en
Feedback
AIRDROP ROOM

AIRDROP ROOM

Open in Telegram
2 485
Subscribers
No data24 hours
-157 days
-5230 days
Posts Archive
የኢዜማ የወላይታ ዞን አስተባባሪ በፖሊስ ቁጥጥር ስር ዋሉ በደቡብ ክልል የወላይታ ዞን የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ ፓርቲ (ኢዜማ) አስተባባሪ የሆኑት አቶ እስራኤል ካሳ ከዞኑ የፖለቲካ ፓርቲዎ
የኢዜማ የወላይታ ዞን አስተባባሪ በፖሊስ ቁጥጥር ስር ዋሉ በደቡብ ክልል የወላይታ ዞን የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ ፓርቲ (ኢዜማ) አስተባባሪ የሆኑት አቶ እስራኤል ካሳ ከዞኑ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ጋር “በተያያዘ ውዝግብ” በፖሊስ ቁጥጥር ስር ዋሉ። ኢዜማ፤ የፓርቲው የወላይታ ዞን አስተባባሪ እንዲፈቱ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ እርምጃ እንዲወስድ ጠይቋል። በደቡብ ክልል ወላይታ ዞን የኢዜማ አስተባባሪ በፖሊስ ቁጥጥር ስር የዋሉት፤ ከትላንት በስቲያ ረቡዕ ሰኔ 7፤ 2015 መሆኑን የፓርቲው የህግ እና የአባላት ደህንነት ጉዳይ መምሪያ ኃላፊ አቶ ስዩም መንገሻ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናግረዋል። አቶ እስራኤል በፖሊስ በቁጥጥር ሲያዙ የተጠረጠሩበት ምክንያት እንዳልተገለጸላቸውም የፓርቲው የመምሪያ ኃላፊ አስረድተዋል። የወላይታ ዞን የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት በበኩሉ፤ የኢዜማ አስተባባሪው በፖሊስ የተያዙት ቀድሞ በኃላፊነት ሲመሩት ከነበረው ከዚሁ ምክር ቤት ጋር በተያያዘ ነው ብሏል። ከህዳር ወር ጀምሮ በወላይታ ዞን የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ሰብሳቢ የነበሩት አቶ እስራኤል፤ በሚያዝያ ወር ውስጥ “አዲስ አመራሮች በመመረጣቸው” ከኃላፊነታቸው መነሳታቸውን የምክር ቤቱ ምክትል ሰብሳቢ አቶ አብርሃም ጦና ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ገልጸዋል። ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/11201/ @EthiopiaInsidernews

የቀድሞ ተዋጊዎችን ወደ መደበኛ ህይወት ለመመለስ የሚያስፈልገው ከፍተኛ ወጪ፤ ዋነኛ ተግዳሮት እንደሆነ የተሃድሶ ኮሚሽን ገለጸ የቀድሞ ተዋጊዎችን በትኖ ከህብረተሰቡ ለማዋሃድ የሚያስፈልገው “እጅግ ከ
የቀድሞ ተዋጊዎችን ወደ መደበኛ ህይወት ለመመለስ የሚያስፈልገው ከፍተኛ ወጪ፤ ዋነኛ ተግዳሮት እንደሆነ የተሃድሶ ኮሚሽን ገለጸ የቀድሞ ተዋጊዎችን በትኖ ከህብረተሰቡ ለማዋሃድ የሚያስፈልገው “እጅግ ከፍተኛ ወጪ” ዋነኛ ተግዳሮት እንደሆነ የብሔራዊ ተሃድሶ ኮሚሽን አስታወቀ። አጋር አካላት የገንዘብ እርዳታ ለመስጠት የገቡት ቃል፤ በተግባር መታየት እንዳለበትም ኮሚሽኑ አሳስቧል። በተደራጀ ኃይል ውስጥ ታጥቀው ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ኃይሎች ትጥቃቸውን ፈትተው ወደ ማህበረሰቡ በዘላቂነት እንዲቀላቀሉና ሰላማዊ ኑሮ መምራት እንዲችሉ ለማድረግ የተቋቋመው ብሔራዊ የተሃድሶ ኮሚሽን ይህን ያስታወቀው፤ ከትላንት በስቲያ ሰኞ ሰኔ 5፤ 2015 በአዲስ አበባው ሃያት ሪጀንሲ ሆቴል በተካሄደው የመልሶ ማቋቋም እና መገንባት ኮንፍረንስ ላይ ነው። በዚህ ኮንፍረንስ ላይ ጦርነት እና ግጭት ባስተናገዱ ስድስት ክልሎች ውስጥ የደረሰው የውድመት እና የኪሳራ መጠን እንዲሁም ለመልሶ ግንባታ የሚያስፈልገው የገንዘብ መጠን ይፋ ተደርጓል። በዚሁ የውይይት መድረክ፤ የብሔራዊ የተሃድሶ ኮሚሽን ኮሚሽነር ተሾመ ቶጋ ተቋማቸው ስለሚያከናውነው ስራ እና ስላሉበት ተግዳሮቶች ዝርዝር ገለጻ አቅርበዋል። የቀድሞ ተዋጊዎችን ትጥቅ ማስፈታት፣ እንዲበተኑ ማድረግ እና እንደገና ወደ ህብረተሰቡ የማዋሃድ ሂደቶች፤ በኢትዮጵያም ሆነ “በሌሎች ቦታዎች” በሚካሄዱበት ወቅት “የተለያዩ ተግዳሮቶች” እንደሚያጋጥሟቸው ኮሚሽነሩ በመድረኩ ላይ ተናግረዋል። ኮሚሽነር ተሾመ “እጅግ አሳሳቢው ተግዳሮት” ሲሉ የጠቀሱት ጉዳይ፤ ሂደቱን ለመተግበር የሚያስፈልገው ገንዘብ “ከፍተኛነትን” ነው። ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/11188/ @EthiopiaInsiderNews

ዐቃቤ ህግ በ51 ግለሰቦች ላይ የመሰረተው የሽብር ወንጀል ክስ ዝርዝር እና የተከሳሾች የፍርድ ቤት ውሎ አምስት የመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች የተካተቱበት እና በእነ ዶ/ር ወንድወሰን አሰፋ መዝገብ በ
ዐቃቤ ህግ በ51 ግለሰቦች ላይ የመሰረተው የሽብር ወንጀል ክስ ዝርዝር እና የተከሳሾች የፍርድ ቤት ውሎ አምስት የመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች የተካተቱበት እና በእነ ዶ/ር ወንድወሰን አሰፋ መዝገብ በፌደራል ዐቃቤ ህግ የተከፈተው የክስ ቻርጅ፤ በትላንትናው ዕለት ለተወሰኑ ተከሳሾች እንዲደርሳቸው ተደርጓል። ተከሳሾቹ የቀረበባቸው ክስ የወንጀል ህግ እንዲሁም የሽብር ወንጀልን ለመቆጣጠር እና ለመከላከል የወጣው አዋጅ ላይ ያሉ ድንጋጌዎችን ተላልፈዋል በሚል ነው። ሃምሳ አንዱም ተከሳሾች “በዋና ወንጀል አድራጊነት፣ የወንጀሉ ድርጊት በሚሰጠው ውጤት ሙሉ ተካፋይ በመሆን እና ውጤቱን የራሳቸው በማድረግ፣ ወንጀሉን በቀጥታ በመፈጸም እና ወንጀል ለመፈጸም ቀድመው ስምምነት በማድረግ በህብረት እና በማደም በፈጸሙት ሽብር ወንጀል” መከሰሳቸውን ዐቃቤ ህግ በክስ ሰነዱ ላይ አስፍሯል። ተከሳሾቹ “ ‘መነሻችን አማራ መድረሻችን ኢትዮጵያ’ በሚል የፖለቲካ እና የርዕዮት አላማቸውን ለማራማድ በማሰብ”፤ “የሽብር ድርጊት ፈጽመዋል” ሲል ዐቃቤ ህግ ወንጅሏል። ተከሳሾቹ “ፈጽመውታል” በተባለው የሽብር ድርጊት፤ “ከ217 በላይ ሰው እንዲሞት፣ በ297 ሰው ላይ የአካል ጉዳት እንዲደርስ” አድርገዋል በሚል ክስ ቀርቦባቸዋል። ከህይወት መጥፋት እና ከአካል ጉዳት በተጨማሪም፤ 1.298 ቢሊዮን ብር የሚገመት የንብረት ውድመት መድረሱን ዐቃቤ ህግ በክሱ አስፍሯል። ይህ ጉዳት የደረሰው፤ ተከሳሾች “የፖለቲካ እና የርዕዮት አላማቸውን ለማራመድ በማሰብ፣ ህዝብን ለማሸበር እና መንግስትን አስገድዶ ከስልጣን ለማውረድ በማሰብ በፈጸሙት የሽብር ድርጊት” መሆኑን ዐቃቤ ህግ በክሱ ላይ ገልጿል። ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/11183/ @EthiopiaInsiderNews

ኢጋድ፤ የዶ/ር ወርቅነህ ገበየሁን ዋና ጸሀፊነት ለተጨማሪ አራት ዓመታት አራዘመ የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ድርጅት (ኢጋድ) የዋና ጸሀፊው ዶ/ር ወርቅነህ ገበየሁን የስራ ዘመን ለተጨ
ኢጋድ፤ የዶ/ር ወርቅነህ ገበየሁን ዋና ጸሀፊነት ለተጨማሪ አራት ዓመታት አራዘመ የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ድርጅት (ኢጋድ) የዋና ጸሀፊው ዶ/ር ወርቅነህ ገበየሁን የስራ ዘመን ለተጨማሪ አራት ዓመታት አራዘመ። የቀድሞው የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በኢጋድ ዋና ጸሀፊነታቸው እንዲቀጥሉ የተወሰነው፤ ዛሬ ሰኞ ሰኔ 5፤ 2015 በጅቡቲ በተካሄደው የድርጅቱ መደበኛ የመሪዎች ጉባኤ ላይ ነው። ከመሪዎቹ ውሳኔ በኋላ ዶ/ር ወርቅነህ በይፋዊ የትዊተር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት፤ “ጉባኤው በእኔ ላይ ሙሉ መተማመን አሳድሮ የስልጣን ዘመኔን ለሁለተኛ 4 አመት ስላራዘመልኝ ጥልቅ ደስታ ይሰማኛል” ብለዋል። ዶ/ር ወርቅነህ ኬንያዊውን ማህቡብ ማሊምን በመተካት የኢጋድ ዋና ጸሀፊ ሆነው የተሾሙት በህዳር 2012 ዓ.ም ነበር። በዛሬው የኢጋድ ስብሰባ፤ አባል ሀገራት በዙር በሚደርሳቸው የሊቀመንበርነት ኃላፊነት ስልጣን ላይም ለውጥ ተደርጓል። ላለፉት አራት ዓመታት ኢጋድን በሊቀመንበርነት ስትመራ የቆየችው ሱዳን የዛሬውን ጉባኤ ላስተናገደችው ጅቡቲ ኃላፊነቱን አስረክባለች። ኢትዮጵያ ይህን የኃላፊነት ቦታ ለሱዳን አሳልፋ ከመስጠቷ በፊት ለዘጠኝ ዓመታት ኢጋድን በሊቀመንበርነት መምራቷ ይታወሳል። ለሙሉ ዘገባው፦ https://ethiopiainsider.com/2023/11170/ @EthiopiaInsiderNews

ምስላዊ መረጃ፦ የኢትዮጵያ መንግስት ለሚቀጥለው ዓመት ካዘጋጀው በጀት ውስጥ 159 ቢሊዮን ብር ያህሉን የመደበው ለዕዳ ክፍያ ነው። ይህ የገንዘብ መጠን፤ ሊገባደድ አንድ ወር ገደማ ከቀረው የዘንድሮው
ምስላዊ መረጃ፦ የኢትዮጵያ መንግስት ለሚቀጥለው ዓመት ካዘጋጀው በጀት ውስጥ 159 ቢሊዮን ብር ያህሉን የመደበው ለዕዳ ክፍያ ነው። ይህ የገንዘብ መጠን፤ ሊገባደድ አንድ ወር ገደማ ከቀረው የዘንድሮው በጀት ጋር ሲነጻጸር በ33.2 ቢሊዮን ብር ገደማ ጭማሪ አሳይቷል። በጀቱን ያዘጋጀው የገንዘብ ሚኒስቴር ለፓርላማ ባቀረበው የበጀት ሰነድ ላይ “የመንግስት የአገር ውስጥ እና የውጭ ዕዳ ክፍያ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መምጣት የመደበኛ ወጪውን ድርሻ ሊያሳድገው እንደቻለ” አመልክቷል። በ2016 በጀት ዓመት ከፌደራል መንግስት የመደበኛ እና የካፒታል ወጪ ውስጥ ከፍተኛው ድርሻ የተመደበው ለዕዳ ክፍያ ነው። ከአጠቃላይ የመንግስት ወጪ ውስጥ 27.76 በመቶ ከያዘው የዕዳ ክፍያ በመቀጠል በሁለተኛ ደረጃ ላይ የተቀመጠው ለመንገድ ግንባታ የተመደበው በጀት ነው። የትምህርት እና የጤና ዘርፎች በሚያስወጡት ወጪ ብዛት በሶስተኛ እና አምስተኛ ደረጃ ላይ ሰፍረዋል። በመገባደድ ላይ ባለው የበጀት ዓመት ሁለተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጦ የነበረው የመከላከያ ወጪ፤ በመጪው በጀት ዓመት 34 ቢሊዮን ብር ቅናሽ አሳይቶ አራተኛ ደረጃን ይዟል። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር) @EthiopiaInsiderNews

ኮንዶሚኒየም ደርሷቸው “በቀበሌ ቤቶች” ውስጥ የሚኖሩ ግለሰቦች፤ በአንድ ወር ውስጥ ቤቶቹን እንዲያስረከቡ ቀነ ገደብ ተሰጣቸው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር፤ ኮንዶሚኒየም ደርሷቸው “በቀበሌ ቤቶች”
ኮንዶሚኒየም ደርሷቸው “በቀበሌ ቤቶች” ውስጥ የሚኖሩ ግለሰቦች፤ በአንድ ወር ውስጥ ቤቶቹን እንዲያስረከቡ ቀነ ገደብ ተሰጣቸው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር፤ ኮንዶሚኒየም ደርሷቸው “በቀበሌ ቤቶች” ውስጥ የሚኖሩ የከተማዋ ነዋሪዎች እስከ ሰኔ 30 ድረስ የተከራዩዋቸውን ቤቶች እንዲያስረክቡ ቀነ ገደብ አስቀመጠ። የከተማ አስተዳደሩ የሚረከባቸውን እነዚህን የቀበሌ ቤቶች “የደሃ ደሃ” ተብለው ለተለዩ ነዋሪዎች ለማከፋፈል እቅድ መያዙን አስታውቋል። የአዲስ አበባ ቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን የግንባታ ዘርፍ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ቶማስ ደበሌ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” እንደተናገሩት፤ የቀበሌ ቤቶቻቸውን አስረክበው ወደ ኮንዶሚኒየም ቤት እንዲገቡ ደብዳቤ የተሰጣቸው የከተማይቱ ነዋሪዎች፤ በየካቲት 2011 ዓ.ም እና በዘንድሮ ዓመት ህዳር ወር ላይ ዕጣ የወጣላቸው ዕድለኞች ናቸው። በቀድሞ የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ከንቲባ ታከለ ኡማ የሚመራው አስተዳደር፤ በየካቲት 2011 ዓ.ም. ዕጣ ያወጣባቸው የኮንዶሚኒየም ቤቶች ብዛት 51,200 ገደማ ነበር። በወቅቱ ለነዋሪዎች ሊተላለፉ በዝግጅት ላይ እያሉ በተነሳባቸው ተቃውሞ ምክንያት ከባለ እድለኞች ጋር ርክክብ ሳይፈጸምባቸው የዘገዩት እነዚህ የኮንዶሚኒየም ቤቶች፤ የቁልፍ ርክክብ የተፈጸመባቸው ግን ባለፈው ዓመት ነው። የከተማ አስተዳደሩ በዚህ ዓመት ህዳር ወር በ25,791 ቤቶች ላይ ዕጣ ያወጣ ሲሆን፤ ከዕድለኞች ጋር ውል የመዋዋል ስራው የተከናወነው ደግሞ ካለፈው ጥር እስከ ግንቦት ወር ባሉት አምስት ወራት ውስጥ ነበር። ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/11162/ @EthiopiaInsiderNews

በ2016 ለአዳዲስ የካፒታል ፕሮጀክቶች ግንባታ የሚውል በጀት አለመያዙ በፓርላማ ጥያቄ አስነሳ በፌደራል መንግስት እንደ ዘንድሮው ሁሉ በቀጣዩ ዓመትም ለአዳዲስ የካፒታል ፕሮጀክቶች ግንባታ የሚውል በ
በ2016 ለአዳዲስ የካፒታል ፕሮጀክቶች ግንባታ የሚውል በጀት አለመያዙ በፓርላማ ጥያቄ አስነሳ በፌደራል መንግስት እንደ ዘንድሮው ሁሉ በቀጣዩ ዓመትም ለአዳዲስ የካፒታል ፕሮጀክቶች ግንባታ የሚውል በጀት አለመያዙ በፓርላማ ጥያቄ አስነሳ። የፌደራል መንግስት በ2016 በጀት ዓመት ለክልሎች የሚሰጠው የድጎማ በጀት መጠን፤ ከዘንድሮ ዓመት ጋር ሲነጻጸር ያለው ጭማሪ አነስተኛ መሆኑም ጥያቄ ቀርቦበታል። እነዚህ ጥያቄዎች በፓርላማው የተነሱት፤ የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ የ2016 በጀት መግለጫን ትላንት ሐሙስ ሰኔ 1፤ 2015 ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ካቀረቡ በኋላ በነበረው የጥያቄ እና ምላሽ ጊዜ ላይ ነው። አቶ አህመድ በትላንቱ ስብሰባ ላይ የ2016 በጀት፤ የመንግስትን የወጪ ፍላጎት ማካተት በማያስችል የፋይናንስ እጥረት ውስጥ የተዘጋጀ መሆኑን አስታውቀዋል። የፌደራል መንግስት ይህን በጀት ሲያዘጋጅ፤ “የተጀመሩ የካፒታል ፕሮጀክቶችም ቢሆኑ የክፍያ ጊዜያቸውን በማሸጋሸግ የወጪ ቅነሳ ማድረግ እንደሚያስፈልግ ታሳቢ” ማድረጉን ተናግረዋል። በቀጣዩ ዓመት አዳዲስ የካፒታል ፕሮጀክቶችን በበጀት ውስጥ እንዳይካተት መደረጉን ያነሱት የገንዘብ ሚኒስትሩ፤ በጦርነት የወደሙ መሰረተ ልማቶችን መመለስ ላይ ትኩረት ለማድረግ መታሰቡን ለፓርላማ አባላቱ አስታውቀዋል። ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/11157/ @EthiopiaInsiderNews

ሕወሓት በራያ በኩል ከ23 ተሳቢ መኪና በላይ የታጠቀ ኃይሉን እያስጠጋ መሆኑ ተነገረ!! ሕወሓት በዋናነት ከባለፈው ሰኞ ዕለት ጀምሮ በራያ በኩል በኩኩስቶ እና መሆኒ ተብለው በሚጠሩ ሥፍራዎች ከፍተኛ
ሕወሓት በራያ በኩል ከ23 ተሳቢ መኪና በላይ የታጠቀ ኃይሉን እያስጠጋ መሆኑ ተነገረ!! ሕወሓት በዋናነት ከባለፈው ሰኞ ዕለት ጀምሮ በራያ በኩል በኩኩስቶ እና መሆኒ ተብለው በሚጠሩ ሥፍራዎች ከፍተኛ ቁጥር ያለው የታጠቀ ኃይል እያስጠጋ መሆኑ ተገለጸ፡፡ ከሰኞ ግንቦት 28 ጀምሮ እስከ ትናንት ጠዋት ግንቦት 30 ድረስ በ23 ተሳቢ መኪና ዲሽቃ፣ ስናይፐር፣ መትረጊስ እና ክላሽ የታጠቀ ከፍተኛ ቁጥር ያለው የሕወሓት ታጣቂ ኃይል እየተጠጋ መሆኑን አዲስ ማለዳ በአካባቢው ከሚገኙ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች ሰምታለች፡፡ የሕወሓት ኃይሎች በተደጋጋሚ ወደ ድንበር መጠጋት ለምን ዓላማ እንደሆነ በግልጽ የታወቀ ነገር የለም የተባለ ሲሆን፤ የሕወሓት ኃይሎች ትንኮሳ የሚያደርጉ ከሆነ የአላማጣ እና አካባቢው ሕዝብ የአፀፋ ምላሽ ለመስጠት ዝግጁ ነው ተብሏል። የሕወሓት ታጣቂዎች በተጠጉበት አካባቢ የአገር መከላከያ ሠራዊት በመኖሩ ወደ ድንበር እየተጠጋ የነበረውን የአላማጣ እና አካባቢውን ሕዝብ የሕወሓት ኃይሎች ከድንበር አልፈው እንደማይመጡ በማሳወቅ ወጣት እና ሚሊሻዎች እንዲመለሱ መደረጉም ተጠቁሟል፡፡ የአላማጣ ከተማ ከንቲባ ኃይሉ አበራ፤ “እኛ የፕሪቶሪያውን ስምምነት ተቀብለን ተግባራዊ እያደረግን ነው፤ ከዚያ ባሻገር ችግር እንፈጥራለን ካሉ የማንታገስ መሆናችን ልናረጋግጥ እንወዳለን።” ሲሉ ተናግረዋል፡፡ በተያያዘ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ምክትል ፕሬዘዳንት ሌትናል ጄኔራል ጻድቃን ገብረ ትንሳኤ እንዲሁ፤ በወራሪዎች ሥር የሚገኙትን የትግራይ ህገ መንግስታዊ ግዛቶች በአጭር ጊዜ ወደ ትግራይ ክልል ለመመለስ እየተረባረብን ነው ማለታቸውም ተሰምቷል፡፡(አዲስማለዳ) @ethiopianinsider1

ምስላዊ መረጃ፦ የፌደራል መንግስት በ2016 በጀት ዓመት ለክልሎች የመደበው የበጀት ድጋፍ 214 ቢሊዮን ብር መሆኑን አስታውቋል። የአዲስ አበባ እና የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደሮች የተካተቱበት የእዚህ
ምስላዊ መረጃ፦ የፌደራል መንግስት በ2016 በጀት ዓመት ለክልሎች የመደበው የበጀት ድጋፍ 214 ቢሊዮን ብር መሆኑን አስታውቋል። የአዲስ አበባ እና የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደሮች የተካተቱበት የእዚህ የድጋፍ መጠን፤ ከዘንድሮው በጀት ዓመት ጋር ሲነጻጸር የ2.24 በመቶ ጭማሪ ያለው ነው። የክልሎች የበጀት ድጋፍ አመዳደብ “የፌደራል መንግስት ያለውን የሀብት መጠን፣ የፌደራል መንግስት የግዴታ ወጪዎች እና የበጀት ጫናን ግምት ውስጥ በማስገባት” የተዘጋጀ መሆኑን የገንዘብ ሚኒስትሩ አህመድ ሽዴ ተናግረዋል። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር) @EthiopiaInsiderNews

ኢትዮጵያ እና አሜሪካ “ከታቀደለት ዓላማ ውጪ ለሽያጭ ውሏል” የተባለውን እርዳታ ጉዳይ ሊመረምሩ ነው “ከታቀደለት ዓላማ ውጪ ለሽያጭ ውሏል” በተባለው የአሜሪካ የምግብ እርዳታ ጉዳይ ላይ፤ የኢትዮጵያ
ኢትዮጵያ እና አሜሪካ “ከታቀደለት ዓላማ ውጪ ለሽያጭ ውሏል” የተባለውን እርዳታ ጉዳይ ሊመረምሩ ነው “ከታቀደለት ዓላማ ውጪ ለሽያጭ ውሏል” በተባለው የአሜሪካ የምግብ እርዳታ ጉዳይ ላይ፤ የኢትዮጵያ መንግስት “ሙሉ ምርመራ” ለማድረግ መስማማቱን የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት አስታወቀ። ከምርመራው በኋላ ጥፋተኛ ሆነው የሚገኙ አካላትን ተጠያቂ ለማድረግም የኢትዮጵያ መንግስት ቁርጠኝነቱን መግለጹን መስሪያ ቤቱ ገልጿል። ይህን ምርመራ በተመለከተ አሜሪካ እና ኢትዮጵያ በጋራ ለመስራት መስማማታቸውንም የመስሪያ ቤቱ ቃል አቃባይ አስታውቀዋል። ሁለቱ አገሮች ጉዳዩን ለመመርመር የተስማሙት፤ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን እና የአሜሪካው አቻቸው አንቶኒ ብሊንከን ዛሬ በሳዑዲ አረቢያ ተገናኝተው ከተወያዩ በኋላ ነው። ሁለቱ ከፍተኛ ባለስልጣናት ወደ ሳዑዲ አረቢያ የተጓዙት 81 ሀገራትን በአባልነት በያዘው ዓለም አቀፍ ጥምረት ስብሰባ ላይ ለመሳተፍ ነው። ውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮቹ ከዚሁ ስብሰባ ጎን ለጎን በነበራቸው ውይይት የተለያዩ ጉዳዮች መነሳታቸውን የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት ቃል አቀባይ ማቲው ሚለር ዛሬ ሐሙስ ባወጡት መግለጫ አስታውቀዋል። ደመቀ እና ብሊንከን ከተወያዩባቸው ጉዳዮች መካከል “በአማራ እና በኦሮሚያ ክልሎች ያለውን ውጥረት መፍታትን” የተመለከተው ይገኝበታል ተብሏል። ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/11149/ @EthiopiaInsiderNews

የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ በመጪው በጀት ዓመት የ7.9 በመቶ እድገት ያስመዘግባል ተብሎ እንደሚገመት የገንዘብ ሚኒስትሩ አስታወቁ የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ በ2016 በጀት ዓመት 7.9 በመቶ እድገት እንደሚያስመዘግ
የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ በመጪው በጀት ዓመት የ7.9 በመቶ እድገት ያስመዘግባል ተብሎ እንደሚገመት የገንዘብ ሚኒስትሩ አስታወቁ የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ በ2016 በጀት ዓመት 7.9 በመቶ እድገት እንደሚያስመዘግብ መተንበዩን የገንዘብ ሚኒስትሩ አህመድ ሽዴ አስታወቁ። የኢትዮጵያ መንግስት በቀጣዩ በጀት ዓመት ሊሰበስብ ባቀደው ገቢ እና ወጪ መካከል የ281 ቢሊዮን ብር ያልተጣራ የበጀት ጉድለት መታየቱንም ገልጸዋል። አቶ አህመድ ይህን የገለጹት የ2016 የፌደራል መንግስት በጀትን አስመልክቶ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዝርዝር መግለጫ ባቀረቡበት ወቅት ነው። የመጪው ዓመት በጀት የተዘጋጀው “የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ከገጠሙት ቀውሶች ተላቅቆ ሙሉ ለሙሉ ጤናማ አቋም ላይ እንደሚደርስ ታሳቢ ተደርጎ” እንደሆነ የገንዘብ ሚኒስትሩ ዛሬ ሐሙስ ሰኔ 1፤ 2015 በተካሄደው የፓርላማ ስብሰባ ላይ ባቀረቡት የበጀት መግለጫ ላይ ጠቅሰዋል። የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ባለፉት ዓመታት በአማካይ 6.1 በመቶ ዕድገት ሲያመዘግብ መቆየቱን ያስታወሱት አቶ አህመድ፤ ሊጠናቀቅ አንድ ወር በቀረው በዘንድሮው በጀት ዓመት ደግሞ በ7.5 በመቶ እንደሚያድግ መገመቱን ተናግረዋል። በኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ላይ ተጋርጠው የነበሩት ተጽዕኖዎች “በተወሰነ ደረጃ ረገብ በማለታቸው” እና መንግስት ኢኮኖሚው እንዲያንሰራራ እያደረጋቸው ያሉ ጥረቶች “የተሻለ ዕድል” የሚፈጥሩ መሆናቸው ለዚህ ዕድገት መመዝገብ ታሳቢ መደረጋቸውን የገንዘብ ሚኒስትሩ አስረድተዋል። * ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/11137/ @EthiopiaInsiderNews

ሁለት የወላይታ ፖለቲካ ፓርቲዎች በፌዴሬሽን ምክር ቤት ላይ ክስ መሰረቱ የወላይታ ዞን ወደፊት በሚመሰረተው የ“ደቡብ ኢትዮጵያ” ክልል ውስጥ ከሌሎች ዞን እና ወረዳዎች ጋር እንዲደራጅ መወሰኑን የተቃ
ሁለት የወላይታ ፖለቲካ ፓርቲዎች በፌዴሬሽን ምክር ቤት ላይ ክስ መሰረቱ የወላይታ ዞን ወደፊት በሚመሰረተው የ“ደቡብ ኢትዮጵያ” ክልል ውስጥ ከሌሎች ዞን እና ወረዳዎች ጋር እንዲደራጅ መወሰኑን የተቃወሙ ሁለት ተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች፤ በፌዴሬሽን ምክር ቤት ላይ በፍርድ ቤት ክስ መሰረቱ። ፓርቲዎቹ በክስ ማመልከቻቸው ላይ የፌዴሬሽን ምክር ቤት የወላይታ ዞን ከሌሎች መዋቅሮች ጋር እንዲደራጅ ያሳለፈው ውሳኔ እንዲሻር እና የዞኑ ምክር ቤት ከአራት ዓመት ተኩል ገደማ በፊት ወላይታ ክልል እንዲሆን የሰጠው ውሳኔ እንዲጸና ጠይቀዋል። ይህንን ክስ ለፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ያቀረቡት፤ በደቡብ ክልል ወላይታ ዞን ውስጥ የሚንቀሳቀሱት የዎላይታ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ግንባር (ዎሕዴግ) እና የዎላይታ ብሔራዊ ንቅናቄ (ዎብን) ናቸው። ሁለቱ ፓርቲዎች የክስ መዝገቡን በፍርድ ቤት የከፈቱት ባለፈው ሳምንት ሐሙስ ግንቦት 24፤ 2015 መሆኑን የዎብን ሊቀመንበር አቶ አማኑኤል ሞጊሶ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናግረዋል። ዎሕዴግ እና ዎብን ክሱን ባለፈው ሳምንት ቢመሰርቱም፤ ጉዳዩ በየትኛው ችሎት መታየት እንዳለበት ለመወሰን እስከ ዛሬ ረቡዕ ግንቦት 30፤ 2015 በተለያዩ ችሎቶች ሲዘዋወር መቆየቱን የዎሕዴግ ሊቀመንበር አቶ ጎበዜ ጎአ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ገልጸዋል። በጉዳዩ ለመወሰን ለዛሬ ቀጠሮ ሰጥቶ የነበረው የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት፤ የፓርቲዎቹ ክስ “በመሰረታዊ መብቶች እና ነጻነት ችሎት” እንዲታይ መወሰኑንም አስረድተዋል። ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/11133/ @EthiopiaInsiderNews

በ15 ቢሊዮን ብር የጨመረው የ2016 በጀት የሚኒስትሮች ምክር ቤት ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲጸድቅ ያስተላለፈው የ2016 በጀት 801.65 ቢሊዮን ብር መሆኑን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት
በ15 ቢሊዮን ብር የጨመረው የ2016 በጀት የሚኒስትሮች ምክር ቤት ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲጸድቅ ያስተላለፈው የ2016 በጀት 801.65 ቢሊዮን ብር መሆኑን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት ዛሬ ባወጣው መግለጫ አስታውቋል። የፌደራል መንግስት በጀት ባለፉት አምስት አመታት ከ107 ፐርሰንት በላይ ጭማሪ አሳይቷል። በ2012 የፌደራል መንግስት አጠቃላይ በጀት 386.9 ቢሊዮን ብር ነበር። በቀጣዩ 2013 የበጀት መጠኑ በ89.1 ቢሊዮን ጭማሪ አሳይቶ ወደ 476 ቢሊዮን ብር ከፍ ብሏል። የ2014 በጀት በአንጻሩ ከቀደመው ዓመት ከ207.7 ቢሊዮን ብር በላይ ለውጥ የታየበት ነበር። በግንቦት 2013 የሚኒስትሮች ምክር ቤት 561. 7 ቢሊዮን ብር አጽድቆ የነበረ ቢሆንም የፌደራል መንግስት ተጨማሪ 122 ቢሊዮን ብር አስፈልጎታል። በጥር 2014 የጸደቀው ተጨማሪ በጀት “ለሀገር ደህንነት ማስጠበቂያ፣ ለሰብዓዊ እርዳታ፣ በጦርነት እና ግጭቶች ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖች ማቋቋሚያ እንዲሁም ለሌሎች አስፈላጊ የመንግስት ስራዎች ማስፈጸሚያ” የተዘጋጀ እንደነበር የገንዘብ ሚኒስቴር በወቅቱ አስታውቋል። ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/11119/ @EthiopiaInsiderNews

በ15 ቢሊዮን ብር የጨመረው የ2016 በጀት የሚኒስትሮች ምክር ቤት ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲጸድቅ ያስተላለፈው የ2016 በጀት 801.65 ቢሊዮን ብር መሆኑን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት
በ15 ቢሊዮን ብር የጨመረው የ2016 በጀት የሚኒስትሮች ምክር ቤት ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲጸድቅ ያስተላለፈው የ2016 በጀት 801.65 ቢሊዮን ብር መሆኑን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት ዛሬ ባወጣው መግለጫ አስታውቋል። የፌደራል መንግስት በጀት ባለፉት አምስት አመታት ከ107 ፐርሰንት በላይ ጭማሪ አሳይቷል። በ2012 የፌደራል መንግስት አጠቃላይ በጀት 386.9 ቢሊዮን ብር ነበር። በቀጣዩ 2013 የበጀት መጠኑ በ89.1 ቢሊዮን ጭማሪ አሳይቶ ወደ 476 ቢሊዮን ብር ከፍ ብሏል። የ2014 በጀት በአንጻሩ ከቀደመው ዓመት ከ207.7 ቢሊዮን ብር በላይ ለውጥ የታየበት ነበር። በግንቦት 2013 የሚኒስትሮች ምክር ቤት 561. 7 ቢሊዮን ብር አጽድቆ የነበረ ቢሆንም የፌደራል መንግስት ተጨማሪ 122 ቢሊዮን ብር አስፈልጎታል። በጥር 2014 የጸደቀው ተጨማሪ በጀት “ለሀገር ደህንነት ማስጠበቂያ፣ ለሰብዓዊ እርዳታ፣ በጦርነት እና ግጭቶች ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖች ማቋቋሚያ እንዲሁም ለሌሎች አስፈላጊ የመንግስት ስራዎች ማስፈጸሚያ” የተዘጋጀ እንደነበር የገንዘብ ሚኒስቴር በወቅቱ አስታውቋል። ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/11119/ @EthiopiaInsiderNews

#AbiyAhmed #ProsperityParty የብልጽግና ፓርቲ አባላት ብዛት 13.5 ሚሊዮን መድረሱን ፕሬዝዳንቱ አስታወቁ የገዢው ብልጽግና ፓርቲ አባላት ብዛት 13.5 ሚሊዮን መድረሱን የፓርቲው ፕሬ
#AbiyAhmed #ProsperityParty የብልጽግና ፓርቲ አባላት ብዛት 13.5 ሚሊዮን መድረሱን ፕሬዝዳንቱ አስታወቁ የገዢው ብልጽግና ፓርቲ አባላት ብዛት 13.5 ሚሊዮን መድረሱን የፓርቲው ፕሬዝዳንት የሆኑት ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ተናገሩ። ፓርቲው ባለፉት ወራት በመቶ ሺህ አባላቱ ላይ “የማጥራት” እርምጃ መውሰዱን የገለጹት አብይ፤ ወደፊትም ተመሳሳይ አካሄድ መከተል እንደሚያስፈልግ ጥቆማ ሰጥተዋል። አብይ ይህን ያሉት ካለፈው ሳምንት ሐሙስ ጀምሮ ስብሰባውን በማካሄድ ላይ ለሚገኘው የብልጽግና ፓርቲ ማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት በሰጡት ገለጻ ነው። አብይ ወቅታዊውን የፓርቲያቸውን አባላት ብዛት ጉዳይ የጠቀሱት፤ “የኢንተርፕሪዩነራል መንግስትን” የመፍጠር አስፈላጊነት ባስረዱበት የገለጻቸው ክፍል ላይ ነው። ብልጽግና ፓርቲን “በአፍሪካ ትልቁ” ሲሉ የጠሩት የፓርቲው ፕሬዝዳንት፤ በአሁኑ ወቅት ፓርቲው 13.5 ሚሊዮን አባላት እንዳሉት በገለጻቸው አስታውቀዋል። ብልጽግና ፓርቲ አንደኛ ጠቅላላ ጉባኤውን በመጋቢት 2014 ባካሄደበት ወቅት፤ ፓርቲው ያሉት አባላት ብዛት 11 ሚሊዮን እንደሆነ አብይ በወቅቱ ባደረጉት ንግግር ላይ ጠቅሰው ነበር። የአብይ የአሁኑ ገለጻ፤ 2.5 ሚሊዮን አዳዲስ አባላት ባለፈው አንድ ዓመት ገደማ ጊዜ ውስጥ ገዢውን ፓርቲ መቀላቀላቸውን ያመለከተ ሆኗል። ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/11111/ @EthiopiaInsiderNews

በደቡብ ኦሞ ዞን በተከሰተ የኮሌራ እና ወባ ወረርሽኝ፤ በሺህዎች የሚቆጠሩ ሰዎች በበሽታዎቹ መያዛቸው ተገለጸ በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን በአምስት ወረዳዎች የኮሌራ እና ወባ ወረርሽኞች መከሰታቸውን
በደቡብ ኦሞ ዞን በተከሰተ የኮሌራ እና ወባ ወረርሽኝ፤ በሺህዎች የሚቆጠሩ ሰዎች በበሽታዎቹ መያዛቸው ተገለጸ በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን በአምስት ወረዳዎች የኮሌራ እና ወባ ወረርሽኞች መከሰታቸውን የዞኑ ጤና መምሪያ አስታወቀ። በዞኑ ውስጥ ባለው ዳሰነች ወረዳ በዚህ ሳምንት ብቻ 3,800 ገደማ ሰዎች በወባ መሽታ መያዛቸው እንደተረጋገጠም መምሪያው ገልጿል። በስሩ አስር ወረዳዎች እና ሶስት የከተማ አስተዳደሮችን የያዘው የደቡብ ኦሞ ዞን፤ 800 ሺህ ገደማ ነዋሪዎች እንዳሉት ይገመታል። ከእነዚህ የዞኑ መዋቅሮች ውስጥ የኮሌራ ወረርሽኝ የተከሰተው በሐመር፣ በና ጸማይ፣ ማሌ እና ሰሜን አሪ በተባሉት አራት ወረዳዎች መሆኑን የደቡብ ኦሞ ዞን ጤና መምሪያ የጤና እና ጤና ነክ ድንገተኛ አደጋዎች መከላከል ዳይሬክተር አቶ ዮሐንስ ነጋሽ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናግረዋል። በወረዳዎቹ በሚገኙ 27 ቀበሌዎች የሚኖሩ 248 ሰዎች በኮሌራ መጠቃታቸውን እና በወረርሽኙ ሳቢያ አንድ ሰው መሞቱን ዳይሬክተሩ ገልጸዋል። ህይወቱ ያለፈው የሰሜን አሪ ወረዳ ነዋሪ በወረርሽኙ ከተያዘ በኋላ “ወደ ህክምና ባለመምጣቱ” ህመሙ ተባብሶ ለሞት መዳረጉን አቶ ዮሐንስ አስረድተዋል። የኮሌራ ወረረሽኙ ከአካባቢው ነዋሪዎች በተጨማሪ በበና ጸማይ ወረዳ ውስጥ በሚገኘው “ናሳ እርሻ ልማት” የተቀጠሩ የቀን ሰራተኞች ላይ መታየቱንም አክለዋል። ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/11104/ @EthiopiaInsiderNews

#ኤርትራ #ሩስያ የሩሲያ ፕሬዚደንት ቭላዲሚር ፑቲን #የኤርትራ ፕሬዚደንት ኢሳይያስ አፈወርቂን በክሬምሊን ቤተ መንግሥት ተቀብለው አነጋገሩ። የኤርትራ የማስታወቂያ ሚንስትር የማነ ገብረ መስቀል በትዊ
+2
#ኤርትራ #ሩስያ የሩሲያ ፕሬዚደንት ቭላዲሚር ፑቲን #የኤርትራ ፕሬዚደንት ኢሳይያስ አፈወርቂን በክሬምሊን ቤተ መንግሥት ተቀብለው አነጋገሩ። የኤርትራ የማስታወቂያ ሚንስትር የማነ ገብረ መስቀል በትዊተር ገጻቸው ባወጡት ቃል ፤ ፕሬዚደንት ኢሳይያስ እና ፕሬዚደንት ፑቲን ዛሬ ረቡዕ ከቀትር በኋላ ባደረጉት ቆይታ የአገሮቻቸውን የሁለትዮሽ ግንኙነት፤ ዐለም አቀፍ ጉዳዮች እንዲሁም በጋራ ትኩረት በሚሰጧቸው ሁኔታዎች ዙሪያ በስፋት መወያየታቸውን አስታውቀዋል፡፡ አያያዘውም ፤ “የኤርትራ ፕሬዚደንት ኢሳይያስ በሩሲያ ፌዴሬሽን ያደረጉት #የመጀመሪያ ጉብኝት ለሁለቱ ሀገሮች ግንኙነት ትልቅ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ፕሬዚደንት ፑቲን አስምረውበታል” ብለዋል፡፡ “የሁለቱ ሀገሮች ግንኙነት ርምጃ ሙሉ በሙሉ አመርቂ ደረጃ ላይ እንደሚገኝ” ፑቲን መናገራቸው አክለው “በመጪው ሐምሌ ወር ሞስኮ በምታስተናግደው ሁለተኛው የሩሲያ እና የአፍሪካ የመሪዎች ጉባዔ ላይ እንዲገኙ ጋብዘዋቸዋል” ብለዋል፡፡ የኤርትራ ፕሬዚደንት በበኩላቸው ጉብኝታቸው የሁለቱን ሀገሮች ከፍተኛ የአጋርነት እና የምክክር ግንኙነት የሚያንጸባርቅ መሆኑን መናገራቸውን የማስታወቂያ ሚኒስትሩ የማነ ገብረ መስቀል አመልክተዋል፡፡ #ቪኦኤ ፎቶ፦ የማነ ገ/መስቀል @Ethiopianinsider1

#ProsperityParty #AdemFarah ብልጽግና ፓርቲ “ፍላጎታቸውን በኃይል ለማሳካት የሚጥሩ ጽንፈኛ” አካላት “በእጅጉ ፈትነውኛል” አለ ገዢው ብልጽግና ፓርቲ “የነጠላ ቡድናዊ ፍላጎታቸውን በ
#ProsperityParty #AdemFarah ብልጽግና ፓርቲ “ፍላጎታቸውን በኃይል ለማሳካት የሚጥሩ ጽንፈኛ” አካላት “በእጅጉ ፈትነውኛል” አለ ገዢው ብልጽግና ፓርቲ “የነጠላ ቡድናዊ ፍላጎታቸውን በኃይል ለማሳካት የሚጥሩ” እና “ጽንፈኛ የሆኑ” ያላቸው አካላት ባለፉት ወራት በእጅጉ እንደፈተኑት አስታወቀ። በነጻነት አስተዳደር እና አጠቃቀም መካከል “ሚዛን ለማስጠበቅ” በሚደረግ ጥረት ረገድም “ፈተናዎች” እና “ጉድለቶች” ማጋጠማቸውንም ገልጿል። ይህ የተገለጸው ለሁለት ቀናት መደበኛ ስብሰባውን ሲያካሄድ የቆየው የብልጽግና ፓርቲ ሾል አስፈጻሚ ኮሚቴ ስብሰባውን ዛሬ ረቡዕ ግንቦት 23፤ 2013 ማጠናቀቁን ተከትሎ ነው። የገዢው ፓርቲ ሾል አስፈጻሚ ኮሚቴ በዚሁ ስብሰባዎች የተወያየባቸውን ጉዳዮች እና ያስቀመጣቸውን አቅጣጫዎች በተመለከተ ገለጻ ያደረጉት የፓርቲው ምክትል ፕሬዝዳንት አደም ፋራህ፤ ብልጽግና ፓርቲ ባለፉት ወራት “ከፖለቲካ አንጻር የገጠሙትን ፈተናዎች እንደነበሩ” ተናግረዋል። “ባለፉት ወራት…የነጠላ ቡድናዊ ፍላጎታቸውን በኃይል ለማሳካት ፍላጎት ያላቸው የሚጥሩ አካላት፤ በተለይ ጽንፈኛ የሆኑ አካላት፤ ሀገራዊ አንድነታችንን በህብረ ብሔራዊ መሰረት ላይ በጽኑ እንዳንገነባ እጅጉኑ ፈትነውናል” ያሉት አደም ፋራህ፤ ፓርቲው ያጋጠመውን ይህን “ፈተና ለመሻገር” የተለያዩ ስራዎች መሰራታቸውን ገልጸዋል። የፓርቲው ምክትል ፕሬዝዳንት ስራዎቹ ምን እንደነበሩ በዝርዝር ባይገልጹም፤ “ከዚህ አንጻር የተጠናከረ ሾል መስራት ያስፈልጋል” ብለዋል። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር) @EthiopiaInsiderNews

#AmharaRegion #AmharaSayint በአማራ ክልል በአምሃራ ሳይንት ወረዳ ስብሰባ ሲያካሄዱ በነበሩ አመራሮች ላይ የቦምብ ጥቃት ሙከራ ተደረገ በአማራ ክልል ደቡብ ወሎ ዞን አምሃራ ሳይንት ወ
#AmharaRegion #AmharaSayint በአማራ ክልል በአምሃራ ሳይንት ወረዳ ስብሰባ ሲያካሄዱ በነበሩ አመራሮች ላይ የቦምብ ጥቃት ሙከራ ተደረገ በአማራ ክልል ደቡብ ወሎ ዞን አምሃራ ሳይንት ወረዳ ስብሰባ በማካሄድ ላይ በነበሩ የዞን፣ የወረዳ እና ቀበሌ አመራሮች ላይ ትላንት ማክሰኞ ግንቦት 22፤ 2015 የቦምብ ጥቃት ሙከራ መደረጉ ተነገረ። በብልጽግና ፓርቲ የተዘጋጀን ድርጅታዊ ኮንፍረንስ ሲሳተፉ የነበሩትን እነዚህን አመራሮች ኢላማ በማድረግ የተወረወረው ቦምብ ቢፈነዳም፤ በሰው ላይ ጉዳት እንዳልደረሰ የወረዳ አስተዳደሩ አስታውቋል። በአምሃራ ሳይንት ወረዳ መቀመጫ በሆነችው አጅባር ከተማ ይካሄድ በነበረው በዚህ ስብሰባ ላይ ቦምብ የተወረወረው፤ ትላንት ከቀኑ አስር ሰዓት ተኩል ገደማ እንደሆነ የወረዳው የአስተዳደር ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሰይፉ ቦጋለ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናግረዋል። ቦምቡ ስብሰባው ይካሄድበት በነበረው የአምሃራ ሳይንት ወረዳ ምክር ቤት አዳራሽ የውጪያኛው ክፍል ላይ ማረፉንም ኃላፊው አስረድተዋል። “[ቦምቡ] ወደ አዳራሹ ለመግባት አንድ 50 ሴንቲ ሜትር ርቀት ነበር የቀረው። ተፈናጥሮ ግንቡን እና መስታወቱን መትቶታል” ያሉት አቶ ሰይፉ፤ ይህን ተከትሎ በተከሰተው ፍንዳታ የወረዳው ምክር ቤት አዳራሽ መስታወት መሰባበሩን እና የአጥሩ ቆርቆሮ መበጣጠሱን ገልጸዋል። በትላንቱ የጥቃት ሙከራ “በሰው ህይወትም ሆነ በሌላ አካል ላይ የደረሰ ጉዳት የለም” ያሉት የወረዳው ጽህፈት ቤት ኃላፊ፤ ሆኖም ግን ቦምቡ የአካባቢው አመራሮች ስብሰባ እያካሄዱ ባሉበት የተወረወረ በመሆኑ ኮንፍረንሱን “ታላሚ እና ታሳቢ ተደርጎ የተፈጸመ ነው” የሚል እምነት እንዳላቸው አስታውቀዋል። ዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/11085/ @EthiopiaInsiderNews

#MikeHammer #HornOfAfrica በሰሜን ኢትዮጵያው የግጭት ማቆም ስምምነት አፈጻጸም ላይ ለመወያየት፤ የአሜሪካ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ ልዑክ ወደ አዲስ አበባ ሊመጡ ነው የኢትዮጵያ መንግስት እ
#MikeHammer #HornOfAfrica በሰሜን ኢትዮጵያው የግጭት ማቆም ስምምነት አፈጻጸም ላይ ለመወያየት፤ የአሜሪካ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ ልዑክ ወደ አዲስ አበባ ሊመጡ ነው የኢትዮጵያ መንግስት እና ህወሓት ባለፈው ጥቅምት ወር በተፈራረሙት የግጭት ማቆም ስምምነት አፈጻጸም ላይ ለመነጋገር፤ የአሜሪካ አፍሪካ ቀንድ ልዩ ልዑክ ማይክ ሐመር በድጋሚ ወደ አዲስ አበባ ሊመጡ ነው። ሐመር ይህንን ጉዳይ በተመለከተ ከኢትዮጵያ መንግስት እና ከአፍሪካ ህብረት ባለስልጣናት ጋር በአዲስ አበባ፤ ከትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር አመራሮች ጋር ደግሞ በመቐለ ከተማ በመጪዎቹ ቀናት እንደሚወያዩ የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት አስታውቋል። ማይክ ሐመር ከነገ ረቡዕ ግንቦት 23፤ 2015 ጀምሮ ለሰባት ቀናት በአፍሪካ ቀንድ የሚያደርጉት ቆይታ፤ ከኢትዮጵያ በተጨማሪ ጅቡቲንም ያካተተ መሆኑን የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የቃል አቃባይ ጽህፈት ቤት ገልጿል። አምባሳደር ሐመር ወደ ጀቡቲ የሚጓዙት ሀገሪቱ በምታስተናግደው የምስራቅ አፍሪካ የጸጥታ ፎረም ስብሰባ ላይ ለመገኘት መሆኑን የቃል አቃባይ ጽህፈት ቤቱ ዛሬ ባወጣው መግለጫው አመልክቷል። ዝርዝሩን ለማንበብ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/11075/ @EthiopiaInsiderNews