en
Feedback
Amhara Medical Association(AMA)

Amhara Medical Association(AMA)

Open in Telegram

Amhara medical Association is all about quality of medical care and physicians satisfaction in the nation.

Show more
410
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
Only 7% of Mothers in the region have ANC follow up with doctors but the regional health bureau become the pushing factors fo
+1
Only 7% of Mothers in the region have ANC follow up with doctors but the regional health bureau become the pushing factors for Gynecologists to leave the region. Look at early childhood deaths and the regional health bureau unable to employ pediatricians to the primary hospitals. What health indicator has been improved for the last 3-4 years? (EDHS 2021)

መረጃ፦ የAMA የፌስቡክ ገፅ በሶስት ሰዎች(አድሚኖች) ይተዳደር የነበር ሲሆን አሁን ላይ ግን ማንም አክሰስ ማድረግ ባለመቻሉ፤ አገልግሎት እየሰጠ አይደለም። ስለሆነም አማራጭ የፌስቡክ ገፅ መጠቀም አስፈላጊ ሆኖ አግኝተነዋል። Link: https://www.facebook.com/profile.php

It was 7 years ago that H.E Mr Gedu Andargachew put the Foundation stone of Debrebirhan Referral Hospital. Remembering that t
It was 7 years ago that H.E Mr Gedu Andargachew put the Foundation stone of Debrebirhan Referral Hospital. Remembering that time makes me cry. H.E Mr Gedu clearly stated that "our people deserve better medical care." Unfortunately, the Amhara regional health bureau didn't follow the where abouts of this hospital. ARHB failed to take the Dreams of Mr Gedu to the next steps.The regional health bureau is severely deteriorating down. What percent of the building achieved now? Why the ARHB kept silent about it? Why the regional health burea ignore it? The people in debrebirhan and  around are being treated with poor infrastructure. Let's ask one important question፡ which hospital started to serve the people in the last 2-3 years?

If you poorly understand the problem, all the efforts towards the solution will be catastrophic. የጤናው ሴክተር ዋነኛ ችግርም ይህ ይመስላል። 1) የጤና ባለሙያው ጤና ቢሮው/ጤና ሚኒስቴር ከሰራተኛው ጥቅም፣ ከሴክተሩ አላማ በተቃርኖ የቆመ ይመስለዋል። የተሳሳተ ድምዳሜ ይይዛል። የመንደርተኛ እና የሙሰኞች ስብስብ ሲል ይተቻል። 2) ጤና ሚኒስቴር/ጤና ቢሮ ደሞ የጤና ባለሙያው ለጤና ሴክተሩ ምንም አበርክቶ የሌለው፣ የጤና ፖሊሲውን ለመተግበር እንቅፋት እየሆነበት ያለው የጤና ባለሙያው እንደሆነ ያስባል። ስለሆነም ከጤና ባለሙያው የሚነሱ ጥያቄዎችን በሙሉ ማፈን ይጀምራል ወይም ፍረጃ ውስጥ ይገባል። //ከላይ ያሉ ሁለቱም ድንጋጌዎች ሥህተቶች ናቸው። የሁለቱ አካላት ማለትም የጤና ሴክተሩ(MOH & RHBs) እና የጤና ባለሙያው ተናበው አለመስራታቸው የሀገራችን ህክምና ኋላቀር ሆኖ የመሻሻል እድሉም ዝግ እንዲሆን አድርጎታል። //በመካከል ያለውን ተቃርኖ ሊያስታርቁ የሚችሉት የሙያ ማህበራት ነበሩ። ምክንያቱ ብዙ ነገር ግን ግልፅ ባልሆነ መንገድ የሙያ ማህበራትም የሚፈይዱ አልሆኑም። //መውጫ፦ አሁንም አንድ እድል ያለ ይመስላል። መወቃቀሱን ወደጎን በመተው የጤናው ሴክተር እንዲሻሻል በጋራ መስራት፣ አቅዶ በእቅድ መሠረት መንቀሳቀስ። ///ምክረ-ሐሳብ 1፦ የየክልል ጤና ቢሮዎች የጤናውን ሴክተር የሚረዱበት አረዳድ በጣም ስስ ነው (too superficial, no deep understanding). በዛ ላይ ክልል ላይ ያለው የጤና የአመራር ጥበብም የራሱ የሆነ ችግር አለው። ረጅም ልምድ ያካበተ አለመሆኑ፣ አዲስ መዋቅር መሆኑ ተጨምሮ ችግርም እድልም አለው። ስለዚህ የችግሮችን ጥልቀት ቀርቦ ማስረዳትና የጤና ባለሙያውንም ያለበትን ጫና በመረጃ ማስረዳት ተገቢ ነው። ለጤና ሴክተሩ የአመራር ዘርፍ ድጋፍ መስጠትም ተገቢ ይመስላል። //ምክረ-ሐሳብ 2፦ የጤና ባለሙያው በተለይም ሐኪሙ የጤና ሊደርሽፑን መቀላቀል ባለበት ልኬት እየተቀላቀለ አይደለም። የሆስፒታል ሐላፊ ሁን ሲባል አልፈልግም ያለ ስብስብ የሆስፒታል አመራርን የመተቸት ተጠዬቃዊ ሞራል የለውም። ጤና ጣቢያውን አንተ ምራውና መሻሻል ያለበትን እንዲሻሻል አድርግ ሲባል እምቢ ይልና በኋላ እንዴት በዚህ የአሰራር ስልት ስራ እባላለሁ ብሎ ያለቅሳል። የምትሰራበት ተቋም አሰራር የህክምና መርህና ህግጋት ከተቃረነብህ ማስተካከል የምትችለው ራስህ ነህ። ምራን ስትባል አልመራም አትበል። ብዙ ነገሮች "በሰው ላይ ያምር ሲይዙት ያደናግር" ነውና። //ምክረ-ሐሳብ 3፦ የጤና ሴክተሩን የሚመሩ አካላት በተለይ ደሞ የክልል የጤና ቢሮ አመራር አካላት በተዋረድ ሁሉም ከሙያ ማህበራት ጋር ለመስራት የሚያሳዩት ቸልተኝነትና ጥላቻ ወይንም ፍራቻ አሳሳቢ ነው። የተወሰኑ ክልሎች ቀና አረዳድ ቢኖራቸውም ብዙ የክልል ጤና ቢሮዎች ግን በተሳሳተ መንገድ ላይ ናቸው። ሥለዚህ የጤና ሴክተሮች አላማቸው የጤና ሴክተሩን ማዘመን ከሆነ ከጤና ማህበራት (ከህክምና ማህበራት፣ ከነርሶች ማህበር፣ የአንስቴቲስቶች ማህበር ወዘተ) ጋር በጋራ መስራት መቻል አለባቸው። ሌላው እና ትልቁ ችግራቸው የፖለቲካ ተወካይ/ተሿሚ እንደሆኑ ማሰባቸው ነው። የጤናው ሴክተር ሬሌቲቭሊ ከቀጥታ የፖለቲካ ተፅዕኖ ነፃ እንደሆነ ይገመታል። የጤና ቢሮዎች ከጤና ማህበራት ጋር ካልሰሩ ከማን ጋር ሆነው ህክምናውን ሊያዘምኑ እንደሆነ ተገማች አይደለም። //የመጨረሻው፦ የጤና ባለሙያው የሚያቀርባቸውን ትችቶች ከተራ አሉባልታ የተፋቱ በመረጃ የተደገፉ መሆን አለባቸው። ሁልጊዜ በተቃውሞ ሐሳብን መግለፅም ትክክል አይደለም። Health Leadership፡ ሊደርሽፕ ከህክምና በላይ የራሱ ውስብስብ ነገሮች ያሉት እና ትምህርት፣ልምድና ተሰጥዖን የሚጠይቅ ዘርፍ ነው። ስለሆነም ሁሉም ሐኪም በተለይ ደሞ ዘርፉን ለማሻሻል የምትሹ/የምትመኙ በሙሉ በየትኛው የጤና አመራር (Health leadership) ላይ ስትመደቡ በቅንነት አገልግሉ። June 22/2023

ክልሉ ላይ ያለው የተሽከርካሪ አደጋ ምን ያክል ነው? ምን መፍትሔዎችስ እየተወሰዱ ነው? .*.*.*. የአማራ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን በማህበራዊ ትስስር ገፁ ባሰፈረው መረጃ መሰረት በክልሉ 818 ሰዎች
ክልሉ ላይ ያለው የተሽከርካሪ አደጋ ምን ያክል ነው? ምን መፍትሔዎችስ እየተወሰዱ ነው? .*.*.*. የአማራ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን በማህበራዊ ትስስር ገፁ ባሰፈረው መረጃ መሰረት በክልሉ 818 ሰዎች በመኪና አደጋ ህይወታቸው አልፏል።ሠዓት ✔ሰኔ 8 ቀን 2015 ዓ.ም ከቀኑ 9:00 በሰ/ሸዋ ዞን በአንጎለለና ጠራ ወረዳ አሊላኒ ቀበሌ ልዩ ቦታው ገዘት ማርያም እየተባለ ከሚጠራው ስፍራ ከአሳግርት ወረዳ ወደ ጫጫ ሲጓዝ የነበረ አነስተኛ የህዝብ ማመላለሻ መኪና በመገልበጡ በአደጋው አንድ ሠው የሞተ ሲሆን 18 የሚሆኑት ከባድና ቀላል ጉዳት መድረሱን ሰምተናል። ✔በተመሳሳይ ሰኔ ቀን10 / 2015 ዓ /ም በደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር አብማ ክፍለ ከተማ ቀበሌ 20 ከቀኑ 5 ሰዓት ከረቡዕ ገበያ ወደ ደብረ ማርቆስ በመጓዝ ላይ የነበረ የህዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪ ህዝብ ጭኖ ቁልቁለት በመውረድ ላይ እንዳለ በአጋጠመው አደጋ መንገድ ስቶ በመውጣቱ እና የፊት ጎማው በሮ በመሄዱ በደረሰው አደጋ ሹፌሩን ጨምሮ የ7 ሰው ህይወት ሲያልፍ 22 የሚሆኑት ከባድና ቀላል አደጋ ደርሶባቸዋል። 👉በአጠቃላይ በክልሉ በበጀት ዓመቱ አስራ አንድ ወራት ብቻ በደረሱ 1765 የትራፊክ አደጋዎች 818 ሰዎች የሞቱ ሲሆን 1474 ደግሞ ከባድና ቀላል ጉዳት ደርሶባቸዋል።ፖሊስ እንዳለው መጭው ክረምት በመሆኑ አሽከርካሪዎች ጥንቃቄ በማድረግ ሊያሽከረክሩ ይገባል ብሏል። @ዋሱ @Wassu

👍ቀን 10/10/15 ዓ.ም ✍ይድረስ ለአማራ ሐኪሞች ቦርድ አመራሮች               ✅ ጉዳዩ :ዝምታን መስበርን ይመለከታል                🙊🙊🙊    ከላይ በርዕሱ ለመግለፅ እንደተሞከረው የአማራ ሀኪሞች ማህበር አመታዊ ጉባኤውን ካካሄደ ድፍን አንድ አመት ሞላው፡፡ነገር ግን በዚህ አንድ አመት ውስጥ ማህበሩ ይሄን ግባ  የሚባል  ስራ ሲያከናውን እየታዬ አይደለም፡፡ሌላው ቢቀር የአማራ ክልል ጤና ቢሮ በሙስና ተዘፍቆ ከብዙ ወንድሞቻችንና እህቶቻችንን በሺዎች የሚቆጠሩ ገንዘብ በሙስና እየተቀበለ ጤና ባለሙያዎችን  እያሳደደ መሆኑ እየታወቀ ማህበሩ በዝምታ ማለፉ ለምን ይሆን???ዝውውርንና ምደባን በገንዘብና በእውቂያ ሲያደርገው የክልሉን ጤና ቢሮ መጀመሪያ መታገል ያለበት የአማራ ሀኪሞች ማህበር አልነበረምን???ባለኝ መረጃ መሰረት ጤና ቢሮው ገንዘብ አሰባሳቢ ኤጄንት አለው፡፡ይህም ኤጀንት በገንዘብ  ሰዎችን ወደተለያዩ ቦታዎች የማዘዋወር ስራ ይሰራል፡፡የምንኮራባቸው ባለሙያዎች ሳይቀሩ ዋነኛ ተባባሪ ሆነው ሲገኙ እጅጉን ያሳዝናል፡፡ይህ ሲሆን የአማራ ሀኪሞች ማህበር ለምን ዝም አለ???አሁንም ዝምታውና ሸረኝነቱ ተሰብሮ ስራ መሰራት አለበት፡፡ምናልባት ማህበሩ ቋሚ የኢኮኖሚ ምንጭ ስሌለለው  የገንዘብ ችግር ገጥሟቹህ ይሆናል፡፡ግን ገንዘብ ለማሰባሰብስ መቼ መድረክ ፈጠራቹህልን???አሁንስ የማህበሩ እጣ ፈንታ ምንድን ነው???ዝምታውስ እስከ መቼ ነው???ሁልጊዜ በስሜት የምንጓዘው ለምንድን ነው??? በአስቸኳይ መወሰድ ያለባቸው መፍትሔዎች 1.ማህበሩ አመታዊ ጉባኤ በቅርቡ ማካሄድና ስራ አላሰራ ያሉ ችግሮችን ነቅሎ መጣል አለበት:: 2.ከተለያዩ ማህበራት ጋር በጋራ መስራት አለበት፡፡ 3.ማህበሩ ቋሚ የሆነ ገንዘብ እንዲኖረው መደረግ አለበት፡፡ለዚህም የራሱ የሆነ ሜዲያ you tubeን ጨምሮ መክፈት አለበት፡፡ 4.አባላትን ማጠናከርና ገንዘብ እንዲከፍሉ ማድረግ አለበት፡፡ 5.የማህበሩ የfb ገጽ admin የሆነው ሰው ከቦርድ አባላት ውጭ መሆኑን አውቃለሁ፡፡ስለዚህ  በፍጥነት ለቦርድ አባላቱ እንዲሰጥና ጥብቅ ቁጥጥር እንዲኖረው፡፡ 6,CPD እየተባለ ከድሃ ጤና ባለሙያ የሚደረገውን የገንዘብ ጋፈፋ ስርአት በአስቸኳይ እንዲቆም በጋራ መታገል አለብን፡፡ 7,በሙስና የተዘፈቁ የጤና ቢሮ ሰራተኞችን አደብ እንዲገዙ መታገል አለብን፡፡ 8,የአማራ ሀኪሞች ማህበር ሎጎ ግልፅ ሆኖ መታወቅ አለበት፡፡ በዚህም መሰረት ማህበሩ በፍጥነት ወደስራ እንደሚገባ ባለሙሉ ተስፋ ነኝ፡፡                                                                                      ለጤናችን በጋራ እንስራ                  ✍✍✍✍✍✍                                                                                       ዶ/ር ታደሰ ፈንታ/የቀዶ ጥገና ስፔሻሊስት/

ልጅዎ ብትሆን ምን ያደረጉ ነበር ? አብዛኛዎቻችን ባህላዊ የአጥንት ጠጋኝ/ወጌሻ ቁስል የሌላቸው/የተዘጉ ስብራቶችን ብቻ ያክማል ብለን እናስባለን። አሁን አሁን ክፍት/ቁስል ያላቸውን ሰብራቶች ሁሉ ንፁህ ባልሆነ ጨርቅ ጠቅልለው : ጥብቅ ባለ ቀርከሃ አስረው በኢንፌክሽን ከተያዙ በኋላ ወደ ሆስፒታል እየላኩ ነው። ሌላው ትኩረት ፈላጊ ጉዳይ ደግሞ ወጌሾች ዝንፍ/ጠመም ያለ የአካል ክፍል ሁሉ ለማስተካከል እየሞከሩ ነው😲😳። ባጭሩ እንዲህ ሆነ፡- ገና የ2 አመት ልጅ ናት። ቤተሰቧ እግሮቿ ቀጥ ያሉ እንዳልሆኑ እና ጠማማ እንደሆኑ አስተዋሉ። ስጋታቸውንም ለአካባቢው ባህላዊ አጥንት ጠጋኝ/ወጌሻ ነገሩት። ወጌሻም የህፃኗ አጥንት ትክክለኛ ቦታው ላይ እንዳልሆነና መስተካከል እንዳለበት ይነግራቸዋል። ከዚያም ደህና የነበረውን የ2 አመት ልጅ እግር ቀጥቅጦ በቀርከሃ ቀጥ አድርጎ በጥብቅ አሰረው። ያለምንም ማደንዘዣ አስቡት 😭! ቤተሰቧችንም ምንም ይሁን ምን እንዳይፊታ ነገራቸውና ወደ ቤት ላካቸው። ልጂቷ ከዚያ በኋላ እያለከሰች ነበር ግን ቤተሰቦቿ ችላ አሏት! ከጥቂት ቀናት በኋላ እግሯ ከእግር ጣት ጀምሮ መጥቆር ጀመረ እና በ3ኛው ቀን ሆስፒታል ስትደርስ እግሯ ጋንግሪን ሁኖ በስብሶ ነበር 😥. ህፃኗ ላይ የነበረው ወላጆችን ያሳሰበው የአጥንት ጉዳይ ሊሆን ሚችለው እሰከ 2 አመት ሊከሰት የሚችልና ከዚያ በኋላ በራሱ ጊዜ የሚስተካከል የአጥንት እድገት ሂደት ነበረ ! በተፈጠረው ክስተት በጣም አዘንን😥 በጠዋቱ ክፍለ ጊዜ ምን ማድረግ እንዳለብን ተወያይን:: ከዚያም ህፃኗን ለማየትና ቤተሰቧን ለመምከር አራት ስፔሻሊስት ሐኪሞች ጋር ሁነን ወደ ተኛችበት ክፍል አመራን። ግን እዚያ አልነበሩም (ጠፍተዋል)። በጠዋት ከሆስፒታሉ ወጥተው ወደ ቤተ ክርስቲያን ሊወስዷት እንደሄዱ በአቅራቢያው ያለ አንድ ታካሚ ነገረን።  'እግዚአብሔር ይርዳት እና ድና በሁለት እግሮቿ ስትራመድ ማየት በጣም ያስደስተናል' ይህን ብቻ ነበር በጊዜው ያልነው ። ከአንድ ሳምንት በኋላ ሴት አያቷ ህፃኗን ይዘው ወደ ግል ክሊኒክ መጡ። ችግሯ ከጉልበቷ በላይ እየገፋ ከጉልበቷ እና ከጭኗ በሚወጣ ኢንፌክሽን ባለው ፈሳሽ ተበክላለች። የልጅቷን የአጎት ልጅ ጨምሬ ስለጉዳዩ ከ አንድ ሰዓት ያላነሰ ቁጭ ብለን ተወያየን። ሕፃኗን ለቀዶ ጥገና ሕክምና ወደ ሆስፒታል እንዲመልሷት አጥብቄ ነገርኳቸው። አያቷ ተስማምተው ከክሊኒኩ ወጡ። ነገር ግን ልጅቷን ቀኑን ሙሉ ወደ ሆስፒታል አላመጡም። ሰለቀሩብኝ ለመጠየቅ ስልክ ቁጥሩን ከካርድ ፈልጌ ደወልኩ እና የልጅቷ አክስት ስልክ ቁጥር ነው። ወደ ሆስፒታል አልመጡም ምን ሁነው ይሆን ስላት 'ለመወሰን ወላጆቿ ስላልነበሩ ወደ ቤት እንደመለሷት' ነገረችኝ።  እሺ እባካችሁ ተጨማሪ ስሕተቶችን አትሥሩ፣ ሂዱና ለወላጆች ንገሯቸው እና ሕፃኗን ጠዋት ወደ ሆስፒታል አምጧት አልኩ። አሁን ከተነጋገርን 72 ሰዓታት አልፈዋል። ስልካቸው አይሰራም። ምናልባት ያቺ ህፃን እስካሁን ምንም አይነት ህክምና አላገኘችም😥😥. ልጅዎ ብትሆን ምን ያደርጋሉ ?  ይህንን አሰራር ለመግታት ሥርዓት መኖር አለበት። ሁሉም የሚመለከተው ማህበረሰብ ሊሰራበት ይገባል። በዚህ ጉዳይ ላይ መንግስት ፖሊሲ ሊኖረው ይገባል:: በልጆች መብት ላይ የሚሰሩ ድርጅቶች በዚህ ላይ መስራት አለባቸው። በሆስፒታል ውስጥ ሊታከም ለሚችል ቀላል ችግር እንደዚህ አይነት ከባድና ውስብስብ ችግር እንዳይፈጠር እንረባረብ! #ሚዳከኝ #የምእራብሸዋዞንጤናቢሮ #ኦሮሚያጤናቢሮ #ጤናሚኒስትር #የሴቶችእናየህፃናትማህበራዊጉዳይሚኒስቴር #የኦሮሚያሀኪሞችማህበር #የኢትዮጵያህክምናማህበር #የኢትዮጵያአጥንትቀዶጥገናማህበር #ESOT ከዶ/ር ሚልኬሳ ሁንዴ (የአጥንት ቀዶ ጥገና ሐኪም) በዶ/ር ኤፍሬም በቀለ (የአጥንት ቀዶ ጥገና ሐኪም) Telegram: t.me/HakimEthio

EM treatment protocol new 2015.pdf5.07 MB

Check out this job at CURE International: https://www.linkedin.com/jobs/view/3322990153