cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

ሀገረ እግዚሐብኤር ፩

✞አመድ ከዘነመ ከአራት ዓመት በዋላ የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ሰማዕት የሆነ በፊቅጦር በገድሉ መጽሐፍ እንደ ተነገረው የስሙ ምልክት < ቴ > ተብሎ የተመለከተው ይነግሣል✞ ✞ድርሳነ ዑራኤል ዘጥቅምት✞ 👉 @agerhigzihaber

Show more
The country is not specifiedThe language is not specifiedThe category is not specified
Advertising posts
223
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

ኢትዮጵያ በረዥም ህልዉናዋ ዉስጥ ካሳለፈችዉ ከመቼዉም ጊዜ ይልቅ በዚህ ዘመን የተለየና ታላቅ ችግር እየደረሰባት መገኘቷ እነሆ ለማንም በግልፅ ይታያል። ታዲያ ከዚህ ከደረሰባት ችግሯ ይታደጎት ዘንድ ከዲያቢሎስና ከሰራዊቱ ጋር በምታካሂደዉ የመጨረሻ ታላቅ ሰልፏም ላይ ተጋፍጠዉ ይታገሉላት ዘንድ የተዘጋጁ እዉነተኞችና ታማኞች አርበኞች ልጆቿ አሉላት ወይ? እኒህ ልጆቿ ለግል ስምና ክብር ጥቅምና ምቿት ሳይሆን ራሳቸዉን ለእግዚአብሄር እዉነት ለመሰዋት ያለ አንዳች ዉልዉልና ጥርጥር በቆራጥ የመንፈስ ቅዱስ ሀይል ይጋደሉላት ዘንድ ይህን የዘመቻ ጥሪዋን ተቀብለዉ ከቤተ ህዝቧም ከቤተ ክህነቷም ከቤተ ምልክናዋ መካከል ብቅ ብቅ እንዲሉላት ትፈልጋለች! ትጠብቃለች! ይህንን ጥሪዋን ለመቀበል ፈቃደኞች ለሚሆኑት ይህን እላለሁ:-"ፍፁም ፍቅር ፍርሀትን አዉጥቶ ይጥላል እንጂ በፍቅር ፍርሃት የለም! ፍርሃት ቅጣት አለዉና የሚፈራም ሰዉ ፍቅሩ ፍፁም አይደለም"። #ንቡረእድ_ኤርምያስ_ከበደ_ወልደ_ኢየሱስ
Show all...
#ኢትዮጵያ_ሀገረ_እግዚአብሔር! የምዕራባውያን የታሪክ አባት ተብሎ የሚጠራው ሔሮድቱስ ስለኢትዮጵያ ባነሳበት መፅሐፍ ኢትዮጵያውያን በውበት በቁመትና በሐይል ከሰዎች ሁሉ የሚበልጡ ናቸው ብሎአል፡፡ በሆሜር መፅሐፍ ቀዩን ወይን ኢትዮጵያ ስለሚለው ኢትዮጵያዊ ማለት ቀይ የቀይ ዳማ ቀለም ያለው ሕዝብ ማለት ነው፡፡ የኢትዮጵያዊያን አባት ኩሽ በሞተ በ2450 ዓመት በ(284 ዓ.ም) በታላቅነቱና በገናናነቱ በዓለም ገኖ የሚታወቀው በጥሊሞስ በነገሠበት ዘመን የብሉይ ኪዳን መፅሐፍትና በዕብራይስጥ ወደ ፅርዕ የለወጡ ሰባው ሊቃውንት ሙሴ ኩሽ እያለ የተፃፈውን ኢትዮጵያ ብለው ፅፈዋል (ለውጠዋል)፡፡ ሊቀ ጠበብት አለቃ አያሌው ታምሩ በ1953 ዓ.ም ባሳተሙት ‹‹የኢትዮጵያ እምነት በሦስቱ ህግጋት›› በተሰኘው መፅሐፋቸው (ከገፅ 54-58) ስለ ኢትዮጵያ መጠሪያ ሲገልፅ ሌሎች የኢትዮጵያ ስያሜዎች ከመታሰቢያ ውስጥ ሆኖ ኢትዮጵያ የሚለው በቤቴል አንፃር ይጠራል ቤቴል ማለትም የእግዚአብሔር ቤት ማለት እንደሆነ ሁሉ ኢትዮጵያ ማለትም ሀገረ እግዚአብሔር ማለት ነው፡፡ ስምነቱን ስንማረውም ትርጓሜው እንደሚከተለው ነው፡፡ ኢ-ማለት እግዚአብሔር (አሌፍ አልፋ) ት-ማለት ታው ትጉህ አብ ዮ-ማለት ዮድ የማን እግዚአብሔር ወልድ ጵ-ማለት ጰራቅሊጦስ መንፈስ ቅዱስ ያ-ማለት የአንድ አምላክ የአብ የወልድ የመንፈስ ቅዱስ ሀገር ማለት ነው በማለት አስቀምጠዋል፡፡
Show all...
ራዕይ ዮሐንስ 20 አጭር መልዕክት 17/9/2013
Show all...
ልቡናውን ሰብስቦ መጸለይ አልችል ያለው ሰው አንድ ታላቅ አባትን እንዲህ ሲል ጠየቃቸው፦ "አባቴ የጸሎት መጽሐፍ ይዤ ስጸልይ ልቡናዬ አይሰበሰብልኝም፡፡ አፌ ቢያነበንብም ልቡናዬ አይተረጕምም፡፡ እርስዎ እንደነገሩኝ ደግሞ ቅዱሳን በፍጹም አሳባቸው እያሰቡና እያራቀቁ እንባንና ጸጸትን እየጨመሩ የደረሱትን እኛ በልባችን ሌላ እያሰብን በአፋችን ብቻ እንደእነርሱ ብንናገር እንደ ገደል እንደ ዋሻ ሆነን በእግዚአብሔር እንደመቀለድ ነው፤ ጸሎትም አይሆንልንም፡፡ እንግዲህ የአፍ ጸሎቴ ቅድመ እግዚአብሔር የማይደርስ ከሆነ ጸሎቴን ብተወው ይሻላል ወይስ ባልተወው ይሻላል?" እርሳቸውም፦ "ዕውር ሰው በዘንጉ ምድር እየመታ ሲሄድ ከመንገድ ላይ ያለ እባብ ለጊዜው ድምጹን ሰምቶ ይመታኛል ብሎ እንደሚሸሽለት ሁሉ አንተም አስተውለህ ባትጸልይም በአፍህ ውስጥ የቃለ እግዚአብሔርን መንኳኳት እየሰሙ አጋንንት መሸሻቸው አይቀርምና ምንም ቅድመ እግዚአብሔር ባይደርስም ጸሎትህን አትተው። አጋንንትን ለማባረርም ጥቅም ነውና። ብዙ ከምትጸልየውም አንዳንድ ጊዜ ልብህ የሚወድቅባት ቃል ተጠራቅማ ወደ እግዚአብሔር ትደርሰልሃለች፤ ምንም ዝርወ ልብ ብትሆንም አፍህም ፍጥረቱ ነውና አንተው በዳይ አንተው አኵራፊ እንዳትሆን ባፍህም ብቻ ቢሆን መነጋገሩን አትተወው፡፡" ሲሉ መለሱለት። (ምንጭ፦ ፍኖተ አእምሮ) @beteafework @beteafework @beteafework @beteafework @beteafework @beteafework
Show all...
ኢትዮጵያ የአለም ብርሃን መልዕክት 1 እና 2 አንድ ላይ፣3፣4፣5፣6 እና 8 (በድምፅ)👇👇👇 https://bit.ly/1_እና_2_ኢትዮጵያ_የአለም_ብርሃን_መልዕክት_mp3 https://bit.ly/3_ኢትዮጵያ_የአለም_ብርሃን_መልዕክት_mp3 https://bit.ly/4_ኢትዮጵያ_የአለም_ብርሃን_መልዕክት_mp3 https://bit.ly/5_ኢትዮጵያ_የአለም_ብርሃን_መልዕክት_mp3 https://bit.ly/6_ኢትዮጵያ_የአለም_ብርሃን_መልዕክት_mp3 https://bit.ly/8_ኢትዮጵያ_የዓለም_ብርሃን_መልዕክት_mp3 Ethiopia the Light of the World Messages 1,2,3 & 5 ( in Aduio )👇👇👇 https://bit.ly/1_EthiopiatheLightoftheWorld_mp3 https://bit.ly/2_EthiopiatheLightoftheWorld_mp3 https://bit.ly/3_EthiopiatheLightoftheWorld_mp3 https://bit.ly/5_EthiopiatheLightoftheWorld_mp3 ከኢትዮጵያ የዓለም ብርሃናዊ መንግሥት የወጣ 9ኛ መልዕክት፤ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅን የያዘ ! 👇 https://bit.ly/9ኛ_መልዕክት_ኢትዮጵያ_የዓለም_ብርሃን_pdf https://bit.ly/ክፍል_1_9ኛ_መልዕክት_ኢትዮጵያ_የዓለም_ብርሃን_በድምፅ https://bit.ly/ክፍል_2_9ኛ_መልዕክት_ኢትዮጵያ_የዓለም_ብርሃን_በድምፅ https://bit.ly/ክፍል_3_9ኛ_መልዕክት_ኢትዮጵያ_የዓለም_ብርሃን_በድምፅ https://bit.ly/ክፍል_4_9ኛ_መልዕክት_ኢትዮጵያ_የዓለም_ብርሃን_በድምፅ https://bit.ly/ክፍል_5_9ኛ_መልዕክት_ኢትዮጵያ_የዓለም_ብርሃን_በድምፅ 👆👆👆 ለfacebook, Email, imo, whatsup ... ላይ ለመልቀቅ ለምትፈልጉ https://bit.ly/RayYohanes20 👆👆👆 *ሁሉንም ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልዕክቶች ( አማርኛው / እንግሊዝኛው /አረብኛው ወዘተ... )፣ ደብዳቤዎች ፣ መግለጫዎች ፣ አጭር መልዕክቶች ፣ ማብራሪያዎች ... በአጠቃላይ ሁሉንም በዚህ ገፅ የተላለፉትን በፅሁፍም በድምፅም ያሉትን የያዘ ነው ። ማንም ይህ ሊንክ ያለው እስካሁን የተላለፉትን ወደፊትም የሚወጡ ካሉ በዚህ ሊንክ ማግኘት ይችላል ለfb ለዋትስ አፕ ለቫይበር እና ለመሳሰሉት ለምትፈልጉ።👉➪ https://bit.ly/RayYohanes20 እነዚህ ደግሞ መልዕክታቱን በቀላሉ በቴሌግራም የሚያገኙባቸው መስመሮች ናቸው።👇 👉 t.me/rayeyohanes20_bot 👉 t.me/rayyohanes20 👉 t.me/ethioBirhan Share ማድረግ አትርሱ!
Show all...
👇👇👇👇👇 የኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን ቤተሰቦች ክርስቶስ በደም ከመሰረታት ሰማእታት ካፀኗት ከቅድስት ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ውጪ ቤት የላቸውም ። የእረኛቸውን ድምፅ ለይተው የሚያውቁ እውነተኛ በጎች ናቸው ከጠፊው ዓለም ውስጥ ለመዳን ከተጠሩት እንደ ብዙ የእግዚአብሔር ህዝብ በምህረት የተጠሩ ናቸው። የሚከተሉት ሰውን ሳይሆን እግዚአብሔርን ነው። ከዓለም ጉድፍ የራቁ ሲደክሙ በንስሀ እንደሚነሱ የሚያምኑ ናቸው። ይህን ዓለም፣ በሀሰተኛነቱ፣ በአስመሳይነቱ፣ በትእቢቱ፣ በከሀዲነቱ የሚኮንኑ ናቸው። ቤተክርስቲያን በፈረሰው ጎኗ የሚቆሙ የአባቶች እንባ ፍሬ ከዋክብት ናቸው። ሀይል እስኪለብሱ መከራን የሚታገሱ ናቸው። ሉቃ 24:49 መስቀሉ መመኪያቸው ሀይላቸው ነው ። የቤተክርስቲያን እና የኢትዮጵያ ትንሳኤ በገሀድ መገለጥ እንዲሁም መንግስተ ሰማያት ተስፋቸው ነው። አባታቸው ልዑል እግዚአብሔር እናታቸው፣ አማላጃቸው ወላዲተ አምላክ፣ ቅዱሳን ፃድቃን ሰማእታት፣ ጠባቂዎቻቸው ቅዱሳን መላእክት ናቸው። ድንበራቸው የአባቶቻችው ድንበር ነው። ምሳ 22:28 የሚያነግሱት እውነትን ብቻ ነው። የእግዚአብሔር ቃል ውሀ ልካቸው፣ አፅኛቸው፣ አፅናኛቸውም ነው። የመልከፄዲቅ ህብስት ፅዋዕ ኪዳን የተቀበሉ በክርስቶስን ስጋ ና ደም የዘለዓለም ህይወት ድህነት እንደሚያገኙ የሚያምኑ የተዋህዶ ልጆች ናቸው። ዘፍ 14 እና ዕብ 7 ከተረሱት፣ ከተጣሉት ፣ ከተገፉት እውነትን ካነገሱት እውነተኞች፣ ዘወትር በእንባ በፀሎት ስለ ቤተክርስቲያን ስለ ኢትዮጵያ ስለ ዓለም የሚማልዱት የተዋህዶ አርበኞች ጎን ናቸው እውነተኛ የቃል ኪዳን የኢትዮጵያ ልጆች ናቸው። "በኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን ቤተሰብ የተሰባሰባችሁ ሁሉ እጅግ እድለኞች ናችሁ ልትበረቱ ይገባል ።ቤተክርስቲያን የምናድን እኛ ነን።" የኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን የማቴዎስ ወንጌል ትምህርት ክፍል 3 ለ 25 ደቂቃ ከ40 ሰከንድ እስከ 26 ደቂቃ 05 ሰከንድ ኢይሀድጋ ሀገረትነ ኢትዮጵያ ቸር መሀሪው ልዑል እግዚአብሔር ፣የመስቀል ስር ስጦታ እናታችን ድንግል ማርያም፣ ቅዱሳን አባት እናቶቻችን ፣ ተራዳኢ መላእከቶቻችን የተመሰገኑ ይሁኑ አሜን። 👇👇👇 https://telegram.me/agerehigzihaber
Show all...
#ኢትዮጵያ_ሀገረ_እግዚአብሔር! የምዕራባውያን የታሪክ አባት ተብሎ የሚጠራው ሔሮድቱስ ስለኢትዮጵያ ባነሳበት መፅሐፍ ኢትዮጵያውያን በውበት በቁመትና በሐይል ከሰዎች ሁሉ የሚበልጡ ናቸው ብሎአል፡፡ በሆሜር መፅሐፍ ቀዩን ወይን ኢትዮጵያ ስለሚለው ኢትዮጵያዊ ማለት ቀይ የቀይ ዳማ ቀለም ያለው ሕዝብ ማለት ነው፡፡ የኢትዮጵያዊያን አባት ኩሽ በሞተ በ2450 ዓመት በ(284 ዓ.ም) በታላቅነቱና በገናናነቱ በዓለም ገኖ የሚታወቀው በጥሊሞስ በነገሠበት ዘመን የብሉይ ኪዳን መፅሐፍትና በዕብራይስጥ ወደ ፅርዕ የለወጡ ሰባው ሊቃውንት ሙሴ ኩሽ እያለ የተፃፈውን ኢትዮጵያ ብለው ፅፈዋል (ለውጠዋል)፡፡ ሊቀ ጠበብት አለቃ አያሌው ታምሩ በ1953 ዓ.ም ባሳተሙት ‹‹የኢትዮጵያ እምነት በሦስቱ ህግጋት›› በተሰኘው መፅሐፋቸው (ከገፅ 54-58) ስለ ኢትዮጵያ መጠሪያ ሲገልፅ ሌሎች የኢትዮጵያ ስያሜዎች ከመታሰቢያ ውስጥ ሆኖ ኢትዮጵያ የሚለው በቤቴል አንፃር ይጠራል ቤቴል ማለትም የእግዚአብሔር ቤት ማለት እንደሆነ ሁሉ ኢትዮጵያ ማለትም ሀገረ እግዚአብሔር ማለት ነው፡፡ ስምነቱን ስንማረውም ትርጓሜው እንደሚከተለው ነው፡፡ ኢ-ማለት እግዚአብሔር (አሌፍ አልፋ) ት-ማለት ታው ትጉህ አብ ዮ-ማለት ዮድ የማን እግዚአብሔር ወልድ ጵ-ማለት ጰራቅሊጦስ መንፈስ ቅዱስ ያ-ማለት የአንድ አምላክ የአብ የወልድ የመንፈስ ቅዱስ ሀገር ማለት ነው በማለት አስቀምጠዋል፡፡
Show all...
⁉️ "የበረኸኞቹ መልዕክት..." ከኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን ጋር በምን ተገናኘ?? እነሆ ለጥያቄያችሁ አጭር መልስ ይሁን ብለናል። የሚሰማ ጤነኛ ጆሮ ያለው እውነቱን ይስማ ! የማይሰማም አይስማ !! እኛ ግን እውነታውን እንናገራለን! የሚጥመው ይጣመው የሚመርረውም ያንገሽግሸው። ◉◉◉ ...የዘመኑ ትውልድ እጅግ ይገርመኛል ! ያልተባለውን "በእውነት! ተብሏል ስምቻለሁ" ያልተደረገውን "በእውነት! ተደርጓል ተመልክቻለሁ" የሚል ከሃዲ፣ ውሸትን እንደሸማ የተጎናጸፈ፣ የሐሰት አባት የወለደው ከንቱ ትውልድ። ይገርመኛል። ◉◉◉ "...የበረኸኞቹ አባቶች እንዲህና እንዲያ በል ብለውኛል፡ እንዲህ ይሆናል፡ የገዳም አባቶች እንዲህ ብለዋል እንዲህ አድርጉ ..." ያላችሁ ማን እንደሆነ ስሙንም ግብሩንም ታውቃላችሁ። ያ ሰው ከእኛ ጋር አብሮ የቆመ እንዳልሆነ እኛም አሳውቀናል እሱም ምላሱን አርዝሞ እየተሳደበ ነግሯችኋል፡ ያዳመጣችሁም አዳምጣችኋል። ይህ ከሆነ እኛ ባላልነው ለምን እንነቀፋለን? ታዲያ በኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልዕክታትም ይሁን ማሳሰቢያ መግለጫና ትምህርቶች ... ውስጥ የትኛው ስፍራ፣ መቼ ነው 'ይህ መልዕክት የበረኸኞቹ፣ ይህ መልዕክት የገዳም አባቶች...' ነው የሚል የት አለ?? መቼ እንዲህ ተባለ? ይገርማል ። ◉◉◉ ቀድሜ እንደገለጽኩት የዘመኑ ትውልድ ያልተባለውን እንደተባለ የሚቆጥርና በባዶ ሀሳብ ሽንጡን ገትሮ ለማሳመን የሚከራከር ውሉ የጠፋበት ልቃቂት ትውልድ ነው። ከልሂቅ እስከ ደቂቅ በዚህ እውነት የምንሰፈርና የምንመዘን ነን ። ከትውልዱ ማን አስተዋለ!? ማንስ በእውነት ላይ ተመስርቶ ቆመ!? ◉◉◉ ይሁንና ብዙዎች የዘመናችን ግንባር ቀደም ተቺዎች የመጥፎ ሀሳብ መፍለቂያ የሆነውን አዕምሯቸውና የመጥፎ ነገር ማፋሰሻ የሆነውን አፋቸውን የሚከፍቱት "ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን የሚባሉት የበረኸኞቹ፡ የገዳም አባቶች መልዕክት ነው ይላሉ ! የትኞቹ ገዳማት ..." ወዘተ እያሉ እኛን በማይመለከተን ጉዳይ ተከሳሾች አድርገውን የቆሻሻ ሀሳቦች ማፋሰሻ አፋቸውን ሲያላቅቁ ሲያንቧርቁ ይውላሉ እኛም ይህንን ዕለት በዕለት የምናስተውለው ቃላቸው ነው። እኛም ሆንን ቀዳማዊ የልዑል አገልጋዮች አባቶቻችን መቼና የት ነው "የገዳም አባቶች መልዕክት ነው ስሙን ታዘዙን..." ያሉ ?? ይህ የእግዚአብሔር መልዕክት ነው ብለው እውነታውን አጸኑ እንጂ የእኛ የአባቶች መልዕክት ነው እንኳን መች አሉ ? እውነት ነው መልዕክቱ የእግዚአብሔር ነው። የሰው ሀሳብና የሰው እቅድ አይደለም የሰው ሥራም ተግባራዊ የሚያደርገው ጉዳይ አይደለም። የእግዚአብሔር አንደበት የተናገረውን የእግዚአብሔር እጅ ይሰራዋል። ልዑል በኤርምያስ፣ በዮሐንስ፣ በሕዝቅኤል ወዘተ በኩል ሲናገር ምን ብለን ነው ስንሰማው ስናነበው የኖርን? "የእግዚአብሔር መልዕክት በነብዩ ሕዝቅኤል፣ በነብዩ ኤርምያስ፣ በሐዋርያው ዮሐንስ ... በኩል .." ወዘተ እያልን አይደለም ስንረዳው የኖርን? ነው ወይስ የሕዝቅኤል፣ የኤርምያስ መልዕክት ነው ብላችሁ ነው የምታነቡት? እነሱ እኮ ለእግዚአብሔር መናገሪያ ይሆኑ ዘንድ የተመረጡ አንደበቶች ናቸው እንጂ ሐሳብ አመንጪ፡ አናጋሪ፡ ውሳኔ አሳላፊ አልነበሩም። የዚህ ሁሉ ባለቤት እግዚአብሔር ነበር። ታዲያ አሁንስ ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን በሚል መልዕክት ተናጋሪ ሰዎች በኩል የሚያናግር፣ የሚያዝዝ፣ የሚወስን እግዚአብሔር እንደሆነ ማን ይንገራችሁ ? ማን ያስረዳችሁና ታምናላችሁ ? ለነገሩ እግዚአብሔር አርጅቶ የሞተ ያህል ከሕሊናችሁ ፍቃችሁታልና እንዲህ ያደርጋል ስትባሉ ለመሳለቅ ጥርሳችሁ የሚገጥባችሁ እምነት የለሽ የጨለማ ትውልዶች ትበዛላችሁ። ◉◉◉ ያልተባለውን ተባለ ብሎ መዘገብ፣ መንጫጫት፣ መክሰስ ከአንድ ጤነኛ አዕምሮ ካለው ሰው ስለማይጠበቅ ነው የመጥፎ ሀሳብ መፍለቂያ አዕምሮ ያልኩ። ያልተባለውን የሚሰማ ጆሮ 'ጤነኛ ጆሮ' አይደለምና ብታክሙ አክሙት ባታክሙት ግን አትመኑት። ለነገሩስ የሥጋ ጆሮ የተባለውን ቢሰማ ልብ ካላዳመጠ ለባለቤቱ ባዳ ነው። ረብ ጥቅም የለውና ሳንናገር በልባችን አስተውለን ብንሰማ ሳንናገር በአዕምሯችን ብናመላልሰው እንዴት ለጥቅም በሆነልን ነበር። ውላችን፡ መፍቻ ማሰሪያችን የጠፋብን ቋጠሮ የተበተበን ትውልዶች አይደለንም ትላላችሁ !? ◉◉◉ ይሁንና ቀድመን እንዳብራራነው "ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን" በሚል ርዕሰ ላለፉት 15 ዓመታት ለአዳም ዘር በሙሉ ሲሰራጭ የኖረው መልዕክት "የበረኸኞቹ ፣ የገዳም አባቶች..." መልዕክት ነው አልተባለምና "ተብሏል" ብላችሁ የምትሟገቱ ጆሯችሁ አንደበታችሁም ጭምር አጠፋችሁ እንጂ ስላልጠቀማችሁ አትመኑት። እውነት ነው ይህንን የእግዚአብሔር እውነት ያጸኑ በየገዳማቱ፣ በየበረሃው፣ በየገደሉ የወደቁ የእግዚአብሔር ባሮች ሞልተውናል። መልዕክቱን ሰምተውም ይሁን በጸጋ እግዚአብሔር ተገልጦላቸው ተረድተውት እውነት ነው ብለው የሚመሠክሩም ቀን የሚጠብቁም ብዙ እውነተኛ ገዳማዊያን አበው ወእመዉ አሉን። በረከታቸው ጸሎት ልመናቸው ለእኛም ትድረስልንና የኢትዮጵያን ትንሣኤ የሚያስተምሩ እውነተኛ አባቶች በየበረሃውም በየደጋውም በተጋድሎ ጸንተው አሉ። ነገር ግን ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልዕክት ጸሐፊዎች፣ በድምጽም የሚተርኩልን አባታችን ከእኒህ ጋር በሐይማኖት ሕብረት አንድ ሆነው በመኖሪያ ቦታ ግን አንድ የሆኑ አይደሉም። የመልዕክቱ አስተላላፊ አባቶች እግዚአብሔር በወሰነላቸውና ባጸናቸው ሥፍራ ሆነው በዓለም ሁሉ እየሆነ ያለው የሚታቀድ የሚፈተፈተውን በእግዚአብሔር ገላጭነት እየተረዱ እንዲህ በሉ ይህንን አድርጉ ሲባሉ የሚያደርጉ ለመጪውም የኢትዮጵያ ትንሣኤ ዘመን አዋላጅና ዋና ነገሥታት ናቸው፡ የመልዕክቱ ጸሐፊ አባትም ለዘመናት ሣልሳዊ ቴዎድሮስ በመባል በሕዝቡና በቤተክርስቲያናችን እውነተኛ አገልጋዮች ዘንድ የሚጠበቁ ደጉ ንጉሥ ስልጣነ ክህነታቸውን ያለ ጉድፍ ጠብቀው የሚገኙ አባት ናቸው እንጂ በብዙዎች ዘንድ እንደሚታሰበው እገሌ የሚባል ገዳም ውስጥ ሆነው በምንኩስና ሕይወት ሆነው በተጋድሎ እንዳሉት አባቶቻችን ያሉ አይደሉም። የምትሰሙትን ልብ አድርጋችሁ አድምጡ! ከዚያ አዕምሯችሁ ያመላልሰው! ተረዱትና ተናገሩት። ይህ ሲሆን ብቻ ነው ጤነኛነታችሁ የሚረጋገጥ እንጂ በግልብ ሐሳብ፣ በግልብ ምኞት ተመርኩዛችሁ "...እንዲህ መሰለኝ እንዲህ ነው ይባላል እንዲህ ነው አሉ..." እያላችሁ ገደል ገብታችሁ ሌላውንም ገደል አትክተቱ። እውነታው ይኸው ነው። የገዳም አባቶች መልዕክት ያስተላልፋሉ ወይ? አዎ ያስተላልፋሉ። አሁን ያሉት እውነተኞችም ሐሰተኞችም አባቶችኮ የሚጠቅምም ይሁን የማይጠቅም ሐሳብ ሲያስተላልፉ ሁላችሁም እየሰማችሁ ነው። አንዳንዶቹ በፖለቲካው ታንቀው እንዲህ ይሁን እንዲያ ይሁን ሲሉ ሌሎቹ ደግሞ በእውነተኛ የአገርና የወገን ፍቅር ተመሥርተው እንዲህና እንዲያ ይሁን ሲሉ ይሰማሉ። ነገር ግን እኛ በተደጋጋሚ የምንከሰስበት "የበረኸኞቹ ፣ የገዳም አባቶች መልዕክት ነው ይላሉ" የሚለው የውሸት ክስ (የሐሰት ፕሮፓጋንዳ) የእኛን እውነት፣ የእኛን ግብር (ተግባር)፣ የእኛን መገኛ የማይወክል መሆኑን ሁላችሁም እንድታውቁትና ያልተባለውን እንደተባለ አድርገው ለሚያናቁሩ ቦታና ጆሯችሁን እንዳታውሱ ለማሳሰብ ጭምር የተሰጠ መልስ ነው። እግዚአብሔር አምላክ እውነተኞችን ገዳማውያን አባቶችና እናቶቻችንን በእድሜ በጸጋ ይጠብቅልን፣ አገራችንን ኢትዮጵያንና እውነተኛ ኢትዮጵያዊያኑን ሁሉ ይጠብቅ ! አሜን ! አልፋና ዖሜጋ ዘተዋሕዶ ፲፬/፱/፪ሺ፲፫ዓ.ም t.me/AlphaOmega930
Show all...
አልፋና ዖሜጋ ✟

◈ምስክርነታችን ለተዋሕዶና ለኢትዮጵያ ትንሣኤ ነዉ! ➘ ▰✥ ◦ኢትዮጵያ #የሥላሴ የክብራቸዉ መገለጫና መመስገኛ ምድር ▰✥ ◦ኢትዮጵያ ርስተ #ድንግል_ማርያም ▰✥ ◦ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን ▰✥ ◦ኢትዮጵያ የዓለሙ ገዢ ◍የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነት የዓለም ሁሉ መዳኛ ናት። ▢➤ ዛሬ ንስሓ እንግባ! ➴ †ቻናል➲ @christian930 †ግሩፕ➲ @AlphaOmega930 ➩📩➝ t.me/EthioBirhan