ኮሌጁ በድረ ምረቃ፣ በቅድመ ምረቃ፣ በቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና
+2
ህዳር 28/2018 የአሻም የምሽት ዜና ናሽናል አቪየሽን ኮሌጅ በተለያዩ መርሃግብሮች ያስተማራቸውን 1628 ተማሪዎች አስመረቀ። ኮሌጁ በድረ ምረቃ፣ በቅድመ ምረቃ፣ በቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና እንድሁም በሰርተፍኬት ፕሮግራሞች ያሰለጠናቸውን ተማሪዎች ዛሬ ህዳር 27/2018 ዓ.ም በአዲስ ኢንተርናሽናል ኮንቬንሽን ማዕከል አስመርቋል። ናሽናል አቪየሽን ኮሌጅ ለ12ኛ ዙር ካስመረቃቸው ተማሪዎች ውስጥ ከሲቪል አቪየሺን ባለስልጣን ባገኘው እውቅና መሰረት፣ በአውሮፕላን ጥገና ቴክኒሺያን ያስተማራቸው የመጀመሪያ ተመራቂዎች እንደሚገኙበት ተገልጿል። በሁለተኛ ዲግሪ ፕሮግራም ኢንተርናሽናል ትሬድ እና ኢኮኖሚክስ እና ሎጅስቲክስ እና ሰፕላይ ቼይን ማኔጅመንት (130 እጩ ተመራቂዎችን) ፣ በመጀመሪያ ዲግሪ ፕሮግራም፤ አቬሽን ማኔጅመንት፣አካውንቲንግ እና ፋይናንስ፣ሆቴል ማኔጅመንት እና ማርኬቲንግ ማኔጅመንት (93 እጩ ተመራቂዎችን) በቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና በደረጃ IV በአካውንቲንግና ፋይናንስ፣ፍሮንት ኦፊስ፣ ሀርድዌርና ኔትወርክ ሰርቪስ፣ማርኬቲንግና ሴልስ ማኔጅመንት ፣ነርሲንግ እና ፋርማሲ 1035 ሰልጣኞችን ማስመረቁ ተገልጿል። በተጨማሪም በሠርተፍኬት ስልጠና በኤርክራፍትና ሜንቴናንስ ቴክኒሻን (ፓወር ፕላንት፣ኤር ፍሬም፣አቪኦኒክስ)፣ ኤርላይን ካቢን ክሪው፣ ፍላይት ኦፕሬሽን ኦፊሰር እና በቲኬቲንግና ሪዘርቬሽን ያሰለጠናቸውን 370 ሰልጣኞችን በጠቅላላ 1628 እጩ ተመራቂዎችን ተመርቀዋል ተብሏል። በቀጣይ ዘርፉን በማስፋት የነርሲንግ እና ፋርማሲ ፕሮግራሞች በኮሌጁ ለመስጠት መታቀዱ ተጠቁሟል። በብርሀን እሸቴ አሻም ለሁላችን !

የህዳር 25/2018 የአሻም የምሽት ዜና 🏷የአዳማ ከተማ አስተዳደር ከሰክሰስ ፕላስ ጋር በመሆን ለአካል ጉዳተኞች 50 ዊልቸር አስረከበ። ሰክሰስ ፕላስ ከከተማ አስተዳደሩ ሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ
+2
የህዳር 25/2018 የአሻም የምሽት ዜና 🏷የአዳማ ከተማ አስተዳደር ከሰክሰስ ፕላስ ጋር በመሆን ለአካል ጉዳተኞች 50 ዊልቸር አስረከበ። ሰክሰስ ፕላስ ከከተማ አስተዳደሩ ሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ፅህፈት ቤት ጋር በመተባበር በከተማዋ ለሚገኙ የአካል ጉዳተኞች የዊልቸር ድጋፍ አድርጓል። ድጋፉ በአለም ለ34ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ33ኛ ጊዜ የሚከበረውን የአካል ጉዳተኞች ቀን ምክንያት በማድረግ እንደሆነ ተገልጿል። በድጋፍ ስነ-ስርዓቱ ላይ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት እና የድርጅቱ አመራሮች ተገኝተዋል። የሰክሰስ ፕላስ ድጋፍ፣ አካል ጉዳተኞች በማህበራዊ ህይወታቸው በንቃት እንዲሳተፉ የሚያግዝ መህኑን የኦሮሚያ ክልል የሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ አቶ አራርሶ ቢቂላ ገልፀዋል። የሰክሰስ ፕላስ በጎ አድራጎት ድርጅት መስራች እና ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ፍሬው መንገሻ በበኩላቸው፣ ይህ የዊልቸር ድጋፍ በሌሎች የሀገሪቱ ክፍሎችም በየሦስት ወሩ ተጠናክሮ የሚቀጥል መርሃ ግብር አካል እንደሆነ ተናግረዋል። ከዚህ ቀደምም ድርጅቱ በአዲስ አበባ እና በትግራይ ክልል ውስጥ ለሚገኙ አካል ጉዳተኞች ተመሳሳይ ድጋፎችን ማድረጉ ይታወሳል። ሰክሰስ ፕላስ የበጎ አድራጎት ድርጅት አካል ጉዳተኞች በተሟላ ሁኔታ ለህብረተሰቡ እያደረገ ያለውን የበጎ አድራጎት ተግባር አበረታች መሆኑ ተገልጿል። በብርሀን እሸቴ አሻም ለሁላችን !

የህዳር 24/2018 የአሻም የምሽት ዜና 🏷የኢትዮጵያን ባህል አልባሳትን በማስተዋወቅ ረገድ ከፍተኛ ሚና ለተጫወቱ የኪነ ጥበብ ባለሙዎች እውቅና ተሰጠ፡፡ የኢትዮጵያን ፋሽንና የባህል አልባሳትን ለረ
+1
የህዳር 24/2018 የአሻም የምሽት ዜና 🏷የኢትዮጵያን ባህል አልባሳትን በማስተዋወቅ ረገድ ከፍተኛ ሚና ለተጫወቱ የኪነ ጥበብ ባለሙዎች እውቅና ተሰጠ፡፡  የኢትዮጵያን ፋሽንና የባህል አልባሳትን ለረጅም ጊዜ በማስተዋወቅ ለአርቲስት ሀመልማል አባተ ለአርቲስት መቅደስ ፀጋዬ  አስተዋፅኦ በማድረጋቸው እውቅና ተሰጥቷቸዋል፡፡   የአዋርዱ አዘጋጅ ኔክስት ፋሽንና ዲዛይን ኮሌጅ፤ ለድምፃዊ ሀመልማል አባተ፣ መቅደስ ፀጋዬ ፣ ዮሀንስ ታጠቅ- ከጆኒ ቪዲዮ እና ሌሎችንም ሸልሟል፡፡ ኮሌጁ በተለያየ ጊዜ በሚያዘጋጀው የAFFA አዋርድ ለኢትዮዽያ ፋሽን አስተዋፅኦ ያደረጉ ታላላቅ ሰዎችን የሚሸልምበት ፕሮግራም ላይ ነው እውቅናውን የሰጠው። በአፋ አዋርድ ቀደም ብሎ የተዘጋጀው የዲፕሎማቲክ ማህበረሰቡ ላይ ትኩረቱን ያደረገው "ዲ ኔክስት ኢቭ የዲፕሎማት ባዛር" በዛሬው እለት በዲሊኦፖል ሆቴል በይፋ ተጠናቋል፡፡ ከአርብ ጀምሮ እስከ ለሁለት ተከታታይ ቀናት በሚቆየው ዲፕሎማት ባዛር የተለያዩ የቆዳ ምርቶች ፣ ከከበሩ ማዕድን የተሰሩ ጌጣጌጦች ፣ የሀገር ባህል ልብሶች ፣ ከተፈጥሮ እፅዋት የተዘጋጁ የፀጉር ቅባቶችና የተለያዩ የእጅ ስራዎች ቀርበውበታል፡፡  ባዛሩ ከ1500 በላይ ሰዎች ይጎበኙታል ተብሎ እንደሚጠበቅ የተገለፀ ሲሆን የባዛሩ ዓላማ የተለያዩ ተቋማትን ማቀራረብ እንዲሁም በሥራቸው ጠንካራ የሆኑ ጀግና ሴቶችን ለማበረታታት መሆኑም ተገልጿል፡፡ ባዛሩን ኤልቬዜት ኢንተርናሽናል ኢቭንት ከዲሊኦፖል ሆቴል እና ከኔክስት ፋሽን ዲዛይን ጋር በጋራ በመሆን እንዳዘጋጁት የተገለጸ ሲሆን፤ በዚህ ባዛር ከተዘጋጁ መርሃግብሮች መካከል በኔክስት ፋሽን ዲዛይን የተዘጋጀ ዓመታዊ "አፋ አዋርድ" ተካሂዷል። በብርሀን እሸቴ አሻም ለሁላችን !

ህዳር 24/2018 የአሻም የምሽት ዜና 🏷ያያ ዋሌት ከጤና ሚኒስቴር ጋር የስትራቴጂክ አጋርነት ስምምነት ፈፀመ። ያያ የክፍያ ስርዓት አክሲዮን ማህበር የጤና ክፍያዎችን በዲጂታል ክፍያ ለመፈጸም የሚ
+2
ህዳር 24/2018 የአሻም የምሽት ዜና 🏷ያያ ዋሌት ከጤና ሚኒስቴር ጋር የስትራቴጂክ አጋርነት ስምምነት ፈፀመ። ያያ የክፍያ ስርዓት አክሲዮን ማህበር የጤና ክፍያዎችን በዲጂታል ክፍያ ለመፈጸም የሚያስችል ስምምነት ይፋ አድርገዋል። ስምምነቱ የተፈፀመው በጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴዔታ ወይዘሮ ሳህረላ አብዱላሂ እና የያያ ዋሌት ስራ አስፈፃሚ አቶ ዮሃንስ በልሁ አማካኝነት ነው። ሁለቱ ተቋማት በጤና ሚኒስቴር ዋና መስሪያቤት ይፋ ያደረጉት አዲሱ ስምምነት ሆስፒታሎች እና ፋርማሲዎች ሁሉን አቀፍ በሆነ የዲጂታል ክፍያ ስርዓት እንዲታገዙ በማድረግ የጤና አገልግሎትን ቀልጠፋ፣ ዘመናዊ እና ተደራሽ ለማድረግ ያለመ ነው ተብሏል። ስምምነቱ በጤና ተቋማት ውስጥ በጥሬ ገንዘብ የሚከናወኑ አሰራሮችን በመቀየር አስተዳደራዊ ጫናዎችን ለመቀነስ ያለመ እንደሆነ ተገልጿል። ያያ ዋሌት ተጠቃሚዎች በሁሉም የፋይናንስ ተቋማት ክፍያዎችን ለመፈፀም ያግዛል የተባለ ሲሆን፣ በሁሉም አማራጮች ውህደትን መፍጠር ያስችላል ተብሏል። ተቋሙ ከኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ ፍቃድ የተሰጠው እና በባንኩ የሚተዳደር የዲጂታል መሳሪያ አውጪ ተቋም ነው።

ህዳር 16/2018 የአሻም የምሽት ዜና 🏷 ኢትዮጵያ በሀገራዊ ሪፎርሙ ለጠንካራ ተቋማት ግንባታ ትኩረት ሰጥታ እየሰራች መሆኑን አደም ፋራህ ተናገሩ፡፡ 🏷የማይክሮ ፋይናንስ ተቋማትን ከብሔራዊ ዲጂታ
ህዳር 16/2018 የአሻም የምሽት ዜና 🏷 ኢትዮጵያ በሀገራዊ  ሪፎርሙ ለጠንካራ ተቋማት ግንባታ ትኩረት ሰጥታ እየሰራች መሆኑን አደም ፋራህ ተናገሩ፡፡   🏷የማይክሮ ፋይናንስ ተቋማትን ከብሔራዊ ዲጂታል ሥነ-ምህዳር ጋር ለማዋሃድ እየተሰራ ነው ተባለ፡፡ 🏷በኢትዮጵያ የፋሽን ዲዛይን ተቀባይነት እያደገ መምጣቱ ተገለጸ፡፡   🏷ኤስ ኦ ኤስ የህጻናት መንደሮች በኢትዮጵያ አርቲስት አለማየሁ ታደሰን የብራንድ አምባሳደር አድርጎ ሾመ፡፡ 🏷ታንዛኒያ ፕሬዝዳንታዊ ምርጫን ተከትሎ በተፈጠረ አለመረጋጋት ምክንያት የነጻነት ቀን እንዳይከበር ሰረዘች፡፡ 🏷የአውሮፓ ህብረት ምክር ቤት ለዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ፣ ቻድ እና ዮርዳኖስ 70 ሚሊዮን ዶላር የሚጠጋ ወታደራዊ ዕርዳታን አፀደቀ፡፡ 📶Live On Asham Tv Social Media 🔵 Facebook & 🔴 Youtube ቀጥታ ስርጭት በፊስ ቡክ እና በዩትዩብ ገጾቻችን ይከታተሉ https://www.youtube.com/ https://web.facebook.com/AshamMedia

ህዳር 15/2018 የአሻም የምሽት ዜና 🏷 ኢትዮጵያ በቡድን 20 አባል ሀገራት የመሪዎች ጉባኤ ወቅት አመርቂ የሚባል የውይይት ጊዜ ማሳለፏ ተመላከተ፡፡ 🏷ኢትዮጵያ የጀመረችው የማክሮ ኢኮኖሚን አስ
ህዳር 15/2018 የአሻም የምሽት ዜና 🏷 ኢትዮጵያ በቡድን 20 አባል ሀገራት የመሪዎች ጉባኤ ወቅት አመርቂ የሚባል የውይይት ጊዜ ማሳለፏ ተመላከተ፡፡ 🏷ኢትዮጵያ የጀመረችው የማክሮ ኢኮኖሚን አስመልክቶ ስኬታማ ውይይት መደረጉን የገንዘብ ሚኒስቴር ተገለፀ፡፡ 🏷ኦሜጋ ብድርና ቁጠባ ህብረት ስራ ማህበር ከሚዲያና ኪነ ጥበብ ባለሙያዎች ጋር ተፈራረመ። 🏷ሆስፒታሉ 25ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን ከህዳር 14 እስከ ግንቦት 13/2018 ዓ.ም በተለያዩ የበጎ አድራጎት ስራዎች እንደሚያከብር አስታወቀ፡፡ 🏷እስራኤል በቤይሩት የሂዝቦላ ጦር መሪን ገደለች። 🏷በፓኪስታን የመከላከያ መስሪያ ቤት ውስጥ በአጥፍቶ ጠፊዎች 3 ሰዎች ሞቱ 📶Live On Asham Tv Social Media 🔵 Facebook & 🔴 Youtube ቀጥታ ስርጭት በፊስ ቡክ እና በዩትዩብ ገጾቻችን ይከታተሉ https://www.youtube.com/ https://web.facebook.com/AshamMedia

ህዳር 13/2018 የአሻም የምሽት ዜና ለሀገራዊ ምክክር ውጤታማነት የሁሉም ዜጎች ተሳትፎ ወሳኝ ነው ሲሉ ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ ገለፁ። ውጤታማ ሀገራዊ ምክክር ለማካሄድ የሁሉም ዜጎ
+4
ህዳር 13/2018 የአሻም የምሽት ዜና ለሀገራዊ ምክክር ውጤታማነት የሁሉም ዜጎች ተሳትፎ ወሳኝ ነው ሲሉ ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ ገለፁ። ውጤታማ ሀገራዊ ምክክር ለማካሄድ የሁሉም ዜጎች ተሳትፎ ወሳኝ ነው ሲሉ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ አስታውቀዋል። ኮሚሽነሩ ይህን ያሉት በኦሮሚያ ክልል የሴቶች፣ ወጣቶችና አካል ጉዳተኞች አደረጃጀቶች የተሳተፉበት የምክክር መድረክ በአዳማ ከተማ በተካሄደበት ወቅት ነው። በመድረኩ ላይ የተገኙት የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ ባደረጉት ንግግር፤  ሴቶች፣ ወጣቶችና አካል ጉዳተኞችን ጨምሮ ሁሉም የሕብረተሰብ ክፍሎችና ባለድርሻ አካላት የሚሳተፉበት ሀገራዊ ምክክር ለማካሄድ ኮሚሽኑ ዝግጅቱን አጠናክሮ መቀጠሉን ገልጸዋል። በዚህ ሂደትም ሴቶች ፣ ወጣቶች እና አካልy ጉዳተኞች በንቃት መሳተፍ እንዳለባቸው ማሳሰባቸውን አሻም ከኮሚሽኑ ያገኘችው መረጃ ያመላክታል። የኮሚሽኑ ዓላማና ተግባር ላይ ዜጎች በቂና ግልጽ ግንዛቤ እንዲያገኙና ለምክክሩ ውጤታማነት የድርሻቸውን እንዲወጡ ለማድረግ የተለያዩ ስራዎች መሰራታቸውን የተናገሩት ዋና ኮሚሽነሩ፤ በዚህም ውጤታማ ተግባራት መከናወናቸውን አብራርተዋል። መስፍን ከተቋማት፣ ከሲቪክ ማህበራት፣ ከፖለቲካ ፓርቲዎች፣ ከዲያስፖራውና ከሌሎችም የተለያዩ የሕብረተሰብ ክፍሎች አጀንዳ መሰብሰቡንም ገልፀዋል። በብርሀን እሸቴ አሻም ለሁላችን !

ህዳር 12/2018 l የአሻም የምሽት ዜና 🏷 የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር የዓሳ ሃብት ምርታማነትን እያሳደገ መሆኑን ሚኒስቴሩ አስታወቀ። 🏷ለማክሮ ኢኮኖሚው በርካታ መሰረቶች መጣላቸውን አንድ የም
ህዳር 12/2018 l የአሻም የምሽት ዜና 🏷 የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር የዓሳ ሃብት ምርታማነትን እያሳደገ መሆኑን ሚኒስቴሩ አስታወቀ። 🏷ለማክሮ ኢኮኖሚው  በርካታ መሰረቶች መጣላቸውን አንድ የምጣኔ ሀብት ባለሙያ ለአሻም ገለፁ፡፡ 🏷የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን ሕብረብሔራዊ አንድነትን በማጎልበት ለሀገር ብልፅግና መረጋገጥ አይተኬ ሚና እየተጫወተ ነው ተባለ፡፡ 🏷የደቡብ አፍሪካ የሴቶች መብት ተሟጋች ተቋማት ፆታዊ ጥቃት አገር አቀፍ ቀውስ ተብሎ እንዲታወጅ የሚጠይቅ ሰላማዊ ሰልፍ ሊያደርጉ ነው ተባለ። 🏷የሩሲያ ሃይሎች የዩክሬኑን ኩፒያንስክ ተቆጣጥረዋል ሲሉ ከፍተኛ ወታደራዊ ባለስልጣናት ቢናገሩም ዩክሬን አስተባበለች፡፡ 🏷በማዕከላዊ ባንግላዲሽ 5.5 በሬክተር የሆነ የመሬት መንቀጥቀጥ በትንሹ 6 ሰዎች ሞቱ፡፡ 📶Live On Asham Tv Social Media 🔵 Facebook & 🔴 Youtube ቀጥታ ስርጭት በፊስ ቡክ እና በዩትዩብ ገጾቻችን ይከታተሉ https://www.youtube.com/ https://web.facebook.com/AshamMedia

ህዳር 11/2018 l የአሻም የምሽት ዜና 🏷 በአፋር ሠመራ ሎጊያ ሲካሄድ የነበረው 10ኛው የኢትዮጵያ ከተሞች ፎረም መርሀ ግብር ተጠናቀቀ ። 🏷በተለያዩ ሀገራት የሚገኙ ቅርሶች እንድመለሱ የሚያበ
ህዳር 11/2018 l የአሻም የምሽት ዜና 🏷 በአፋር ሠመራ ሎጊያ ሲካሄድ የነበረው   10ኛው የኢትዮጵያ ከተሞች ፎረም መርሀ ግብር  ተጠናቀቀ ። 🏷በተለያዩ ሀገራት የሚገኙ ቅርሶች እንድመለሱ የሚያበረታታ ስራ እየተሰራ ነው ሲሉ  የቱሪዝም ሚኒስትር ሰላማዊት ካሳ ገለፁ። 🏷መንግስት ለኢንቨስመንት በር ከፋች የሆኑ ስራዎችን እየሰራ ነው ተባለ፡፡ 🏷በማዕከላዊ ቬትናም የጎርፍ መጥለቅለቅ ተባብሶ የሟቾች ቁጥር 16 ደረሰ፡፡ 🏷ሂዩማን ራይትስ ዎች በዌስት ባንክ እስራኤልን በጦርነት ወንጀል ከሰሰ 📶Live On Asham Tv Social Media 🔵 Facebook & 🔴 Youtube ቀጥታ ስርጭት በፊስ ቡክ እና በዩትዩብ ገጾቻችን ይከታተሉ https://www.youtube.com/ https://web.facebook.com/AshamMedia

Share

ህዳር 10/2018 l የአሻም የምሽት ዜና 🏷የመንግስት አገልግሎት ተቋማት ዘመን ተሻጋሪ መሆን አለባቸው ሲሉ ሙፈሪያት ካሚል ተናገሩ፡፡ 🏷ኢትዮጵያ የጥራጥሬና የቅባት እህሎችን ወደ ውጭ በመላክ ዓ
ህዳር 10/2018 l የአሻም የምሽት ዜና 🏷የመንግስት አገልግሎት  ተቋማት ዘመን ተሻጋሪ መሆን አለባቸው ሲሉ ሙፈሪያት ካሚል ተናገሩ፡፡ 🏷ኢትዮጵያ የጥራጥሬና የቅባት እህሎችን ወደ ውጭ በመላክ ዓለም አቀፍ መሪ ለመሆን በቁርጠኝነት እየሰራች ነው ተባለ፡፡ 🏷አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲን ወደ ራስ ገዝነት የሚያሸጋግሩ የዝግጅት ተግባራት መጠናቀቃቸውን የዩንቨርሲቲው ተጠባባቂ ፕሬዝዳንት ሳሙኤል ክፍሌ ገለጹ። 🏷በኢትዮጵያ የድጅታል የገንዘብ ዝውውር ከጊዜ ወደጊዜ እየጨመረ መምጣቱ ተገለጸ፡፡ 🏷የሜክሲኮ ፕሬዝዳንት ክላውዲያ ሺንባም ትራምፕ በሜክሲኮ ካርቴሎች ላይ ያቀዱትን ወታደራዊ ጣልቃገብነትን ውድቅ አደረጉ፡፡ 🏷ትራምፕ የሳዑዲ አረቢያ  ልዑል ስለ ካሾጊ ግድያ ምንም የሚያውቁት ነገር የለም ሲሉ ገለጹ። 📶Live On Asham Tv Social Media 🔵 Facebook & 🔴 Youtube ቀጥታ ስርጭት በፊስ ቡክ እና በዩትዩብ ገጾቻችን ይከታተሉ https://www.youtube.com/ https://web.facebook.com/AshamMedia

ህዳር 9/2018 l የአሻም የምሽት ዜና 🏷በኢትዮጵያ ማዕድን ኢንዱስትሪ ውስጥ ሲታዩ የነበሩ ችግሮች መሻሻል ተደርጎባቸዋል ሲል ሚኒስቴሩ አስታወቀ ። 🏷ኪነ ጥበብ የሀገርን ታሪክ ለማስተዋወቅ ወሳ
ህዳር 9/2018 l የአሻም የምሽት ዜና 🏷በኢትዮጵያ ማዕድን ኢንዱስትሪ  ውስጥ ሲታዩ የነበሩ ችግሮች መሻሻል ተደርጎባቸዋል ሲል ሚኒስቴሩ አስታወቀ ። 🏷ኪነ ጥበብ የሀገርን ታሪክ ለማስተዋወቅ ወሳኝ ሚና እንደሚጫዎት ተገለጸ፡፡ 🏷ጃፓን በቻይና ያሉ ዜጐቿ በዲፕሎማሲያዊ ቀውሱ ምክንያት የደኅንነት ማስጠንቀቂያ አውጥታለች። 🏷ትራምፕ ዩናይትድ ስቴትስ በሚቀጥለው የሜክሲኮ የአደንዛዥ ዕፅ አቅራቢዎችን ልትመታ እንደምትችል ተናግረዋል። 📶Live On Asham Tv Social Media 🔵 Facebook & 🔴 Youtube ቀጥታ ስርጭት በፊስ ቡክ እና በዩትዩብ ገጾቻችን ይከታተሉ https://www.youtube.com/ https://web.facebook.com/AshamMedia

ህዳር 5/2018 l የአሻም የምሽት ዜና 🏷አዲስ አበባ በ2022 አ.ም ፍጹም የጸዳች የአፍሪካ ተምሳሌት የሆነች ከተማ ሆና ማየት ዋነኛ ራዕያችን ነው ሲሉ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ ገለጹ። 🏷ማህበሩ የ
ህዳር 5/2018 l የአሻም የምሽት ዜና 🏷አዲስ አበባ በ2022 አ.ም ፍጹም የጸዳች የአፍሪካ ተምሳሌት የሆነች ከተማ ሆና ማየት ዋነኛ ራዕያችን ነው ሲሉ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ ገለጹ። 🏷ማህበሩ የአካል ጉዳተኞችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየሰራ እንደሚገኝ ገለጸ፡፡ 🏷ኢኳዶራውያን በአገሪቱ ውስጥ የውጭ ወታደራዊ ጦር ሠፈሮችን መፍቀድን በመቃወም ድምጽ መስጠታቸው ተነገረ፡፡ 🏷ዩናይትድ ስቴትስ የ'ዴ ሎስ ሶልስ' የወንጀል ቡድንን በአሸባሪነት ልትፈርጅ አስታወቀች፡፡ 📶Live On Asham Tv Social Media 🔵 Facebook & 🔴 Youtube ቀጥታ ስርጭት በፊስ ቡክ እና በዩትዩብ ገጾቻችን ይከታተሉ https://www.youtube.com/ https://web.facebook.com/AshamMedia

ህዳር 6/2018 የአሻም ዜና የ10ኛው የኢትዮጵያ ከተሞች ፎረም ኤግዚቢሽን በሠመራ ሎጊያ ከተማ ተከፈተ። በአፋር ክልል በተዘጋጀው በዚህ ፎረም በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ስርዓት
+2
ህዳር 6/2018 የአሻም ዜና የ10ኛው የኢትዮጵያ ከተሞች ፎረም ኤግዚቢሽን በሠመራ ሎጊያ ከተማ ተከፈተ። በአፋር ክልል በተዘጋጀው በዚህ ፎረም በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊ እና የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አደም ፋራህ 10ኛውን የኢትዮጵያ ከተሞች ፎረም ኤግዚቢሽን በሠመራ ሎጊያ ከተማ አስጀምረዋል። 10ኛው የኢትዮጵያ ከተሞች ፎረም "የከተሞች ዕድገት ለኢትዮጵያ ልህቀት” በሚል መሪ ሀሳብ ዛሬ በአፋር ክልል ሰመራ ሎጊያ ከተማ መካሄድ ጀምሯል፡፡ ኤግዚቢሽኑ ከተሞች ራሳቸውን የሚያስተዋውቁበት መድረክ መሆኑ ተገልጿል። በተጨማሪም ከተሞች ያላቸውን ምርጥ ተሞክሮ ልምድ የሚለዋወጡበት መድረክ መሆኑን አሻም ከክልሉ መንግስት ኮሚኒኬሽን ቢሮ ያገኘችው መረጃ ያመላክታል። አሻም ለሁላችን !