en
Feedback
Bita Woreda Communication

Bita Woreda Communication

Open in Telegram

Government organization

Show more
986
Subscribers
No data24 hours
+67 days
No data30 days

Data loading in progress...

Tags Cloud
No data
Any problems? Please refresh the page or contact our support manager.
Incoming and Outgoing Mentions
---
---
---
---
---
---
Attracting Subscribers
June '26
June '26
+6
in 0 channels
May '26
+14
in 0 channels
Get PRO
April '26
+15
in 0 channels
Get PRO
March '26
+20
in 0 channels
Get PRO
February '26
+29
in 0 channels
Get PRO
January '26
+35
in 0 channels
Get PRO
December '25
+18
in 0 channels
Get PRO
November '25
+45
in 0 channels
Get PRO
October '25
+37
in 0 channels
Get PRO
September '25
+24
in 0 channels
Get PRO
August '25
+34
in 0 channels
Get PRO
July '25
+19
in 0 channels
Get PRO
June '25
+21
in 0 channels
Get PRO
May '25
+38
in 0 channels
Get PRO
April '25
+21
in 0 channels
Get PRO
March '25
+50
in 0 channels
Get PRO
February '25
+23
in 0 channels
Get PRO
January '25
+23
in 0 channels
Get PRO
December '24
+26
in 0 channels
Get PRO
November '24
+36
in 0 channels
Get PRO
October '24
+35
in 0 channels
Get PRO
September '24
+28
in 0 channels
Get PRO
August '24
+33
in 0 channels
Get PRO
July '24
+26
in 0 channels
Get PRO
June '24
+33
in 0 channels
Get PRO
May '24
+38
in 0 channels
Get PRO
April '24
+36
in 0 channels
Get PRO
March '24
+27
in 0 channels
Get PRO
February '24
+29
in 0 channels
Get PRO
January '24
+468
in 0 channels
Date
Subscriber Growth
Mentions
Channels
02 June+5
01 June+1
Channel Posts
2
+9
No text...
0
3
"በግብርናው ዘርፍ የሴቶችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በትኩረት ይሠራል" አቶ አብዱ ዑስማን፦ የቢጣ ወረዳ ግብርና፣ አካባቢ ጥበቃና ህብረት ሥራ ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ ቢጣ ገነት፤ መጋቢት 06 ቀን፣ 2018 ዓ.ም (የቢጣ ወረዳ መንግስት ኮምኒኬሽን) በቢጣ ወረዳ ኦስሪያ በተሰኘ ፕሮጀክት በጀት ድጋፍ በተደራጀ የሴቶች ማህበር የቡና ችግኝ ጣቢያ ተቋቋመ። የፕሮጀክቱ አስተባባሪ አቶ አለሙ ተስፋዬ እንደጠቀሱት የፕሮጀክቱ ዋና አላማ ሴቶች ከልማት ስራው ከሚያገኙት ጥቅም ባሻገር የካርበን ሽያጭ በማከናወን በየአመቱ ከ20 ሚሊየን ብር በላይ ገቢ እንዲያገኙ ማስቻል ነው ብለዋል። ፕሮጀክቱ ለቀጣይ 30 አመታት አቅዶ በመስራት ላይ የሚገኝ ሲሆን በወረዳው 16 ቀበሌዎች ወደ 2 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ 8 ሺህ የሚደርሱ አርሷደሮችን በማቀፍ 300 ሺህ የቡና ችግኞችን እንዲሁም 10 ሺህ የጥላ ዛፎችን በማልማት ለማህበሩ አባላትና ለአካባቢው አርሷደር በማሰራጨት አረንጓዴ ልማትን ያጠናክራል ብለዋል። በፕሮጀክቱ የካርበን ኤክስፐርት ዶክተር ዮናስ ዮሐንስ በበኩላቸው የቡና ችግኞች በሚዘጋጁበት ወቅት የተፈጥሮ ማዳበሪያን ብቻ መጠቀም እንደሚያስፈልግ በመጠቆም ሴትች ጥምር እርሻ ደንን በመፍጠር ዘርፈብዙ ጥቅም ለማግኘት በትኩረት ሊሠሩ ይገባል ብለዋል። በችግኝ ጣቢያው የሚያስፈልጉ ግብዓቶች በፕሮጀክቱ የሚቀርብ ሆኖ ችግኙ እስኪደርስ ክትትልና እንክብካቤ ማድረግ የማህበሩ አባላት ድርሻ ይሆናል ብለዋል ዶክተር ዮናስ። የወረዳው ግብርና፣ አካባቢ ጥበቃና ህብረት ሥራ ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አብዱ ዑስማን ባስተላለፉት መልዕክት ሴቶች በፕሮጀክቱ የተፈጠረላቸውን አጋጣሚ ተጠቅመው ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸውን ሊያረጋግጡ ይገባል ብለዋል። በማህበሩ የታቀፉ ሴቶች ለቀጣይ አምሰት አመታት የችግኝ ማፍላት ስራውን በማጠናከር በትኩረት ሊሰሩ እንደሚገባ የጠቀሱት አቶ አብዱ በስራቸው ወቅት የባለሙያዎችን ምክረ ሀሳብ መተግበር እንደሚገባ አፅንኦት ሰጥተዋል። በካርበን ጭያጭ የሚገኘውን ጥቅም ለማግኘት ቡናን ጨምሮ ሙዝና ጥላ ዛፎችን በመትከል ተጨባጭ ለውጥ ማስመዝገብ እንደሚገባም ኃላፊው አክለዋል። የወረዳው መንግስት ለችግኝ ጣቢያው ብታ ከማመቻቸት ጀምሮ በግብርናው ዘርፍ የሴቶችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በትኩረት ይሠራል ነው ያሉት አቶ አብዱ። የቢጣ ወረዳ መንግስት ኮምኒኬሽን
0
4
የኢትዮጵያ ወንጌላዊት መካነ እየሱስ የቢጣ ገነት ከተማ ማህበረ ምዕመናን በቢጣ ወረዳ ፖሊስ ጣቢያ በእስር ለሚገኙ ተጠርጣሪዎች የምገባ መርሐግብር አከናወኑ ምዕመናኑ አለም አቀፍ የሴቶች ቀን (March 8)ን በማስመልከት ነው በፖሊስ ጣቢያው ተገኝተው ተጠርጣሪዎችን የመገቡት። በኢትዮጵያ ወንጌላዊት መካነ እየሱስ ቤተ ክርስቲያን የቢጣ ገነት ከተማ ማህበረ ምዕመናን ሰብሳቢ አቶ አስማማው ወልደማርያም እንደገለፁት ምዕመናኑ አለም አቀፍ የሴቶች ቀን (March 8)ን አስመልከተው ከራሳቸው ከ40 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ በማዋጣት ይህንን በጎ ተግባር መፈፀማቸውን ገልፀዋል። ይህ ተግባር የተለያዩ ቁሳቁሶችን ጨምሮ በሌሎች ሁኔታ ውስጥ ለሚገኙ አቅመ ደካሞችም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የጠቆሙት አቶ አስማማው አለም አቀፍ የሴቶች ቀንን አስመልክተው በዚህ መርሐግብር በመሳተፍ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ላበረከቱ ሴቶችና ወጣቶች ምስጋና አቅርበዋል። የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነ እየሱስ የቢጣ ወረዳ ፕርስቢተሪ አስተባባሪ ቄስ ጌታቸው ብርሃኑ በበኩላቸው ጌታ የተራቡትን እንድንመግብ፣ የታሰሩትን እንድንጠይቅ ባስተማረን መሠረት በዛሬው ዕለት ምዕመናን ያደረጉት በጎ ተግባር ይህንኑ የተከተለ ነው ብለዋል። ምዕመናኑ በፖሊስ ጣቢያው ያደረጉትን መልካም ስራ አጠናክረው እንዲቀጥሉ ጥሪ ያቀረቡት ቄስ ጌታቸው በሌሎች አካባቢዎች የሚገኙ የቤተ እምነቱ ተከታዮች የቢጣ ገነት ምዕመናንን ፈለግ በመከተል ከተቸገሩት ጎን ሊቆሙ ይገባል ብለዋል። ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን! የቢጣ ወረዳ መንግስት ኮምኒኬሽን
0
5
+2
No text...
0
6
+9
No text...
0
7
መንግስት ደረጃ በደረጃ የህብረተሰቡን ጥያቄ ለመመለስ በትኩረት እየሰራ እንደሚገኝ ተገለፀ በቢጣ ወረዳ ኦጊዳኪቲ ቀበሌ ከተለያዩ ቀበሌዎች ከተገኙ የህብረተሰብ ተወካዮች ጋር ውይይት ተካሂዷል። በመድረኩም ከያውራ ደጋኬላ የተጀመረው የመንገድና ድልድይ ፕሮጀክት አለመጠናቀቅ በህብረተሰቡ ላይ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳቶችን እያስከተለ እንደሚገኝ የውይይቱ ተሳታፊዎች ተናግረዋል። በመንገዱ ተሰርቶ አለመጠናቀቅ ከአካባቢው ማህበረሰብ እንግልት ባለፈ የወረዳው መንግስት ከአካባቢው መጠቀም ያለበትን ያህል እየተጠቀመ ስላለመሆኑ አንስተዋል። በቀጠናው የሚገኙ ቀበሌዎች የመንግስትን ግብር በወቅቱ የሚያጠናቅቁ እንዲሁም በመንግስትና ፓርቲ ስራዎች ግምባር ቀደሞች ቢሆኑም በዚሁ ልክ ከመሠረተ ልማት አንፃር ተጠቃሚ አለመሆናቸውን ተወያዮች ጠቅሰዋል። በአካባቢው የኔትወርክ አለመኖር ከፍተኛ ጉዳቶችን እያስከተለ ስለመሆኑም አብራርተዋል። በኦጊዳኪቲ ቀበሌ የሚገኘው ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት በአሁኑ ሰዓት እየተዳከመ በመሆኑ ባለድርሻዎች ተጠቃሚ ቀበሌዎችንና ባለሀብቶችን በማስተባበር ለተቋሙ መደራጀት ሊሰሩ ይገባል ብለዋል። ከዚህ ቀደም የተጠየቁ ጥያቄዎች በወቅቱ አለመመለሳቸው በህብረተሰቡ ላይ ቅሬታን እየፈጠረ በመሆኑ በሸጣይ መንግስት ከህብረተሰቡ ለተነሱ ጥያቄዎች ተገቢውን ምላሽ በወቅቱ ሊሰጥ እንደሚገባ ሀሳብ አንስተዋል። ከወጣቶች ስራ ዕድል ፈጠራ አንፃር በገጠር ቀበሌዎች የወረዳው መንግስት በትኩረት እንዲሰራ ጥሪ አቅርበዋል። የወረዳው ምክትል አስተዳዳሪና የጤና ጥበቃ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ተክለአብ አየለ በተነሱ ሀሳቦች ላይ በሰጡት ምላሽ ከመንገድ ጋር በተያያዘ ከህብረተሰቡ የተሰበሰበው ገንዘብ በህብረተሰቡ ተወካዮች ጣምራ አካውንት ተከፍቶ ሲንቀሳቀስ መቆየቱንና ከወረዳው ፋይናንስ ጋር የተያያዘ ስለመሆኑ ጠቅሰዋል። የኡዲ ድልድይን ለማጠናቀቅ የወረዳው መንግስት በቅርቡ ወደስራ የሚገባ መሆኑን የጠቀሱት ምክትል አስተዳዳሪው የመንገድ ፕሮጀክቱን ለማጠናቀቅ ህብረተሰቡን በማሳፍሰፍ የሚከወን ይሆናል ብለዋል። ከጤና አኳያ በቀጠናው የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች ተጠቃሚ የሚያደርግ መለስተኛ ጤና ጣቢያ ለመገንባት የወረዳው መንግስት ስለማቀዱ ጠቁመዋል። ኔትወርክን ጨምሮ አጠቃላይ የመሠረተ ልማት ጥያቄዎች ለመመለስ በትኩረት ይሰራል ያሉት አቶ ተክለአብ ህብረተሰቡ ከመንግሥት ጎን በመቆም የልማት ስራዎችን ሊደግፍ እንደሚገባ መልዕክት አስተላልፈዋል። መንግስት ደረጃ በደረጃ የህብረተሰቡን ጥያቄ ለመመለስ በትኩረት እየሰራ እንደሚገኝ የገለፁት በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የቢጣ ጌሻ ምርጫ ክልል ተወካይ ወ/ሮ ተስፋነሽ ወልደማርያም ህብረተሰብ ከመንግሥት ጋር በቅንጅት ሊሰራ ይገባል ብለዋል። ከህብረተሰቡ የተነሱ የተለያዩ የመሠረተ ልማት ጥያቄዎች እልባት እንዲያገኙ ከወረዳ ጀምሮ በየደረጃው ከሚገኙ ባለድርሻዎች ጋር ውይይት በማድረግ የመፍትሔ አቅጣጫዎች እንደሚቀመጡ ወ/ሮ ተስፋነሽ ጠቅሰዋል። የወረዳው ምክር ቤት ዋና አፈጉባኤ አቶ ካሳሁን ገብረሚካኤል በበኩላቸው ማህበረሰቡ እያነሳ የሚገኘውን የመሠረተ ልማት ጥያቄዎች ባለድርሻዎች ደረጃ በደረጃ ለመመለስ በትኩረት ሊሰሩ እንደሚገባ አሳስበው ህብረተሰቡም ከወረዳው መንግስት ጎን በመቆም ተገቢውን ድጋፍ ሊያደርግ ይገባል ብለዋል። የቢጣ ወረዳ መንግስት ኮምኒኬሽን
0
8
ግብርን በወቅቱና በአግባቡ በመሰብሰብ የህብረተሰቡን የመሠረተ ልማት ጥያቄዎች መመለስ ይገባል ተባለ ቢጣ ገነት፤ የካቲት 18 ቀን፣ 2018 ዓ.ም (የቢጣ ወረዳ መንግስት ኮምኒኬሽን) የቢጣ ወረዳ ገቢዎች ጽ/ቤት በአገልግሎት አሰጣጥና የ6 ወራት አፈፃፀም ዙሪያ ከነጋዴ ማህበረሰብ ጋር የውይይት መድረክ አካሂዷል። በዕለቱም የውይይቱ ተሳታፊዎች የቀረበውን ሪፖርት መነሻ በማድረግ የተለያዩ ሀሳቦችን አንስተዋል። የደረሰኝ ህትመት አዲስአበባ ብቻ መሆኑን ተከትሎ ሸለነጋዴው በወቅቱ አለመድረሱ በርካታ መስተጓጐል እየፈጠረ ነው ብለዋል። የግብር አከፋፈሉ በየሶስት ወሩ መሆኑ በእጅጉ የሚመሰገን ነው ያሉት አስተያየት ሰጪዎች ይኸንንም በአግባቡ በመሰብሰብ ለወረዳይቱ ልማት ማዋል ይገባል ብለዋል። በወረዳው ኦዲተር ካለመኖሩ የተነሳ የነጋዴው ማህበረሰብ ኦዲት ያልተደረጉ ካርኒዎች መወዘፋቸውን ተከትሎ ስጋት እንዳደረበትና ቀጣይ የመፍትሔ አቅጣጫ እንዲቀመጥ ጠይቀዋል። ነጋዴዎችን ከካርኒ አቆራረጥ ጀምሮ የተለያዩ ስልጠናዎችን በመስጠት ከኪሳራ የማዳን ስራ ሊከናወን ይገባልም ብለዋል። የወረዳው ገቢዎች ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ መስፍን ቆጶ እንደጠቀሱት በገቢ አሰባሰብ ወቅት የሚስተዋሉ ክፍተቶችን በማረም በቀጣይ የተሻለ አፈፃፀም ለማስመዝገብ ይሰራል ብለዋል። ኦዲተር ከመቅጠር አኳያ የክልሉ መንግስት በመዋቅር ሲያካትት የሚተገበር ስለመሆኑ የጠቀሱት ኃላፊው የዘርፍ ማህበራት ከነጋዴዎች የሚሰበስቡትን ገንዘብ ስልጠናን ጨምሮ ለታለመለት አላማ በማዋል ነጋዴዎችን ሊያገለግሉ ይገባል ብለዋል። የካፋ ዞን ትምህርት መምሪያ ኃላፊ አቶ ሙሉጌታ መሸሻ በበኩላቸው ግብርን መክፈል የዜግነት ግዴታ በመሆኑ የነጋዴው ማህበረሰብ በወቅቱ በመክፈል ለሀገር ዕድገት አስተዋጽኦ ማበርከት አለበት ብለዋል። የደረጃ ሽግግር እየተደረገ ያለው የሀገሪቱን የዕድገት ደረጃ መሠረት አድርጎ መሆኑን የጠቀሱት አቶ ሙሉጌታ በሂደቱ ግልፅ አሰራር መዘርጋት እንደሚገባ አንስተዋል። በአሰራር ወቅት የተለያዩ አሻጥሮችን በማስወገድ የወረዳውን የገቢ አቅም ከፍ በማድረግ የተለያዩ የመሠረተ ልማት ጥያቄዎችን መመለስ እንደሚገባም አቶ ሙሉጌታ አስገንዝበዋል። የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዳግማዊ ማሞ መድረኩን ሲያጠቃልሉ ባስተላለፉት መልዕክት በወረዳው ከጋራ ገቢ ባለፈ በጥረት የሚሰበሰቡ ገቢዎችን አሟጦ መሰብሰብ እንደሚገባ ጠቅሰው ማህበረሰቡም ያለቀስቃሽ በወቅቱ ሊከፍል ይገባል ብለዋል። በበረት አካባቢ ከፍተኛ የአሰራር ክፍተቶች ስለመኖራቸው የገለፁት ዋና አስተዳዳሪው ማህበረሰቡ መሰል የአሰራር ክፍተቶችን በማጋለጥ ከመንግስት ጎን መቆም እንዳለበት ጠቁመዋል። የካርኒ ህትመት እንዲከናወን ባለሙያ አዲስአበባ ስለመላኩ በመጠቆም በአሰራር ሂደት የሚስተዋሉ ክፍተቶችን በማረም ለህብረተሰቡ ተገቢውን አገልግሎት ለመስጠት ጥረት ይደረጋል ብለዋል። የቢጣ ወረዳ መንግስት ኮምኒኬሽን
0
9
የዳኝነት አገልግሎት አሰጣጥ ጥራት ያለውና ግልፀኝነት የተሞላበት እንዲሆን ለማስቻል ከባለድርሻዎች ጋር በቅንጅት መስራት ይገባል ተባለ ቢጣገነት፤ የካቲት 17 ቀን፣ 2018 ዓ.ም (የቢጣ ወረዳ መንግስት ኮምኒኬሽን) የቢጣ ወረዳ ፍርድ ቤት የመልካም አስተዳደር ችግሮችን መቅረፍ የሚያስችል የውይይት መድረክ ከባለድርሻ አካላት ጋር አካሄደ። በመድረኩም የፍርድ ቤት አገልግሎት አሰጣጥ ሂደትን ከመልካም አስተዳደር ችግር የፀዳ ማድረግ እንዲቻል በየደረጃው የሚገኙ ባለድርሻዎች ተገቢውን መረጃ በማደራጀት ለፍትሀዊ አገልግሎት አሰጣጥ መስፈን የድርሻቸውን ሊወጡ እንደሚገባ ተመላክቷል። የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ለመቅረፍ በየደረጃው የሚስተዋሉ የስነምግባር ጉድለቶችን፣ የኪራይ ስብሳቢነት መሻቶችን መቅረፍ ይገባል ተብሏል። በቀበሌ ደረጃ ሀሰተኛ ማሰረጃን ከመስጠት ጀምሮ ለህገወጥ አካሄዶች መዛመት አስተዋጽኦ እያበረከቱ የሚገኙ አንዳንድ የቀበሌ አመራሮች ከድርጊታቸው ሊቆጠቡ እንደሚገባ ተጠቁሟል። ባጠቃላይ ባለድርሻዎች የእርስ በእርስ ቅንጅታዊ አሰራርን በማጠናከር ለመልካም አስተዳደር መስፈን እና ለህግ የበላይነት መረጋገጥ የድርሻቸውን ሊወጡ እንደሚገባ መልዕክት ተላልፏል። መድረኩን የወረዳው ምክር ቤት ዋና አፈጉባኤ አቶ ካሳሁን ገብረሚካኤል እና የወረዳው ፍርድ ቤት ፕረዝዳንት አቶ ግዛቸው ግችሎ በጋራ የመሩት ሲሆን የፖሊስ ማኔጅመንት አባላት፣ የወረዳው ፍትህ ጽ/ቤት ማኔጅመንት አባላት እንዲሁም የባለድርሻ ተቋማት የስራ ኃላፊዎችና ሌሎች ባለድርሻዎች ተሳትፈዋል። የቢጣ ወረዳ መንግስት ኮምኒኬሽን
0
10
+5
No text...
0
11
በቢጣ ወረዳ በ2018 ዓ.ም በግማሽ አመት 278.1 ሚሊየን ብር መሰብሰብ መቻሉን የወረዳው ገቢዎች ጽ/ቤት አስታወቀ ቢጣ ገነት፤ የካቲት 17 ቀን፣ 2018 ዓ.ም (የቢጣ ወረዳ መንግስት ኮምኒኬሽን) የቢጣ ወረዳ ገቢዎች ጽ/ቤት በአገልግሎት አሰጣጥና የ6 ወራት አፈፃፀም ዙሪያ ከነጋዴ ማህበረሰብ ጋር የውይይት መድረክ እያካሄደ ይገኛል። በመድረኩም የተቋሙን የግማሽ አመት አፈፃፀም ሪፖርት እያቀረቡ የሚገኙት የወረዳው ገቢዎች ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ መስፍን ቆጶ እንደገለፁት በ2018 ዓ.ም በግማሽ አመት 278.1 ሚሊየን ብር መሰብሰብ መቻሉን ጠቁመዋል። የወረዳውን በጀት በተመለከተ 38% ከመንግሥት የሚደጎም ሲሆን ቀሪው 62% ከውስጥ ገቢ እንደሚሸፈን የጠቀሱት አቶ መስፍን ይህንንም ለመሸፈን የተለያዩ የገቢ አማራጮችን አሟጦ መሰብሰብ እንደሚገባ አመላክተዋል። በመድረኩም የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዳግማዊ ማሞን ጨምሮ የካፋ ዞን ትምህርት መምሪያ ኃላፊ አቶ ሚሉጌታ መሸሻ እንዲሁም ነጋዴዎችና ሌሎች ባለድርሻዎች እየተሳተፉ ይገኛል። የቢጣ ወረዳ መንግስት ኮምኒኬሽን
0
12
+3
No text...
0
13
በቢጣ ወረዳ በእዩ ካፌ ፕሮጀክት በጀት ድጋፍ ከ7 ሚሊየን ብር በላይ ለሚገነቡ ሁለት የቡና መጋዘኖች ሳይት ርክክብ ተካሄደ ፕሮጀክቱ ግንባታዎቹን በወረዳው "ቱጋ ተራመድ" እና "ኦዳ ገበሬዎች" ለተሰኙ የቡና ግብይት ህብረት ስራ ማህበራት አገልግሎት እንዲውል በማቀድ ሲሆን ይኸውም የቡናን ጥራት በማስጠበቅ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳለው ተመላክቷል። በርክክብ ስነ-ስርዓቱ የተገኙት የደቡብ ምዕራብ ክልል ቡና፣ ሻይና ቅመማ ቅመም ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ አስራት መኩሪያ እንደጠቀሱት የእዩ ካፌ ፕሮጀክት ለቡና ምርትና ምርታማነት መሻሻል እንዲሁም ጥራት መጠበቅ እያበረከተ ያለው አስተዋጽኦ ከፍተኛ መሆኑን ጠቅሰዋል። ፕሮጀክቱ በክልሉ አራት ዞኖች ውስጥ በሚገኙ አራት ወረዳዎች እየሰራ መሆኑን ጠቁመው ለአርሷደሮች ከቡና ችግኝ ዝግጅት ጀምሮ የማምረት ሰንሰለቱን ጠብቆ እስከ ምርት ማሰባሰብ ስልጠና በመስጠት ለቡና ጥራት መጠበቅ ጥረት እያደረገ ይገኛል ብለዋል። ለአርሷደሮች የግብዓት ድጋፍ ከማድረግ ባሻገር በወረዳዎች በቅርበት ለሚከታተሉ ባለሙያዎች የሚውል የመኪና እና ሞተር ድጋፍ በማበርከት ስራዎች እንዲሳለጡ እያደረገ እንደሆነ አንስተዋል። በአሁኑ ደግሞ ፕሮጀክቱ ከፍተኛ በጀት በመመደብ በታቀፉ ወረዳዎች ለእያንዳንዳቸው ሁለት የቡና መጋዘኖችን ገንብቶ ለማስረከብ ቅድመ ዝግጅት ማድረጉን ጠቅሰው በሳይት ርክክቡ የተገኙ ባለድርሻዎች ለስራው በስኬት መጠናቀቅ የድርሻቸውን እንዲወጡ አሳስበዋል። የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዳግማዊ ማሞ በበኩላቸው ፕሮጀክቱ ለቡና ምርት ጥራት መጠበቅ እያበረከተ ያለው አስተዋጽኦ ከፍተኛ መሆኑን ጠቅሰው በዚህም በወረዳው የሚገኙ ቡና አምራች አርሶደአሮችን ተጠቃሚ እያደረገ ስለመሆኑ ጠቅሰዋል። በወረዳው ቡና በስፋት የሚመረት ከመሆኑ አንፃር ፕሮጀክቱ በዘርፉ እያበረከተ ያለው አስተዋጽኦ የማይተካ ሚና አለው ያሉት ዋና አስተዳዳሪው በማህበራቱ የሚገኙ አርሶደአሮች የተፈጠረላቸውን ዕድል በመጠቀም ቡናን በጥራት እንዲያመርቱ አደራ ብለዋል። የወረዳው መንግስት ግንባታው ተጠናቆ ለአርሷደሩ አገልግሎት እስኪውል አስፈላጊውን ሁሉ ድጋፍ እንደሚደረግ አቶ ዳግማዊ አስረድተዋል። እዩ ካፌ ፕሮጀክትን በመወከል የተገኙት ወ/ሮ ሶፊያ አህመድ ባስተላለፉት መልዕክት አርሷደሮች የመጣውን ዕድል በአግባቡ በመጠቀም የቡናን ምርትና ምርታማነት በማረጋገጥ ፕሮጀክቱ ግቡን እንዲመታ የድርሻቸውን ሊወጡ ይገባል ብለዋል። የወረዳው መንግስት ተገቢውን ድጋፍ ከማድረግ ባለፈ የግንባታውን ሂደት የመከታተልና የመቆጣጠር ኃላፊነት አለበት ያሉት ወ/ሮ ሶፊያ ጨረታውን አሸንፎ የገባውም ኮንትራክተር ከሁለት ወር ባልበለጠ ጊዜ ውስጥ በማጠናቀቅ ሊያስረክብ እንደሚገባው አስገንዝበዋል። የወረዳው ግብርና፣ አካባቢ ጥበቃና ህብረት ስራ ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አቶ አብዱ ዑስማን ፕሮጀክቱ ከዚህ ቀደም ለአርሷደሮች ስልጠናን ጨምሮ በቡናው መስክ በርካታ ስራዎችን ሲያከናውን መቆየቱን አስታውሰው አሁንም ለቡና ምርት ጥራት መጠበቅ የመጋዘን ግንባታዎችን ሊያከናውን መሆኑ የሚያስመሰግን ነው ብለዋል። ግንባታዎቹ እያንዳንዳቸው 14 ሜትር በ7 ሜትር የሆነ ስፋት ያላቸው መሆኑ ተጠቅሷል። በርክክብ ስነ-ስርዓቱ የደቡብ ምዕራብ ክልል ቡና፣ ሻይና ቅመማ ቅመም ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ አስራት መኩሪያን ጨምሮ የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዳግማዊ ማሞ፣ ከፌደራል ቡናና ሻይ፣ ገንዘብ ሚኒስቴር እና እዩ ካፌ ፕሮጀክት የተገኙ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች እንዲሁም የወረዳና ዞን የስራ ኃላፊዎችና የዘርፉ ባለሙያዎች ተሳትፈዋል። የቢጣ ወረዳ መንግስት ኮምኒኬሽን
0
14
+2
No text...
0
15
በቢጣ ወረዳ የፋይዳ መታወቂያ ምዝገባ በተለያዩ ቀበሌዎች እየተከናወነ ይገኚል። ይኸውም የቀበሌውን የማህበረሰብ ክፍል ያለ እንግልት ባለበት ሆኖ የዲጂታል መታወቂያ ባለቤት እንዲሆን የሚያስችለው መሆኑ ተጠቁሟል። የፋይዳ መታወቂያ ምዝገባው የወረዳው መንግስት ከተለያዩ ባንኮች ጋር በመቀናጀት እየተከናወነ ስለመሆኑ ተመልክቷል። የምዝገባው ሂደት በአመሻ መቸታ ቀበሌ ያለበትን ደረጃ በምስል እናስቃኛችሁ። የቢጣ ወረዳ መንግስት ኮምኒኬሽን
0
16
+1
No text...
0
17
ማህበረሰቡ የእርስ በእርስ አንድነትን በማጠናከር ለዘላቂ ሠላም መረጋገጥ አስተዋጽኦ ሊያበረክት እንደሚገባ ተገለፀ ቢጣገነት፤ የካቲት 09 ቀን፣ 2018 ዓ.ም (የቢጣ ወረዳ መንግስት ኮምኒኬሽን) የቢጣ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዳግማዊ ማሞ ከሾታ ቀበሌ ነዋሪዎች ጋር ተወያዩ። በውይይቱም የሾታ ቀበሌ ነዋሪዎች የህብረተሰቡን የእርስ በእርስ አንደነት ለማደፍረስ የሚንቀሳቀሱ አካላት ከድርጊታቸው ሊታቀቡ እንደሚገባ አሳስበዋል። ነዋሪዎቹ በቀበሌው መንገድን ጨምሮ የተለያዩ መሠረተ ልማት እንዲዘረጋላቸው ጠይቀዋል። ከኦዳ ጀምሮ ሾታን አልፎ ወሸሮ መዳረሻውን ያደረገው መንገድ አለመጠናቀቁን ተከትሎ ህብረተሰቡ ለማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳት እየተዳረገ ስለመሆኑ ጠቅሰዋል። ከጤና አገልግሎት አንፃርም ጤና ጣቢያዎች ከቀበሌው ያላቸው ርቀት ከፍተኛ በመሆኑ ማህበረሰቡ ለእንግልት ተዳርጓል ብለዋል። የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዳግማዊ ማሞ በተነሱ ሀሳቦች ላይ በሰጡት ምላሽ መንገድን በተመለከተ ኦዳ ጀምሮ እስከ ወሸሮ ያለውን መንገድ ለመጠገን የወረዳው መንግስት ጅምር እንቅስቃሴዎችን እያደረገ ስለመሆኑ ገልጸው ሂደቱም የተሳካ እንዲሆን የህብረተሰቡ ተሳትፎ ወሳኝ ነው ብለዋል። የዚህ መንገድ ተጠግኖ መጠናቀቅ የአካባቢውን እምቅ ሀብት ወደ ገበያ ለማውጣት ካለው ፋይዳ ባሻገር የወረዳውንም የገቢ አቅም ከማሳደግ አንፃር ከፍተኛ ድርሻ ይኖረዋል ብለዋል። ለሁሉም መሠረተ ልማቶች መረጋገጥ የዘላቂ ሠላም ዕውን መሆን ወሳኝ ነው ያሉት ዋና አስተዳዳሪው ማህበረሰቡ የእርስ በእርስ አንድነትን በማጠናከር ለዘላቂ ሠላም መረጋገጥ አስተዋጽኦ ሊያበረክት እንደሚገባ አስገንዝበዋል። ከጤና አንፃርም ያሉ ተግዳሮቶችን ለመቅረፍ የወረዳው መንግስት ጥረት እንደሚያደርግ አቶ ዳግማዊ ተናግረዋል። በውይይቱም የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዳግማዊ ማሞን ጨምሮ የወረዳው ሠላምና ፀጥታ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አጥናፉ አሰፋ፣ የወረዳው ፖሊስ ዋና አዛዥ ምክትል ኮማንደር አየነው አበበ እንዲሁም የፖሊስ ማኔጅመንት አባላትና የሾታ ቀበሌ ነዋሪዎች ተገኝተዋል። የቢጣ ወረዳ መንግስት ኮምኒኬሽን
0
18
https://www.facebook.com/100066985236713/posts/pfbid02QZaskJUDt8UdouuKMGYDhxmbHd2UWAMyb5EGT37nnQ8aCGzpJm21SrPsEeGtrtqhl/?app=fbl
0
19
ተፋሰስን መሠረት ያደረገ ዘላቂ የመሬት አያያዝና አጠቃቀም ስርዓት በመዘርጋትና በመተግበር የተፈጥሮ ሀብት ልማትን ማሻሻል እንደሚገባ ተገለፀ ቢጣ-ገነት፤ ታህሳስ 27 ቀን፣ 2018 ዓ.ም (የቢጣ ወረዳ መንግስት ኮምኒኬሽን) በቢጣ ወረዳ ግብርና አካባቢ ጥበቃና ህብረት ስራ ልማት ጽ/ቤት በካልም (CALM P4R) ፕሮግራም በጀት ድጋፍ በህብረት ስራ ማህበር አደረጃጀት እና በተዘዋዋሪ ፈንድ አጠቃቀም ዙሪያ ለባለድርሻ አካላት ስልጠና ተሰጥቷል። ተፋሰስን መሠረት ያደረገ ዘላቂ የመሬት አያያዝና አጠቃቀም ስርዓት በመዘርጋትና በመተግበር የተፈጥሮ ሀብት ልማትን ማሻሻል እንደሚገባ የወረዳውን ዋና አስተዳዳሪ በመወከል የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት አቶ ጌታቸው ገ/ሚካኤል ገልጸዋል። አቶ ጌታቸው እንደተናገሩት የካልም (CALM P4R) ፕሮግራም የተፈጥሮ ሀብታችን ተጠብቆ እንዲኖር ለማስቻል ማህበራትን በማደራጀት የአፈር ውሃ ጥበቃ ስራዎች በትኩረት እንዲከናወን አስተዋጽኦ እያበረከ የሚገኝ ሀገራዊ ፕሮግራም ስለመሆኑ ጠቁመዋል። የወረዳው ግብርና አካባቢ ጥበቃና ህብረት ስራ ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አብዱ ዑስማን በበኩላቸው ይህ ፕሮግራሙ በመሬት መሸርሸር ምክንያት የተጎዳውን መሬት መጠን በመቀነስ ምርትና ምርታማነት እንዲረጋገጥ በትኩረት እየሰራ መሆኑን ጠቅሰው ህብረተሰቡ ተግባሩን ሊደግፍ እንደሚገባ አሳስበዋል። በፕሮግራሙ በታቀፉ ቀበሌዎች ስራ ለተደራጁ የማህበር አባላት የተለያዩ የኑሮ ማሻሻያ ፓኬጆችን እንዲጠቀሙ እየተደረገ መሆኑን የጠቀሱት ኃላፊው በጀቱ ተዘዋዋሪ ፈንድ በመሆኑ የማህበር አባላት ትርፋማና ተጠቃሚ በመሆን ለሌሎች የማህበረሰብ ክፍሎች ተጠቃሚነት በር ሊከፍቱ ይገባል ብለዋል። መድረኩ ያለፈውን አፈፃፀም ከመገምገም ባሻገር የ2018 ዓ.ም የተፋሰስ ልማት ማስጀመሪያ መድረክ መሆኑን በመገንዘብ ማህበራት ለቀጣይ ተግባር ቅድመ ዝግጅት ሊያደርጉ እንደሚገባም አቶ አብዱ መልዕክት አስተላልፈዋል። በወረዳው የካልም (CALM P4R) ፕሮግራም አስተባባሪ አቶ ቅዱሴ ገብረመድህን ፕሮግራሙ በዋናነት የአየር ንብረት ለዉጥ የሚያመጣው ተፅዕኖ እንዲቀንስ የመሬት ሀብቶችን መሰረት ያደረገ የተፋሰስ ልማት ስራዎችን በተቀናጀ መንገድ በመተግበር የተራቆቱ መሬቶች መልሰው እንዲያገግሙ በማድረግ ምርትና ምርታማነትን ማረጋገጥ ላይ አቅዶ እየሰራ ነው ብለዋል። አስተባባሪው ሲቀጥሉም በወረዳው ውስጥ የሚገኙ 6 ንዑስ ተፋሰሶች የተፋሰስ አዋጅን ተግባራዊ በማድረግና ወጥ የሆነ አሰራር ስርዓትን በመተግበር የተራቆተውን መሬት እንዲሁም የተዛባውን የአየር ንብረት በማስተካከል ተጨባጭ ለውጥ ለማስመዝገብ በትኩረት ሊሰሩ እንደሚገባ አመላክተዋል። በዕለቱም በህብረት ስራ ማህበራት አደረጃጀት፣ በተዘዋዋሪ ፈኔደ አጠቃቀምና አስተዳደር እንዲሁም በቅሬታ አፈታት ዙሪያ በዘርፉ ባለሙያዎች ስልጠና ተሰጥቷል። በመድረኩም የተደራጁ የማህበር አመራሮች፣ የህብረት ስራ ባለሙያዎች እና ሌሎች ባለድርሻዎች ተገኝተዋል። የቢጣ ወረዳ መንግስት ኮምኒኬሽን
0
20
+6
No text...
0