cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

ትምህርት በቤቴ/Timehirtbebet

ትምህርት በቤቴ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ከአፍሪኸልዝ ቴሌቪዥን ጋር በመተባበር የሚያቀርብላቹ ፕሮግራም ነው።

Show more
The country is not specifiedThe language is not specifiedThe category is not specified
Advertising posts
210Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

ጅማ ዩንቨርሲቲ ሲካሄድ በቆየው የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የውይይት መድረክ የተነሱ ኃሳቦችን ከመድረኩ ተሳታፊ አካላት ጠይቀን ተከታዩን መርጃ ሰጥተውናል ፦ - ዩኒቨርስቲዎች ተማሪዎችን የመቀበል ዝግጁነታቸውን እስከ መስከረም 25/2013 ዓ/ም ድረስ እንዲያሳውቁ በመድረኩ አቅጣጫ የተቀመጠ ሲሆን ዝግጁ የሆኑ ዩኒቨርሲቲዎች ተማሪዎቻቸውን ከመስከረም 25 ጀምሮ መጥራት ይችላሉ፡፡ - በቀድሚያ ተመራቂ ተማሪዎችን ወደ ትምህርት ገበታቸው እንዲመለሱ ይደረጋል፡፡ - ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት የተወጣጣ የዩኒቨርስቲዎችን ዝግጁነት የሚያረጋግጥ ግብረ-ኃይል የተቋቋመ ሲሆን ዩኒቨርስቲዎች ተማሪዎችን ለመቀበል ዝግጁ መሆናቸውን ይመለከታል። - ዩኒቨርሲቲዎች በጥሪ ጊዜ የትራንስፖርት መጨናነቅ እንዳይኖር ዩኒቨርሲቲዎች ተናበው እንዲሰሩ እንዲሁም የትራንስፖርት አገልግሎቶችን ለተማሪዎች እንዲያመቻቹ ኃሳብ ተነስቷል፡፡ - የተማሪዎች ህብረት ተወካዮች ወደ ግቢ እንዲገቡ ጥሪ እየተደረገ ይገኛል፡፡ - በዚህ ዓመት ሌላው ከፍተኛ ትኩረት የተሰጠው የዲሲፒሊን ጉዳይ ሲሆን ባለፈው ዓመት የተፈጠሩ ክስተቶች እንዳይደገሙ ሁሉም ባለድርሻ አካል ልዩ ትኩረት ሰጥቶ ይሰራል።
Show all...
ትምህርት ቤቶችን ዳግም መክፈት በሚቻልበት የውሳኔ ሃሳብ ላይ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን በተገኙበት ውይይት እየተካሄደ ነው። በጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት እየተካሄደ ባለው ውይይት የትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎችና ሌሎች ሚኒስትሮችም ተገኝተዋል። የትምህርት ሚኒስትሩ ዶክተር ኢንጂነር ጌታሁን መኩሪያ ትምህርት ቤቶችን ዳግም ለመክፈት ስለቀረበው የውሳኔ ሃሳብ ገለፃ አድርገዋል። በዚሁ መሰረት የትምህርት ቤት አከፋፈት ሂደቱ በሶስት ዙር እንደሚከናወን አስታውቀዋል ፦ - በመጀመሪያው ዙር ጥቅምት 9 ቀን 2013 ዓ.ም በገጠር ወረዳ እና ቀበሌ ከተሞች የሚገኙ ትምህርት ቤቶች ትምህርት እንዲጀምሩ፤ - በ2ኛ ዙር ጥቅምት 16 ቀን 2013 በሁሉም የዞን እና የክልል ከተሞች የሚገኙ ትምህርት ቤቶች ትምህርት እንዲጀምሩ፤ - በአዲስ አበባና በፊንፊኔ ዙሪያ የሚገኙ ትምህርት ቤቶችም ጥቅምት 30 ቀን 2013 ዓ.ም ትምህርት እንዲጀምሩ የውሳኔ ምክረ ሀሳብ ቀርቧል።
Show all...
ተጨማሪ ፦ የ8ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ሕዳር 22 እና 23 ቀን 2013 ዓ/ም የሚሰጥ ሲሆን ፈተና ላይ መቀመጥ የሚችሉት 7ኛ ክፍልን ተምረው ያጠናቀቁና የ8ኛ ክፍልን የአንደኛ ሴሚስተር ትምህርት የተከታተሉ ብቻ ናቸው። በተመሳሳይ ደግሞ የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና መውሰድ የሚችሉት የ11ኛ ክፍል ትምህርት ያጠናቀቀቁ እና የ12ኛ ክፍልን የመጀመሪያ ሴሚስተር ትምህርት የተከታተሉ ብቻ ናቸው ተብሏል። የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ከሕዳር 28 እስከ ታህሳስ 1 ቀን 2013 ዓ/ም እንደሚሰጥ ምክረ ሀሳብ ቀርቧል። (MoE
Show all...
#UPDATE የትምህርት ሚኒስቴር የኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክተር ሐረጓ ማሞ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በስልክ እንደገለፁት ፥ የትምህርት ሚኒስቴር አመራሮችና የክልል ትምህርት ቢሮ ሃላፊዎች በቀጣይ የትምህርት ሁኔታ ላይ ውሳኔ ለማሳለፍ እያካሄዱት ያለው ውይይት ዛሬ አልተጠናቀቀም ፤ ነገ ጥዋት መግለጫ ይሰጣል ብለውናል።
Show all...
የትምህርት ሚኒስቴር አመራሮች እና የክልል ትምህርት ቢሮ ሃላፊዎች በቀጣይ የትምህርት ሁኔታ ላይ ውሳኔ ለማሳለፍ ውይይት እያካሄዱ ነው! ውይይት እየተካኔደባቸው እና ውሳኔ ከሚያገኙ ጉዳዮች መካከል ፦ - የመደበኛ ትምሀርት የሚጀመርበት ቀን ፣ - የ8ኛና 12ኛ ክፍል ክልላዊና ሀገራዊ ፈተና የሚሰጥበት ቀን - እንዲሁም በግል ትምህርት ቤቶች ላይ እየቀረበ ባለ ቅሬታ ላይ ውሳኔ የሚሰጥ ነው። ከዚህ በተጨማሪ አዲሱ የትምህርት ስርዓት ዝግጅት አካሄድ እና ሁኔታ በውይይቱ ላይ የሚገመገም እና ውሳኔ የሚሰጠው ይሆናል። የጎልማሶች ትምህርት አሰጣጥ እና አፈፃፀምም በውይይቱ ውሳሄ ከሚያገኙ ጉዳዮች መካከል ነው። በውይይቱ ላይ የተደረሰው ውሳኔ ነገ በ9:00 ለህዝብ ይፋ የሚደረግ ይሆናል። (MoE) https://t.me/Timehirtbebete https://t.me/Timehirtbebete
Show all...
ትምህርት በቤቴ/Timehirtbebet

ትምህርት በቤቴ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ከአፍሪኸልዝ ቴሌቪዥን ጋር በመተባበር የሚያቀርብላቹ ፕሮግራም ነው።

ትምህርት በፈረቃ እንደሚሰጥ ትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ! ትምህርት ሲጀመር የትምህርት አሳጣጥ ሂደቱ በፈረቃ እንደሚሆን የትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ። በፈረቃ የሚሰጠው ትምህርት እንደየአካባቢው ሁኔታ ከ2 እስከ 3 ፈረቃ ተከፍሎ ሊሰጥ እንደሚችልም ተገልጿል። የመማር ማስተማር ሥራው በአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች እንደሚጀመር ትምህት ሚኒስቴር አመልክቷል። ሚኒስቴሩ እንዳለው በኮቪድ-19 ወረርሽኝ ምክንያት ለሰባት ወራት ተቋርጦ የቆየው መደበኛ ትምህርት አስፈላጊውን ጥንቃቄ በማድረግ ዳግም ለማስጀመር አስፈላጊው ዝግጅት ተጠናቋል። መንግስት በትምህርት ቤቶች የአፍና አፍንጫ መሸፈኛ ጭምብል ፣ ውሃ እና የእጅ ማጽጃዎችን በማሟላት እንዲሁም ትምህርት ቤቶችን በማጽዳት መደበኛው ትምህርት እንደሚጀመር አስታውቋል (ENA)
Show all...
Biology G.9 – Unit 3 – Human Biology and Health Share via https://t.me/Timehirtbebete https://t.me/Timehirtbebete
Show all...
PHYSICS GRADE 9 Share via https://t.me/Timehirtbebete
Show all...
Maths G.9 Geometry and Measurement Share via https://t.me/Timehirtbebete https://t.me/Timehirtbebete
Show all...