Bahir Dar Academy Middle School Channel
Open in Telegram
2 524
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
የተከበራችሁ የተማሪዎቻችን ወላጆች እንደምን አላችሁ፡፡ የ2015 ዓ.ም የነባር እና አዲስ ተማሪዎች ምዝገባ ከሐምሌ 15 ቀን 2014 ዓ.ም ጀምሮ በስራ ስዓት ከጥዋቱ 2፡00 - 8፡00 ስዓት ይከናወናል፡፡ የምዝገባ ወቅት ክፍያዎች ሙሉ በሙሉ ካልተከፈሉ (የተቆራረጠ ሂሳብ ካለ) ተማሪዎችን መዝግቦ ክፍል ለመደልደል ስለሚያስቸግር፣ ደንበኞቻችን ቀሪ ሂሳብ አስተካክለው ምዝገባ ለማከናወን መጉላላት እንዳይደርስባቸውና የተማሪዎች ምዝገባም በአመት አንድ ጊዜ ብቻ የሚከናወን በመሆኑ ከዚህ በታች ባለው ቅደም ተከተል መሰረት ምዝገባ የሚከናወን ይሆናል፡፡
1. በመጀመሪያ ከት/ቤቱ ሂሳብ ክፍል በአካል በመሄድ ለክፍል ደረጃው ለምዝገባ የሚስፈልገውን የገንዘብ መጠን እና የአከፋፈል ስዓት የሚገልፅ ቅፅ መቀበል፣
2. ወዲያውኑ ወደ ባንክ በመሄድ የተጠየቀውን ገንዘብ በመክፈል ከከፈሉበት ባንክ ኦሪጅናልና ኮፒ ደረሰኝ መቀበል፣
3. በዕለቱ የከፈሉበትን የባንክ ደረሰኝ ኮፒውን እንዲሁም ከት/ቤቱ የተሰጠዎትን የክፍያ መረጃ ቅፅ ለት/ቤቱ ሂሳብ ክፍል በአካል መጥቶ መስጠትና ወዲያውኑ የክፍል ደረጃውን ዋና ዋና መረጃ የያዘ 2 ገፅ ወረቀት መቀበል ያስፈልጋል፡፡
የት/ቤቱን ባስ የምትጠቀሙ ደንበኞች የትራንስፖርት ክፍያ የሚከፈለው ለብቻ ሲሆን (ከሌሎች ክፍያዎች ጋር ሳይጨመር) የትራንስፖርት ክፍያ የባንክ ደረኝ ኮፒ ለትራንስፖርት ክፍል መስጠት ያስፈልጋል፡፡
ማሳሰቢያ፡- አዲስ የኬጂ 1 ልጅ (ህፃን) ለማስመዝገብ ያሰባችሁ፤ ነባር ደንበኞቻችን ከእህት/ ወንድማቸው ጋር አብረው እንዲማሩ በምዝገባ መጀመሪያ ቀን አምጥታችሁ እንድታስመዘግቡ እናሳስባለን፡፡ የኬጅ 1 ተማሪዎች ምዝገባ በተጀመረ በጥቂት ቀናት ውስጥ ስለሚሞላና የሚፈለገው ቁጥር ከተመዘገበ በኋላ እህት/ወንድም አላት/አለው የሚሉ አስተያየቶችን ለመቀበል የምንቸገር መሆኑን እናሳውቃለን፡፡
ጉዳዩ፡- የ2015 ዓ.ም የነባር እና አዲስ ተማሪዎች ምዝገባ ሐምሌ 15 ቀን 2014 ዓ.ም (አርብ) ከጥዋቱ 2፡00 ላይ ይጀምራል፡፡
የተከበራችሁ ወላጆች እንዲሁም የተወደዳችሁ ተማሪዎቻችን እንደምን አላችሁ፡፡ የ2014 ዓ.ም የአመቱ ትምህርት ማጠቃለያ የውጤት ካርድ ለተማሪዎች የሚሰጠው እና የወላጆች በዓል የሚከበረው ሐምሌ 03 ቀን 2014 ዓ.ም (እሁድ) ከጥዋቱ 2፡00 ሰዓት ጀምሮ ስለሆነ የት/ቤቱ ተማሪዎችና ወላጆች በሰዓቱ እንድትገኙልን በአክብሮት እናሳውቃለን፡፡ እናመሰግናለን፡፡
ለ2014 ዓ.ም 8ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና ተፈታኝ ተማሪዎች ብቻ
የተወደዳችሁ ተማሪዎቻችን እንደምን አላችሁ፡፡ የ2014 ዓ.ም የ8ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና ሰኔ 28 እና 29 ይሰጣል፡፡ እንዲሁም ሰኔ 27 ቀን 2014 ዓ.ም የፈተና ኦሬንቴሽን ስለሚሰጥ ከጥዋቱ 3፡00 ሰዓት ላይ ት/ቤት ግቢ እንድትገኙ እናሳውቃለን፡፡
የክፍያ መልዕክት ለወላጆች
የተከበራችሁ የተማሪዎቻችን ወላጆች እንደምን አላችሁ፡፡ አብዛኞቹ ወላጆች የተማሪዎችን (የልጆቻቸውን) ወርሃዊ ክፍያ በወቅቱ በመክፈል የአመቱን የ10 ወር ክፍያ ስላጠናቀቃችሁ ከልብ እናመሰግናለን፡፡ ነገር ግን የተወሰኑ ወላጆች ክፍያውን ከፍለው ባለማጠናቀቃቸው ት/ቤቱ በተደጋጋሚ ለወላጅ ስልክ በመደወል እንዲሁም የክፍያ ይፈፀም ደብዳቤ በመላክ ለማሳሰብ ሞክሯል፡፡ የውጤት ካርድ ለተማሪዎች በሚሰጥበት ጊዜ የአመቱን ክፍያ ያላጠናቀቁ ተማሪዎች ላይ መጉላላትን እንዲሁም በሂሳብ ክፍል ሠራተኞች ላይ ከፍተኛ የስራ ጫናን ይፈጥራል፡፡ ስለዚህ የአመቱን የተማሪ ክፍያ ያላጠናቀቃችሁ ወላጆች እስከ ሰኔ 23 ቀን 2014 ዓ.ም ክፍያውን ፈፅማችሁ ደረሰኙን ይዛችሁ በአካል ባህርዳር አካዳሚ ሂሳብ ክፍል በመምጣት እንድታሳዩ እናሳስባለን፡፡ እናመሰግናለን፡፡
የተከበራችሁ ወላጆች እንደምን አላችሁ፡፡ ከ5 - 7ኛ የ2ኛው ወሰነ ትምህርት የማጠቃለያ ፈተና ከሰኔ 17 - 24/2014 ዓ.ም ይሰጣል፡፡ ተማሪዎችም ት/ቤት የሚቆዩት እስከ ቀኑ 6፡00 ስዓት ድረስ ብቻ መሆኑን እንገልፃለን፡፡ ስለሆነም ተማሪዎቻችን (ልጆቻችሁን) በስዓቱ እንድትረከቡልን እንዲሁም ከስዓት በኋላ ያለውን ጊዜያቸውን በጥናት እንዲያሳልፉ እንድታበረታቱልን ከአደራ ጋር እናሳውቃለን፡፡ እናመሰግናለን፡፡
ለ8ኛ ክፍል ተማሪ ወላጆች ብቻ
ጉዳዩ፡- ሞዴል ፈተናን ይመለከታል፡፡
በባህርዳር ከተማ አስተዳደር ደረጃ የ8ኛ ክፍል ሞዴል ፈተና ሰኔ 13 እና 14/2014 ዓ.ም ይሰጣል፡፡ ፈተናውም ከጥዋት ከ3፡00 - 5፡00 ሰዓት እንዲሁም ከሰዓት ከ8፡00 - 10፡00 ሰዓት ይሰጣል፡፡ ስለዚህ ተማሪዎች ት/ቤት ግቢ ከገቡ በኋላ ወደ ውጭ መውጣት ስለማይፈቀድላቸው ምሳ ይዘው እንዲመጡ እንዲሁም ምናልባት ተማሪዎች የት/ቤቱን ትራንስፖርት የሚጠቀሙ ከሆነ እና ፈተና ከመጨረሳቸው በፊት ባሱ ቀድሞ ከወጣ 10፡00 ሰዓት ላይ ወላጆች መጥታችሁ ልጆችን እንድትረከቡን እናሳስባለን፡፡ የፈተና ፕሮግራሙን ከዚህ በታች አያይዘናል (attach አድርገናል)፡፡
ባህርዳር አካዳሚ አባይ ካምፓስን ብቻ ይመለከታል
ጉዳዩ፡- ባህርዳር አካዳሚ አባይ ካምፓስ በ2015 ዓ.ም ከኬጂ እስከ 6ኛ ክፍል ያሉ ተማሪዎችን ብቻ እንደሚያስተምር (እንደሚያስተናግድ) ስለማሳወቅ፡፡
ለተከበራችሁ ወላጆች እንደምን አላችሁ፡፡ ባህርዳር አካዳሚ አባይ ካምፓስ በ2010 ዓ.ም ከኬጂ እስከ 6ኛ ክፍል ባሉ ተማሪዎች ትምህርት የጀመረ ሲሆን በ2011 ዓ.ም እስከ 7ኛ ክፍል እንዲሁም ከ2012 ዓ.ም ጀምሮ እስከ 8ኛ ክፍል ተማሪዎችን ተቀብሎ ባሉት የመማሪያ ክፍልና ውስን ድጋፍ ሰጭ ክፍሎች የትምህርት አገልግሎት በመስጠት የአካባቢውን ማህበረሰብ በማገልገል ላይ ይገኛል፡፡ ይሁን እንጂ ባለፉት 5 አመታት ውስጥ የስመ ንብረት ዝውውር ሊፈፀም ባለመቻሉ ተጨማሪ የመማሪያና አገልግሎት ሰጭ ክፍሎችን ለምሳሌ ሳይንስ ላቦራቶሪ በመገንባት መማር ማስተማሩን በታሰበው መልክ ማስኬድ አልተቻለም፡፡ ይህ የስመ ንብረት ዝውውርም መቸ ሊጠናቀቅ እንደሚችል መገመት አልቻልንም፡፡ ስለሆነም፡-
1. የኬጂ ተማሪዎች ቁጥር ብዙ ስለነበረ ከኬጂ 3 ወደ 1ኛ ክፍል የሚሄዱት ተማሪዎች 3 ክፍል ሲሆኑ ከ8ኛ ወደ 9ና ክፍል በመዛወር ግቢውን የሚለቁት ተማሪዎች 1 ክፍል ብቻ ናቸው፡፡ ከዚህም የተነሳ የ1ኛ ደረጃ ተማሪዎቸ የኬጂ ግቢን መማሪያ ክፍል ስለሚጠቀሙ እና በኬጂ ተማሪዎች የምኝታ ስዓት የ1ኛ ደረጃ ተማሪዎች የምሳ ስዓት የጨዋታ ጊዜ ስለሚሆን የመዋዕለ ህፃናት ተማሪዎች በእጅጉ እየተረበሹ ስለሆነ የ1ኛ ደረጃ ተማሪዎች በራሳቸው ግቢ ብቻ እንዲማሩ ስለተፈለገ እንዲሁም፣
2. በት/ቤቱ ግቢ ውስጥ ለሳይንስ ላቦራቶሪ የሚሆን በስታንዳርዱ መሰረት የተገነባ ክፍል ስለሌለ ሳይንስ ላቦራቶሪ ክፍልን በአግባቡ አደራጅቶ 7ኛ እና 8ኛ ክፍል ተማሪዎችን ማስተማር ተቸግረናል፡፡
ስለዚህ ለ2015 ዓ.ም ባህርዳር አካዳሚ አባይ ካምፓስ ከኬጂ እስከ 6ኛ ክፍል ያሉ ተማሪዎችን ብቻ ስለሚያስተምር (ስለሚያስተናግድ) የባህርዳር አካዳሚ አባይ ካምፓስ 7ኛ እና 8ኛ ክፍል ተማሪዎችን በእናንተ ወላጆች ምርጫ ወደ ባህርዳር አካዳሚ ዋናው ግቢ መጥተው እንዲማሩ ወይም በሚመቻቸው ሌላ ት/ቤት እንዲማሩ ከአሁኑ ቅድመ ዝግጅት እንድታደርጉ በአክብሮት እናሳውቃለን፡፡
የክፍያ መልዕክት ለወላጆች
የተከበራችሁ የተማሪዎቻችን ወላጆች እንደምን አላችሁ፡፡ የተማሪዎች ወርሃዊ ክፍያ ወሩ በገባ በ10 ቀናት ውስጥ መከፈል እንዳለበት ይታወቃል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ሰኔ የበጀት መዝጊያ ስለሆነ ለአሠራር ያመች ዘንድ የሰኔ ወር ክፍያ እስከ 10/10/2014 ዓ.ም ባለው ጊዜ ውስጥ ተከፍሎ እንዲጠናቀቅ እናሳውቃለን፡፡
ምናልባት ከሰኔ ወር በተጨማሪ የሌሎች ወራት ያልተከፈለ ውዝፍ ክፍያ ካለ በአመት ውስጥ የ10 ወራት ክፍያ መከፈል ስላለበት ከሰኔ ወር ክፍያ ጋር ውዝፍ የተማሪዎችን ወርሃዊ ክፍያ እስከ ሰኔ 10 ቀን 2014 ዓ.ም ድረስ እንድትከፍሉ እናሳስባለን፡፡
ለባህርዳር አካዳሚ አባይ ካምፓስ ወላጆች ብቻ
በድጋሜ የተላከ የስብሰባ ማስታወቂያ
የተከበራችሁ ወላጆች እንደምን አላችሁ፡፡ ባህርዳር አካዳሚ አባይ ካምፓስ ለ2015 ዓ.ም የተማሪ ወርሃዊ ክፍያ ጭማሪ ላይ ከወላጆች ጋር ውይይት ግንቦት 28 ቀን 2014 ዓ.ም (እሁድ) ጥዋት 3፡00 ሰዓት ላይ በባህርዳር አካዳሚ አባይ ካምፓስ ግቢ ውስጥ ያካሂዳል፡፡ ስብሰባው ለሌላ ጊዜ ስለማይራዘም እና የወርሃዊ ክፍያ ጭማሪው በተገኙት ወላጆች ስለሚወሰን ሁላችሁም ወላጆች ሰዓቱን አክብራችሁ እንድትገኙልን በአክብሮት እናሳውቃለን፡፡
