en
Feedback
Alamura Seventh Day Adventist Church , Hawassa (የሀዋሳ አላሙራ 7ኛ ቀን አድቬንቲስት ቤተክርስቲያን)

Alamura Seventh Day Adventist Church , Hawassa (የሀዋሳ አላሙራ 7ኛ ቀን አድቬንቲስት ቤተክርስቲያን)

Open in Telegram
1 197
Subscribers
+124 hours
-17 days
-630 days
Posts Archive
እንኳን ለአድሱ ዓመት ዋዜማ ጌታ በሰላም አደረሳችሁ። ይህንን ምክንያት በማድረግ ስላደረገልን ነገር ለእግዚአብሔር ምስጋና ለመስጠት ፣በቀጣይም ስላለው ነገር ወደ እግዚአብሔር ምልጃ ለማቅረብ ቤተክርስ
እንኳን ለአድሱ ዓመት ዋዜማ ጌታ በሰላም አደረሳችሁ። ይህንን ምክንያት በማድረግ ስላደረገልን ነገር ለእግዚአብሔር ምስጋና ለመስጠት ፣በቀጣይም ስላለው ነገር ወደ እግዚአብሔር ምልጃ ለማቅረብ ቤተክርስቲያን ሳምንቱን በፀሎት እያሳለፈች ትገኛለች። ፕሮግራም መርሃግብር ከሰኞ እስከ አርብ ጤዋት 1:00 ሰዓት - 6:00 ሰዓት ድረስ ማታ ደግሞ 12:00 ሰዓት -2:00 ሰዓት ባለዉ ጊዜ ልዩ የትምህርት ጊዜ የእናንተን መምጣት ይጠብቃል። ስለሆነም ከላይ በተጠቀሰው ሰዓት በቤተክርስቲያናችን በመገኘት የበረከቱ ተካፋዮች እንድትሆኑ በጌታ ፍቅር እንጋብዛችኋለን። ተባረኩ!

ከመጠን በላይ ማሰብን በጤና ሳይንስ አተያይ ስንመለከት፣ አንድ ሀሳብ በተደጋጋሚ መመለስ—በተለይ ሊፈታ የማይችል ያለፈ ነገር ወይም ያልተከሰተ የወደፊት ነገር—ከጭንቀትና ከውጥረት ጋር ሊያያዝ ይችላል። 🧠 1. አእምሮ ላይ የማያቋርጥ ጭንቀት አእምሮ ሁልጊዜ “ችግር አለ” ብሎ እንዲጠባበቅ ሊያደርገው ይችላል። ይህም የአእምሮ ድካም፣ ትኩረት መቀነስ እና ውሳኔ መስጠት መከበድ ሊያስከትል ይችላል። 😟 2. ጭንቀት (Anxiety) Overthinking እና anxiety ተመሳሳይ አይደሉም፣ ግን እርስ በርሳቸው ሊያጠናክሩ ይችላሉ። ብዙ ጊዜ “ቢሆንስ?” የሚል ሀሳብ መደጋገም ጭንቀትን ሊጨምር ይችላል። 😴 3. የእንቅልፍ ችግር አእምሮ በሌሊት ሀሳብ ማቆም ካልቻለ መተኛት ሊዘገይ ወይም እንቅልፍ ሊቋረጥ ይችላል። የእንቅልፍ እጥረት ደግሞ ትኩረትንና ስሜትን ሊጎዳ ስለሚችል የ“ማሰብ → እንቅልፍ ማጣት → የበለጠ ማሰብ” ዑደት ሊፈጠር ይችላል። 💓 4. በሰውነት ላይ የሚታዩ የStress ምልክቶች የረጅም ጊዜ ውጥረት የሰውነትን stress response ሊያነቃቃ ይችላል። ይህም፦ የልብ ምት መጨመር ፈጣን መተንፈስ የጡንቻ መጠንከር ላብ የሆድ/የምግብ መፍጫ መረበሽ ራስ ምታት ያሉ ምልክቶችን ሊያመጣ ይችላል። 🧬 5. የStress hormones ሚና ሰው በተደጋጋሚ ሲጨነቅ ሰውነቱ እንደ cortisol እና adrenaline ያሉ የstress ሆርሞኖችን ይጠቀማል። ይህ ለአጭር ጊዜ ሰውነትን ለአደጋ ለመዘጋጀት ጠቃሚ ቢሆንም፣ የረጅም ጊዜ ውጥረት ግን በጤና ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ ሊኖረው ይችላል። 🫀 6. የልብና የደም ሥርዓት ረጅም ጊዜ የሚቆይ ከፍተኛ stress ከደም ግፊት መጨመርና ከሌሎች የልብና የደም ሥር ችግሮች ጋር ግንኙነት አለው። ይህ ማለት overthinking ብቻውን የልብ በሽታ ያመጣል ማለት አይደለም—stress ከሌሎች የጤና ምክንያቶች ጋር ይሰራል። 🛡️ 7. የሰውነት መከላከያ ሥርዓት ረጅም ጊዜ የሚቆይ stress የimmune system ሥራን ሊነካ ይችላል። ስለዚህ በቂ እንቅልፍ፣ ጤናማ ምግብ፣ እንቅስቃሴና የstress አስተዳደር አስፈላጊ ናቸው። 🍽️ 8. የምግብ መፍጫ ሥርዓት አእምሮና የምግብ መፍጫ ሥርዓት በgut–brain axis በኩል ተያይዘዋል። Stress በአንዳንድ ሰዎች የሆድ ህመም፣ ማቅለሽለሽ፣ የምግብ ፍላጎት መቀየር ወይም የሆድ መንቀሳቀስ ላይ ለውጥ ሊያመጣ ይችላል። 😔 9. የስሜት ጤና በተደጋጋሚ የሚከሰት rumination—ያለፈ ነገርን በተደጋጋሚ መመለስና መተንተን—ከድብርትና ከጭንቀት ምልክቶች ጋር ሊያያዝ ይችላል። ⚠️ አስፈላጊ ልዩነት ማሰብ ራሱ መጥፎ አይደለም። ችግር የሚሆነው ሀሳቡ ቁጥጥር ሲያጣ፣ እንቅልፍህን/ትምህርትህን/ዕለታዊ ሕይወትህን ሲያስተጓጉል ነው። በአጭሩ፦ Overthinking Stress/Anxiety እንቅልፍ  ትኩረትና ስሜት  የበለጠ ማሰብ የሚል ዑደት ሊፈጠር ይችላል።

Repost from N/a
ከመጠን በላይ ማሰብን በጤና ሳይንስ አተያይ ስንመለከት፣ አንድ ሀሳብ በተደጋጋሚ መመለስ—በተለይ ሊፈታ የማይችል ያለፈ ነገር ወይም ያልተከሰተ የወደፊት ነገር—ከጭንቀትና ከውጥረት ጋር ሊያያዝ ይችላል። 🧠 1. አእምሮ ላይ የማያቋርጥ ጭንቀት አእምሮ ሁልጊዜ “ችግር አለ” ብሎ እንዲጠባበቅ ሊያደርገው ይችላል። ይህም የአእምሮ ድካም፣ ትኩረት መቀነስ እና ውሳኔ መስጠት መከበድ ሊያስከትል ይችላል። 😟 2. ጭንቀት (Anxiety) Overthinking እና anxiety ተመሳሳይ አይደሉም፣ ግን እርስ በርሳቸው ሊያጠናክሩ ይችላሉ። ብዙ ጊዜ “ቢሆንስ?” የሚል ሀሳብ መደጋገም ጭንቀትን ሊጨምር ይችላል። 😴 3. የእንቅልፍ ችግር አእምሮ በሌሊት ሀሳብ ማቆም ካልቻለ መተኛት ሊዘገይ ወይም እንቅልፍ ሊቋረጥ ይችላል። የእንቅልፍ እጥረት ደግሞ ትኩረትንና ስሜትን ሊጎዳ ስለሚችል የ“ማሰብ → እንቅልፍ ማጣት → የበለጠ ማሰብ” ዑደት ሊፈጠር ይችላል። 💓 4. በሰውነት ላይ የሚታዩ የStress ምልክቶች የረጅም ጊዜ ውጥረት የሰውነትን stress response ሊያነቃቃ ይችላል። ይህም፦ የልብ ምት መጨመር ፈጣን መተንፈስ የጡንቻ መጠንከር ላብ የሆድ/የምግብ መፍጫ መረበሽ ራስ ምታት ያሉ ምልክቶችን ሊያመጣ ይችላል። 🧬 5. የStress hormones ሚና ሰው በተደጋጋሚ ሲጨነቅ ሰውነቱ እንደ cortisol እና adrenaline ያሉ የstress ሆርሞኖችን ይጠቀማል። ይህ ለአጭር ጊዜ ሰውነትን ለአደጋ ለመዘጋጀት ጠቃሚ ቢሆንም፣ የረጅም ጊዜ ውጥረት ግን በጤና ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ ሊኖረው ይችላል። 🫀 6. የልብና የደም ሥርዓት ረጅም ጊዜ የሚቆይ ከፍተኛ stress ከደም ግፊት መጨመርና ከሌሎች የልብና የደም ሥር ችግሮች ጋር ግንኙነት አለው። ይህ ማለት overthinking ብቻውን የልብ በሽታ ያመጣል ማለት አይደለም—stress ከሌሎች የጤና ምክንያቶች ጋር ይሰራል። 🛡️ 7. የሰውነት መከላከያ ሥርዓት ረጅም ጊዜ የሚቆይ stress የimmune system ሥራን ሊነካ ይችላል። ስለዚህ በቂ እንቅልፍ፣ ጤናማ ምግብ፣ እንቅስቃሴና የstress አስተዳደር አስፈላጊ ናቸው። 🍽️ 8. የምግብ መፍጫ ሥርዓት አእምሮና የምግብ መፍጫ ሥርዓት በgut–brain axis በኩል ተያይዘዋል። Stress በአንዳንድ ሰዎች የሆድ ህመም፣ ማቅለሽለሽ፣ የምግብ ፍላጎት መቀየር ወይም የሆድ መንቀሳቀስ ላይ ለውጥ ሊያመጣ ይችላል። 😔 9. የስሜት ጤና በተደጋጋሚ የሚከሰት rumination—ያለፈ ነገርን በተደጋጋሚ መመለስና መተንተን—ከድብርትና ከጭንቀት ምልክቶች ጋር ሊያያዝ ይችላል። ⚠️ አስፈላጊ ልዩነት ማሰብ ራሱ መጥፎ አይደለም። ችግር የሚሆነው ሀሳቡ ቁጥጥር ሲያጣ፣ እንቅልፍህን/ትምህርትህን/ዕለታዊ ሕይወትህን ሲያስተጓጉል ነው። በአጭሩ፦ Overthinking Stress/Anxiety እንቅልፍ ትኩረትና ስሜት የበለጠ ማሰብ የሚል ዑደት ሊፈጠር ይችላል።

🌿 ሳምንታዊ ልዩ መንፈሳዊ ፕሮግራም 🌿 በ አላሙራ ሰባተኛው ቀን አድቬንቲስት ቤተክርስቲያን የህፃናት ዘርፍ ክፍል 📅 ነሐሴ 24–30/2018 ዓ.ም ⏳ ለተከታታይ 7 ቀናት ✨ “እንደ ሕፃናት እን
🌿 ሳምንታዊ ልዩ መንፈሳዊ ፕሮግራም 🌿 በ አላሙራ ሰባተኛው ቀን አድቬንቲስት ቤተክርስቲያን የህፃናት ዘርፍ ክፍል 📅 ነሐሴ 24–30/2018 ዓ.ም ⏳ ለተከታታይ 7 ቀናት ✨ “እንደ ሕፃናት እንመለስ!” ✨ “እንዲህም አለ፦ እውነት እላችኋለሁ፥ ካልተመለሳችሁ እንደ ሕፃናትም ካልሆናችሁ፥ ወደ መንግሥተ ሰማያት ከቶ አትገቡም።”   — ማቴዎስ 18፥3 📖 በቃል አገልግሎት በተለያዩ ተጋባዥ አገልጋዮች አማካኝነት፣ ከጌታ የሆነውን ቃል እንማራለን፣ ልዩ የበረከት ጊዜ ይሆናል። 🎶 በዝማሬ አገልግሎት 🎤 ካቮድ መዘምራን 🎤 ሄቨን መዝሙር ህብረት 👧👦 ቅዳሜ — ልዩ የህፃናት ፕሮግራም ከ ሰኞ እስከ አርብ ጠዋት ከ 2:30-6:00 ለልጆቻችን በሚመች መልኩ የተዘጋጁ መንፈሳዊ ትምህርቶች ፣ ዝማሬዎች፣ ጨዋታዎች እና የተለያዩ ልዩ ፕሮግራሞች። 💛 ውድ ወላጆች! ልጆቻችሁን ይዛችሁ ኑ! አብረን እንማር፣ አብረን እንዘምር፣ አብረን ኢየሱስን እንቅረብ! 🙏 እርስዎም የዚህ ታላቅ የበረከት ሳምንት አካል ይሁኑ! 📍 ቦታ፦ አላሙራ ሰባተኛው ቀን አድቬንቲስት ቤተክርስቲያን ⏰ ሰዓት፦  12:00-2:00 ❤️ ሁላችሁም በደስታ ተጋብዛችኋል!

ከደቡብ ግሪን ኢት/ ሰበካ የጎዳና ፈላጊ ክለብ በሐዋሳ ካምፖሬ ጉዞ መልስ በአንድ አገልጋይ ላይ ከአቅም በላይ የሆነ አደጋ ደርሶበት ሐዋሳ ያኔት ሆስፒታል የራስ ቅል ቀዶ ጥገና ህክምና ተደርጎለት በ
+1
ከደቡብ ግሪን ኢት/ ሰበካ የጎዳና ፈላጊ ክለብ በሐዋሳ ካምፖሬ ጉዞ መልስ  በአንድ አገልጋይ ላይ ከአቅም በላይ የሆነ አደጋ ደርሶበት ሐዋሳ ያኔት ሆስፒታል የራስ ቅል ቀዶ ጥገና ህክምና ተደርጎለት በአሳሳቢ ሆኔታ ላይ (@Hawassa referral hospital) ስላለ እባካችሁ እንጸልይለት የበኩላችንንም ድጋፍ እናድርግለት:: የጎዳና ፈላጊው ስም ሺበሺ ደምሴ ሲሆን ፀልዩለት እንደግፍ :: አከዉንት ቁጥር 1000235484017 አያሌው ደምሴ ጌታ ይባርካችሁ!

ትላንት ባደረግነው የከሰዓት መንገድ ዳር ሥርጭት አንድ አድስ ነብስ እና አንድ ወደኃላ የቀረች ተመልሳለች። እግዚአብሔር ይመስገን።

ሰላም ሰላም! ይህ ከሀዋሳ መናኸሪያ አጥቢያ ቤ/ክ የተላለፈ መልዕክት ነው:: ------ እንደምን ሰነበታችሁ ወገኖች! እግዚአብሔር ቢፈቅድና ብንኖር ከጳጉሜ 01/2018 እስከ መስከረም 02/2019
ሰላም ሰላም! ይህ ከሀዋሳ መናኸሪያ አጥቢያ ቤ/ክ የተላለፈ መልዕክት ነው:: ------ እንደምን ሰነበታችሁ ወገኖች! እግዚአብሔር ቢፈቅድና ብንኖር ከጳጉሜ 01/2018 እስከ መስከረም 02/2019 ዓ.ም የሚካሄደውን የቤተሰብ ሥልጠና መከታተል የምንፈልጉ ወገኖች በሙሉ: ቅደመ ሁኔታዎችን ለማሟላትና በመጨረሻው ቀን ለተሳታፊ ባለትዳሮች የሚሰጠውን ሰርትፊኬት ለማዘጋጀት እንዲረዳን ስማችሁን ለአጥቢያ ቤተ ክርስቲያናችን ወንጌላዊያን ወይንም ሽማግሌዎች በመስጠት ወይም ከሥር በተጠቀሰው ስልክ ቁጥር እየደወላችሁ እንድታስመዘግቡ እያሳሰብን፤ እነዚሁ ጥንዶች ከመጀመሪያው የማክሰኞ ምሽት የቤተሰብ ትምህርት አንስቶ እስከ ሰንበት ጠዋት የጋብቻ ተሀድሶ ድረስ ትምህርቶቹን ያለ ማቋረጥ እንዲከታተሉ የሚጠበቅ ሲሆን ይህንን ላደረጉ ደግሞ ቤተ ክርስቲያን እና ኢትዮ ባርናባስ የወንጌል አገልግሎት ያዘጋጁት የምስክር ወረቀት በሰንበት ቀን ዋናው አገልግሎት ላይ የሚሰጥ ይሆናል። ማሳሰቢያ: ከሐሙሱ የባለ ትዳሮች ስልጠና በስተቀር ሁላችንም በሁሉም መንፈሳዊ ፕሮግራሞች የተጋበዝን ስለሆነ ተገኝተን ሌሎችንም እንጋብዝ ጌታ ይባርካችሁ! 0916836762

አስደሳች ዜና የቤተክርስቲያናችን ምዕመናን በሙሉ ዛሬ በቀን 23/12/2018/ ዓ.ም. በታቦር ተራራ ላይ በተወሰኑ ወንድሞችና እህቶች በኩል የእግዚአብሔርን እዉነት በመስማት ካለን የአምልኮ ቦታ በመጽሐፍ ቅዱስ መሠረት አይደለም ብለዉ የእግዚአብሔር ቤት ይሻለናል ብለዉ የተለዩ ወንድሞች 1. ሀጎስ ሻላ ከመካነ ኢየሱስ ቤ/ክ 2. ተስፋዬ ዘካሪያስ ከቃል ብርሃን ቤ/ክ 3. አዱኛ ገመቹ ከቃል ብርሃን ቤ/ክ 4. ዮሴፍ ዳጊ ከሕይወት ብርሃን ቤ/ክ 5. ካቲሪና ከካቶሊክ ቤ/ክ 6 አዳነች ከሕይወት ብርሃን 7. ተሰማ ሚካኤል ከቃል ብርሃን ቤ/ክ 8 የአዱኛ ገመቹ ባለቤት ሲሆን እነኝህ ወንድሞች በተራራ ስብከት ተምረው ወደ ጌታ የተመለሱ ወንድሞቻችን ናቸዉ

Hello dears, We received requests that some couldn't apply for the Space Science virtual session to be held at Hawassa American Corner announced earlier. Having arranged with the central organizers of the training we got permission to accommodate a few more trainees for that on a new link: https://tally.so/r/gDPxVJ?address=Hawassa So, please get registered as soon as possible and let us know if you face any inconvenience while registering. You may reach us at: hawassaac@gmail.com Kind regards,

ለቅሶ ለመድረስ አቶ ታዬ ቶማስ ጋር የተመዘገባችሁ ነገ ጠዋት 3:00 ላይ ቤ/ያን ቅጥር ግብ ዉስጥ እንገናኝ።

ምናልባት ይጠቅማል ብለን ነዉ! የስራ ማስታወቂያ የስራ አይነት:- የኮምፒዩተር ባለሙያ (ኮፒ፣ print ማድረግ የሚችል/የምትችል) ቦታው:- ሐዋሳ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ በዝህ በሁለት ቀን ዉስጥ የሚጠናቀቅ ነዉ።

በቅድሚያ የጌታ ሰላምና ፀጋ ይብዛላችሁ! ማስታወቂያ! የቤ/ክያናችን አባል የሆኑት አቶ ማቴዎስ ማርሳ እህት ማረፋቸውን ሰምተናል። እግዚአብሔር አምላክ ለቤተሰብ እንድሁም ለወዳጅ ዘመድ መጽናናቱን እንድሰጣቸው ቤተክርስቲያናችን ይመኛል። ቀብር ሥነሥርዓት የሚፈፀመው ዕሮብ ቀን በነሐሴ 13/2018 ዓ.ም ከቀኑ 6:00 ሰዓት ላይ በሀዋሳ ዙሪያ ወረዳ ኡዶ ጎርፋሞ ቀበሌ ሰባተኛ ቀን አድቬንቲስት ቤ/ክ አከባቢ ይሆናል ። ስለሆነም የምንችል ሁላችን ወንድማችንን ደርሰን እንድናፅናናዉ ይሁን። ተባረኩ!