en
Feedback
AIRDROP ROOM

AIRDROP ROOM

Open in Telegram
2 485
Subscribers
No data24 hours
-157 days
-5230 days
Posts Archive
የሰላም ሚኒስትሩ፤ በኢትዮጵያ በተለያዩ አካባቢዎች የሚንቀሳቀሱ ታጣቂዎች ለዜጎች “በጣም ትልቅ አደጋ እና ስጋት ፈጥረዋል” አሉ በኢትዮጵያ አሁን ባለው ተጨባጭ ሁኔታ ለዜጎች “በጣም ትልቅ አደጋ እና ስጋት” እየፈጠሩ ያሉት “የታጠቁ ኃይሎች” መሆናቸውን የሰላም ሚኒስትር አቶ ብናልፍ አንዷለም ተናገሩ። ችግሩን ለመፍታት የሰላም ሚኒስቴር ከሀገር መከላከያ ሰራዊት እና ከህግ አስከባሪ ተቋማት ጋር በቅንጅት እየሰራ መሆኑንም ሚኒስትሩ አስታውቀዋል። የሰላም ሚኒስትሩ ይህን የተናገሩት፤ የሚኒስቴር መስሪያ ቤታቸው የ2015 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ሩብ ዓመት የስራ አፈጻጸም ሪፖርቱን ለተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ግንኙነት እና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ባቀረበበት ወቅት ለተነሱላቸው ጥያቄዎች በሰጡት ማብራሪያ ነው። በዛሬው የፓርላማ ውሎ ጥያቄዎችን ካቀረቡ የቋሚ አባላት መካከል አንዱ የሆኑት አቶ ሞጋ አባቡልጉ፤ በኦሮሚያ ክልል በወለጋ፣ ኢሉባቡር እና ሌሎችም አካባቢዎች የታጠቁ ኃይሎች “በስፋት እየተንቀሳቀሱ” መሆኑን አንስተዋል። “ህዝቡ ከፍተኛ ስቃይ እያየ ነው። የሰው ህይወት እየጠፋ ነው። ንብረት እየጠፋ ነው። ከፍተኛ የሆነ ግጭት ነው ያለው። የብሔር ግጭት አለ። ሌሎችም ችግሮች እየታዩ ስለሆነ፤ ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ እና ህዝቡ በሰላም እንዲኖር የሰላም ሚኒስቴር ድርሻ ምን ይሆናል?” ሲሉ የፓርላማ አባሉ ጥያቄ አቅርበዋል። የሰላም ሚኒስቴር ይህን ችግር ለመፍታት ከሌሎች አካላት ጋር በመተባበር የሚሰራቸው ስራዎችን የመስሪያ ቤቱ ኃላፊዎች እንዲያስረዱ በአቶ ሞጋ ተጠይቀዋል። የሰላም ሚኒስትሩ አቶ ብናልፍ ለዚህ ጥያቄ በሰጡት ምላሽ፤ በ“ሸኔ” እና በሀገሪቱ ነፍጥ አንግበው በሚንቀሳቀሱ ሌሎች ታጣቂዎች ምክንያት “በዜጎች ላይ የሚደርሱ ጉዳቶች አሉ” ሲሉ የጠያቂውን ገለጻ አጠናክረዋል። ታጣቂዎቹ በምዕራብ እና በደቡብ ኢትዮጵያ በሚገኙ አካባቢዎች በዋነኛነት እንደሚንቀሳቀሱ የጠቀሱት ሚኒስትሩ፤ “እነኚህ አካላት ለዜጎች ደህንነት ትልቅ ስጋት ናቸው” በማለት የሁኔታውን አሳሳቢነት አስረድተዋል። * * ዝርዝር ዘገባውን ለማንበብ ይህን ሊንክ ይጫኑ፦ https://ethiopiainsider.com/2022/8525/ @Ethiopianinsider1

" ዳኞች በወንጀል ሲጠረጠሩ ምክንያቱ ታምኖበት ያለመከሰስ መብታቸዉ ከተነሳ በኋላ መሆን ይገባዋል " - ወ/ሮ መአዛ አሸናፊ በኦሮሚያ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ምሥራቅ ምድብ ችሎት የወንጀል ችሎት ዳኛ የሆኑት ፦ 1ኛ ዳኛ ደሳለኝ ለሚ፣ 2ኛ ዳኛ ሙሀመድ ጅማ 3ኛ ዳኛ አብዲሳ ዋቅጅራ ጥቅምት 25 ቀን 2015 ዓ.ም. ከሚሠሩበት ፍርድ ቤት በአዳማ ከተማ ኦሮሚያ ፖሊስ ተወስደው ታስረዋል። ይህን ተከትሎ የኢሰመኮ ዋና ኮሚሽነር ዶ/ር ዳንኤል በቀለ እስራቱ ፈጽሞ ሕገወጥ እና በዳኝነት ነጻነት ላይ የተፈጸመ ጥቃት በመሆኑ በአስቸኳይ ከእስር ሊለቀቁና ድርጊቱ ተጣርቶ ተገቢው እርምጃ ሊወሰድ ይገባል ሲሉ አሳስበዋል። ኢሰመኮ ስለጉዳዩ ባደረገው ማጣራት ዳኞቹ በሕግ የተሰጣቸው ልዩ ጥበቃ መብት በሕጋዊ መንገድ ሳይነሳ እና ዳኞች መሆናቸው ሳይገለጽ ከወረዳ ፍርድ ቤት ተሰጥቷል በተባለ የእስር ትእዛዝ ከሥራ ገበታቸው ላይ ተነስተው የታሰሩ መሆኑን ገልጿል። የእስር ትእዛዙን የሰጠው የወረዳ ፍርድ ቤት ታሳሪዎቹ ዳኞች መሆናቸውን እንደተረዳ የእስር ትእዛዙን የሻረ መሆኑን አሳውቋል፡፡ ዶ/ር ዳንኤል በቀለ ፥ ዳኞቹ ያለ አንዳች ቅድመ ሁኔታ በአስቸኳይ እንዲፈቱ አጥብቀው አሳስበዋል። ትላንት አርብ ኢሰመኮ እስሩን በተመለከተ መግለጫ እስካወጣበት አመሻሽ ድረስ ዳኞቹ በእስር ላይ ነበሩ ፤ ዛሬም ስለመፈታታቸው የተባለ ነገር የለም። ዛሬ የጠቅላይ ፍ/ቤት ፕሬዜዳንት ወ/ሮ መአዛ አሸናፊ የዳኞቹ መታሰር " በጣም አሳሳቢ ነው " ብለዋል። " በትላንትናው ዕለት የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ባወጣው ሪፖርት ሥስት የኦሮሚያ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ዳኞች በአዳማ ከተማ መታሠራቸው በጣም አሳሳቢ ነው " ያሉት ወ/ሮ መአዛ ፥ " ዳኞች የሕግ የበላይነት እንዲረጋገጥ ቁልፍ ሚና ይጫወታሉ " ብለዋል። ወ/ሮ መአዛ ፤ ዳኞች በወንጀል ሲጠረጠሩ ምክንያቱ ታምኖበት ያለመከሰስ መብታቸዉ ከተነሳ በኋላ መሆን እንደሚገባው አስገንዝበው " ስለተከሰተዉ ሁኔታ የበለጠ ለመረዳት እየሞከርን ነዉ። " ሲሉ ገልፀዋል። " ከዚህ ቀደም እንደዚህ ያሉ ተመሳሳይ ድርጊቶች በአንዳንድ ክልሎች በዳኞች ላይ ሲፈጸሙ የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤትና የክልል ፍርድ ቤቶች ፕሌነም አውግዘው ውሳኔ አስተላልፈው ነበር ። " ሲሉ ወ/ሮ መአዛ አስታውሰዋል። @ethiopianinsider1

ኢዜማ በሌሎች የሀገሪቱ ክፍሎች ካሉ የታጠቁ ኃይሎች ጋር በሚደረግ ሰላማዊ ንግግር መፍትሔ እንዲፈለግ ጠየቀ የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ ፓርቲ (ኢዜማ) በሌሎች የሀገሪቱ ክፍሎች ካሉ የታጠቁ ኃ
ኢዜማ በሌሎች የሀገሪቱ ክፍሎች ካሉ የታጠቁ ኃይሎች ጋር በሚደረግ ሰላማዊ ንግግር መፍትሔ እንዲፈለግ ጠየቀ የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ ፓርቲ (ኢዜማ) በሌሎች የሀገሪቱ ክፍሎች ካሉ የታጠቁ ኃይሎች ጋር በሚደረግ ሰላማዊ ንግግር መፍትሔ እንዲፈለግ ጠየቀ። ፓርቲው ዛሬ ሐሙስ በሰጠው መግለጫ፤ በኢትዮጵያ መንግስት እና በህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) መካከል የተደረሰው የሰላም ስምምነት “መርህን የተከተለ” ነው ብሏል። ኢዜማ የዛሬውን ጋዜጣዊ መግለጫ የጠራው በደቡብ አፍሪካ የተደረገውን የሰላም ስምምነት በማስመልከት መሆኑን አስቀድሞ አሳውቆ የነበረ ቢሆንም፤ አብዛኛውን የመግለጫ ጊዜ የወሰደው ግን ዛሬ ሁለተኛ ዓመቱን ለደፈነው የሰሜኑ ጦርነት የተዘጋጀ ዝክር ነበር። በኢዜማ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ ዶ/ር ሙሉዓለም ተገኘወርቅ በንባብ የቀረበው መግለጫ፤ ፓርቲው የሰላም ስምምነቱን በተመለከተ ያለውን አቋም ያሳወቀበት ነው። የትላንቱን የሰላም ስምምነት “ይበል የሚያሰኝ መልካም ጅማሮ” ሲል በመግለጫው የጠራው ኢዜማ፤ “መንግስት የተደረገውን ስምምነት እንዳይጨናገፍ እና ተመልሰን የጦርነት አዙሪት ውስጥ እንዳንገባ ከፍተኛ ጥንቃቄ ማድረግ ይኖርበታል” ሲል አሳስቧል። “የሀገር ሉዓላዊነት እና የግዛት አንድነት ለማስከበር ትጥቅ ይዞ የሚንቀሳቀስ እና የማዘዝ ስልጣን ሊኖረው የሚገባው፤ የፌደራል መንግስት ብቻ ስለመሆኑ ሀገራዊም ዓለም አቀፋዊ ድንጋጌዎች አስረግጦ በማስገንዘብ፤ ህወሓት ትጥቁን እንዲፈታ ሊደረግ ይገባል” ሲል ፓርቲው አቋሙን አስረግጧል። * * ሙሉ ዘገባውን ለማንበብ ይህን ሊንክ ይጫኑ፦ https://ethiopiainsider.com/2022/8489/ @ethiopianinsider1

ስለ ኢትዮጵያ የሰላም ስምምነት ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ምን አለ? የኢትዮጵያ ፌደራል መንግስት እና ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) ትላንት ረቡዕ የተፈራረሙት የሰላም ስምምነት፤ የሁለት ዓመ
ስለ ኢትዮጵያ የሰላም ስምምነት ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ምን አለ? የኢትዮጵያ ፌደራል መንግስት እና ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) ትላንት ረቡዕ የተፈራረሙት የሰላም ስምምነት፤ የሁለት ዓመታቱ ደም አፋሳሽ ጦርነት በድርድር እንዲቋጭ ግፊት ሲያደርግ ከቆየው ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ አዎንታዊ ምላሽ አግኝቷል። የኢትዮጵያ ጎረቤት ሀገራት መሪዎች እና ሌሎች የአፍሪካ ፖለቲከኞችም አድናቆታቸውን ገልጸዋል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ጸሀፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ፤ ሁለቱ ተፋላሚ ኃይሎች የተፈራረሙት ስምምነት “የበርካታ ኢትዮጵያውያን ህይወት እና መተዳደሪያ የጠፋበትን የሁለት ዓመት ጦርነት ለማቆም ወሳኝ እርምጃ” ሲሉ ገልጸውታል። ዋና ጸሀፊው የኢትዮጵያ ፌደራል መንግስት እና ህወሓት ወስደውታል ያሉትን “ደፋር እርምጃ”፤ የአገሪቱ ህዝብ እና ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ እንዲደግፍ ጥሪ አቅርበዋል። ለሁለት ዓመት ያህል በተካሄደ ደም አፋሳሽ ጦርነት ሲዋጉ የቆዩ ኃይሎች ለድርድር እንዲቀመጡ ግፊት ስታደርግ የቆየችው አሜሪካም ለሰላም ስምምነቱ ተመሳሳይ አድናቆቷን ገልጻለች። የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን፤ የኢትዮጵያ ፌደራል መንግስት እና ህወሓት ግጭት ለማቆም እና በዋና ዋና ልዩነቶቻቸው ላይ ድርድር ለመቀጠል በመስማማታቸው አሞግሰዋል። * * ዝርዝር ዘገባውን ለማንበብ ይህን ሊንክ ይጫኑ፦ https://ethiopiainsider.com/2022/8480/ @Ethiopianinsider1

የኢትዮጵያ ፌደራል መንግስት እና ህወሓት ግጭት ለማቆም መስማማታቸውን ኦሊሴጉን ኦባሳንጆ አስታወቁ የኢትዮጵያ ፌደራል መንግስት እና ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) ግጭት ለማቆም መስማማታቸው
የኢትዮጵያ ፌደራል መንግስት እና ህወሓት ግጭት ለማቆም መስማማታቸውን ኦሊሴጉን ኦባሳንጆ አስታወቁ የኢትዮጵያ ፌደራል መንግስት እና ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) ግጭት ለማቆም መስማማታቸውን የአፍሪካ ህብረት የአፍሪካ ቀንድ ልዩ ልዑክ ኦሊሴጉን ኦባሳንጆ ተናገሩ። ካለፈው ሳምንት ማክሰኞ በአፍሪካ ህብረት መሪነት ሲካሄድ የቆየው የሰላም ንግግር ወደ ስምምነት ማምራቱን ኦባሳንጆ የገለጹት፤ ዛሬ በደቡብ አፍሪካ ፕሪቶሪያ ከተማ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ነው። በቀድሞው የናይጄሪያ ፕሬዝዳንት ኦሊሴጉን ኦባሳንጆ አመቻችነት ሲካሄድ የቆየው የሰላም ንግግር ለሁለት ዓመታት ገደማ ውጊያ ውስጥ የቆዩት የኢትዮጵያ ፌደራል መንግስት እና የህወሓት ተደራዳሪዎች በይፋ ለመጀመሪያ ጊዜ ፊት ለፊት የተገናኙበት ነው። በሰላም ንግግሩ የቀድሞው የኬንያ ፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬንያታ እና የቀድሞዋ የደቡብ አፍሪካ ምክትል ፕሬዝዳንት ዶክተር ፑምዚ ለምላምቦ “በደጋፊነት” ተካፍለውበታል። ከአንድ ሳምንት በላይ የተካሔደው የሰላም ንግግር የተባበሩት መንግስታት ድርጅት (ተመድ)፣ የአሜሪካ መንግስት እና የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ድርጅት (ኢጋድ) ተወካዮች “በታዛቢነት ተሳትፈውበታል። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር) @Ethiopianinsider1

የ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ጥያቄ፦ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መንግስት፤ ከግዢ፣ ከቢሮ ኪራይ እንዲሁም ከተሽከርካሪ አጠቃቀም እና ጥገና ጋር በተያያዘ ብዙ ወጪዎች እንዳሉበት በመመሪያው ተገልጿል። ከእነዚህን ወጪዎች ጋር በተያያዘ የነበረው የበጀት አጠቃቀም፤ ክፍተቶች ነበሩበት? አዲሱ “የወጪ ቅነሳ እና ቁጠባ ስርዓት መመሪያ” ምን አይነት ገደቦችን እና ክልከላዎችን ነው ያደረገው? የአቶ ዚያድ አብዱላሂ (የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የገንዘብ እና ኢኮኖሚ ቢሮ ኃላፊ) ምላሽ፡- በአመራር ደረጃ፤ አንዱ ከፍተኛ ወጪ የምናወጣው ለነዳጅ ነው። አመራሩ ያለገደብ ነበር ነዳጅ በወር የሚጠቀመው። በክልላችን አንድ መኪና መስክ እንኳን ሳይሄድ እዚህ [ከተማ] ዙሪያ ላይ በሚያደርጋቸው እንቅስቃሴዎች ብቻ በወር ከ200 እስከ 300 [ሊትር] ድረስ ይጠቀማል። አሁን ኮር አመራሮችን ሳይጨምር “ከ70 ሊትር በላይ መጠቀም አይቻልም” የሚለው አንዱ ገደብ የጣልንበት ጉዳይ ነው። ሌላው luxury [ቅንጡ] ላፕቶፕ እና የሞባይሎች ስልክ አንዳንድ ጊዜ ይገዛሉ። ከሌሎች ክልሎች ጋር ስናነጻጽረው ብዙም የተጋነነ ነው ባይባልም፤ በእኛ ክልል ተጨባጭ ሁኔታ ለአንድ ሞባይል ከ70 እስከ 80 ሺህ ብር ድረስ ይወጣል። በዚህ ዓመት ይህን በሙሉ ለልማት ለማዋል ሲባል፤ ምንም አይነት የላፕቶፕም ሆነ የሞባይል ግዢ ለየትኛውም አመራር መግዛት እንደማይቻልና በራሱ ገንዘብ እንዲገዛ የሚል ነው አንዱ መመሪያው ላይ ያስቀመጥነው። አዲስ አመራር ተሹሞ ከመጣ እና ምናልባትም በተለየ መልኩ መገዛት ካለበት ተፈቅዶ ይገዛል። መኪና ጥገና ላይም ዝም ብሎ ያለ ውድድር በቀጥታ በተለያዩ ኩባንያዎች እና የግል ጋራጆች ገብተው የሚጠገኑበት ሁኔታ ነበር። ከዚህም ጋር ተያይዞ የክልሉ ጋራጅ በአፋጣኝ ወደ ስራ እንዲገባ እያደረግን ነው። የክልሉ የገጠር መንገዶች ባለስልጣን የሚባል ጋራጅ አለ። እሱን እስከ መስከረም 30 ወደ ስራ አስገብተን፤ አብዛኛው [የተሽከርካሪ] ጥገና በመንግስት፤ ወጪ ቆጣቢ በሆነ አግባብ ይደረጋል። ከፍ ከፍ ያሉትን እና ሞተራቸው ውስብስብ የሆኑትን “በሞኢንኮ” ማስጠገን እንደተጠበቀ ሆኖ፤ ከጋራጁ [አቅም] በላይ የሚሆኑ ካሉ ደግሞ በቀጥታ መግባታቸው ቀርቶ በውድድር ብቻ በመንግስት አሠራር ይከናወናል። ሌላው እንደኛ ክልል፤ አላቂ እቃዎች ላይ ከፍተኛ ወጪ እናወጣለን። እዚያ አካባቢም ገደብ ጥለናል። ግንባታዎች አካባቢም ሆን ብሎ ግንባታን ማጓተት ይስተዋላል። ግንባታዎችን አጓትቶ፤ የጊዜም ሆነ የጥራት እንዲሁም የበጀት ጉድለት የሚያስከትሉ ኃላፊዎችም ሆኑ የስራ ክፍሎች [ላይ] እስካሁን ድረስ ተጠያቂነት የሚያስከትል አሰራር አልነበረም። አሁን ግን ህጋዊም ሆነ አስተዳደራዊ እርምጃ እንደሚወሰድ መመሪያችን ላይ አመላክተናል። ለጨረታ ተብሎ አዲስ አበባ በተደጋጋሚ [የሚደረጉ] መመላለሶች ነበሩ። እንደምታውቀው በኮሚቴ ነው ግዢ የሚፈጸመው። የጨረታ ኮሚቴ የሚባል አለ። አዲስ አበባ ላይ ብዙ ተጽዕኖ ላይፈጥር ይችላል። እንደኛ ክልል ግን ከአንድ ቢሮ ብቻ ከ10 ያላነሰ ሰው በዓመት ቢያንስ ሁለት እና ሶስት ጊዜ ይመላለሳል። ከአሁን በኋላ ባሉት የጨረታ ሂደቶች ለጨረታ አዲስ አበባ መሄድ ቀርቶ አሶሳ በክልል ማዕከል ብቻ ይከናወናል። * * ከቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የገንዘብ እና ኢኮኖሚ ቢሮ ኃላፊ አቶ ዚያድ አብዱላሂ ጋር የተደረገውን ሙሉ ቃለ ምልልስ ለማንበብ ይህን ሊንክ ይጫኑ፦ https://ethiopiainsider.com/2022/8199/

የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል፤ አዲሱ “የወጪ ቅነሳ እና ቁጠባ ስርዓት መመሪያ” ምን አይነት ገደቦችን በውስጡ ይዟል? የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልላዊ መንግስት ለ2015 በጀት ዓመት ጥብቅ “የወጪ ቅነሳ እና ቁጠባ ስርዓት መመሪያ” ተግባራዊ ማድረግ መጀመሩን አስታውቋል። በክልሉ መንግስት መስተዳድር ምክር ቤት የዛሬ ሁለት ሳምንት ገደማ የጸደቀው ይህ መመሪያ፤ በደመወዝ አከፋፈል፣ በሰራተኛ ቅጥር፣ ለመንግስት ሰራተኞች በሚሰጥ የትምህርት ዕድል ላይ ብርቱ ቁጥጥር የሚያደርግ ነው። በዚሁ የክልሉ መመሪያ ላይ፤ የቢሮ ኪራይ፣ የቋሚ እና አላቂ ዕቃዎች ግዢ፣ የተንቀሳቃሽ ስልኮች፣ ላፕቶፖች፣ ሞተር ሳይክሎች ግዢ እና የጨረታ ሂደት ላይ የተደረጉ ገደቦች ተካትተዋል። አዲሱ መመሪያ፤ የክልሉ መስሪያ ቤቶች ከተመደበላቸው በጀት በላይ “ወጪ ማድረግን ወይም በጀት ሳይጸድቅ በታሳቢ እየተባለ ከፍተኛ ወጪ” ማውጣትን ይከለክላል። በመመሪያው መሰረት፤ የክልሉ የመንግስት መስሪያ ቤቶች “የተለያዩ ጥቅማ ጥቅሞችን በራስ ተቋም ብቻ በማጽደቅ ክፍያ መፈጸም” አይችሉም። መስሪያ ቤቶቹ “ደመወዝ እና ጥቅማ ጥቅምን” በተመለከተ ለክልሉ መስተዳድር ምክር ቤት አቅርበው በካቢኔ ካልጸደቀላቸው በስተቀር፤ ከዚህ ቀደም እንደነበረው “በሰርኩላር በተዋረድ ማስተላለፍ” እንደማይፈቅድላቸው በመመሪያው ተቀምጧል። በ14 ገጾች የተዘጋጀው ይህ መመሪያ፤ በጥቅማ ጥቅም ክፍያዎች፣ በተሽከርካሪዎች አጠቃቀም እና ጥገና እንዲሁም በነዳጅ እና ቅባት አጠቃቀም ላይ ተግባራዊ የሚደረጉ የወጪ ቅነሳ እና ቁጠባ እርምጃዎችን ዘርዝሯል። የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል አመራሮች ለስልጠና እና የመስክ ስራ በሚያደርጓቸው ጉዞዎች ተሽከርካሪዎችን “በተናጠል ሳይሆን ስራዎችን በማቀናጀት እና በማስተባበር በቅንጅት መጠቀም” እንዳለባቸው የሚያሳስበው መመሪያው፤ ለስራ ኃላፊዎች የሚፈቀደውን የነዳጅ ፍጆታ መጠንም በሊትር ገድቧል። የክልሉ ኮር አመራሮች፣ የጸጥታ እና የፖሊስ ኮሚሽን የስራ ኃላፊዎች፤ በከተማ ውስጥ ለሚኖራቸው እንቅስቃሴ እስከ 150 ሊትር ነዳጅ እንዲጠቀሙ በመመሪያው ተፈቅዶላቸዋል። ሌሎች የበላይ ኃላፊዎች ለሚያደርጓቸው ተመሳሳይ ጉዞዎች በወር 70 ሊትር ነዳጅ መፈቀዱን የሚገልጸው መመሪያው፤ ከዚያ በላይ ለሚደረግ እንቅስቃሴ ግን ኃላፊዎች ወጪውን ራሳቸው እንደሚሸፍኑ ደንግጓል። ከመስከረም 4፤ 2015 ጀምሮ ተግባራዊ መደረግ እንደጀመረ በተነገረለት በዚህ መመሪያ፤ በክልሉ የሚካሄዱ ስብሰባዎች እና ስልጠናዎችን በተመለከተም ገደቦች ተቀምጠዋል። ስብሰባዎችን እና ስልጠናዎችን ለማካሄድ ለአዳራሽ ኪራይ የሚወጣ ክፍያ ለማስቀረት፤ የክልሉ መስሪያ ቤቶች በመንግስት ተቋማት አዳራሾች እንዲጠቀሙ መመሪያው አዝዟል። በመደበኛ በጀትም ሆነ ከልማት አጋሮች ወይም ባለድርሻ አካላት ጋር ለሚካሄዱ ስብሰባዎች እና ክብረ በዓል ተሳታፊዎች፤ ቦርሳ፣ ቲ ሸርት፣ ኮፊያ እና ሻርፕ መግዛትም በመመሪያው ተከልክሏል። በርከት ያሉ የወጪ ቅነሳ እና ቁጠባ እርምጃዎች የተካተቱበት ይህን መመሪያ በተመለከተ የ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደሩ” ሃሚድ አወል፤ ከቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የገንዘብ እና ኢኮኖሚ ቢሮ ኃላፊ አቶ ዚያድ አብዱላሂ ጋር በስልክ ቆይታ አድርጓል። ሙሉ ቃለ ምልልሱን ለማንበብ ይህን ሊንክ ይጫኑ፦ https://ethiopiainsider.com/2022/8199/ @ethiopianinsider1

ማስታወቂያ ‼️ ከማጭበርበር/ቺት በኋላ እንዴት ማመን ይቻላል? በሚታወቀው የአንድ ነጠላ ግንኙነት ውስጥ ከሆንክ እና ከተታለልክ "ሰውን እንደገና እንዴት ማመን ይቻላል?" አግባብነት የለውም። መልሱ ምንም ዳግመኛ ማመን መንገድ አይደለም. ከዚህ በፊት ባመኑበት መንገድ ይህን ሰው የማመን ችሎታዎን መልሰው ማግኘት አይችሉም። እና ሁለት አማራጮች አሉዎት፡ አንድም ከእሱ ጋር ግንኙነት ለመፍጠር እና አለመተማመንዎን እንደ ተሰጠ እና የማይቀር አድርገው መውሰድ ወይም መለያየት። ደህና ፣ በግንኙነት ውስጥ በመቆየት ፣ እራስዎን በማሰቃየት እና በማሰቃየት ፣ "እንዴት እንደሚታመን?" - አማራጭ አይደለም. እሱ በኒውሮቲክ ራስ ላይ ማሾፍ ብቻ ነው : https://t.me/sexologistGirum

አዲስ አበባ የሚዘጉ መንገዶች ! ሰኞ መስከረም 16 ቀን 2015 ዓ/ም በመስቀል አደባባይ የሚካሄደውን የደመራ የመለኮስ ስነ-ስርአት ተጀምሮ እስከሚጠናቀቅ ድረስ ፦ •  ከመገናኛ ወደ መስቀል አደባባይ እንዲሁም  ከኤድናሞል በአትላሳ ወደ ካዛንቺስ የሚወስደው መንገድ  ኡራኤል አደባባይ • ከጎተራ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ አጎና ሲኒማ • ከጎፋ በአዲሱ መንገድ ወደ  ለገሃር  ለሚመጡ ቂርቆስ ቤተ ክርስቲያን መስቀለኛ ላይ • ከቡልጋሪያ በሜክሲኮ አደባባይ ወደ ለገሃር የሚሄዱ ጠማማ ፎቅ አካባቢ •  ከሳር ቤት ወደ ሜክሲኮ አደባባይ እንዲሁም ከጦር ኃይሎች በልደታ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ወደ ለገሃር  የሚወስደው ሚክሲኮ አደባባይ • ከተከለ ሃይማኖት በጎማ ቁጠባ  ወደ ለገሃር ሰንጋተራ 40/60 ኮንደሚኒዬም አካባቢ • ከጌጃ ሰፈር ፣ በአምስተኛ ፖሊስ ጣቢያ የሚሄዱ አሽከርካሪዎች ጎማ ቁጠባ • ከመርካቶ በተክለ ሃይማኖት ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ሜትሮሎጂ በር ላይ • ከራስ ቴአትር በጎላ ሚካኤል ውስጥ ለውስጥ ጎላ ሚካኤል መስቀለኛ • ከተክለ ሃይማኖት ጥቁር አንበሳ ኢሚግሬሽን ጥቁር አንበሳ ሼል • ከፒያሳ በቸርችር ጎዳና ለገሃር ቴዎድሮስ አደባባይ • በአሮጌው ቄራ ፍል ውሃ ንግድ ማተሚያ ቤት • ከካዛቺስ ወደ ሂልተን ካዛንቺስ ቶታል • ከአዋሬ በካዛንቺስ ወደ ፍል ውሃ የሚወስደው መንገድ የቀድሞ 6ኛ ፖሊስ መታጠፊያ ላይ ከቀኑ 5 ሰዓት ጀምሮ ዝግጅቱ እስከሚጠናቀቅ ለተሽከርካሪዎች ዝግ እንደሚሆን የአዲስ አበባ ፖሊስ አሳውቋል። ህብረተሰቡ ይህን አውቆ አማራጭ መንገዶችን እንዲጠቀም መልዕክት አስተላልፏል። በተገለፁት መንገዶች ላይ ለአጭርም ሆነ ለረጅም ሰዓት ተሽከርካሪ አቁሞ መሄድ ፍፁም ክልክል ነው ተብሏል። @ethiopianinsider1

ከኮንዶሚኒየም ዕጣ ማጭበርበር ጋር በተያያዘ በታሰሩ ኃላፊዎች ላይ ክስ የሚመሰረትበት ጊዜ በአምስት ቀናት ተራዘመ ከኮንዶሚኒየም ዕጣ ማጭበርበር ጋር በተያያዘ ታስረው ምርመራ ሲደረግባቸው በቆዩት የቀ
ከኮንዶሚኒየም ዕጣ ማጭበርበር ጋር በተያያዘ በታሰሩ ኃላፊዎች ላይ ክስ የሚመሰረትበት ጊዜ በአምስት ቀናት ተራዘመ ከኮንዶሚኒየም ዕጣ ማጭበርበር ጋር በተያያዘ ታስረው ምርመራ ሲደረግባቸው በቆዩት የቀድሞው የአዲስ አበባ ከተማ ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ሙሉቀን ሀብቱ እና ሌሎች ግለሰቦች ላይ ክስ ለመመስረት ተጨማሪ አምስት ቀናት ተፈቀደ። የክስ መመስረቻ ጊዜውን ያራዘመው የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ የጊዜ ቀጠሮ ችሎት ነው። ችሎቱ ለሁለተኛ ጊዜ የክስ መመስረቻ ጊዜውን የፈቀደው፤ ዐቃቤ ህግ “በሰነዶች ብዛት” ምክንያት ክስ ለመመስረት አለመቻሉን ገልጾ ተጨማሪ ቀናት እንዲሰጡት ከጠየቀ በኋላ ነው። ዐቃቤ ህግ ዛሬ አርብ መስከረም 6፤ 2014 በዋለው ችሎት ተጨማሪ ቀናትን የጠየቀው፤ ማስረጃዎችን ማስተንተን እንደሚያስፈልገው በመግለጽ ነው። ይህንን የፖሊስ ጥያቄ የተጠርጣሪው ጠበቃ አቶ ሞላልኝ መለሰ ተቃውመውታል። ባለፈው ሳምንት በነበረው የፍርድ ቤት ውሎ፤ ዐቃቤ ህግ ክስ ለመመስረት ያስችለው ዘንድ ሰባት ቀናት እንደተፈቀዱለት ያስታወሱት ጠበቃው፤ ለሁለተኛ ጊዜ ተጨማሪ ቀናት ሊፈቀድለት አይገባም ሲሉ ተከራክረዋል። ችሎቱ የዐቃቤ ህግን ጥያቄ ውድቅ በማድረግ የደንበኛቸውን የዋስትና መብት እንዲያስከብርላቸው ጠበቃው ጠይቀዋል። * * ሙሉ ዘገባውን ለማንበብ ይህን ሊንክ ይጫኑ፦ https://ethiopiainsider.com/2022/8120/ @ethiopianinsider1

በጋዜጠኛ መዓዛ መሐመድ እና ጎበዜ ሲሳይ ላይ “ለመጨረሻ ጊዜ” አምስት የምርመራ ቀናት ተፈቀደ የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት፤ “በሽብር ፈጠራ ወንጀል” በተጠረጠሩት ጋዜጠኛ መዓዛ መሐመድ እና ጎበዜ ሲ
በጋዜጠኛ መዓዛ መሐመድ እና ጎበዜ ሲሳይ ላይ “ለመጨረሻ ጊዜ” አምስት የምርመራ ቀናት ተፈቀደ የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት፤ “በሽብር ፈጠራ ወንጀል” በተጠረጠሩት ጋዜጠኛ መዓዛ መሐመድ እና ጎበዜ ሲሳይ ላይ ለሁለተኛ ጊዜ አምስት የምርመራ ቀናት ፈቀደ። ፍርድ ቤቱ የምርመራ ቀናቱን የፈቀደው ለመጨረሻ ጊዜ መሆኑን ዛሬ አርብ መስከረም 6፤ 2015 በዋለው ችሎት አስታውቋል። የጊዜ ቀጠሮ ችሎቱ ለዛሬ ቀጥሮ የነበረው፤ ፖሊስ ከዚህ በፊት በነበረው የፍርድ ቤት ውሎ በተፈቀዱለት ሰባት የምርመራ ቀናት ያከናወናቸውን ተግባራት ለማድመጥ ነበር። ፖሊስ በተፈቀዱለት ቀናት ተጠርጣሪዎችን ማነጋገሩን እንዲሁም ከኢትዮ ቴሌኮም እና ከብሔራዊ መረጃ እና ደህንነት አገልግሎት ማስረጃዎች መጠየቁን አስረድቷል። ከዚህ በተጨማሪም የተጠርጣሪዎችን የጣት አሻራ መውሰዱን እና የኤሌክትሮኒክስ እቃዎች ለምርመራ መላኩን ለችሎቱ ገልጿል። ካለፈው ሳምንት ረቡዕ ጷጉሜ 2፤ 2014 ጀምሮ ሁለቱን የመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች አስሮ እየመረመረ የሚገኘው የፌደራል ፖሊስ “ቀሪ ስራዎችን ለማከናወን” በሚል 14 የምርመራ ቀናት እንዲፈቀዱለት የጊዜ ቀጠሮ ችሎቱን ጠይቋል። ሁለቱን ጋዜጠኞች ወክለው በችሎት የተገኙት አራት ጠበቆች ፍርድ ቤቱ ፖሊስ ያቀረበውን ጥያቄ ውድቅ በማድረግ የተጠርጣሪዎችን ዋስትና እንዲያስጠብቅ ጠይቀዋል። * * ዝርዝር ዘገባውን ለማንበብ ይህን ሊንክ ይጫኑ፦ https://ethiopiainsider.com/2022/8113/ @ethiopianinsider1

ኡሁሩ ኬንያታ ለሰሜን ኢትዮጵያው ግጭት “የሰላም ልዩ ልዑክ” ሆነው መሾማቸውን አሜሪካ አደነቀች በሰሜን ኢትዮጵያ እና በዴሞክራቲክ ሪፐብሊንክ ኮንጎ እየተካሄዱ ላሉ ግጭቶች የቀድሞው የኬንያ ፕሬዝዳን
ኡሁሩ ኬንያታ ለሰሜን ኢትዮጵያው ግጭት “የሰላም ልዩ ልዑክ” ሆነው መሾማቸውን አሜሪካ አደነቀች በሰሜን ኢትዮጵያ እና በዴሞክራቲክ ሪፐብሊንክ ኮንጎ እየተካሄዱ ላሉ ግጭቶች የቀድሞው የኬንያ ፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬንያታ “የሰላም ልዩ ልዑክ” ሆነው መሾማቸውን አሜሪካ አደነቀች። ኡሁሩ በሰላም ልዩ ልዑክነት የተሾሙበት ወቅት “ለሁለቱም ግጭቶች ወሳኝ በሆነ ጊዜ” መሆኑን በአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪካ ጉዳዮች ቢሮ ገልጿል። በአሜሪካ ውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት ረዳት ሚኒስትር በሆኑት ሞሊ ፊ የሚመራው የአፍሪካ ጉዳዮች ቢሮ፤ ለኡሁሩ ኬንያታ ሹመት ድጋፉን የገለጸው ትላንት ሐሙስ ለሊት በይፋዊ የትዊተር ገጹ ባሰፈረው መልዕክት ነው። ቢሮው በዚሁ መልዕክቱ የቀድሞው የኬንያ ፕሬዝዳንት ስራ “ከፍተኛ ጠቀሜታ” ያለው እንደሚሆን ተስፋውን ገልጿል። ኡሁሩ ሹመቱ እንደተሰጣቸው ይፋ የሆነው፤ ባለፈው ማክሰኞ መስከረም 3፤ 2015 ለአዲሱ የኬንያ ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ ስልጣናቸውን በይፋ ካስረከቡ በኋላ ነው። ሩቶ በበዓለ ሲመታቸው ላይ ባደረጉት ንግግር “የኢትዮጵያ እና የታላላቅ ኃይቆች ቀጠናን ጨምሮ በአካባቢያችን የሚካሄዱ የሰላም ጥረቶችን የኬንያን ሕዝብ ወክለው መምራታቸውን እንዲቀጥሉ ታላቅ ወንድሜ ፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬንያታን ጠይቄያቸው በደስታ ተቀብለዋል” ሲሉ ተናግረዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ በተገኙበት በሩቶ የበዓለ ሲመት ስነ ስርዓት ላይ የታደሙት የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ረዳት ሚኒስትር ሞሊ ፊ፤ በኢትዮጵያ እየተካሄደ ያለውን ውጊያ በተመለከተ ውይይቶች ማካሄዳቸው ተገልጿል። * * ሙሉ ዘገባውን ለማንበብ ይህን ሊንክ ይጫኑ፦ https://ethiopiainsider.com/2022/8104/ @ethiopianinsider1

#ETHIOPIA በሰሜን ኢትዮጵያ ዳግም ግጭት ከተቀሰቀሰ በኃላ እስካሁን ምን ሆነ (እጅግ በጥቂቱ) ? - ህወሓት ቆቦና የአካባቢው ቦታዎችን መቆጣጠሩን ተከትሎ ከፍተኛ የሰው ቁጥር ሰላም እና ደህንነት ፍለጋ ወደ አጎራባች ከተሞች እንዲፈናቀል ምክንያት ሆኗል። - እንደ ዓይደር ሪፈራል ሆስፒታል በመቐለ በተፈፀመ የአየር ጥቃት 4 ሰዎች ተገድለዋል ፤ 2ቱ ህፃናት ናቸው። የኢትዮጵያ መንግስት ግን ንፁሃንን ዒላማ ያደረገ ጥቃት እንደማይፈፅም በመግለፅ የወጡ ክሶችን አስተባብሎ ነበር። - ህወሓት በአፋር ክልል " ያሎ " በኩል በሰነዘረው የከባድ መሳሪያ ጥቃት በአካባቢው ንፁሃን ነዋሪዎች ላይ ጉዳት መድረሱን የዱብቲ ጠቅለላ ሆስፒታል የገለፀ ሲሆን በጥቃቱ ህፃናት ተገድለዋል። አንዲት እናት ሁለት ህፃናት ልጆቿ በከባድ መሳሪያ ጥቃት ተገድለውባታል። የቆሰሉም በርከት ያሉ ናቸው። - የዋግ ኽምራ ብሄረሰብ አስተዳደር እንደገለፀው " ወለህ " አካባቢ ህወሓት 10 ሰላማዊ ሰዎችን በግፍ መግደሉን፣ ከሟቾች መካከል አንዲት እናት ከነ ልጆቿ እንደምትገኝበት ገልጿል። በተጨማሪ ቡድኑ ወደ ወለህ መጠለያ ጣቢያ በመግባት 25 ሰዎችን መግደሉን አስተዳደሩ ገልጿል። - ህወሓት በአፍሪካ ህብረት (AU) መሪነት ለሰላም ንግግር ዝግጁ መሆኑ በገለፀ በሰዓታት ውስጥ ይዟቸው በሚገኙ የራያ ቆቦ ወረዳዎች በንፁሃን ላይ ጥቃት መዘንዘሩን ነዋሪዎች መግለፃቸውን ቪኦኤ ዘግቧል። ህወሓቶች በቀበሌ 02 ሰው መግደላቸው፣ ማቁሰላቸው ነዋሪዎች ገልፀዋል። ከጥቂት ቀናት በፊትም አራዱም ላይ ሰላማዊ ሰው መግደላቸውን ገልፀዋል። ባለፉት 18 ቀናት ሌሎች ያልታጠቁ ንፀሃን ሰዎችን መግደላቸውና በተጨማሪ ዝርፊያ እንደፈፀሙ ለሬድዮ ጣቢያው ገልፀዋል። - የመቐለ ዓይደር ሪፈራል ሆስፒታል እንደገለፀው 2 ጊዜ በተፈፀመ የአየር ጥቃት 10 ሰዎች ተገድለዋል። ከእነዚህ መካከል አብዛኞቹ የመጀመሪያዎቹን ተጎጂዎች ለመርዳት በተሰበሰቡበት ወቅት በተፈፀመ ጥቃት የተገደሉ ናቸው ብሏል። (ይህ የሆነው ትላንት ነው) - UN OCHA በሰሜን ኢትዮጵያ ክፍል ዳግም ባገረሸ ግጭት በርካታ ሰዎች መፈናቀላቸውን አመልክቷል። እንደ UN OCHA መረጃ ፦ 👉 በአማራ ፣ አፋር፣ እና ትግራይ ክልሎች በ10 ሺዎች መፈናቀለቸውን ገልጿል። 👉 የሰብዓዊ እርዳታ ተሽከርካሪዎች ወደ ትግራይ መግባት እንዳቆሙ፣ ከአዲስ አበባ ወደ መቐለ በረራ እንደተቋረጠ መሆኑን ገልጿል። 👉 በአማራ ክልል ሰሜን ወሎ ለመገኙ ተፈናቃዮች ድጋፍ ለማድረግ እየሰራ መሆኑን ገልጿል። 👉 በመርሳ ከተማ በ5 ት/ቤቶች አብዛኞቹ #ህፃናት እና #ሴቶች ከቆቦ እና አካባቢው ተፈናቅለው ተጠልለው የሚገኙ ሲሆን ለእነሱ ምግብ እና ምግብ ያልሆኑ ድጋፎችን ማሰራጨት ጀምራለሁ ብሏል። - የሰሜን ወሎ ዞን አስተዳደር ለቪኦኤ ሬድዮ በሰጠው ቃል በዞኑ የተፈናቃዮች ቁጥር እጅግ እየጨመረ መሆኑን ገልጾ ድጋፍ እንደሚያስፈልግ ገልጿል። መርሳ በሚገኙ ት/ቤቶቹ ውስጥ ያሉት ሴቶች እና ህፃናት ሲሆኑ ወንዶች ወጣቶች እንዲገቡ አልተደረገም። በአጠቃላይ ወልድያ እና መርሳ ከተሞች ላይ 92,400 ተፈናቃይ አለ። - ጦርነቱ ዳግም ካገረሸ ወዲህ በርካታ ንብረቶች ወድመዋል። - የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ወደ ባህርዳር ቢሮው የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች መልዕክቶች እየመጡለት ሲሆን አካባቢዎቹ ላይ ምቹ ሆኔታ ሲፈጠር ምርመራ አድርጎ እንደሚያሳውቅ ገልጿል። NB. የተዘረዘሩት ክስተቶች ግጭት ዳግም ካገረሸ ወዲህ #በተለያዩ_ጊዜያቶች የተሰሙ ናቸው። የሰላም ሂደቱ ምን ያህል ተስፋ ሰጪ ነው ? የኢትዮጵያ መንግስት በአፍሪካ ህብረት (AU) መሪነት ለሰላማዊ ንግግር ዝግጁ መሆኑን ከሳምንታት በፊት ገልጾ ነበር። ህወሓት በአፍሪካ ህብረት (AU) አፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ የቀድሞ የናይጄሪያ ፕሬዜዳንት ኦባሳንጆ ላይ እምነት እንደሌለውና በሂደቱ መተማመን እንደሌለው ሲገልፅ ከቆየ በኃላ ከቀናት በፊት በህብረቱ መሪነት ለሚደረግ የሰላም ንግግር ዝግጁ መሆኑን ገልጿል። ይህንን የህወሓት የሰላም ሂደት መቀበል እና ግጭት ለማቆም ዝግጅቱነት እንዳለው መግለፁን በተመለከተ በርካታ አስተያየቶች የተሰጡ ሲሆን የተለያዩ ሀገራት እና ተቋማት ውሳኔውን በማድነቅ የሰላም ሂደቱ እንዲፋጠን ጥሪ አቅርበዋል። ዳግም ያገረሸው ጦርነት ግን አሁንም አልቆመም። የኢትዮጵያ መንግስት እስካሁን ህወሓት ላወጣው መግለጫ በግልፅ ቀጥተኛ ምላሽ ባይሰጥም ትላንት ምክትል ጠ/ሚ እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን ከአውሮፓ ህብረት የአፍሪካ ማኔጂንግ ዳይሬክተር ጋር በተወያዩበት ወቅት መንግስት ለአፍሪካ ህብረት የሰላም ሂደት ቁርጠኛ መሆኑን ገልፀዋል። በሌላ በኩል ፤ የኢትዮጵያ መንግስት ለሰላም ቁርጠኛ መሆኑን በዩናይትድ ኪንግደም ያለው የኢትዮጵያ ኤምባሲ ገልጿል። የሰሜን ኢትዮጵያ ግጭት ሰላማዊ የሆነ መፍትሄ እንዲያገኝ መንግስት ዝግጁነት እንደነበረው ነገር ግን ህወሓት በቅርቡ ወረራ መፈፀሙን ኤምባሲው ዛሬ አመልክቷል። አሁንም ቢሆን የኢትዮጵያ መንግስት ግጭቱ እንዲፈታ የሚያምንበት ብቸኛ አማራች ሰለማዊ መፍትሄ መሆኑን ገልጿል። በተጨማሪ አምባሳደር ተፈሪ መለሰ አልጀዚራ ላይ ባወጡት ፅሁፍ መንግስት በየትኛውም ጊዜ እና ቦታ ለሰላም ውይይት ዝግጁ እንደሆነ አስታውሰው ህወሓት የሰላም ጥሪ ገፍቶ ጦርነት ከፍቷል ብለዋል። ህወሓት የጀመረውን ጥቃት በማቆምም ወደ ሰላም ድርድር እንዲመለስ ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ጫና ሊያደርግ ይገባልም ብለዋል። በአፍሪካ ህብረት ስር ለሚደረገው ድርድር ፍላጎቱን ማሳየቱን ተከትሎ በቃሉ እንዲፀና ዓለም አቀፍ ማህበረሰብ ሚናውን ሊወጣ ይገባል ሲሉ ገልፀዋል። ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ከዝምታው በመውጣት የመንግስትን የሰላም አማራጭ በመደገፍ ህወሓት ታጣቂዎቹን ትጥቅ በማስፈታት ወደ ድርድር እንዲገባ ጫና ማድረግ አለበት ሲሉም አሳውቀዋል። ህወሓት ወደሰላም እንዲመለስና ሰላምን ለማረጋገጥ ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ጫና ማድረግ ያለበት አሁን ነው ያሉት አምባሳደሩ ይህ ካልሆነ መንግስት ህዝብን የመጠበቅ ግዴታ ስላለበት ግዴታውን ይወጣል ብለዋል። ከቀናት በፊት " ህወሓት " ፤ በአፍሪካ ኅብረት (AU) የሚመራ ተዓማኒ የሰላም ሒደት እንደሚጠብቅ ፤ በአፍሪካ ህብረት መሪነት ለመደራደር ዝግጁ መሆኑን ፤ ለድርድሩ ምቹ ሁኔታ ለመፍጠር ፣ ለአፋጣኝ እና በሁለቱም ወገኖች ስምምነት ተግባራዊ ለሚደረግ የተኩስ አቁም ዝግጁ መሆኑን መግለፁ እንዲሁም ለግጭት ዘላቂ የሆነ መፍትሄ ማምጣት የሚቻለድ በሰላማዊ ውይይት ብቻ እንደሆነ እግጠኛ መሆኑን ማሳወቁ ይታወሳል። @ethiopianinsider1

#Update የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ለዶ/ር ዊሊያም ሩቶ በዓለ ሲመት ኬንያ ገብተዋል። አብረዋቸው የብሄራዊ ደህንነት አማካሪያቸው አምባሳደር ሬድዋን ሁሴንም አሉ። የኢጋድ ዋ
#Update የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ለዶ/ር ዊሊያም ሩቶ በዓለ ሲመት ኬንያ ገብተዋል። አብረዋቸው የብሄራዊ ደህንነት አማካሪያቸው አምባሳደር ሬድዋን ሁሴንም አሉ። የኢጋድ ዋና ፀሀፊ ዶ/ር ወርቅነህ ገበየሁም ለሩቶ በዓለ ሲመት ኬንያ ገብተዋል። ከዶ/ር ዐቢይ አህመድ በተጨማሪ ፦ - የሶማሊያ ፕሬዜዳንት ሀሰን ሼክ መሀመድ ፣ - የጅቡቲ ፕሬዜዳንት ኢስማኤል ኦማር ጌሌ ፣ - የኮንጎ ሪፐብሊክ ፕሬዜዳንት ዴኒስ ሳሱ፣ - የዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ፕሬዚዳንት ፌሊክስ ሺሰካዲ ፣ - የዚምባብዌ ፕሬዚዳንት ኤመርሰን ምናንጋግዋ ፣ - የኡጋንዳ ፕሬዜዳንት ዩዌሪ ሙሴቬኒ ፣ - የታንዛኒያ ፕሬዜዳንት ሳሚያ ሱሉሁ እና ሌሎችም የአፍሪካ ሀገራት መሪዎች ለዶ/ር ዊሊያም ሩቶ በዓለ ሲመት ናይሮቢ ይገኛሉ @Ethiopianinsider1

photo content

ኤርትራ እና ሌሎች አካላት የሰሜን ኢትዮጵያውን ግጭት “ከማቀጣጠል እንዲቆጠቡ” አሜሪካ አሳሰበች ኤርትራ እና ሌሎች አካላት የሰሜን ኢትዮጵያውን ግጭት “ከማቀጣጠል እንዲቆጠቡ” የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን አሳሰቡ። ዓለም አቀፍ አጋሮች ግጭቱን በሰላም ለመፍታት የሚደረገውን ሂደት ለመደገፍ ዝግጁ እንዲሆኑም ውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ጥሪ አቅርበዋል። አንቶኒ ብሊንከን ማሳሰቢያውን እና ጥሪውን ያቀረቡት የኢትዮጵያን አዲስ ዓመት በማስመልከት ዛሬ እሁድ መስከረም 1፤ 2015 እኩለ ሌሊት ገደማ ባወጡት መግለጫ ነው። ውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ በዚሁ መግለጫቸው፤ ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) ዛሬ ባወጣው መግለጫ ውጊያ ለማቆም እና ያልተፈቱ ጉዳዮችን በውይይት ለመፍታት ዝግጁ መሆኑን ማስታወቁን “እናበረታታለን” ብለዋል። የትግራይ ክልል መንግስት ዛሬ ምሽት ባወጣው መግለጫ በአፍሪካ ህብረት ጥላ ስር በሚደረግ የሰላም ሂደት ለመሳተፍ ዝግጁ መሆኑን ይፋ አድርጎ ነበር። የክልሉን መንግስት መግለጫ ተከትሎ የወጣው የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር መግለጫ፤ በኢትዮጵያ በመካሄድ ያለው ግጭት መፍትሔ እንዲያገኝ የኢትዮጵያ መንግስት እና ህወሓት በአፋጣኝ ወደ ንግግር እንዲመጡ የአፍሪካ ህብረት እያከናወነ ያለውን ስራ አድንቋል። ብሊንከን በዛሬው መግለጫቸው፤ የኢትዮጵያ መንግስት ለሰላም ሲል ከትግራይ ኃይሎች ጋር “በየትኛውም ስፍራ፣ በማንኛውም ጊዜ” ለመነጋገር ዝግጁ መሆኑን መግለጹን አስታውሰው፤ ለዚህ የመንግስት ዝግጁነት የሚሰጥ ምላሽን ሀገራቸው እንደምታበረታታ አመልክተዋል። የአዲስ አመት መንፈስን ታሳቢ በማድረግ፤ የኢትዮጵያ መሪዎች ሀገሪቱን መከራ ወደሚያበቃበት እና ዘላቂ ሰላም ለማጎናጸፍ ወደሚያስችል መንገድ እንደሚሯት ውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ጥሪ አቅርበዋል። ዩናይትድ ስቴትስ የኢትዮጵያን አንድነት፣ ሉዓላዊነት እና የግዛት አንድነት እንደምትደግፍ የጠቆሙት ውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ፤ አሜሪካ ከሀገሪቱ ጋር ወደነበራት “ጠንካራ አጋርነት” መመለስ እንደምትሻ በዛሬው መግለጫቸው አስታውቀዋል። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)

photo content

የኢትዮጵያ ተፋላሚ ወገኖች በአስቸኳይ የፊት ለፊት ንግግር እንዲያደርጉ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ጥሪ አቀረቡ የኢትዮጵያ ተፋላሚ ወገኖች በአስቸኳይ ተኩስ ለማቆም እንዲሰሩ እና የፊት ለፊት ንግግር እንዲያካሄዱ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ-መንበር ሙሳ ፋኪ ማህማት ጥሪ አቀረቡ። የኮሚሽኑ ሊቀ-መንበር ዛሬ እሁድ ምሽት ባወጡት መግለጫ፤ የትግራይ ክልል መንግስት ግጭቱን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት እና በአፍሪካ ህብረት በሚመራ የሰላም ሂደት ለመሳተፍ ፍቃደኝነት ማሳየቱን በበጎ መቀበላቸውን አስታውቀዋል። ሙሳ ፋኪ ማህማት በዛሬው መግለጫቸው፤ በአፍሪካ ህብረት መሪነት የሚደረገው ድርድር የኢትዮጵያ የፌደራል መንግስት እና የትግራይ ክልል መንግስት የሚስማሙባቸው “ዓለም አቀፍ አጋሮችን” እንደሚያካትት ጠቁመዋል። የህብረቱ ኮሚሽን ሊቀመንበር ትላንት ቅዳሜ ከአሜሪካው የአፍሪካ ቀንድ ልዩ ልዑክ አምባሳደር ማይክ ሐመር ጋር በተገናኙበት ወቅት፤ በኢትዮጵያ ያለውን ግጭት እልባት ለመስጠት በአፍሪካ ህብረት መሪነት በተፋላሚ ወገኖች መካከል ለሚደረገው ድርድር “የዓለም አቀፍ አጋሮች ድጋፍ አስፈላጊነት ላይ ተሰማምተናል” ብለው ነበር። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ይህን መግለጫ ያወጡት፤ የትግራይ ክልል መንግስት በሰሜን ኢትዮጵያ ዳግም የተቀሰቀሰውን ግጭት በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት ያለውን ቁርጠኝነት ባስታወቀ በሰዓታት ልዩነት ነው። የትግራይ ክልል መንግስት በዚሁ መግለጫው፤ በአፍሪካ ህብረት ጥላ ስር በሚደረግ የሰላም ሂደት ለመሳተፍ ዝግጁ መሆኑን ይፋ አድርጓል። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር) * * ሙሉ ዘገባውን ለማንበብ ይህን ሊንክ ይጫኑ፦ https://ethiopiainsider.com/2022/8069/

የቀድሞው የመከላከያ ሰራዊት ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም የትግራይ ክልል አንደኛው ተደራዳሪ መሆናቸው ይፋ ተደረገ የትግራይ ክልል መንግስት ከፌደራል መንግስት ጋር ለሚደረገው ድርድር፤ የቀድሞው የመከላከያ ሰራዊት ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ሌተናል ጄነራል ጻድቃን ገብረትንሳኤ እና የህወሓት ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባል አቶ ጌታቸው ረዳ የሚገኙበት ቡድንን መወከሉን አስታወቀ። ለዚህም ምቹ ሁኔታን ለመፍጠር በሁሉም ወገን ከስምምነት ላይ የሚደረስበትን የግጭት ማቆምን ወዲያውኑ ተግባራዊ እንደሚያደርግ ገልጿል። የትግራይ ክልል መንግስት ይህን ያስታወቀው የውጭ ጉዳይን በሚከታተለው ጽህፈት ቤቱ በኩል ዛሬ መስከረም 1፤ 2015 ምሽት ባወጣው መግለጫ ነው። የክልሉ መንግስት በዛሬው መግለጫው “አሳዛኝ” ሲል ለጠራው ግጭት ዘላቂ መፍትሄ ማምጣት የሚቻለው “በሰላማዊ ንግግር ብቻ እንደሆነ እናምናለን” ብሏል። የክልሉ መንግስት በዛሬው መግለጫው ከግጭት ማቆም ሂደት በኋላ ቀጣዩ እርምጃ “በሁሉን አቀፍ ድርድር የተኩስ አቁም” ማድረግ መሆኑን ጠቅሷል። ይህንን ተከትሎ ደግሞ “አሁን ላለው ግጭት መንስኤ የሆኑትን ጉዳዮች ለመፍታት ሁሉን ያሳተፈ የፖለቲካ ውይይት ማካሄድ” እንደሚገባ ጠቁሟል። ይህን ድርድር እውን ለማድረግ “ያለምንም መዘግየት የሚሰማራ የድርድር ቡድን” ማዘጋጀቱን ይፋ አድርጓል። የትግራይ ክልል መንግስት በአፍሪካ ህብረት በሚመራ የሰላም ሂደት ላይ ቅሬታዎችን ሲያቀርብ ቢቆይም በዛሬው መግለጫው ግን በህብረቱ ጥላ ስር በሚደረግ የሰላም ሂደት ለመሳተፍ ዝግጁ መሆኑን ይፋ አድርጓል። የክልሉ መንግስት በዚሁ መግለጫው በአፍሪካ ህብረት የሚመራው የሰላም ሂደት “እምነት የሚጣልበት ይሆናል” ብሎ እንደሚጠብቅ ገልጿል። የሰላም ድርድሩ በሁለቱም ወገኖች ተቀባይነት ያላቸውን አሸማጋዮች ማካተት እንዳለበትም ጠቁሟል። * * ዝርዝር ዘገባውን ለማንበብ ይህን ሊንክ ይጫኑ፦ https://ethiopiainsider.com/2022/8059/

photo content