en
Feedback
Bahir Dar Academy Middle School Channel

Bahir Dar Academy Middle School Channel

Open in Telegram

educational

Show more
Ethiopia8 692The category is not specified
2 524
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
መስከረም 18 ቀን 2015 ዓ.ም የተላከ

የባህርዳር አካዳሚ አባይ ካምፓስ ተማሪዎችን ብቻ ይመለከታል፡፡ ጉዳዩ፡- የልጆቻችሁን የትምህርት ቤት ክፍያ በዳሽን ባንክ እንድትከፍሉ ስለማስታወቅ፡፡ የተከበራችሁ የተማሪዎቻችን ወላጆች እንደምን አላችሁ፡፡ የባህርዳር አካዳሚ አባይ ካምፓስ የተማሪ የት/ቤት ክፍያ በብርሃን ባንክ በኩል ሲከፈል እንደነበረ ይታወቃል፡፡ ይሁን እንጂ ከዚህ ወር ጀምሮ የአባይ ካምፓስ ተማሪዎች የት/ቤት ክፍያ በዳሽን ባንክ በኩል እንዲፈፀም ስምምነት ላይ ስለተደረሰ ከዚህ በቻች በተቀመጠው መረጃ መሠረት ክፍያ እንዲፈፀም እናሳውቃለን፡፡ 1. የባንክ ስም፡- ዳሽን ባንክ 2. የሒሳቡ ባለቤት፡- ባህርዳር አካዳሚ አባይ ማዶ ካምፓስ 3. የሒሳብ ቁጥር፡- 0237973381021 ማሳሰቢያ፡- የባንክ ቅያሬ ስለተደረገና የተማሪዎች የክፍያ መለያ ቁጥር (Payment ID) በአዲስ ስለሚሰራ በቅርቡ የምናሳውቃችሁ ሲሆን እስከዚያው ግን ከላይ የተቀመጠውን የዳሽን ባንክ ሒሳብ ቁጥር ብቻ በመጠቀም ክፍያ እንድትፈፅሙ በድጋሜ እናሳውቃለን፡፡ እናመሰግናለን፡፡

የባህርዳር አካዳሚ አባይ ካምፓስ ተማሪዎችን ብቻ ይመለከታል፡፡ ጉዳዩ፡- የልጆቻችሁን የትምህርት ቤት ክፍያ በዳሽን ባንክ እንድትከፍሉ ስለማስታወቅ፡፡ የተከበራችሁ የተማሪዎቻችን ወላጆች እንደምን አላችሁ፡፡ የባህርዳር አካዳሚ አባይ ካምፓስ የተማሪ የት/ቤት ክፍያ በብርሃን ባንክ በኩል ሲከፈል እንደነበረ ይታወቃል፡፡ ይሁን እንጂ ከዚህ ወር ጀምሮ የአባይ ካምፓስ ተማሪዎች የት/ቤት ክፍያ በዳሽን ባንክ በኩል እንዲፈፀም ስምምነት ላይ ስለተደረሰ ከዚህ በቻች በተቀመጠው መረጃ መሠረት ክፍያ እንዲፈፀም እናሳውቃለን፡፡ 1. የባንክ ስም፡- ዳሽን ባንክ 2. የሒሳቡ ባለቤት፡- ባህርዳር አካዳሚ አባይ ማዶ ካምፓስ 3. የሒሳብ ቁጥር፡- 0237973381021 ማሳሰቢያ፡- የባንክ ቅያሬ ስለተደረገና የተማሪዎች የክፍያ መለያ ቁጥር (Payment ID) በአዲስ ስለሚሰራ በቅርቡ የምናሳውቃችሁ ሲሆን እስከዚያው ግን ከላይ የተቀመጠውን የዳሽን ባንክ ሒሳብ ብቻ በመጠቀም ክፍያ እንድትፈፅሙ በድጋሜ እናሳውቃለን፡፡ እናመሰግናለን፡፡

መስከረም 16 ቀን 2015 ዓ.ም የተላከ

ጉዳዩ፡- የ2015 ዓ.ም የትምህርት መከፈትን ይመለከታል፡፡ ውድ የባህርዳር አካዳሚ ተማሪዎች እንዲሁም የተከበራችሁ የተማሪዎቻችን ወላጆች እንደምን አላችሁ፤ እንኳን ለ2015 ዓ.ም የትምህርት ዘመን በሰላም አደረሳችሁ፡፡ ትምህርት መስከረም 09 ቀን 2015 ዓ.ም (ሰኞ) ይከፈታል ፤ ሰኞ እና ማክሰኞ ተማሪዎች ት/ቤት የሚቆዩት ግማሽ ቀን (እስከ 6፡00 ስዓት) ነው፡፡ ከመስከረም 11 ቀን 2015 ዓ.ም (ረቡዕ) ጀምሮ ሙሉ ቀን (እስከ 9፡00 ስዓት) ስለሚቆዩና በመደበኛ ፕሮግራሙ መሠረት ትምህርት ስለሚሰጥ ምሳ ይዘው እንዲመጡ ከአደራ ጋር እናሳውቃለን፡፡ የኬጂ (KG) ተማሪዎች መስከረም 9 እና 10 (ሰኞ እና ማክሰኞ) ወላጆች ልጆቻችሁን ከዚህ በታች በተቀመጠው ፕሮግራም መሠረት ት/ቤት ይዛችሁ መጥታችሁ የመማሪያ ክፍሉን አይታችሁ፣ ከልጃችሁ መምህራን ጋር ተዋውቃችሁ እንዲሁም በምዝገባ ጊዜ ከወረቀት ላይ ተፅፈው እንዲገዙ የተሰጧችሁን ማቴሪያሎች እና የመማሪያ መጽሐፍት ክፍያ የባንክ ደረሰኝ አስረክባችሁ ከልጆቻችሁ ጋር ወደ ቤት ትመለሳላችሁ፡፡ ማሳሰቢያ፡- ከኬጂ 1 - ኬጂ 3 ያሉ ተማሪዎች ከወላጆቻቸው ጋር ት/ቤት መጥተው መምህራኖቻቸውን የሚተዋወቁበት፣ ማቴሪያል የሚያስረክቡበት እና ትምህርት የሚጀምሩበት ፕሮግራም፡- 1. ስማቸው ከA – L ባሉት የእንግሊዝኛ ፊደላት የሚጀምሩ ተማሪዎች መስከረም 09 ቀን 2015 ዓ.ም (ሰኞ) ይሆናል፡፡ 2. ስማቸው ከM – Z ባሉት የእንግሊዝኛ ፊደላት የሚጀምሩ ተማሪዎች መስከረም 10 ቀን 2015 ዓ.ም (ማክሰኞ) ይሆናል፡፡ 3. ከመስከረም 11 ቀን 2015 ዓ.ም (ረቡዕ) ጀምሮ ሙሉ ቀን (እስከ 9፡00 ስዓት) ስለሚቆዩ ምሳ ይዘው ይመጣሉ፡፡ እናመሰግናለን፡፡

ጉዳዩ፡- የ2015 ዓ.ም የትምህርት መከፈትን ይመለከታል፡፡ ውድ የባህርዳር አካዳሚ ተማሪዎች እንዲሁም የተከበራችሁ የተማሪዎቻችን ወላጆች እንደምን አላችሁ፤ እንኳን ለ2015 ዓ.ም የትምህርት ዘመን በሰላም አደረሳችሁ፡፡ ትምህርት መስከረም 09 ቀን 2015 ዓ.ም (ሰኞ) ይከፈታል ፤ በዚሁ ዕለት ተማሪዎች ት/ቤት የሚቆዩት ግማሽ ቀን (እስከ 6፡00 ስዓት) ነው፡፡ ከመስከረም 10 ቀን 2015 ዓ.ም (ማክሰኞ) ጀምሮ ሙሉ ቀን (እስከ 9፡00 ስዓት) ስለሚቆዩና በመደበኛ ፕሮግራሙ መሠረት ትምህርት ስለሚሰጥ ምሳ ይዘው እንዲመጡ ከአደራ ጋር እናሳውቃለን፡፡ የኬጂ (KG) ተማሪዎች መስከረም 9 እና 10 (ሰኞ እና ማክሰኞ) ወላጆች ልጆቻችሁን ከዚህ በታች በተቀመጠው ፕሮግራም መሠረት ት/ቤት ይዛችሁ መጥታችሁ የመማሪያ ክፍሉን አይታችሁ፣ ከልጃችሁ መምህራን ጋር ተዋውቃችሁ እንዲሁም በምዝገባ ጊዜ ከወረቀት ላይ ተፅፈው እንዲገዙ የተሰጧችሁን ማቴሪያሎች እና የመማሪያ መጽሐፍት ክፍያ የባንክ ደረሰኝ አስረክባችሁ ከልጆቻችሁ ጋር ወደ ቤት ትመለሳላችሁ፡፡ ማሳሰቢያ፡- ከኬጂ 1 - ኬጂ 3 ያሉ ተማሪዎች ከወላጆቻቸው ጋር ት/ቤት መጥተው መምህራኖቻቸውን የሚተዋወቁበት፣ ማቴሪያል የሚያስረክቡበት እና ትምህርት የሚጀምሩበት ፕሮግራም፡- 1. ስማቸው ከA – L ባሉት የእንግሊዝኛ ፊደላት የሚጀምሩ ተማሪዎች መስከረም 09 ቀን 2015 ዓ.ም (ሰኞ) ይሆናል፡፡ 2. ስማቸው ከM – Z ባሉት የእንግሊዝኛ ፊደላት የሚጀምሩ ተማሪዎች መስከረም 10 ቀን 2015 ዓ.ም (ማክሰኞ) ይሆናል፡፡ 3. ከመስከረም 11 ቀን 2015 ዓ.ም (ረቡዕ) ጀምሮ ሙሉ ቀን (እስከ 9፡00 ስዓት) ስለሚቆዩ ምሳ ይዘው ይመጣሉ፡፡ እናመሰግናለን፡፡

መስከረም 06 ቀን 2015 ዓ.ም የተላከ

ጉዳዩ፡- የመዋዕለ ህፃናት (KG) ተማሪዎች የመማሪያ መጽሐፍት (Workbook) ኮፒ ዋጋን ይመለከታል፡፡ የተከበራችሁ የተማሪዎቻችን ወላጆች እንደምን አላችሁ፡፡ የመዋዕለ ህፃናት (KG) ተማሪዎች የሁሉም ዓይነት መማሪያ መጽሐፍት (Workbook) የኮፒ ዋጋ፡- 1ኛ. ለኬጂ 1 ተማሪዎች 920.00 ብር፣ 2ኛ. ለኬጂ 2 ተማሪዎች 1525.00 ብር፣ 3ኛ. ለኬጂ 3 ተማሪዎች 1285.00 ብር ስለሆነ ከጳጉሜ 02/2014 ዓ.ም እስከ መስከረም 03/2015 ዓ.ም ባሉት 7 ቀናት ውስጥ ክፍያውን በባንክ እንድትፈፅሙ እናሳውቃለን፡፡ ባንክ የተከፈለበትን ደረሰኝ ኮፒ ት/ቤት በሚከፈትበት ዕለት ይዛችሁ በመምጣት ልጅዎ በሚማርበት/በምትማርበት ሴክሽን (Section) የክፍል ኃላፊ መምህር እንድታስረክቡ እናሳስባለን፡፡ እናመሰግናለን፡፡ ማሳሰቢያ፡- የመጽሐፍት ኮፒ ክፍያ ስንከፍል የተማሪዎችን የክፍያ መለያ ኮድ (ID) መጠቀም የለብንም፡፡ ምክንያቱም የተማሪዎችን የክፍያ መለያ ኮድ (ID) የምንጠቀመው ለወርሃዊ ክፍያ ብቻ ስለሆነ፡፡

ጳጉሜ 02 ቀን 2014 ዓ.ም የተላከ

ጉዳዩ፡- በ2014 ዓ.ም ከ8ኛ ክፍል ወደ 9ኛ ክፍል የተዛወራችሁ ተማሪዎች ይመለከታል፡፡ የተከበራችሁ የተማሪ ወላጆች እና የተወደዳችሁ ተማሪዎቻችን እንደምን አላችሁ፡፡ በ2014 ዓ.ም የ8ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና ወስዳችሁ ወደ 9ኛ ክፍል የተዛወራችሁ ነባር ተማሪዎች በዛሬው ዕለት የውጤት ካርዳችሁን ት/ቤት መጥታችሁ እንድትወስዱ እንዲሁም ለ9ኛ ክፍል ምዝገባ ፎርም ሃይስኩል ቢሮ ስትሞሉ 2 ጉርድ የተማሪ ፎቶ ግራፍና 1 ጉርድ የወላጅ (ተያዥ) ፎቶ ግራፍ ይዛችሁ መምጣት ያለባችሁ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡

ነሃሴ 24 ቀን 2014 ዓ.ም የተላከ

ጉዳዩ፡- በ2014 ዓ.ም ከ8ኛ ክፍል ወደ 9ኛ ክፍል የተዛወራችሁ ተማሪዎች ብቻ ይመለከታል፡፡ የተከበራችሁ የተማሪ ወላጆች እና የተወደዳችሁ ተማሪዎቻችን እንደምን አላችሁ፡፡ በ2014 ዓ.ም የ8ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና ወስዳችሁ ወደ 9ኛ ክፍል የተዛወራችሁ ነባር ተማሪዎች የምዝገባ ቀን ነሃሴ 24 እና 25/2014 ዓ.ም (ማክሰኞ እና ረቡዕ) ስለሆነ በተሰጠው የጊዜ ገደብ ባህርዳር አካዳሚ በአካል በመሄድ ክፍያ በመፈፀም የምዝገባ ፎርም እንድትሞሉ እናሳውቃለን፡፡

በ2014 ዓ.ም ከ8ኛ ክፍል ወደ 9ኛ ክፍል ለተዛወራችሁ ተማሪዎች ብቻ የተከበራችሁ የተማሪ ወላጆች እና የተወደዳችሁ ተማሪዎቻችን እንደምን አላችሁ፡፡ በ2014 ዓ.ም የ8ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና ወስዳችሁ ወደ 9ኛ ክፍል የተዛወራችሁ ነባር ተማሪዎች የምዝገባ ቀን ነሃሴ 24 እና 25/2014 ዓ.ም (ማክሰኞ እና ረቡዕ) ስለሆነ በተሰጠው የጊዜ ገደብ ባህርዳር አካዳሚ በአካል በመሄድ ክፍያ በመፈፀም የምዝገባ ፎርም እንድትሞሉ እናሳውቃለን፡፡

ነሃሴ 23 ቀን 2014 ዓ.ም የተላከ

በ2014 ዓ.ም ነባር እህት እና/ ወንድም ያላቸው የኬጅ 1 አመልካች ተማሪዎች ዛሬ ከቀኑ 8፡00 ስዓት ላይ በተወካይ ወላጆች አማካኝነት መመዝገባችሁ ይታወቃል። ስለሆነም ነገ ማክሰኞ 5:00 ሰዓት ለምዝገባ ት/ቤት ስትመጡ ተመዝጋቢ ህፃናትን እንዲሁም የልደት/ የክትባት ካርዱን ኦሪጅናልና 1 ኮፒ ይዛችሁ እንድትመጡ እናሳውቃለን። እናመሰግናለን፡፡

ጉዳዩ፡- የነባር ተማሪዎችን ምዝገባ ይመለከታል፡፡ ባህርዳር አካዳሚ የ2015 ዓ.ም የነባር ተማሪዎች ምዝገባ እስከ ሐምሌ 22 ቀን 2014 ዓ.ም ብቻ ስለሆነ ከነገ 2፡00 ሰዓት ጀምሮ ት/ቤት በአካል በመምጣት የክፍያ ፎርማት እንድትወስዱ እናሳውቃለን፡፡ እናመሰግናለን፡፡

ጉዳዩ፡- የነባር ተማሪዎችን ምዝገባ ይመለከታል፡፡ ባህርዳር አካዳሚ በ2014 ዓ.ም የነባር ተማሪዎች ምዝገባ እስከ ሐምሌ 22 ቀን 2014 ዓ.ም ብቻ ስለሆነ ከነገ 2፡00 ሰዓት ጀምሮ ት/ቤት በአካል በመምጣት የክፍያ ፎርማት እንድትወስዱ እናሳውቃለን፡፡ እናመሰግናለን፡፡

ጉዳዩ፡- በ2014 ዓ.ም ነባር እህት እና/ ወንድም ያላቸው የኬጅ 1 አመልካች ተማሪ ወላጆችን ይመለከታል፡፡ በ2014 ዓ.ም ነባር እህት እና/ ወንድም ያላቸው የኬጅ 1 አመልካች ተማሪ ወላጆች እህት ወይም ወንድም መኖራቸውን (መሆናቸውን) ለማረጋገጥ የ2014 ዓ.ም የክፍል ካርዳቸውን ኮፒ በማድረግ ዛሬ ሐምሌ 18 (ሰኞ) ከቀኑ 8፡00 ስዓት መጥታችሁ እንድታመለክቱ እናሳውቃለን፡ናመሰግናለን፡፡

ሐምሌ 18 ቀን 2014 ዓ.ም የተላከ

የተከበራችሁ የተማሪዎቻችን ወላጆች እንደምን አላችሁ፡፡ የ2015 ዓ.ም የነባር እና አዲስ ተማሪዎች ምዝገባ ከሐምሌ 15 ቀን 2014 ዓ.ም ጀምሮ በስራ ስዓት ከጥዋቱ 2፡00 - 8፡00 ስዓት ይከናወናል፡፡ የምዝገባ ወቅት ክፍያዎች ሙሉ በሙሉ ካልተከፈሉ (የተቆራረጠ ሂሳብ ካለ) ተማሪዎችን መዝግቦ ክፍል ለመደልደል ስለሚያስቸግር፣ ደንበኞቻችን ቀሪ ሂሳብ አስተካክለው ምዝገባ ለማከናወን መጉላላት እንዳይደርስባቸውና የተማሪዎች ምዝገባም በአመት አንድ ጊዜ ብቻ የሚከናወን በመሆኑ ከዚህ በታች ባለው ቅደም ተከተል መሰረት ምዝገባ የሚከናወን ይሆናል፡፡ 1. በመጀመሪያ ከት/ቤቱ ሂሳብ ክፍል በአካል በመሄድ ለክፍል ደረጃው ለምዝገባ የሚስፈልገውን የገንዘብ መጠን እና የአከፋፈል ስርዓት የሚገልፅ ቅፅ መቀበል፣ 2. ወዲያውኑ ወደ ባንክ በመሄድ የተጠየቀውን ገንዘብ በመክፈል ከከፈሉበት ባንክ ኦሪጅናልና ኮፒ ደረሰኝ መቀበል፣ 3. በዕለቱ የከፈሉበትን የባንክ ደረሰኝ ኮፒውን እንዲሁም ከት/ቤቱ የተሰጠዎትን የክፍያ መረጃ ቅፅ ለት/ቤቱ ሂሳብ ክፍል በአካል መጥቶ መስጠትና ወዲያውኑ የክፍል ደረጃውን ዋና ዋና መረጃ የያዘ 2 ገፅ ወረቀት መቀበል ያስፈልጋል፡፡ የት/ቤቱን ባስ የምትጠቀሙ ደንበኞች የትራንስፖርት ክፍያ የሚከፈለው ለብቻ ሲሆን (ከሌሎች ክፍያዎች ጋር ሳይጨመር) የትራንስፖርት ክፍያ የባንክ ደረኝ ኮፒ ለትራንስፖርት ክፍል መስጠት ያስፈልጋል፡፡ ማሳሰቢያ፡- አዲስ የኬጂ 1 ልጅ (ህፃን) ለማስመዝገብ ያሰባችሁ፤ ነባር ደንበኞቻችን ከእህት/ ወንድማቸው ጋር አብረው እንዲማሩ በምዝገባ መጀመሪያ ቀን አምጥታችሁ እንድታስመዘግቡ እናሳስባለን፡፡ የኬጅ 1 ተማሪዎች ምዝገባ በተጀመረ በጥቂት ቀናት ውስጥ ስለሚሞላና የሚፈለገው ቁጥር ከተመዘገበ በኋላ እህት/ወንድም አላት/አለው የሚሉ አስተያየቶችን ለመቀበል የምንቸገር መሆኑን እናሳውቃለን፡፡