en
Feedback
Amhara Medical Association(AMA)

Amhara Medical Association(AMA)

Open in Telegram

Amhara medical Association is all about quality of medical care and physicians satisfaction in the nation.

Show more
410
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
https://m.facebook.com/story.php?story_fbid=5873434649390761&id=100001728532919 #አንገብጋቢው_የሪፈራል_ጉዳይ መፍትሔ የሚሹ አሳሳቢ እውነታዎች 1. ሕመምተኛውን ወደምንልክበት ሆስፒታል አገልግሎቱ እየተሰጠ መሆኑን ሳያረጋግጡ መላክ። - ከፊቴ ገለል ይበልልኝ አይነት አካሄድ ነው። ሕመምተኛው በተላከበት ሆስፒታል ሲደርስ ፣ አገልግሎቱ እንደሌለ ሲነገረው ፣ እንዴት እንደሚያዝን ፣ እንዴት እንደሚንገላታ ፣ ለላኪው ሐኪም ግብረ መልስ የሚሰጥበት መንገድ የለም። ተጠያቂ ማድረጊያ መንገድም የለም። አስታማሚ እና ታማሚ አሳዛኝ በሆነ ቅሬታ ውስጥ ይወድቃሉ። በሌለ ገንዘብ ፣ ገንዘባቸውን ያባክናሉ። መፍትሔ:- - ተደዋውሎ አጣርቶ መላክ ቢቻል። - በየሪፈራል ሆስፒታሎች የሚሰጠው አገልግሎት መታወቅ የሚችልበት መዝገብ ወይም ድህረ ገጽ ማዘጋጀት ቢቻል - ይኼ እስኪሆን ሐኪሙ አጣርቶ እርግጠኛ ሲሆን መላክ ቢችል 2. አገልግሎቱ እየተሰጠ ቢሆንም ከህመምተኛ መብዛት የተነሳ ቀጠሮ በሚበዛባቸው ሆስፒታሎች ፣ አሁኑኑ ካልሄድክ መሞትህ ነው እያሉ መላክ። - ሕመምተኛው ሲደርስ ያልጠበቀው አይነት የቀጠሮ ጊዜ ርዝመት ያማርረዋል። ከተቀበለው ባለሙያ ጋር ዱላ ቀረሽ ግብግብ እንዲገባ እና ቅሬታ ውስጥ እንዲገባ ያደርገዋል። - እውነታውን አጣርቶ እና ነግሮ መላክ ቢቻል። 3. ሪፈር ስናደርግ ለሕመምተኛው ሾለ ሕመሙ አለመንገር - ብዙ ጊዜ በካንሰር ሕመም ላይ ይዘወተራል። ሕመምተኛው ሁሉን ምርመራ አድርጎ ፣ የተረጋገጠ የካንሰር ሕመም እንዳለው በያዘው ወረቀት ላይ ሰፍሮ እንኳን ፣ ምንም ነገር ሳይነግሩት መላክ። - ይህ አይነቱ ደግሞ በጣም የሚደንቅ ነው። ሲደርስ ያገኘውን ሐኪም ጠይቆ ሲረዳ ድንጋጤው ፣ የስነ-ልቦና ጫናው ከበድ ያለ ነው። - ቢቻል ስለተረጋገጠው ሕመም ተጨማሪ አንብቦ ፣ ሾለ ሕክምና አማራጮቹ ፣ ስለደረሰበት የስርጭት ደረጃ፣ ሪፈር ተደርጎ ቢታከም ስለሚያገኘው የእገዛ ደረጃ መክሮ መላክ ቢቻል። ከተቻለ ደግሞ በፅሑፍ መስጠት ቢቻል። 4. ያልተሟላ ምርመራ አስይዞ መላክ - ከቀላል ሽንትና ደም ምርመራ ጀምሮ ፣ እስከ መቅን ምርመራ፣ ሲቲ ፣ MRI ናሙና ምርመራ (FNA, Biopsy ጨምሮ) ከሰሩ በኋላ ፣ ሕመምተኛውም በአንድ ባልተሟላ ወረቀት ብቻ መላክ። - ይኼኛው ደግሞ የከፋ ነው። ሕመምተኛው ሲደርስ ምንም እንዳልተመረመረ ፣ ገንዘቡን እንዳላባከናና እንዳልደከመ ፣ ድጋሚ ከዜሮ እንዲጀምር ያደርገዋል። ባለበት ሆስፒታል ኮፒ አስቀርቶ ዋናውን አስይዞ መላክ ከሚታሰበው በላይ ያግዛል። ውጤቱን በሲዲ ፣ ናመኖዎችን በ slide መስጠት በእጅጉ ያግዛል። 5. የማረፊያ አልጋ ሞልቶባቸው በተጨናነቁ ሆስፒታሎች ሳይደዋወሉ ፣ ሳያመቻቹ ሕመምተኛውን መላክ። ይህ ደግሞ አንዳንዴም በማያውቀው ከተማ ፣ ረዳት በሌለበት አስታማሚን ጨምሮ በየድንገተኛ ክፍሉ ለእንግልት የሚዳርግ ነው። 6. አዘግይቶ መላክ - ከምርመራ ምርመራ ፣ ከቀጠሮ ቀጠሮ በተራዘመ ሂደት ካለፈ በኋላ ሁኔታዎች ተባብሰው ፣ መረዳት የሚቻልበት ደረጃ ካለፈ በኋላ ፣ ለሕመምተኛው ስለህመሙ ደረጃ በቂ መረጃ ሳይሰጡ መላክ። - በቶሎ መላክ ከማከም አይተናነስም። 7. ገንዘቡን ከጨረሰ በኋላ መላክ - ይህ በግል የህክምና ተቋማት የተለመደ ነው። - ከትንሽ እስከ ትልቅ ምርመራ ካደረጉ በኋላ ፣ በአልጋ እና ሌሎች ወጪዎች ሕመምተኛው ገንዘቡን ከስክሶ ፣ መጨረሻው ላይ ህክምናው እኛ ጋር ስለሌለ ሂድ ብሎ ማሰናበት። - ይህ ደግሞ ጠያቂም ፣ ተጠያቂነትም የሌለበት የአደባባይ በደል ነው። ቢያንስ የህክምናውን አጠቃላይ ወጪ አስቀድሞ ገምቶ መንገር ቢቻል፣ ምርመራው እንጂ ህክምናው እንደሌለ ቀድሞ መንገር ቢቻል። ቋሚ ንብረት ሸጦ ገንዘቡን ሲጨርስ ብቻ ዛሬውኑ ለቀህ ውጣልኝ አይነት አካሄድ የከፋ ግፍ ነው። - በጽኑ የታመመን ሰው ያለ ባለሙያ መላክ 8. እየሞተ መሆኑ እየታወቀ እንኳን መላክ (dead body on arrival) - አንዳንድ ሕመሞች ህመምተኛው ከቦታ ቦታ እንዲንቀሳቀስ የማያስቻሉ ፣ ባለበት ቦታ በቶሎ ህክምና የሚሹ ናቸው። የድንገተኛ ህክምናውን በማጠናከር የሚቻለውን ሁሉ ማድረግ ሲገባ ፣ ወደ ሌላ ለመላክ በሚደረግ ሙከራ ህመምተኛው መንገድ ላይ ሞቶ እንኳን ረዥም ርቀት ተጉዞ መድረስ። ይኼ ልብ የሚሰብር የሚያጋጥመን እውነታ ነው። * በሪፈራል ሆስፒታል ሾሰል ከታዘብኳቻው ፣ ትኩረት የሚሹ የሪፈራል ችግሮች ውስጥ ጥቂቶቹን ከነመፍትሔው አካፈልኩ። መፍትሔ ከባለሙያው ፣ መፍትሔ ከሚንስትር መስሪያ ቤቱ ይሻሉ። * እንደ ባለሙያ ብቻ እያሰብን ያልታዩን ችግሮችን እና የመፈትሔ ሀሳቦችን  ጨምሩበት። Dr. Demelash Gezahegn (Emergency and critical care specialist, Black lion  hospital)

https://m.facebook.com/story.php?story_fbid=5873434649390761&id=100001728532919 #አንገብጋቢው_የሪፈራል_ጉዳይ መፍትሔ የሚሹ አሳሳቢ እውነታዎች 1. ሕመምተኛውን ወደምንልክበት ሆስፒታል አገልግሎቱ እየተሰጠ መሆኑን ሳያረጋግጡ መላክ። - ከፊቴ ገለል ይበልልኝ አይነት አካሄድ ነው። ሕመምተኛው በተላከበት ሆስፒታል ሲደርስ ፣ አገልግሎቱ እንደሌለ ሲነገረው ፣ እንዴት እንደሚያዝን ፣ እንዴት እንደሚንገላታ ፣ ለላኪው ሐኪም ግብረ መልስ የሚሰጥበት መንገድ የለም። ተጠያቂ ማድረጊያ መንገድም የለም። አስታማሚ እና ታማሚ አሳዛኝ በሆነ ቅሬታ ውስጥ ይወድቃሉ። በሌለ ገንዘብ ፣ ገንዘባቸውን ያባክናሉ። መፍትሔ:- - ተደዋውሎ አጣርቶ መላክ ቢቻል። - በየሪፈራል ሆስፒታሎች የሚሰጠው አገልግሎት መታወቅ የሚችልበት መዝገብ ወይም ድህረ ገጽ ማዘጋጀት ቢቻል - ይኼ እስኪሆን ሐኪሙ አጣርቶ እርግጠኛ ሲሆን መላክ ቢችል 2. አገልግሎቱ እየተሰጠ ቢሆንም ከህመምተኛ መብዛት የተነሳ ቀጠሮ በሚበዛባቸው ሆስፒታሎች ፣ አሁኑኑ ካልሄድክ መሞትህ ነው እያሉ መላክ። - ሕመምተኛው ሲደርስ ያልጠበቀው አይነት የቀጠሮ ጊዜ ርዝመት ያማርረዋል። ከተቀበለው ባለሙያ ጋር ዱላ ቀረሽ ግብግብ እንዲገባ እና ቅሬታ ውስጥ እንዲገባ ያደርገዋል። - እውነታውን አጣርቶ እና ነግሮ መላክ ቢቻል። 3. ሪፈር ስናደርግ ለሕመምተኛው ሾለ ሕመሙ አለመንገር - ብዙ ጊዜ በካንሰር ሕመም ላይ ይዘወተራል። ሕመምተኛው ሁሉን ምርመራ አድርጎ ፣ የተረጋገጠ የካንሰር ሕመም እንዳለው በያዘው ወረቀት ላይ ሰፍሮ እንኳን ፣ ምንም ነገር ሳይነግሩት መላክ። - ይህ አይነቱ ደግሞ በጣም የሚደንቅ ነው። ሲደርስ ያገኘውን ሐኪም ጠይቆ ሲረዳ ድንጋጤው ፣ የስነ-ልቦና ጫናው ከበድ ያለ ነው። - ቢቻል ስለተረጋገጠው ሕመም ተጨማሪ አንብቦ ፣ ሾለ ሕክምና አማራጮቹ ፣ ስለደረሰበት የስርጭት ደረጃ፣ ሪፈር ተደርጎ ቢታከም ስለሚያገኘው የእገዛ ደረጃ መክሮ መላክ ቢቻል። ከተቻለ ደግሞ በፅሑፍ መስጠት ቢቻል። 4. ያልተሟላ ምርመራ አስይዞ መላክ - ከቀላል ሽንትና ደም ምርመራ ጀምሮ ፣ እስከ መቅን ምርመራ፣ ሲቲ ፣ MRI ናሙና ምርመራ (FNA, Biopsy ጨምሮ) ከሰሩ በኋላ ፣ ሕመምተኛውም በአንድ ባልተሟላ ወረቀት ብቻ መላክ። - ይኼኛው ደግሞ የከፋ ነው። ሕመምተኛው ሲደርስ ምንም እንዳልተመረመረ ፣ ገንዘቡን እንዳላባከናና እንዳልደከመ ፣ ድጋሚ ከዜሮ እንዲጀምር ያደርገዋል። ባለበት ሆስፒታል ኮፒ አስቀርቶ ዋናውን አስይዞ መላክ ከሚታሰበው በላይ ያግዛል። ውጤቱን በሲዲ ፣ ናመኖዎችን በ slide መስጠት በእጅጉ ያግዛል። 5. የማረፊያ አልጋ ሞልቶባቸው በተጨናነቁ ሆስፒታሎች ሳይደዋወሉ ፣ ሳያመቻቹ ሕመምተኛውን መላክ። ይህ ደግሞ አንዳንዴም በማያውቀው ከተማ ፣ ረዳት በሌለበት አስታማሚን ጨምሮ በየድንገተኛ ክፍሉ ለእንግልት የሚዳርግ ነው። 6. አዘግይቶ መላክ - ከምርመራ ምርመራ ፣ ከቀጠሮ ቀጠሮ በተራዘመ ሂደት ካለፈ በኋላ ሁኔታዎች ተባብሰው ፣ መረዳት የሚቻልበት ደረጃ ካለፈ በኋላ ፣ ለሕመምተኛው ስለህመሙ ደረጃ በቂ መረጃ ሳይሰጡ መላክ። - በቶሎ መላክ ከማከም አይተናነስም። 7. ገንዘቡን ከጨረሰ በኋላ መላክ - ይህ በግል የህክምና ተቋማት የተለመደ ነው። - ከትንሽ እስከ ትልቅ ምርመራ ካደረጉ በኋላ ፣ በአልጋ እና ሌሎች ወጪዎች ሕመምተኛው ገንዘቡን ከስክሶ ፣ መጨረሻው ላይ ህክምናው እኛ ጋር ስለሌለ ሂድ ብሎ ማሰናበት። - ይህ ደግሞ ጠያቂም ፣ ተጠያቂነትም የሌለበት የአደባባይ በደል ነው። ቢያንስ የህክምናውን አጠቃላይ ወጪ አስቀድሞ ገምቶ መንገር ቢቻል፣ ምርመራው እንጂ ህክምናው እንደሌለ ቀድሞ መንገር ቢቻል። ቋሚ ንብረት ሸጦ ገንዘቡን ሲጨርስ ብቻ ዛሬውኑ ለቀህ ውጣልኝ አይነት አካሄድ የከፋ ግፍ ነው። - በጽኑ የታመመን ሰው ያለ ባለሙያ መላክ 8. እየሞተ መሆኑ እየታወቀ እንኳን መላክ (dead body on arrival) - አንዳንድ ሕመሞች ህመምተኛው ከቦታ ቦታ እንዲንቀሳቀስ የማያስቻሉ ፣ ባለበት ቦታ በቶሎ ህክምና የሚሹ ናቸው። የድንገተኛ ህክምናውን በማጠናከር የሚቻለውን ሁሉ ማድረግ ሲገባ ፣ ወደ ሌላ ለመላክ በሚደረግ ሙከራ ህመምተኛው መንገድ ላይ ሞቶ እንኳን ረዥም ርቀት ተጉዞ መድረስ። ይኼ ልብ የሚሰብር የሚያጋጥመን እውነታ ነው። * በሪፈራል ሆስፒታል ሾሰል ከታዘብኳቻው ፣ ትኩረት የሚሹ የሪፈራል ችግሮች ውስጥ ጥቂቶቹን ከነመፍትሔው አካፈልኩ። መፍትሔ ከባለሙያው ፣ መፍትሔ ከሚንስትር መስሪያ ቤቱ ይሻሉ። * እንደ ባለሙያ ብቻ እያሰብን ያልታዩን ችግሮችን እና የመፈትሔ ሀሳቦችን  ጨምሩበት። Dr. Demelash Gezahegn (Emergency and critical care specialist, Black lion  hospital)

Happy New Year to All Ethiopians! Let's Hope The New Year Bring Us Solidarity,Health,professional Excellency and Prosperity T
Happy New Year to All Ethiopians! Let's Hope The New Year Bring Us Solidarity,Health,professional Excellency and Prosperity To Our People. #Love #peace #Solidarity #Professionalism

Professional injustice against #DrTazebachew. Such professional breaches shouldn't be ignored as a Normal events of Medical school. All medical shools shall stop from deciding unwise and unprofessional decisions. #standforjustice https://t.co/mtrekw57Ue

የአማራ ህክምና ማህበር 3ኛውን አመታዊ ጉባዔ በባህርዳር ከተማ አካሄደ ። በጉባዔው የክልሉን የጤና አሁናዊ ሁኔታ የሚያሳይ ጥናታዊ ፁሁፍ በዶ.ር ኃ/ማርያም አወቀ(AMA EB Member) ፣ የጤና ባለሙያዎች ሚና በድንገተኛ የህበረተሰብ ጤና አደጋዎች ምላሽ አሰጣጥ የሚል አስተማሪ ፁሁፍ በፕሮፌሰር ፈንቴ አምባው(EPHA Amhara Charter Chair) እንዲሁም የማህበሩ አመታዊ የስራ አፈፃፀም በዶ.ር አብራራው ታደሰ(AMA President ) ቀርበዋል። በተጨማሪም በማህበሩ መተዳደሪያ ደንብ ላይ ማሻሻያ የተደረገባቸው አንቀፆች በዶ.ር ኃይሉ ይነስ (AMA Membership Director) ቀርቦ ፀድቋል። በጉባኤው ማህበሩን ሲያግዙ ለነበሩ ተቋማት እና ግለሰቦች የእውቅና የምስክር ወረቀት ተሰጥቷል ። በመጨረሻም ማህሩን ለሚቀጥሉት ሁለት አመታት የሚመሩ አዲስ ስራ አስፈፃሚ ተመርጧል ። በጉባዔው የተገኙት የዕለቱ የክብር እንግዳ የአብክመ ጤና ቢሮ ም/ቢሮ ኃላፊ ዶ.ር ጋሹ ክንዱ የማጠቃለያ መልክት አስተላልፈዋል። ማህበሩን እስካሁን ስታገለግሉ የነበራችሁ የስራ አስፈፃሚ አባላት እና ዳይረክተሮችን እያመሰገንን አዲስ ለተመረጣችሁ አባላት መልካም የስራ ዘመን እንዲሆንላችሁ እንመኛለን ። የአማራ ህክምና ማህበር ሰኔ 19,2014 ዓ.ም ባህር ዳር

ውድ የጉባኤው ተሳታፊዎቻችን የአማራ ሀኪሞች ማህበር ሶስተኛውን አመታዊ ጉባኤ የሚያካሂደው በባህር ዳር ከተማ ቤተ ዳንኤል ሆቴል ቅዳሜ ሰኔ 18,2014 ዓ.ም ከጧቱ 2:30 ጀምሮ ስለሆነ አስፈላጊውን ዝግጅት እንድታደርጉ በድጋሚ እናስታውቃለን ። አዘጋጅ ኮሚቴው

ለአማራ ሀኪሞች ማህበር አባላት እና ደጋፊዎች በሙሉ ማህበራችን ሶስተኛውን አመታዊ ጉባዔ ሰኔ 18,2014 ዓ.ም በባህርዳር ከተማ ስለሚካሄድ በጉባዔው መሳተፍ የምትፈልጉ ከታች ባለው የመመዝገቢያ ፎርም እንድትመዘገቡ እናስታውቃለን ።

ለአማራ ሀኪሞች ማህበር አባላት እና ደጋፊዎች በሙሉ ማህበራችን ሶስተኛውን አመታዊ ጉባዔ ሰኔ 18,2014 ዓ.ም በባህርዳር ከተማ ስለሚካሄድ በጉባዔው መሳተፍ የምትፈልጉ ከታች ባለው የመመዝገቢያ ፎርም እንድትመዘገቡ እናስታውቃለን ።

ወደ የት እየተሄደ ነው። እንዲህ አይነት አካሄዶች ሐገርን ጎጅ ናቸው።
ወደ የት እየተሄደ ነው። እንዲህ አይነት አካሄዶች ሐገርን ጎጅ ናቸው።

Share 'Amhara Health .pdf'

Amhara Region Heath Atlas 2021, presents key results from EPHI and IHME collaborative subnational burden of disease analysis as part of the Global Burden of Disease Study 2019 for Amhara, a region of Ethiopia.  All-cause mortality in Amhara reduced from about 2,370 per 100,000 persons in 1990 to about 955 per 100,000 persons in 2019. The number of DALYs has significantly reduced from about 20 million DALYs in 1990 to 8 million in 2019. Total fertility declined from 6.8 births per woman in 1990 to 3.9 births per woman in 2019, a 43% change. Of the leading causes of YLLs and YLDs in Amhara in 2019, Diarrheal diseases, Neonatal encephalopathy due to birth asphyxia and trauma and Lower respiratory infections are the leading three causes. Child and maternal malnutrition is the source of the greatest number of attributable DALYs, followed by Air pollution. The life expectancy in Amhara region increased from 46 years in 1980 to 69 years in 2019. Amhara region population will live, on average, 61 healthy years, with 9 years lived with disability.

ህብረተሰቡ የጤና መድህን ተጠቃሚ እንዲሆን በጎንደር ዩኒቨርሲቲ የሚሰሩት ዶ/ር ካሳዬ ደመቀ አሳሰቡ። የድንገተኛና ፅኑ ህሙማን እስፔሻሊስት የሆኑት ዶ/ር ካሳዬ እንዳሉት ማህበረሰቡ የህክምና ወጭን በ
ህብረተሰቡ የጤና መድህን ተጠቃሚ እንዲሆን በጎንደር ዩኒቨርሲቲ የሚሰሩት ዶ/ር ካሳዬ ደመቀ አሳሰቡ። የድንገተኛና ፅኑ ህሙማን እስፔሻሊስት የሆኑት ዶ/ር ካሳዬ እንዳሉት ማህበረሰቡ የህክምና ወጭን በወቅቱ መክፈል ባለመቻሉ ለብዙ እንግልትና ለህክምና እጦት እንደሚዳረግ አውስተዋል። የጤና መድህን በአመት አንድ ጊዜ በሚከፈል ቀላል ወጭ የጤና ኢንሹራንስ የሚገኝበት ሥርዓት ነው።ህብረተሰቡ ይህን በማድረግ በገንዘብ እጦት ምክንያት የሚደርስበትን የህክምና እጦት ማስቀረት ይችላል። ህብረተሰቡ የጤና መድህን ተጠቃሚ እንዲሆን ባለድርሻ አካላት ጠንክረው መሥራት ይጠበቅባቸዋልም ብለዋል። (ከያንዳንዱ የሚጠበቀው ክፍያ ከታች ተያይዟል።)