cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

ኦርቶዶክስ ተዋህዶ➕➕

The Ethiopian Orthodox Tewahedo Church is the largest of the Orthodox Christian churches t.me/Orthodox_lezelaleme_tenure የአባቶች ምክርና ተግሳፅ ኦርቶዶክሳዊ የሆኑ አበው እና ጥቅስ የሚቀርቡበት መንፈሳዊ ገፅ ነው "የአባቶቼን ርስት አልሰጥም" 💒 1ኛ ነገስት🙏

Show more
The country is not specifiedThe language is not specifiedThe category is not specified
Advertising posts
225
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

• ልጅ ዮናታን ሙሴ /ኪያ ይባላል ‼️ ገና በልጅ እድሜው ነበር , ሚስኪን ደሀ እናቱን ለመርዳት በዲሽ ስራ ተሰማርቶ ሲያግዛት የነበረው ! ዛሬ ላይ ግን ይሄ ገና የ 18 አመት ህፃን አልቻለም ! የነበረበት የስኳር ህመም ተባብሶ ሁለቱ ኩላሊቶቹ Fail አስደርገውበታል ! ይባሱን ብሎም ሁለቱ አይኖቹን እየጋረደበት ጭምር ለኩላሊት እጥበት እንኳን ብር አጥቶ በጣም በስቃይ ላይ ይገኛል ! • ወዳጄ ምትጠቀመው Telegram ' youtube ' Tiktok ' facebook ይሄን መረጃ ለማድረስ /SHARE ለማድረግ ለመረዳዳት እንኳን ካልሆነ ብተወው ነው ሚሻልህ ! • በቻልነው እንረዳዳ ! ለመልካምነት ሰአት አይመረጥም ! ላንተ ትንሽ ምትለው ለሌላው የህይወት ዋጋ አለው ! እባካችሁን ለመልካምነት 1 ጊዜ እንኳን አናመንታ ! • የቻልነውን እናድርግ የሀገሬ ልጆች " ሀዘኔታ ብቻውን አያድነውም ! 1000114377388 - ገነት ሀይሉ የእናቱ Bank Ac ነው ! 0941561516 - የእናቱ ስልክ ነው ‼️
Show all...
Wake up folks!!! ክርስቲያኖች ዮሀንስ ራዕይን አስታውሱ!!! ማይክሮ ቺፕስ የለም ምናምን የምትል እስቲ ይሄን ስታይ ምን ልትል ይሆን እባክህ ራስህን አታታል ተነስተህ ተቃወም mark of the beast 666 ሊወጉህ ነው Please share share ወገን መንቃት አለበት ወገን ንቃ ንቃ እባክህ!!! Join 👇👇👇👇 @amanuelhoy
Show all...
ቅድስት ድንግል ማርያም ብቻ ‼️ 💌 ይህንን መልእክት SHARE የማያደርግ የማርያም ወዳጅ አይደለም ! 1• አምላክን የወለደች-ማርያም ብቻ ! 2• ከመውለዳ በፊትም ሆነ ኋላ ድንግል የሆነች - ማርያም ብቻ! 3• ከሰው ወገን ተለይታ መርገም ያልነካት - ማርያም ብቻ! 4•የእግዚአብሔር ሀገር ከተማ የተባለች - ማርያም ብቻ! 5• በድምጽዋ መንፈስ ቅዱስን የምትሞላ ንግስት- ማርያም ብቻ! 6• ጽንስ በማሕፀን የዘለለላት ብጽዕት - ማርያም ብቻ! 7• ያላፈውም የሚመጣውም ትውልድ የሚያመሰግናት - ማርያም ብቻ! 8• ጸሐይን ተጎናፅፋ ጨረቃን የተጫማች ልዩ እናት - ማርያም ብቻ! 9• በጌታ ሞት ያዘነውን ዓለም እንድታፅናና ጌታ የሰጠን ሥጦታችን - ማርያም ብቻ! 10• በስጋዋ፣ በነፍስዋና በሕሊናዋ በሶስት ወገን ድንግል የሆናች - ማርያም ብቻ! 11• ከፈጣሪ በታች ከፍጡራን በላይ የሆነች - ማርያም ብቻ! 12• ከፍጥረት ሁሉ ተላይታ አምላኳን "ልጄ" የምትል - ማርያም ብቻ! 13• ፍቅርዋ በልቤ የሚቀጣጠል አማላጅነትዋን ነፍሴ የሚመሰክርላት እናቴ - ማርያም ብቻ! 14• ከሰው ወገን 'ቤዛዊተ ዓለም' የሚል የጸጋ ስም ያላት - ማርያም ብቻ! 15• በንጉሱ ቀኝ ቆማ የምትማልድ ንግስት - ቅድስት ድንግል ማርያም 16• ሰው ሁሉ እናታችን ጽዮን የሚላት - ማርያም ብቻ! 17• አባ ኤፍሬም ያወደሳት፣ አባ ሕርያቆስ ያመሰገናት፣ ቅ.ያሬድ የተቀኘላት እመቤት - ማርያም ብቻ! 18• ከሰው ወገን በስጋ ከሞት ተነስታ ያረገች ንጽሕት እናት - ማርያም ብቻ! 19• የመላእክት እህታቸው፣ የሰማዕታት አክሊላቸው፣ የመነኮሳት መመኪያቸው - ማርያም ብቻ! 20• ዘንዶው በሰው ልብ እንዳትቀረፅ ሊውጣት የሚፈልግ፣ ዘርዋንም ሊዋጋ የሚሻቸው ባለ ሁለት ክንፍ እመቤት - ማርያም ብቻ! 21• ጌታ ከፍጥረት ሁሉ ለይቶ "እናቴ" የሚላት - ማርያም ብቻ ‼️ ይሄን ሼር የማያደርግ የማርያም ወዳጅ አደለም ‼️ ━━━━━━━━━━━━━━━━━━━ 💚 •✥• @amanuelhoy •✥•💚 💛 •✥• @amanuelhoy •✥•💛 ❤️ •✥• @amanuelhoy •✥•❤
Show all...
Join this channel @amanuelhoy
Show all...
share በማድረግ ሁሉም የእምነቱ ተከታይ ያንብበው Share በማድረግ ሀይማኖታችንን እንጠብቅ Share በማድረግ ታሪካዊ ቦታዎችን ከዝርፊያ እንከላከል ኦርቶዶክሳውያን ሁላችሉም አንብቡት ፉክክሩ Digitized ሆኗል መስቀል አደባባይን ጎግል ማፕ ላይ እየገቡ ኢድ አደባባይ እያሉ ኢዲት እያደረጉት ነው። ይህ ደግሞ የአንድ ሰው ኢዲት ብቻ ሳይሆን ሙስሊሞች እየተረባረቡ ኢዲት እያደረጉ ስለሆነ ጎግል መስቀል አደባባይን ''መስቀል አደባባይ ወይም ኢድ አደባባይ ብሎ ቀይሮታል። ኦርቶዶክሳወያን መበሳጨት አያስፈልግም ነገሩ ቀላል ነው ሁላችንም እንረባረብና ኢዲት ያደረጉትን እኛም ኢዲት አድርገን ''ወይም ኢድ አደባባይ'' የሚለውን እናጥፋው። እንዲያውም ''Land mark'' የሚለው ላይ ባለቤቱ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ስለሆነች ''Orthodox church'' የሚል እንጨምርበታለን። በቀላሉ አሻራዎን ያሳርፉ ከቤ/ክ ጎን ይቁሙ ። ይህንን ለማድረግ ስልኮት ላይ ጎግል ማፕ (Google map) ይክፈቱ እና ደረጃ በደረጃ ያዘጋጀሁትን አጭር የ Screen shoot instruction ይመልከቱ። N.B ይህንን ለማድረግ የGmail account (email) login info ከጠየቀዎ User name እና password ያስገቡ ከዛም: 1. Google Map Application ይክፈቱ 2. Search Bar ላይ ሄደውMeskel square ብለው ይጻፉ እና Meskele Square, Addis Ababaን ይምረጡ 3. ቀዩን የ ፒን( ) ምልክት ይጫኑ 4. ከመጡት አማራጮች ውስጥ Sugest Edit የሚለውን ይምረጡ 5. Change Name or other details ይጫኑ 6. Meskel Square ከሚለው በታች በአማረኛ የተጻፈውን ''መስቀል አደባባይ ወይም ኢድ አደባባይ'' የሚለውን ይንኩ እና ''ወይም ኢድ አደእናድርግሚለውን'' ያጥፉ እና መስቀል አደባባይን የሚለውን ብቻ ያስቀሩ 7. Historical Land mark ላይ የሚለው ላይ ይግቡ (ባለቤቱ የኦርቶዶክስ ቤ/ክ ስለሆነች) 8. ከአማራጮች ውስጥ Religion የሚለውን ይንኩ 9. ''search more category'' የሚለው መፈለጊያ ባር ላይ Orthodox church የሚል ይጻፉ እና Orthodox church የሚለውን አማራጭ ይጫኑ 10. መጨረሻ ላይ ዝርዝሩ ቼክ ያድርጉ ከላይ በእንግሊዘኛ : Meskel Square በአማረኛ : መስቀል አደባባይ Category : Orthodox church ከዛም ከአናቱ ላይ ያለችውን የቀስት(የ telegram ወይም Send ምልክት) የምትመስለውን ይጫኑ። እርማትዎ ለጎግል ይደርሰዋል። ጎግል የእርማቱን (Edit) ብዛታ ተመልክቶ ''ወይም ኢድ አደባባይ የሚለውን ከቀናት በኋላ ያጠፋዋል። እርሶ ወደነበረበት ''መስቀል አደባባይ'' አርመው (Edit) አድረገው መመለስዎ የቤ/ክ ክብረን መመለስዎ እንደሆነ አይርሱ። ሲጨርሱ ይሄንን ፖስት ለኦርቶዶክሳውያን ያጋሩ! #መስቀል_አደባባይ 💚 •✥• @amanuelhoy •✥•💚 💛 •✥• @amanuelhoy •✥•💛 ❤️ •✥• @amanuelhoy •✥•❤ እባክዎን ሁላችሁንም ሼር እናድርግ
Show all...
⚠️ማስጠንቀቂያ❌❌ ይህ በገሀድ ተጀመሯል። በተለያዩ የቴሌግራም ገፆችና የፌስቡክ አድራሻዎች ነፍስን ለስይጣን ማሥገዛት በሚል የቁም ቅዠት ክቡር የሆነውን የሰውን ልጅ በገንዘብ ብዛት አቅልን አስቶ ከማንነቱ የማስወጣቱ ስራ በእጅጉ እየተስፋፋ ነው። እባካችሁ ወዳጆቼ እኔ ብዙ እምላችሁ የለኝም ነገር ግን ለማመን በሚከብድ ድርጊት በገንዘብ ብዛት በመታለል ብቻ ነፍስን ለሲኦል/ለሣጥናኤል አሳልፎ በመሥጠት ዋጋ ከፍሎ ያዳነን አማላካችን እግዚአብሔርን አናሥቆጣው። እባካችሁ ይህን መልዕክት ለእናንተ ማድረስ የኔ አቅም ነው እናንተም ይህን መልክት ሼር በማድረግ በደካማ ጎናቸው ሜዳ ላይ እንደተዘራ ስንዴ ለሚንከራተቱት ወገኖቻችሁ አስተላልፉልኝ🙏 ቢያንስ ለ10 ሰው ከቻላችሁ ግሩፖች ላይ🙏 ይህን ምታደርጉ ብዙዎችን ትታደጋላችሁ!😍 "ሰዎች ወደዳችሁም ጠላችሁም ምድር ሀላፊ ነች" !!! @yegetemkalat @yegetemkalat
Show all...
ስለ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ውለታና ፍቅር ራሷን እብድ ያደረገችው መነኲሲት ቅዱስ ጳኩሚስ ከመሠረታቸው የታቤኔዝ (ታቤኔሲዮት) ገዳማት መካከል ከወንዶች ገዳማት ራቅ ብሎ የተመሠረተ የሴቶች ገዳም ነበር። በዚያም ውስጥ አራት መቶ ሴቶች መነኮሳይያት ይኖሩ ነበር። በዚያ ገዳም ውስጥ ራሷን እንዳበደችና ርኲስ መንፈስ እንደያዛት የምታስመስል ድንግል ሴት ነበረች። ሌሎቹ እርሷን ከመጸየፋቸው የተነሣ አብረዋት እንኳን አይበሉም ነበር ፤ እርሷ ግን ይህን ወደደችው። በምግብ ማዘጋጃ ቤት ውስጥ ወዲያ እና ወዲህ ትንከራተታለች፣ ሌሎች የተዉትንና የተናቀውን ማንኛውም ሥራ ትሠራለች፣ እነርሱ እንደሚሉት "የገዳሙ ቆሻሻ አስወጋጅ" ነበረች። በሕይወት ዘመኗ ሁሉ ከእህቶች መነኮሳይያት መካከል ማንም በአፏ ስታላምጥ አይተዋት አያውቁም፣ በማዕድም ተቀምጣ አታውቅም ነበር። ከማዕድ የሚወድቀውን ፍርፋሪና የማዕድ ቤት እቃዎችን ስታጥብ ከዚያ በሚገኘው ነገር ብቻ ትኖር ነበር። ማንንም ተሳድባ ወይም ትንሽም ሆነ ብዙ አውርታ አታውቅም፤ ምንም እንኳ ብዙ ትሰደብ፣ ትነቀፍና ትረገም የነበረች ብትሆንም። የእግዚአብሔር መልአክ ፒተሮአም ለሚባል ታላቅና ታዋቂ ለነበረ ታላቅ ባሕታዊ ተገለጠለትና እንዲህ አለው፦ "እንዲህ ባለ ቦታ ስለመኖርህና ስለ ሃይማኖተኛነትህ ለምን በራስህ ትመካለህ? ከአንተ የበለጠ ሃይማኖተኛና ፍጹም የሆነችን ሴት ማየት ትፈልጋለህ? ወደ ታቤኔሲዮት ገዳም ሴቶች ሂድ በዚያም በራሷ ዘውድ የደፋች ሴት ታገኛለህ። እርሷ ከአንተ የበለጠች ናት፤ በብዙዎች መካከል ብትሆንም ልቧ ከፈጣሪዋ ከእግዚአብሔር ውጪ እንዲሄድ ፈጽሞ ፈቅዳለት አታውቅምና፣ አንተ ግን እዚህ ተቀምጠህ በሃሳብ በተለያዩ ቦታዎች ትዞራለህና" አለው። ይህን ሲሰማ ከበኣቱ ወጥቶ የማያውቅ የነበረው ባሕታዊ ወደዚያ ገዳም ሄደና ወደ ገዳሙ ለመግባት ጠየቀ። የታወቀና በዕድሜው የገፋ አረጋዊ ባሕታዊ ስለነበር ወደ ሴቶቹ ገዳም እንዲገባ ፈቀዱለት። በዚያም ሁሉንም መነኮሳይያት ያያቸው ዘንድ ጠየቀ። ሆኖም እርሷ አልመጣችም። በመጨረሻም፦ "የቀረች አንዲት አለችና ሁሉንም አምጡልኝ" አላቸው። እነርሱም፦ "በማዕድ ማዘጋጃ ቤት ያለች አንዲት እብድ ብቻ ናት የቀረችው" አሉት። እርሱም፦ "እርሷንም ጭምር አምጡልኝና ልያት" አላቸው። ሊጠሯት ሄዱ እርሷ ግን ነገሩን አውቃው ይሁን ወይም ጉዳዩ ተገልጦላት መልስ አልሰጠቻቸውም። በግድ ጎተቷትና፦ "ታላቁ ፒተሮአም ሊያይሽ ይፈልጋል" አሏት። በመጣች ጊዜ ከራሷ ላይ ያለውን ብጣሽ ጨርቅ አሰበና ከእግሯ ላይ ወድቆ "ባርኪኝ" አላት። እርሷም እንዲሁ ከእግሩ ላይ ወድቃ "አባቴ ሆይ አንተ ባርከኝ" አለችው። ሁሉም መነኮሳይያት ተገረሙና፦ "አባ እንዳትሰድብህ ተጠንቀቅ እብድ ናት" አሉት። አባ ፒተሮአምም ሁሉንም፦ "እብዶችስ እናንተ ናችሁ እርሷ ግን የእኔም የእናንተም እናት ናት። በፍርድ ቀንም እንደርሷ የተዘጋጀሁና የተገባሁ ሆኜ እገኝ ዘንድ ምኞቴ ነው" አላቸው። እነዚህን ነገሮች ከዚህ አባት ሲሰሙ ሁሉም ያደረጉባትን ነገር እየተናዘዙ ከእግሩ ላይ ወደቁ። አንዲቱ የውኃ እጣቢ አፍስሼባታለሁ ትላለች፣ ሌላዋ ደግሞ መትቻታለሁ ትላለች፣ ብቻ ብዙዎች አንዷ አንድ ሌላዋ ደግሞ ሌላ ነገር እንደፈጸሙባት በመናገር ይናዘዙ ጀመር። እርሱም ከጸለየላቸው በኋላ ሄደ። ከጥቂት ቀናት በኋላ በእህቶቿ መነኮሳይያት የሚደረግላትን ክብር መሸከም ስለከበዳት እንዲሁም ፊት በበደሏት ነገር ሁሉ ይቅርታ አድርጊልን የሚሉት ነገራቸው ስለበዛባት ገዳሙን ጥላ ጠፋች። ወዴት እንደሄደችም ሆነ የት እንደተሰወረች ወይም እንዴት እንደሞተች ግን ማንም ያወቀ የለም። በረከቷ ይደርብን! © በዲ/ን ያረጋል አበጋዝ
Show all...
ቦረዳ ገዳመ ዮርዳኖስ የዋሻ ገዳም በዋሻ ውስጥ የሚከብሩ ታቦታት ያሉበት፣የስውራን አባቶች በዓት ከ1527-43 በተፈፀሙ የግራኝ አህመድ የጥፋት ዘመን ወቅት አባቶች ከየአድባራትና ገዳማት ፅላት ይዘው ይሸሻሉ። በኦቶማን ቱርክ እገዛ ካህናትን እየሰየፈ፣ነዋዬተ ቅዱሳንን እያቃጠለ ፣ቤተክርስቲያንን እያወደመ፣ምዕመናን እያጠፋ ከመጣው የጥፋት መልእክተኛ ሽሽት ብለው ቅዱስን አባቶች ፅላቱን ከእነክብሩ ይዘው ያ ክፉ ዘመን እስኪያልፍ በጋሞ ምድር በቦረዳ ወረዳ በሚገኝ በድንጋይ ተነባብሮ ከተሰራ ድብቅ ዋሻን አደላድለው መቅደስ ሰርተው ያጥኑ ፣ያመሰግኑ፣ መሰዋቱ ያቀርቡ ጀመር። በእዚህ ስርዓት ላይ ሳሉ የእግዚአብሔር መልካም ፍቃድ ሆኖ ሁሉም አባቶች የያዙት ፅላት ሳያወርዱ በስጋ ዕረፍት ወደ ሚናፍቁት ክርስቶስ ተጠሩ። ከግማሽ ክፍለዘመን በላይ በዋሻ ውስጥ የተሰወሩት ታቦታት በቅዱሳን መላእክት እየታጠኑ ምስጋና ከዋሻ ውስጥ ይቀርብ ነበር። ጊዜው ደርሶ በአንድ ኢ-አማኝ በኩል በዋሻው ውስጥ የነበሩት ታቦታት ክብራቸው ገልፀው ለማህበረ ምዕመኑ ተገለጡ። የጢስ እና የምስጋና ድምፅ ከዋሻው ውስጥ ይወጣ ጀመር። ይህን የሰሙት የቤተክህነት አካላት የቅዱስ ሚካኤል እና የቅድስት ስላሴን ታቦተ ህግ ከአባቶች አፅመ ቅዱሳን ላይ አንስተው ከዋሻው አውጥተው ህንፃ መቅደስ አሰርተው ወደ መንበረ ክብሩ መለሱ። በቦታውም ያልወጡ ቀሪ ከ44 በላይ ፅላቶች በዋሻው ውስጥ እስከአሁን ድረስ ከብረው አሉ። በቦታውም ከ44 በላይ ምንጮች ፈልቀው ታላላቅ ታምራትን በቦታው ተደረገ። ሽባ ተተርትሮ ቦረቀ፣ዓይነ ስውሮች ዓይናማ ሆነው አመሰገኑ፤መካኖች ልጅ አቅፈው ተመለሱ፤በደዌ የሚሰቃዩት ከህመማቸው ድነው ነፁ፤ ሸክማቸው የደከመባቸው ግለሰቦች ቀንበራቸው ጥለው አርነት ወጡ። ያለዕምነት ልዩነት ከሁሉም ቤተዕምነት የሚመጡ ሰዎች የስጋና የነፍስ ዕረፍት አገኙ። ይህ ገዳም ቦረዳ ገዳመ ዮርዳኖስ ገዳም ይባላል። በጋሞ ጎፋ ሀገረስብከት በአርባምንጭ ቦረዳ ወረዳ የሚገኝ ትልቅ ሚስጥር የያዘ በዋሻ ውስጥ የሚከብሩ ታቦታት ያሉበት ብቸኛ ገዳም ነው። ዋሻዎች በአንበሳ ነብር እና በልዩ ልዩ አራዊቶች ስለሚጠበቁ ከአባቶች በቀር ማንም ወደ ዋሻው ተጠግቶ አያውቅም ። ይህን ገዳም በመሳለም የበረከቱ ተከፋይ ትሆኑ ዘንድ እናሳስባለን ። # ወስብሐት_ለእግዚአብሔር ╭══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ══╮ @gedamochachn13 ╰══•ೋ•✧๑♡๑✧• ══╯
Show all...
ተዓምራዊቷ ቅድስት ማርያም ውቕሮ ገዳም ግንቦት/6/2013 የቅድስት ማርያም ውቕሮ ገዳም፤ ትግራይ የትግራይ ምድር አቅፎ ከያዛችው ከ120 በላይ የሆኑት ከአለት ተፈልፍለው የታነፁት አብያተ ክርስትያን ለዛሬ አንዱን እናስተዋውቃችሁ። ቅድስት ማርያም ውቕሮ ትባላለች። ወደ አካባቢው ለመድረስ በጣም አስቸጋሪ የጠጠር መንገድና ወንዝ መሻገር የግድ ነው። መኪናችን ወንዙን መሻገር አቅቷት ስትንገዳገድ የተመለከቱት የአከባቢው አርሶ አደሮች ተጠራርተው መንገዱን አስተካክለው አሻግረውናል። ወደ ገዳሙ ቅጥር ግቢ ከተገባ በኋላ መጀመርያ ከአለት የተሰራው ሙዳዬ ምጽዋት ይገኛል። የገዳሙ አስተዳዳሪ ቄስ ዘሚካኤል ወልደጊዮርጊስ ሙዳዬ ምጽዋቱን ከማለፋችን በፊት ጫማችንን እንድናወልቅ ቀጭን ትዕዛዝ አስተላለፉ። በሰንሰለት ዙርያ ጥምጥም የተቆለፈው የገዳሙን በር ከፍተው አስገቡን። የበሩ መዝጊያ ከአንድ የዛፍ እንጨት ብቻ እንደተዘጋጀ ለመረዳት አይከብድም። ቄስ ዘሚካኤል፤ ገዳሟ መቼና እንዴት እንደተቆረቆረች ይናገራሉ። "ይህች ገዳም ንግሥት ማርያም በ333 ጐንደር ላይ ሆነው በህልም ተገልፆላቸው ነበር የታነፀው። ደግሞ የሰው ልጅ በዶማ ቆፍሮ ነው ያነፀው በሉና እመኑ" ሲሉ አፌዙብን። ብታምኑም ባታምኑም 'አብ ሃነጸ ወልድ መንፈስ ቅዱስ' ራሱ መንፈስ ቅዱስ ነው ያነፃት ብለን ነው የምናምነው" ይላሉ። ገዳሟ ውስጥ የአንድ ትልቅ የጥድ ዛፍ ቁመት ያላቸው 44 ዓምዶች ይገኛሉ። በሌሎች ገዳማትና አድባራት እንደሚደረገው ሁሉ በቅድስት ማርያምም ወንዶችና ሴቶች ተለያይተው ነው የሚቀመጡት። በጣሪያው ላይ ሦስት እምነ አድማስ ነበሩ። አንደኛው ወድቆ እንድያውም ጣልያን ለመውሰድ ሞክሮ አልተሳካለትም። ሁለቱ እስከ አሁን ድረስ አሉ። ድንጋዩ ላይ በእብራይስጥ ቋንቋ የተፃፈ ፅሑፍም ይታያል። እምነ አድማስ ድንጋይን ለመቁረጥና ለመጥረብ ኃይል የተሰጠው የድንጋይ ዘር ነው። ገዳሟ ውስጥ ከሚታወቅ ይልቅ የማይታወቀው ስለሚበዛ ቄስ ዘሚካኤል ያስታወሱትንና የነገሩንን ብቻ አሳጥሬ ልንገራችሁ። በአንድ የገዳሟ ጓዳ ውስጥ ልጅ መውለድ የዘገየባችው እንስቶች ተቀምጠው ፈጣርያቸውን የሚለምኑበት ከአለቱ ተፈልፍሎ የተዘጋጀ ወንበር ይታያል። ከፊት ለፊቱ ደግሞ መባ የሚያስቅምጡበት መደርደርያ አለ። በአንደኛው የገዳሟ ክፍል የቅድስት ማርያም መንበረ ታቦት አለ። መንበረ ታቦቱ ራሱ ሙሉ ለሙሉ ከአለት ተፈልፍሎ ነው የተሰራው። ከመንበረ ታቦቱ አናት ላይ 4 ጉልላት ይታያል። ወደ መንበረ ታቦቱ ከካህንና ከዲያቆን ውጪ ምዕመን እንዲገባ አይፈቀድለትም። ገዳሟ ውስጥ የሚገኘው የጨለመው በር ፈለገ ኦር ይባላል። ሊቃውንቱ ጉድጓዱ ቀጥ አድርጐ እስራኤል ነው የሚያስገባው ብለው ያምናሉ። ድሮ ነው አሉ 5 ካህናት ማሾና ጧፍ ይዘው ገብተው በዛው አልተመለሱም ብለውናል። መሪጌታ ቁጭ ብሎ ወደ ታቦቱ እያየ የሚጸልይበት ዙፋንም ተቀርጾ ይታያል። ዙፋኑ ከላይ ዘውድ አለበት፤ ይህም ከአለት ተፈልፍሎ ነው የተዘጋጀው። ገዳሟ ውስጥ የተለያየ ትርጉም ሊሰጣቸው የሚገቡ 5 ጉልላት አሉ፤ የኮከቦች ተምሳሌት ብለው የሚጠሩዋቸው ቅርፆችም አሉ። የገዳሟ የበር መዝጊያዎች ከእየሩሳሌም በቀስተ ደመና ተጠፍረው እንደመጡ ይነገራል። ገዳሟ በር የሌላቸው 12 መስኮቶችም አሉት። ልክ እንደ መንበረ ታቦቱ ከካህንና ዲያቆን ውጪ ሌላው ምዕመን የማይገባበት ቤተልሔምም አለ። በአንድ ትልቅ አለት ላይ ሆኖ ከቅድስት ማርያም በተጨማሪ የቅዱስ ጊዮርጊስ ገዳም አለ። ገዳሟ መወጣጫ አልነበራትም። በቅርቡ አንድ ምግባረ ሰናይ ግለሰብ ከብረት የተዘጋጀ መሰላል አሰርቶላታል። ✞✞✞ ወስብሐት ለእግዚአብሔር ✞✞✞ ✞✞ ወለወላዲቱ ድንግል ✞✞ ✞ ወለመስቀሉ ክቡር ✞ ይቆየን በሌላ የገዳም ታራክ እስከ ምንገናኝ ሠናይ ሶቤ መልካም ጊዜ ╭══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ══╮ @gedamochachn13 ╰══•ೋ•✧๑♡๑✧• ══╯
Show all...