cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking ÂŤAccept allÂť, you agree to the use of cookies.

avatar

📚ከልቦለድ አለም 📚

🚩 Channel was restricted by Telegram

Show more
The country is not specifiedThe language is not specifiedThe category is not specified
Advertising posts
12 471
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

አልቀርም """""""""" ከሩቅ ተቀምጠሽ ኮቴዬን ጠብቀሽ በናፍቆት አለንጋ፥ልቦናሽ ተገርፎ፤ እያገላበጠ ጉጉት ምን ቢያነድሽ ውስጥሽ አይከፋ፥አይቀየም ደርሶ... እኔ እየመጣሁ ነው ስችል አፈትልኬ፥ ቢያቅት በእንብርክኬ፥ ብወድቅ ተንፏቅቄ፥አልቀርብሽ ከቶ፤ ቢዘገይ ነው እንጂ ፍቅር እየገፋው፥ሰው አይቀርም ታክቶ! #አልቀርም_መጣለሁ አብርሃም ፍቅሬ (የቅዳስ ልጅ) ከወደዱት ለወዳጅዎ ያጋሩት!
Show all...
/// ናርዶስ /// ======================== ቀን ፈቅዶ አካሌ ከአካሏ ቢርቅም የናፍቆት ጉዞአችን ከፍጻሜ ሳይደርስ ለአመታት ቢዘልቅሞ ክፍተት ጎዶሎአችን እያደር ቢሰፋ ከአምናው ቢተልቅም ፍቅር ደግነቷ ትዝ ትዝ ይለኛል ከአይኔ ጠፍቶ አያቅም እሷ የናርዶስ ሽቱ አንዴ ከተቀቧት መዐዛዋ አይለቅም ! By ኪዮርና ከወደዱት ለወዳጅዎ ያጋሩት!
Show all...
የሌት ማሕሌት (በእውቀቱ ስዩም) ትንሽ ቆየት ብሎ ፥ ኮረንቲው ይጠፋል እሱን ተከትሎ፥ደምኖ ያካፋል ከናፍቆትሽ በቀር፥ ሁሉ ነገር ያልፋል :: አሁን መብራት ጠፋ ፥ ተረኛ ነን አይደል ቁና ይዠ ቀረብሁ፥ ጨለማ ሲታደል ፤ እያገላበጠ ብቻነት አመሰኝ፥ “ ዝናቡ እየጣለ ጋራ ጋራውን ጎርፍ ያመጣሽ ‘ንደሁ ልጠብቅ ጎርፉን “ የሚል እንጉርጉሮ፥ በድንገት ታወሰኝ :: ግን ይሄ ትውስታ አራራይ ትዝታ ለቆሰለው ልቤ፥ መዳኒት አልሆነም ያባቶቼ ዘፈን፤ ለኔ አልተዘፈነም፤ ማዶ ዝናብ ዘንቧል፤ ዶፉን ተከናንቧል- -እንጦጦ-ዲልዲላ በገፈጅ ይመስል ፥ቀበናም ቢሞላ ምንም አያመጣም፤ ከ’ድፍ ውሀ ሌላ እሳት ነው ፍጥረትሽ፥ ከውሃ ጋ አትኖሪም አንቺ መብረቅ እንጂ፥ ጎርፍ አትሳፈሪም:: ( አዳምኤል) ከወደዱት ለወዳጅዎ ያጋሩት!
Show all...
መስታውት ቅን ነው ማንነት አይደብቅ ቁልጭ አርጎ አሳየኝ ደጋግሜ ስስቅ። ከሳቄም ቡሃላ ከደስታዬም ቡሃላ እጅግ ያመረረ አንድ ሰው አሳየኝ ከአይኖቹ ኮሮጆ እንባ የቋጠረ። ብሶት የወለደው ህይወት የቀፈፈው ለመኖር የሚጥር የሆነ ሰው ታየኝ ከቆምኩበት ሆኜ ከመስታወቱ ስር። እኔው ነኝ እንዳልል እግሬም እሄው ሸሸ ምን ተሻለ ታድያ መስታውት ካልዋሸ ?! ✍️በረከት_ሐ ከወደዱት ለወዳጅዎ ያጋሩት!
Show all...
🍂🍂🍂🍂🍂 ጥርት ያለው ሰማይ ከውሃው ጋር ተመሳስሎ ውሃውም ልክ እንደሰማዩ ሰማያዊ ሆኗል። ጥቂት ጀልባዎች በዛፎች በተከበበው ሀይቅ ላይ ሰንበታቸውን በመዝናናት የሚያስላፉ ሰዎችን ይዘው ወዲህ ወዲያ ይላሉ። አየሩ ከፀጥታው እና ከጥቂት ወፎች ጫጫታ ጋር ተዳምሮ ለነፍስ ሀሴትን ይሰጣል። በተመስጦ ሀይቁ ዳር ቁጭ ብዬ በጄ ውሃውን ነካ ረጨት እያደረኩ ሳምንታት ያላየሁትን ፍቅሬን እያሰብኩ ነው። ስወደው ከልቤ ነው... ሳፈቅረው ከአካሉ የበለጠ ነፍስያውን፣ ማንነቱን ጥንካሬውን፣ ድክመቱንም ጭምር ነው። ለደቂቃዎች ከአጠገቤ ሲርቅ ነፍሴ ነፍስያውን ትናፍቃለች። እያንዳንዱ አካሌ ተነቅሎ የተዝረከረከ ይመስለኝና በክንዶቹ ተሰብስቤ መታቀፍን እናፍቃለሁ። እይኔ መምጫው መንገድ ላይ ቡዝዝ ብሎ ይቀራል። ከንፈሬ ከናፍርቶቹን አካሌ አካሉን ይራባል። አንዳንድ ጊዜ ደግሞ ለቀናት ከአጠገቤ ርቆ እንኳን አሁን ስሞኝ የሄደ ይመስል የከንፈሩ ትኩሳት ከናፍርቶቼ እና ጉንጮቼ ላይ ይሰማኛል። የንግግሩ ድምፀት ደጋግሞ በጆሮዬ ያቃጭላል። እቅፌ ውስጥ ያለ ያክል ጠረኑ አፍንጫዬን ያውደዋል። አሁንም እየተሰማኝ ያለው ስሜት ያ ነው። ካየሁት ሳምንታት ቢያልፉኝም እንደሌላው ጊዜ በናፍቆቱ አልተብሰከሰኩም። አጠገቤ ያለ ያቀፍኩት ይመስል ፊት ለፊቴ እንዳለው ሀይቅ ስሜቴ ተረጋግቷል። " እንዴት ግን ይህን ያክል ልወደው ቻልኩ" እያልኩ ከማልመልሰው ጥያቄ ጋር ስፋጠጥ ትኩስ ከንፈር አንገቴ ላይ አረፈ፣ ቶሎ አልተነሳም ምጥጥ አድርጎ ሳመኝ። አልደነገጥኩም በኔ አካል ላይ ድፍረቱም ስልጣኑም ያለው የኔ መልዓክ የልቤ ግማሽ ብቻ ነዋ። እንደውም አይኔን ጨፈንኩና ስሜቱን በተመስጦ አጣጣምኩት። ከተቀመጥኩበት ተነስቼ ለማቀፍ እጄን ዘርግቼ ፊቴን ሳዞር.... የኔ መልዓክ ራቅ ብሎ ቆሞ እያየኝ ነው። አጠገቤ ደግሞ "አንቺ የኔ ባትሆኝ እንኳን የማንም እንድትሆኚ አልፈቅድልሽም" እያለ ለዘመናት ሲዝትብኝ የነበረው ብሩክ ቆሟል። ለማቀፍ የተዘረጋ እጄ በድንጋጤ እንደተንከረፈፈ ብሩክ መጥቶ ተጠመጠመብኝ... እጄ እንደዛው ነው አላቀፈውም አልገፋውምም። የኔ መልዓ ፊቱን አዞረ፣... አንድ እግሩን አነሳ፣.... ሌላኛውን ደገመው.... እየሄደ ነው። እቅፉ ውስጥ ያስገባኝን ብሩክን የኔ ባልሆነ ሀይል ገፈተርኩት ሳሩ ላይ በጀርባው ተዘረረ... በቻልኩት አቅም ወደ ፍቅሬ ሮጥኩ..... የልቤ ግማሽ ወደኋላ ሳይዞር እየሄደ ነው። ድምፄን ከፍ አድርጌ ስሙን ጠራሁት... አልዞረም። እንደውም ፍጥነቱን ጨምሮ ወደፊት ገሰገሰ። አይቀጥልም። ✍ ፀሀፊ ፅዮን በየነ ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨ ቻናላችንን ይቀላቀሉ👇👇 @itsmetsiyearsemalj @itsmetsiyearsemalj ♥♥♥♥♥❤️❤️
Show all...
ሀሣብ አስተያየት በ @mintua27 ላይ ይላኩልን
Show all...
ውድ የቻናላችን ተከታዮች ሠሞኑን በአዲስ መለክ ልቦለዶችን እንጀምራለን
Show all...
😘አለሜ ነሽ😘 🔥ክፍል 14 ✍️ደራሲ፦ቤዛዊት ፋንታዬ የሽዋ ልጅ "" "" ምን መሰለሽ "በህይወትጉዞ ውስጥ የምታፈቅሪው ሰው አንድ ብቻ ነው ፍቅር የፈጣሪ ስጦታ ነው ደስ የሚል ግዴታ ፈጣሪ የህይወታችንን አጋር እንድናፈቅር ግዴታ አስተላልፎብናል ደስ የሚል ግዴታ በእዚህ ግዴታ ውስጥ መናፈቅ፣ መጨነቅ ፣ማስብ ፣ማልቀስ፣ ማዘን በጣምም መደስት ፣በጣም ማዘን በፍቅር ውስጥ የሁሉም ሰው ልብ ስስ ነው ። አንድ ሰው ብዙ ሰው ይወዳል አንድ ሰው ያፈቅራል የሚወደውን መጥላት ይቻላል። በመውደድ ውስጥ ሁለት ልቦች ሁለት ናቸው። በማፍቀር ውስጥ ደሞ ሁለት ልቦች አንድ ናቸው። ከምናፈቅርው ሰው ጋር የምንጣላውም፦ ለምን አልበላክም፤ ለምን አልጠጣክም ፤ለምንስ ነው ብርድ ሆኖ ሳለ ጃኬት የማትደርበው ፤እየበላክ ከሆነ ቢያንቅህስ ለምን ውሀ አጠብክ አላስቀመጥክም ፤መንገድ ተጠንቅቀክ ሄድ ፤ ፍቅር ዛሬ እኔ ነኝ ምሳ የምጋብዝክ፤ ራስክን ጠብቅ ፤ሲሆን የሚወድሽ ሰው ደሞ ሲሆን፦ ለምንድን ነው ይህንን ያልስራክልኝ፤ ለምድነው ምሳ የማትስጠኝ ፤ስበላ ቢያንቀኝስ ለምድነው እንደ ሌላ ቀኑ የማትንከባከበኝ ነው የሚለው። ሰው ሰውን ለመውደድ ምክንያት ይፈልጋል ጥቅም ይፍልጋል ። ፍቅር ግን ከምክንያት የፀዳ ነው የሚወደን ሰው እንዲወደን ያርገውን ነገር ሲያጣ ይርቀናል ከዛም አልፎ ይጠላናል። ያፈቀርን ግን ያፈቀርን ያለ ምክንያት ስለሆነ በጭራሽ አይጠላንም። ሰው ውስጣችን ሲገባ ፍቅር ይሁን መውደድ የምናቀው እራሳችንን በማዳመጥ ነው። ይህ ሰው ምኑ ነው የሳበኝ ብለሽ እራስሽን ስትጠይቂ የሳበሽን ነገሮች መዘርዘር ከቻልሽ እሱ መውደድ ነው። ምክንያቱም ቅድም ያልኩሽን አስታውሺ ነገር ግን ለእራስሽ ይህ ሰው ምኑ ነው የሳበኝ? ስትይ መልስ የምታጪ ከሆነ እሱ ፍቅር ነው ጊዲዮን የመጣ እለት ከሄደ በኋላ ስለ ሄዋን ላንቺ ማውራትን የመርጠው እኔ ሳልሆን ልቤ ነው ያዘዘኝ። በፍቅር ምርኮኛ ሆኖ በልብ መታዘዝ እጅክ ያስደስታል " ሲል ዲና በጣም ተመስጣ ከሰማች በኋላ "ዋውውው በጣም በሚገርም ቃላት እና ማብራሪያ ጋር በሚገባኝ መልኩ ነው ያስርዳከኝ " ስትል አዳም ምንም አደል አላት ። "አሁን ሁለት ጥያቄዎች እጠይቅሻለው" አለ ዲናም "እሺ "አለች ፈጠን ብላ የሆነ ሹል ነገር ላይ ድቡልቡል ነገር ማስቀመጥ ትችያለሽ? ዲና ፈጠን ብላ" አይ አይ እንዴት ሆኖ"አለች አዳምም ፈገግ ብሎ "ፍቅር ያልያዘው ልብ እንዲ ነው ያቅበጠብጠዋል። ያንቺን ልምር፤ አይ አይ ይህቺ ትሻላላለች። እያለ ይቆይና በስተመጨርሻ ፍቅር ሲይዘው ሹሉ ነገር ተነስቶ ድቡልብሉን ነገር ማስቀመጥ የሚችል ነገር ሲመጣ ድብልብሉ ነገር እርፍ እንደሚለው። ልብም እርፍ ይል እና አፈቀርኳቸው ላላቸው ሰዎች ነበርው ስሜት መውደድ እንጂ ፍቅር እንዳልነበር ይርዳል" አለና ኡፍፍፍፍፍ አለ ዲና በአግራሞት ቀና ብላ ፈገግ እያለች በተቆራረጠ ድምጽ "እሺ ሁለተኛውስ " አለች አዳምም አቀርቅሮ እያያት" ስላንቺ ማወቅ ከተቻለ ብትነግረኝ ደስ ይለኛል "አለና ያቀርቀር አንገቱን ቀና አደርገ ዲና "ስለ እኔ ስለእኔ ምን ልንገርክ እንዳንተ መሳጭ ታሪክ የለኝም" ስትለው አዳም ፍጠን ቀልጠፍ ብሎ "መቼም ማንም ሰው ያለ ታሪክ አይኖርም አደል" አላት ዲናም እንደመፈገግ እያለች "እእእ ያው እኔ ተወልጄ ያደኩት ድሬደዋ ሳፕያን በምትባል ስፈር ነው እድሜ ለትምሕርት ሲደርስ ቤተስቦቼ ሀብታም ስለነበሩ ጥሩ ትምህርት ቤት ገባው ከዛም እስከ 6ተኛ ክፍል ከተማርኩኝ በኋላ አቋርጥኩት" ስትል አዳም "ለምን? "አላት። እሷም የሆነ ሀዘን የረጨው ፊት እያሳየችው "ምክንያቱም አባቴ በነበርበት የስኳር በሽታ በድንገት ሞተ ከዛም እኔ እና እናቴ ብቻ ቀረን አባቴ ከብዙ ባንኮች ለስራ ማስኬጃ ብሎ ተበድሮ ነበር ተባለና ተወራ እኔም ሆንኩኝ እናቴ ግን በጭራሽ አናቅም አባቴ የሞተው በሰው ተገሎ ነው ይባላል ግን ሞቶ ሲገኝ ምንም አይነት አሻራ ስላልተገኘ እና በሚሰራበት ቢሮ ወንበር ላይ ተቀምጦ ጠረቤዛ ላይ ተደፍቶ ነበር። ከዛ ሀዘናችንም ሳይወጣልን አባቴ የተበደርው ብር ስላለበት እና ጊዜው ስላለፈ በሚል የነበሩን ነገሮች አንድም ሳይቀር ተሸጠ የቀረው ቤታችን ነበር እሱንም ትንሽ ቆይቶ የተሸጠው እቃ እዳውን አልከፈለም ብለው ቤታችንን ሽጠው የቤታችንን አንድ አራተኛ ብር ሰጡን እና ሌላውን ወስዱት እናቴ በብስጭት እና በጭንቀት አልጋ ላይ ዋለች እኔም ትምርቴን አቋርጬ እናቴን ማስታመም ጀመርኩኝ ከቤታችን በቀረው ብር አነስተኛ እና በጣም ትንሽ ቤት ተከራየን ግን ይህ ብር ብዙ አላቆየንም አለቀ። ከዛም እናቴ መንቀሳቀስም ስላቃታት እኔ ጎረቤቶቻችን አዋጥተው ለስራ ብለው በስጡኝ ብር መንገድ ላይ ምግብ መሽጥ ጀመርኩኝ ቢሆንም ግን ለእናቴ መሆን አልቻልኩም እኔ የምስራው ለእለት ምግብ እንጂ ለእናቴ ህክምና አልሆነም እናቴን የኔን ህይወት በእዚህ መሀል ነበር ዳግመኛ ላታየኝ ላላያት ያሽለበችው። እኔ ስልችቻት ነው? ወይስ ተገዳ እንጃ ብቻ የሚወዱትን ማጣት ምን ያክል እንደሚከብድ አቀዋለው ለእዛም ነው አንተ ስትጎዳ ማየት ያቃተኝ እና ላፅናናክ የወስንኩት"። "በህይወታችን ውስጥ ህይወታችን አድርገን የሾምነውን ሰው ማጣት ውስጥ ያለውን ስቃይ አውቀዋለው ልክ እንዳንተ ልናጣው ሲመስንም የሚስማንን ጭንቀት እናቴ ሳትሞት በፊት በጣም ሲያማት ላጣት ነው ብዬ የተስማኝን " "የሆነ ቀን ቤት ስገባ እናቴ ፍራሽ ላይ ጥቅልል ብላ ተኝታለች እራታችንን እንደተለመደው አቅርቤ ስቀስቅሳት ግን እንደ ሊላ ቀኑ አልተነሳችልኝም። በጣም ጮክ ብዬ ብጠራትም አቤት አላለችኝም አበድኩ ልክ እንደ እብድ አረገኝ እናቴ ከእዚህ በኋላ ከጎኔ እንደማትሆን ስርዳ ፤ከእዚህ በኋላ ስመርቅ ከትምህርት ቤት ሽልማት ሳገኝ ፣ስጨነቅ፣ ስደሰት አጠገቤ እንደማትሆን ሳስበው ውስጤን አመመኝ አልቻልኩም በቃ አልቻልኩም። ጎረቤት ተሰበሰበ እናቴን ገናዥ ጠርተው አስገነዟት ከዛም በቃ በነጋታው ተቀበረች እንደ ዋዛ እንደቀልድ እናቴን አጣዋት"። "ለቅሶ ካለፈ በኋላ ብቻዬን ለ3ወራት ኑሮ በማይባል መልኩ ኖርኩኝ። ቤተስብ እና ብዙ ነገር አጥቼ። ከዛም ማታ ከስራ ስመለስ አክስቴ መጥታ ወደ አዲስ አበባ እወስድሻለው ብላኝ በነጋታው ያለኝን እቃ ሽጠን ወደ እዚህ አመጣችኝ አክስቴ ስልጧኗን ለእኔ ለማሳየት የተቻላትን አደርገች እኔም ጠንክሬ መማር ጀመርኩኝ። የማታ ትምህርት አስገባችኝ። ቀን ለእሷ ለባሏ እና ለልጆቿ መገልገያ ነኝ። "ማታ ከትምርት ስመለስም እንደዛው። እኔ ግን ከስራዬ ስአት መቀነስ ባልችልም ከእንቅልፌ ቀንሼ አጠና ነበር። መብራት ይቆጥራል ለሊት አታብሪ ስለምትለኝ በርንዳ ወጥቼ በባትሪ እያጠናው ተማርኩኝ። " ልጆቹ ሲያጠኑ ምንም አትልም ለእኔ ግን በቃ ተወዉ ብቻ "አለችና እንባዋን ዘርገፈችው አዳምም አለቀሰ ከዛም "አሁን የት ነው ያለሽው" አላት ዲናም" አሁንማ በቃኝ ብዬ ቤቶን ትቼላት ከወጣው 6ወር ሆነኝ ጓደኞቼ ናቸው ለቤት ክራይ የከፈሉልኝ እቃም ያሞሉልኝ ያው ሀብታም ጓደኞች ነው ያሉኝ "ብላ ፈገግ አለች። "እኔ ደሞ ለጊዜው ስራ እየፈለኩኝ ነው" አለች።አዳም ፈጠን ብሎ
Show all...
ትከሻና ትከሻዋን ይዞ" አይዞሽ ከእዚህ በኋላ አይቸግርሽም አንቺ ስው ስለማጣት ስለምታቂ እረድተሽናል እኔም እረዳሻለው አንቺን ባረዳሽ ፈጣሪም ይቅር አይለኝም እቃዎችሽን ሽጫቸው ሻንጣሽን ብቻ ይዘሽ እኔ ጋር ነይ እኔ እርዳሻለው "።አላት ዲና ጆሮዋን ማመን ተሳናት አዳም ነገ ሻንጣዋን ይዛ እንድመጣ ነገራት ከሄዋን እና ከእሱ ጎን ሁሌም እንደምትሆን ቃል ገባችለት። ዲና አዳም ያቀርበላትን ሀሳብ ያለ መግደርደር መቀበልዋ የድሬ ልጅ እንደሆነች አሳብቆባታል። ዲና ደስስስ ብሏት አዳምን አቀፈችው እና እጁን እያገላበጠች ሳመችው አለቀስች አዳም ስላስደሰታት ደስስስ አለው ነገ ቤቱን እንደሚያሳያት ነገራት በድንገት የአዳም ስልክ አቃጨለ የሄዋን የቀድሞ ዶክተር ነበሩ። ✨ይቀጥላል.... ╔═══❖•📚📚•❖═══╗ https://t.me/lebwel ╚═══❖•📚📚•❖═══╝ 4 any comment @mintuwa_19 ❥❥________⚘_______❥❥
Show all...