cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

ፍኖተ አበዉ አሰላ አጥቢያ

ይሄ መንፈሳዊ ቻናል ነው ፍኖተ አበው የክርስቶስ ኢየሱስ ቤተ ክርስትያን አሰላ አጥቢያ 👉 ተሰምተው የማይጠገቡ መዝሙሮች 👉 ሕይወት ለዋጭ ትምህርቶች 👉 መንፈሳዊ ትረካዎች፣ግጥሞች 👉 ስብከቶች 👉 የመ.ቅ ጥቅሶችን ሚያገኙበት ሁላቹም ይከታተሉን የለወጡ ይባረኩበት 😘 ✍ ሰዎች ክርስቶስን እንዲያሳዩ ለማድረግ ቆርጠን ተነስተናል ይቀላቀሉ @Fnotabewasellaat

Show more
The country is not specifiedThe language is not specifiedThe category is not specified
Advertising posts
149
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

🔆 ዘሪ ዘሩን ሊዘራ ወጣ። 🛣 ሲዘራም አንዳንዱ በመንገድ_ዳር ወደቀ፤ ተረገጠም፥ የሰማይ ወፎችም በሉት። 🏔 ሌላውም በዓለት_ላይ ወደቀ፥ በበቀለም ጊዜ እርጥበት ስላልነበረው ደረቀ። 🕸 ሌላውም በእሾህ_መካከል ወደቀ፥ እሾሁም አብሮ በቀለና አነቀው። 🖼 ሌላውም በመልካም_መሬት ላይ ወደቀ፤ በበቀለም ጊዜ መቶ እጥፍ አፈራ። ይህን በተናገረ ጊዜ፦ የሚሰማ ጆሮ ያለው ይስማ ብሎ ጮኸ። ምሳሌው ይህ ነው። 📖 ዘሩ የእግዚአብሔር_ቃል ነው። 💸 በመንገድ_ዳርም ያሉት የሚሰሙ ናቸው፤ ከዚህ በኋላም ዲያብሎስ ይመጣል፤ አምነውም እንዳይድኑ ቃሉን ከልባቸው ይወስዳል። ⌛️ በዓለት_ላይም ያሉት ሲሰሙ ቃሉን በደስታ የሚቀበሉ ናቸው፤ እነርሱም ለጊዜው ብቻ ያምናሉ እንጂ በፈተና ጊዜ የሚክዱ፣ ሥር የሌላቸው ናቸው። 🎁 በእሾህ_መካከልም የወደቀ እነዚህ የሚሰሙት ናቸው፤ መንገዳቸውንም ሄደው፣ በሕይወት ዘመን በአሳብና በባለ ጠግነት ምቾት ይታነቃሉ፥ ሙሉ ፍሬም አያፈሩም። 🙏 በመልካም_መሬት ላይም የወደቀ እነርሱ በመልካምና በበጎ ልብ ቃሉን ሰምተው የሚጠብቁት፣ በመጽናትም ፍሬ የሚያፈሩ ናቸው። (የሉቃስ ወንጌል 8 ) 👉 If you could just listen with a closer attention, without shutting him off, God is always there; speaking to your heart. Even now, He is advising you. OBEY! 👉 እንደምንም ተረጋግተን፣ ባልሰማ ሳናልፍ፣ በሙሉ ልባችን ማዳመጥ ብንችል፣ ድምጹ ሁሌም አለ፤ እየጮኸ። አሁን እንኳን፣ እየመከረ ነው። መታዘዝ ነዋ! Join us @Nubegetadesyibelen @Nubegetadesyibelen
Show all...
ማነው እንዳንተ የነፍሴ ቤዛ ከሞት ወደ ሕይወት ማምለጫ ታዛ አንተ ብቻ ነህ የተቤዥከኝ አማኑኤል ሆይ ክበርልኝ ማነው እንዳንተ ጎኑን ተወግቶ ደሙን አፍሶ ዓይኔን ያበራ ደርሶ ሲመሻሽ በሕይወቴ ላይ ታሪክ የሰራ ሁሉ ሲተወኝ ከወደኩበት ቀና ያረገኝ ሳምራዊነቴን ሳይጸየፈኝ ሞገስ ሆነልኝ ማነው እንዳንተ ከለሜዳውን ስለኔ ብሎ የተሸለመ ሕመሜን ወስዶ በደሙ ጅረት ቁስሌን ያከመ ጥሜን ሊያረካ የተጎነጨ ሐሞት ስፍንጎ እርግማን ነውሬን የተቀበለ ኃጢአት አድርጎ ማነው እንዳንተ የእዳዬን ጡማር በደሙ ማኅተም የደመሰሰ የጋረደኝን የጠብ ግድግዳ የገረሰሰ ከአዕምሮ በላይ በማይተካ በጽኑ ፍቅር ታምኖ ያሳየ ጥልቅ መውደዱን እስከ መቃብር ማነው እንዳንተ ያለ በደሉ ቀንበሬን በፍቅር የተሸከመ ጽኑ ሕመሜን እየታመመ ቁስሌን ያከመ የሕይወት ውሃ እያስጎነጨኝ ሐሞት የጠጣ ስለኔ ማለፍ እየታወከ ጽድቄን ያመጣ ━━━━━━━━━━━━━ “፤ ልሄድ ከክርስቶስም ጋር ልኖር እናፍቃለሁ፥ ከሁሉ ይልቅ እጅግ የሚሻል ነውና፤” ፊልጵስዩስ 1፥23
Show all...
ሰላም🙌 በ2012 ብዙ ነገር አይተናልም ገጥሞናልም ጥሩም መጥፎም ብዙ ነገሮችንም ተምረንበታል ጌታ ይመስገን ስለ ሁሉ🙏🙏🙏 በ2013 🌼🌼🌼 ✝እግዚአብሄርን የምንፈራ😍 ✝የጌታችንን ቃል የምንወድ😍 ቃሉን የምንኖረዉ ይሁንልን🛐🙏 መ🌼 ል🌼 ካ🌼 ም🌼 አ🌻 ዲ🌻 ስ🌻 አ🌼 መ🌼 ት🌼 ሀገራችን🇪🇹 ሰላም ፍቅር.....ይብዛላት😁🙏🙏🙏 🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
Show all...
አዲሱ ዝማሬ ተለቀቀ 👇👇👇👇👇👇 በወቅታዊ ጉዳይ ላይ የተሰራ ድንቅ ዝማሬ ይስሙትና ይባረኩበት 👇👇 subscribe ያድርጉ ??? 👇👇👇👇👇👇 https://youtu.be/WV1XO0lVlmY
Show all...
meharen keresetose መሐረነ ክርስቶስ በወቅታዊ ጉዳይ ላይ የተዘመረ ድንቅ ዝማሬ

የዕለቱ መልዕክት 📖📖መዝሙረ ዳዊት 118:24 - Psalms 118:24 እግዚአብሔር የሠራት ቀን ይህች ናት፤ ሐሤትን እናድርግ፥ በእርስዋም ደስ ይበለን። This is the day which the LORD hath made; we will rejoice and be glad in it. ይ🀄️ላ🀄️ሉን @Fnotabewasellaatibiya @Fnotabewasellaatibiya
Show all...
🌿ከዘማሪ ዘላለም ይንገስ🌿 የእግዚአብሔር ልጅ ✥ ኢየሱስ✥ ✥ ኢየሱስ✥ ✥ኢየሱስ✥ ✥ኢየሱስ✥ 🌿 ቤዛዬ በልቤ ክበር አዳኜ በነፍሴ ንገስ የመጣህልኝ ከሠማይ ያስቀረህልኝ የነፍሴን ስቃይ ከአባትህ ያስታረከኝ አምጠህ የወለድከኝ 🌿 አሮጌው ትላንትናዬ ታድሷል ባንተ ጌታዬ ተባረክ ውዴ ወዳጄ ያሸብሽብ ያክብርህ እጄ ጠርቼ የማልጠግብህ ዘላለም የምወድህ ደስታዬ የነፍሴ እርካታ ፍቅር ነህ አንተኮ ጌታ 🌿በሞትህ ሞቴን ገደልከው ትላንቴን ታሪክ አረከው ልረሳህ እንደምን ችዬ ሸክሜን ባንተላይ ጥዬ ነፅቼ በቅዱስ ደምህ ተውቤ በውቡ ስምህ አልቻለም ጠላት ሊረታኝ ሞገሴ አንተ እያለኸኝ 🌿 ቃልህን ታጥቆ ወገቤ ስምህን አትሞት ልቤ ሰላም ነው አሁን መንገዴ ስላለህ ከእኔ ጋር ውዴ የመጣህልኝ ከሠማይ ያስቀረህልኝ የነፍሴን ስቃይ ከአባትህ ያስታረከኝ አምጠህ የወለድከኝ 🌿አሮጌው ትላንትናዬ ታድሷል ባንተ ጌታዬ ተባረክ ውዴ ወዳጄ ያሸብሽብ ለክብርህ እጄ ይ🀄️ላ🀄️ሉን @Fnotabewasellaatibiya @Fnotabewasellaatibiya
Show all...
በመንፈስ ድሆች የሆኑ ብፁዓን ናቸው፥ መንግሥተ ሰማያት የእነርሱ ናትና። 4 የሚያዝኑ ብፁዓን ናቸው፥ መፅናናትን ያገኛሉና። 5 የዋሆች ብፁዓን ናቸው፥ ምድርን ይወርሳሉና። 6 ጽድቅን የሚራቡና የሚጠሙ ብፁዓን ናቸው፥ ይጠግባሉና። 7 የሚምሩ ብፁዓን ናቸው፥ ይማራሉና። 8 ልበ ንጹሖች ብፁዓን ናቸው፥ እግዚአብሔርን ያዩታልና። 9 የሚያስተራርቁ ብፁዓን ናቸው፥ የእግዚአብሔር ልጆች ይባላሉና። 10 ስለ ጽድቅ የሚሰደዱ ብፁዓን ናቸው፥ መንግሥተ ሰማያት የእነርሱ ናትና። 11 ሲነቅፉአችሁና ሲያሳድዱአችሁ በእኔም ምክንያት ክፉውን ሁሉ በውሸት ሲናገሩባችሁ ብፁዓን ናችሁ። 12 ዋጋችሁ በሰማያት ታላቅ ነውና ደስ ይበላችሁ፥ ሐሴትም አድርጉ፤ ከእናንተ በፊት የነበሩትን ነቢያትን እንዲሁ አሳድደዋቸዋልና። 13 እናንተ የምድር ጨው ናችሁ፤ ጨው አልጫ ቢሆን ግን በምን ይጣፍጣል? ወደ ውጭ ተጥሎ በሰው ከመረገጥ በቀር ወደ ፊት ለምንም አይጠቅምም። 14 እናንተ የዓለም ብርሃን ናችሁ። በተራራ ላይ ያለች ከተማ ልትሰወር አይቻላትም። 15 መብራትንም አብርተው ከዕንቅብ በታች አይደለም እንጂ በመቅረዙ ላይ ያኖሩታል በቤት ላሉት ሁሉም ያበራል። 16 መልካሙን ሥራችሁን አይተው በሰማያት ያለውን አባታችሁን እንዲያከብሩ ብርሃናችሁ እንዲሁ በሰው ፊት ይብራ። 17 እኔ ሕግንና ነቢያትን ለመሻር የመጣሁ አይምሰላችሁ፤ ልፈጽም እንጂ ለመሻር አልመጣሁም። 18 እውነት እላችኋለሁ፥ ሰማይና ምድር እስኪያልፍ ድረስ፥ ከሕግ አንዲት የውጣ ወይም አንዲት ነጥብ ከቶ አታልፍም፥ ሁሉ እስኪፈጸም ድረስ። 19 እንግዲህ ከነዚህ ከሁሉ ካነሱት ትእዛዛት አንዲቱን የሚሽር ለሰውም እንዲሁ የሚያስተምር ማንም ሰው በመንግሥተ ሰማያት ከሁሉ ታናሽ ይባላል፤ የሚያደርግ ግን የሚያስተምርም ማንም ቢሆን እርሱ በመንግሥተ ሰማያት ታላቅ ይባላል። 20 እላችኋለሁና። ጽድቃችሁ ከጻፎችና ከፈሪሳውያን ጽድቅ ካልበለጠ፥ ወደ መንግሥተ ሰማያት ከቶ አትገቡም። 21 ለቀደሙት። አትግደል እንደ ተባለ ሰምታችኋል፤ የገደለም ሁሉ ፍርድ ይገባዋል። 22 እኔ ግን እላችኋለሁ፥ በወንድሙ ላይ የሚቆጣ ሁሉ ፍርድ ይገባዋል፤ ወንድሙንም ጨርቃም የሚለው ሁሉ የሸንጎ ፍርድ ይገባዋል፤ ደንቆሮ የሚለውም ሁሉ የገሃነመ እሳት ፍርድ ይገባዋል። 23 እንግዲህ መባህን በመሠዊያው ላይ ብታቀርብ፥ በዚያም ወንድምህ አንዳች በአንተ ላይ እንዳለው ብታስብ፥ 24 በዚያ በመሠዊያው ፊት መባህን ትተህ ሂድ፥ አስቀድመህም ከወንድምህ ጋር ታረቅ፥ በኋላም መጥተህ መባህን አቅርብ። 25 አብረኸው በመንገድ ሳለህ ከባላጋራህ ጋር ፈጥነህ ተስማማ፤ ባላጋራ ለዳኛ እንዳይሰጥህ ዳኛም ለሎሌው፥ ወደ ወህኒም ትጣላለህ፤ 26 እውነት እልሃለሁ፥ የመጨረሻዋን ሳንቲም እስክትከፍል ድረስ ከቶ ከዚያ አትወጣም። ይ🀄️ላ🀄️ሉን @Fnotabewasellaatibiya @Fnotabewasellaatibiya
Show all...
(መዝሙረ ዳዊት ምዕራፍ 46) ---------- 1፤ አምላካችን መጠጊያችንና ኃይላችን፥ ባገኘን በታላቅ መከራም ረዳታችን ነው። 2፤ ስለዚህ ምድር ብትነዋወጥ፥ ተራሮችም ወደ ባሕር ልብ ቢወሰዱ አንፈራም። 3፤ ውኆቻቸው ጮኹ ተናወጡም፥ ተራሮችም ከኃይሉ የተነሣ ተናወጡ። 4፤ የወንዝ ፈሳሾች የእግዚአብሔርን ከተማ ደስ ያሰኛሉ፤ ልዑል ማደሪያውን ቀደሰ። 5፤ እግዚአሔር በመካከልዋ ነው አትናወጥም፥ እግዚአብሔርም ፈጥኖ ይረዳታል። 6፤ አሕዛብ ተናወጡ መንግሥታትም ተመለሱ፤ እርሱ ቃሉን ሰጠ፥ ምድርም ተንቀጠቀጠች። 7፤ የሠራዊት ጌታ ከእኛ ጋር ነው፤ የያዕቆብ አምላክ መጠጊያችን ነው። 8፤ የእግዚአብሔርን ሥራ፥ በምድር ያደረገውንም ተኣምራት እንድታዩ ኑ። 9፤ እስከ ምድር ዳርቻ ድረስ ጦርነት ይሽራል። ቀስትን ይሰብራል፥ ጦርንም ይቈርጣል በእሳትም ጋሻን ያቃጥላል። 10፤ ዕረፉ፥ እኔም አምላክ እንደ ሆንሁ እወቁ፤ በአሕዛብ ዘንድ ከፍ ከፍ እላለሁ፥ በምድርም ላይ ከፍ ከፍ እላለሁ። 11፤ የሠራዊት ጌታ ከእኛ ጋር ነው፤ የያዕቆብ አምላክ መጠጊያችን ነው።
Show all...
በማለዳ 1ኛ የዮሐንስ መልእክት 2:1 1 ልጆቼ ሆይ፥ ኃጢአትን እንዳታደርጉ ይህን እጽፍላችኋለሁ። ማንም ኃጢአትን ቢያደርግ ከአብ ዘንድ ጠበቃ አለን እርሱም ጻድቅ የሆነ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። ያማረ የተወደደቀ ቀን
Show all...