1 745
Subscribers
+224 hours
+57 days
-230 days
Posts Archive
#ኢትዮጵያዊ_ነኝ!
ኢትዮጵያዊ ነኝ ለማለት የማልሳቀቅ
ድንቅ ህዝብ የወለደኝ
በሰሜን በደቡብ
በምስራቅ በምዕራብ ላይ
አስገራሚ ታሪክ ያለኝ
የሰው ዘር መገኛ
የከዋክብት አጥኚ
የቋንቋና ፊደል ቀራፂ
የሙሴ ጸላት ባለቤት
የነጃሺ መስጊድ
የሶፍሁመር ዋሻ
የእክሱም ሐውልት
የጥያ ድንጋይ
የባሌ ተራሮች
የኤርታሌ
የሀረር ግንብ
የጣና ገዳማት
የላሊበላ ውቅር
የሉሲ መገኛ
የማይበገር የማይደፈር አባት አያት ያለኝ!
ሰላም ለዚህ ቤት ሲባል
ሰላም ለእናንተ ብሎ መደቡን ለቆ የሚያስተናግድ ዘመድ ያለኝ
እነአበበ ቢቂላ፣ ምሩጽ ይፈጠር፣ ሀይሌ፣ደራርቱ ፣ብርሀኔ፣ ጥሩነሽ፣ መሰረት፣ ቀነኒሳ፣ ስለሺን ያፈራች ሀገር...
የሉሲና ዋልያ መንደር
የቅዱስ ያሬድ ደብር
የአድዋ ፈርጥ
ሰንደቋ ከራሷ አልፎ ለአፍሪካ ለአለም የሚተርፍ..
የነ ጥላሁን፣ መሀሙድ፣ አለማየሁ፣ ...
የነ ብዙነሽ፣ ሜሪ፣ አስቴር .... ባለቤት
የአፄ ዩሃንስ፣ የአፄ ቴዎድሮስ፣ የአፄ ሚኒልክ፣ የአፄ ኀይለስላሴ... ሀገር
የነ ፕሮፌሰር መስፍን ወ/ማርያም፣የነ ፕሮፌሰር አሥራት ወ/የስ ፣ የነ ዶ/ር ኃይሌ፣ የነ ሀኪም ማሞ፣ የነ ዶ/ር ሐዲስ አለማየሁ፣ የነሎሬት ፀጋዬ ገ/መድህን፣ የነወጋየሁ ንጋቱ፣ የነፕሮፌሰር ሀይሌ ገሪማ፣ የነአጅጋየሁ ሽባባው፣ የነ ቴዲ አፍሮ ሀገር.....
የነንግስተ ሳባ፣ የነ ንግድት እሌሊ፣ የነ ንግስት ካሲዮፒያ ... ሀገር
የራሷ የዘመን አቆጣጠር ያላት፣... መስቀል፣ አረፋ፣ ልደት(ገና)፣ ኢድ ፣ ጥምቀት፣ ረመዷን፣ ስቀለት፣ ፋሲካና ቡሄ .... አሸንዳና ሶለል አሸንድዬ... የዚህ ሁሉ ሀብት
ባለቤት የዘመነ ኦሪት ስርዓት ከዘመነ ሐዲስ ጠብቃ የቆየች... እንግዳ ለመቀበል እጆቿን ያላጠፈች... በቃልኪዳን የተጠበቀች... እፁብድንቅ ሀገር ....
ያልጠቀስኩት ብዙ ያላነሳሁት እልፍ እንደሆነ ይገባኛል!!
ለማንኛውም ሁሌም እንደምንለው 👇
#ኢትዮጵያ_ብዙ_ይገባታል !
#ሻሎም_ኢትዮጵያ
ቢያንስ ለ 1,000.00 ሰወች ይደርስ ዘንድ
ወገን
አደጋ ላይ ነን!
ባስቸኳይ ይነበብ!!
=============
አስቸኳይ ማስጠንቀቂያ ለመላው ህብረተሰብ
ለእህትና ወንድሞች
ካነበባችሁ በሇላ ለሁሉም እንዲደርስ Share እና Like ያድርጉ
⇄⇄⇄⇄⇄⇄⇄⇄⇄⇄⇄⇄===================
↨
↨
የ254 የአይን ስፔሻሊስት ሃኪሞች አደራ
ሞባይል ስልክ የሚያመጣብን ጣጣ
የአይን ማኩላር እርጅና እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ እድሜአቸው በገፋ ሰዎች ላይ ብቻ
ነበር የሚታየው።አሁን ግን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ከ30 እስከ 40 አመት የሆኑ ወጣቶች
ሁሉ ‘ማኩላር ዲጀኔሬሽን’ የተባለና ወደ አይነ ስውርነት የሚያደርስ ሕመም
እየተጠናወታቸው መጥተዋል ይላሉ የሲንጋፖር የአይን ሕክምና ሆስፒታል ዋና
ዳይሬክተር ፕሮፌሰር ሊሊ።
ይሄም የሆነበት ማክንያት ብዙ ሰዎች ማታ መብራት ካጠፉ በኋላ ተንቀሳቃሽ ስልክ
እየከፈቱ ያያሉ።በጭለማ ውስጥ ወይም ጨለም ባለ አካባቢ የሞባይል ስልክን ለ30
ደቂቃ እንኳን መጠቀም መታረም የማይችል አደጋ ውስጥ የሚከት ነው።ሕመሙም
ካታራክት አይነት ሕመም ማስከተል ብቻ ሳይሆን የአይን ካንሰርም ያስከትላል።ይህ
ደግሞ መድሃኒት የሌለው በመሆኑ አይን ሲጠፋ ብቻ ቁጭ ብሎ መመልከት ነው ይላሉ
ሃኪሙ።ይህን መልዕክት ያስተላለፉት 254 የሚሆኑ የአይን ስፔሻሊት ሃኪሞች አንድ
ላይ በመሆን ነው።
ብዙ ሰዎች ማታ አልጋቸው ላይ ሆነው መብራት አጥፍተው ወይም ፈዘዝ ባለ መብራት
ተንቀሳቃሽ ስልካቸውን እንደሚጠቀሙ ስለምናውቅ አደራ፣አደራ፣ራሳችሁን ከማይድን
ሕመም ጠብቁ ብለዋል።
ልብ ያለው ልብ ይበል!!!
⇄⇄⇄⇄⇄⇄⇄⇄⇄
↨
↨
ሞባይልን ቻርጅ ላይ አድርገው እንዳይጠቀሙ ተጠንቀቁ ። የአለም ዶክተሮች "
አስጠንቅቀዋል ካንሰር የሚባል ቫይረስ በውስጡ እንዳለ ፈንድቶም ሒወት ሊያጠፋ
እንደሚችል ይመክራሉ ይህ የሞባይል ቫይረስ በዓለማችን ላይ በጣም አደገኛ ቫይረስ
ነው ከፍተኛ የመግደል ፍጥነት አለው። እባካችሁ ይህን SMS ወይም ቪዲኦ ኮንታክት
ዝርዝራችሁ ላይ ላሉ ሰዎች ወይም ለቤተሰብ አጋሩ ሕይወት ወይም ሕይወቶችን
አትረፉ እኔ የኔን ድርሻ ተወጥቻለሁ አሁን የናንተ ተራ ነው በሉ ሼር አድርጉ
የእህትህ የወንድምህ
ሀዘን የማያስደስትክ
ከሆንክ/ሽ
ይሄንን ትምህርት ሰጭ ፅሁፍ
ቢያንስ ለ 117 ሰወች ይደርስ ዘንድ በየግሩፑ
ሼር
ሼር
በማድረግ አስተላልፈው
እናንተም ድርሻችውን
ተወጡ ሜዳውም ፈረሱም ይሄው!!
የቢቢሲ የአየር ንብረት አገልግሎት ክፍል በኢትዮጵያ እና ሱማሊያ ከፍተኛ ዝናብ በሚቀጥሉት ሁለት ቀናት(በአርባ ስምንት ሰዓታት ውስጥ) እንደሚኖር ትንበያውን ከወዲሁ አስቀምጧል። ባሳለፍነው ሳምንት በምዕራብ እና ምስራቅ አፍሪካ የጣለው ዝናብ ከፍተኛ የመሬት መንሸራተት ሲያስከትል በሺዎች ለሚቆጠሩ ሰዎች መፈናቀል ምክንያት ሆኗል።
ምንጭ: BBC Africa News
ለታክሲ 🚕እንደምንጋፋው ዘረኝነትን🦂 ብንጋፋ ኖሮ አሁን ኢትዮጵያ🇪🇹 አምርራ ባላነባችን ነበር።😔😔😔😔
ኢትዮጵያን አናውቃትም !
ኢትዮጵያን አናውቃትም! አውቃታለሁ የሚል ደፋር ነው። ከምናስባት ሁሉ በላይ የማትገመት ሀገር ናት።
እኛኮ ያልሞከርነው ክፋት የለም። እንደ ሂትለር ዘር ተኮር ስብከትን አስፋፍተናል። እንደ አይሁድ ሰውን እርቃኑን ሰቅለናል፤ በድንጋይ ወግረን ገድለናል። እንደ ስታሊን ቁልቁል ሰቅለን ገርፈናል፤ አሰቃይተናል።
እኛ ኢትዮጵያውያን ሩዋንዳን ከበተነው የዘር ተኮር ጥላቻ ስብከት በላይ ተሰብከናል፤ ሶማሊያን መንግሥት አልባ ካደረገው በላይ ችግር ተፈጽሞብናል፤ ሶሪያን ካፈራረሰው በላይ ሴራና ግጭት ተከናውኖብናል። ተከፋፍለንና ተበታትነን እንድንጠፋ እስከመገንጠል መብት ተሰጥቶናል። ይህ ሁሉ ተሞክሮም ግን አለን። ይህችን ኢትዮጵያ የምትባል ሀገር ልዩ ምሥጢር ካልሆነ በቀር ማነው የሚያኖራት?
ሳስበው ክፋትን ሁሉ ሞክረን ስለጨረስን አሁን መልካም ነገር የሚሞከርበት ጊዜ ላይ ነው። ካሁን በኋላ በዚህች ሀገር ላይ ያልተሞከረ አዲስ ክፋት ፈልጎ ሊያገኝ የሚችል ስለማይኖር ሁሉም በጎ በጎውን ማሰብና መሥራት መጀመሩ አይቀርም። ለኢትዮጵያ የተሻለ ጊዜ እየመጣ ነው።
"ኢትዮጵያን አውቃታለሁ" የሚል ሰው ድፍረቱ ይገርመኛል። እኔ እንደማላውቃት ነው ማውቀው። ኢትዮጵያን አናውቃትም። ፈጽሞ አላስተዋልናትም። ኢትዮጵያ የራሷ ማንነት ያላት ሀገር ስለሆነች ከሌላ ሀገር በተቀዳ ሐሳብ ልትመራ አትችልም። ማንም ሀገር የሌለው የራሷ የሆነ ጥበብና እውቀት አላት። በድህነት መነፅር ስለምናያት ነው እንጅ... ልዩና ማንም የሚመኛት ሀገር ናት።
አንዳንዱ "የኢትዮጵያ ሕዝብ ያውቀኛል፣ ለኢትዮጵያ ሕዝብ ነው የምታገለው፣ ሕዝቡ ከእኔ ጋር ነው..." ሲል ይሰማል። ምን ማለቱ ነው? የትኛው ሕዝብ? ፌስቡክ ላይ ያለው? ሚዲያ ያለው? ፖለቲከኛው? ሃይማኖተኛው? ወይስ የቱ? መለየት አለበት። ሁሉም ኢትዮጵያዊ የሚያውቀውም የሚሰማውም ሰው ያለ አይመስለኝም። እያስተዋልን እንናገር።
===●===●===●===
ዶክተር ዓለማየሁ ዋሴ
የእመጓ ዝጎራ እና መርበብት ደራሲ
ኅዳር 5/2011 ዓ/ም በራስ ሆቴል አዳራሽ የተናገረው
@newsetv
Available now! Telegram Research 2025 — the year's key insights 
