en
Feedback
AIRDROP ROOM

AIRDROP ROOM

Open in Telegram
2 485
Subscribers
No data24 hours
-157 days
-5230 days
Posts Archive
ፖሊስ የፍርድ ቤቱን ትዕዛዝ ተቀብሎ በችሎት አለመገኘቱን በተመለከተ፤ አቶ ልደቱ አያሌው ለፍርድ ቤቱ ቅሬታቸውን በግልጽ ማቅረባቸውን የኢዴፓ ፕሬዝዳንት አቶ አዳነ ታደሰ አስረድተዋል። “እኔም ፖሊስም በህጉ ላይ እኩል መብት ነው ያለን። ፖሊስን ይህን ያህል በታገሳችሁት ልክ፤ እኔን አንድ ተራ ዜጋውን ይህን ያህል ትታገሱኛላችሁ ወይ? በዚህ አይነት እንዴት አድርጌ ነው ከፍትህ ስርዓቱ ውጤት አገኛለሁ የምለው?” ሲሉ ችሎቱን መጠየቃቸውን አቶ አዳነ ተናግረዋል። የዕውቁን ፖለቲከኛ ቅሬታ ያደመጠው ፍርድ ቤቱ “እኛ እንግዲህ ጦር አናዘምትም። ያለን አቅም ህጉን መተርጎም ነው። ፖሊሶቹ ራሳቸው ናቸው ሊያፍሩ የሚገባው፣ ተቋሙ ራሱ ነው ሊያፍር የሚገባው። ህገ መንግስቱን ነው እየጣሱ ያሉት” ሲል ምላሽ መስጠቱን የኢዴፓ ፕሬዝዳንት ጠቅሰዋል። ዝርዝር ዘገባውን ለማንበብ፦ https://ethiopiainsider.com/2020/2146/

ኢዴፓ በኢትዮጵያ የፖለቲካ ውጥረት በነገሰበት “ምርጫ በፍፁም መታሰብ የለበትም” አለ የኢትዮጵያውያን ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ኢዴፓ) ኢትዮጵያ በፖለቲካ ውጥረት ውስጥ ባለችበት በአሁኑ ወቅት “አገራዊ ምርጫ ለማካሄድ በፍፁም መታሰብ የለበትም” አለ። ፓርቲው ምርጫው ከመካሄዱ በፊት በሀገሪቱ ላሉ መሰረታዊ ጥያቄዎች መፍትሄ ማመንጨት የሚያስችል ሁሉን አቀፍ የውይይትና የድርድር ሂደት (National Dialogue) በአስቸኳይ እንዲጀመርም ጠይቋል። ኢዴፓ ይህን አቋሙን ይፋ ያደረገው፤ የፓርቲ የስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ዛሬ ማክሰኞ ጥቅምት 3፤ 2013 ባወጣው መግለጫ ነው። ኢትዮጵያ ከውድቀት ለመዳን “ዛሬም ዕድል አላት” ብሎ እንደሚያምን የገለጸው ኢዴፓ፤ ሀገሪቱ ወደ ተሻለ ሁኔታ ለመሸጋገር ያስችላት ዘንድ አራት ተጨባጭ እርምጃዎች ሊወሰዱ እንደሚገባም አሳስቧል። ፓርቲው በቀዳሚነት እርምጃ ሊወሰድበት ይገባል ያለው፤ በኢትዮጵያ “እጅግ አሳሳቢ በሆነ ሁኔታ እየከፋ መጥቷል” ባለው “የህግ የበላይነት መጥፋት” ጉዳይ ላይ ነው። ለዚህም የአመራሩን የአቶ ልደቱ አያሌውን ጉዳይ በምሳሌነት ጠቅሷል። ዝርዝሩን ለማንበብ ይህን ሊንክ ይጫኑ፦ https://ethiopiainsider.com/2020/2106/

ኢዜማ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ላይ በፍርድ ቤት ክስ መሰረተ የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) ፓርቲ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደርን በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ከሰሰ። ፓርቲው ክሱን የመሰረተው የከተማው አስተዳደር ከንቲባ ጽህፈት ቤት በሰጠው ትዕዛዝ፤ የፓናል ውይይት እንዳያደርግ መከልከሉን በመቃወም ነው። በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ፍትሐ ብሔር ችሎት ባለፈው አርብ መስከረም 30፤ 2013 የተከፈተው የክስ መዝገብ፤ በፓርቲው ላይ የደረሰው “የሁከት ተግባር እንዲታገድ” የሚጠይቅ ነው። ኢዜማ ይህን ክስ ለማቅረብ የተገደደው ሕገ መንግስታዊ የሆነው “የመሰብሰብ መብት” በተከሳሽ መስሪያ ቤት በተሰጠ ትዕዛዝ በመገደቡ መሆኑን ገልጿል። ዝርዝር ዘገባውን ለማንበብ ይህን ሊንክ ይጫኑ፦ https://ethiopiainsider.com/2020/2097/

Happy Irreechaa
Happy Irreechaa

photo content
+1

የደቡብ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት፤ የወላይታ ዞን የቀድሞ አመራሮችን ጨምሮ ለ20 ተጠርጣሪዎች የስር ፍርድ ቤት በፈቀደው ዋስትና ላይ እና ፖሊስ በጠየቀው ተጨማሪ የምርመራ ቀናት ላይ ብይን ለመስጠት ለመጪው ረቡዕ መስከረም 27፤ 2013 ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጠ። ፍርድ ቤቱ ዛሬ ረፋዱን በነበረው ችሎት፤ በዋስትናው ጉዳይ እና ተጠርጣሪዎች ባቀረቡት አቤቱታ ላይ የደቡብ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን በጹሁፍ ያቀረበውን የመልስ መልስ ተቀብሏል። በዛሬው ችሎት ማናቸውም ተጠርጣሪዎች በፍርድ ቤት አለመቅረባቸውን የስድስቱ ጠበቃ ተመስገን ዋጃና ለ “ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናግረዋል። በማረሚያ ቤት እንዲቆዩ ከተደረጉ 15 ተጠርጣሪዎች ውስጥ አስራ ሁለቱ በዛሬው ችሎት የተወከሉት፤ በሶስት ጠበቆች መሆኑንም ገልጸዋል። ቀሪዎቹ ሶስት ተጠርጣሪዎች በራሳቸው የሚከራከሩ እንደሆኑም አክለዋል። ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ከትላንት በስቲያ ማክሰኞ በነበረው ችሎት በሰጠው ትዕዛዝ መሰረት፤ ተጨማሪ ስምንት ተጠርጣሪዎች በሶዶ ማረሚያ ቤት በእስር እንዲቆዩ መደረጋቸው ይታወሳል። በማክሰኞው የፍርድ ቤቱ ትዕዛዝ ወደ ሶዶ ከተማ ማረሚያ ቤት ከተወሰዱ ተጠርጣሪዎች ውስጥ የቀድሞው የወላይታ ዞን አስተዳዳሪ አቶ ዳጋቶ ኩምቤ እና የዞኑ ብልጽግና ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ጥበቡ ዩሃንስ ይገኙበታል። ሁለቱ አመራሮች ከስልጣናቸው የተነሱት ባለፈው ነሐሴ ወር አጋማሽ ነበር። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)

ችሎት! አቶ ጃዋር መሃመድ እና 24 ሰዎች ላይ የተመሰረተውን ክስ በዛሬው እለት መሰማት #BBC (ቢቢሲ) ዘግቧል። ክሳቸው እየተሰማ ያለው በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ሲሆን ፤ አቶ ጀዋር መሐመድ፣
ችሎት! አቶ ጃዋር መሃመድ እና 24 ሰዎች ላይ የተመሰረተውን ክስ በዛሬው እለት መሰማት #BBC (ቢቢሲ) ዘግቧል። ክሳቸው እየተሰማ ያለው በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ሲሆን ፤ አቶ ጀዋር መሐመድ፣ አቶ በቀለ ገርባ ፣ ሐምዛ አዳነ ፣ ሸምሰዲን ጠሃ ፍርድ ቤት የተገኙት የማረሚያ ቤቱን ቢጫ ደንብ ልብስ ለብሰው ነው። ከዚህም በተጨማሪ የሃጫሉ ምስል ያለበት የአፍና የአፍንጫ መሸፈኛ አድርገው ታይተዋል። ተከሳሾቹ ለ2 በሰንሰለት ታስረው ችሎት ላይ የቀረቡ ሲሆን አቃቤ ሕጎች ወደ ችሎቱ ሲገቡ እጃቸውን ከፍ አድርገው እንደታሰሩ አሳይተዋል። በመቀጠልም አቃቤ ሕግ ሰንሰለቱ ከእጃቸው ላይ እንዲፈታ በማዘዙ ተፈትቶላቸዋል። ከዚህ በፊት ሌላ ክስ ስላለባቸው መገኘት ያልቻሉት የኦፌኮ አባሉ አቶ ደጀኔ ጣፋ በዛሬው ዕለት ተገኝተዋል። ችሎቱ መታየት የጀመረው በፍትሕ አዳራሽ ሲሆን በአዳራሾቹ የተከሳሽ ቤተሰቦችን ጨምሮ ሃያ (20) ሰዎች ተገኝተዋል። MORE : https://telegra.ph/JM-10-01 @ethiocheck

የፕሮፌሰር መስፍን ወልደማርያም የመጨረሻ ቀናት ፕሮፌሰር መስፍን ወደ ሆስፒታል የተወሰዱት አጠገባቸው የነበረ ሰው በመታመሙ ምክንያት እንደነበር የሚገልጹት ልጃቸው፤ ሁለቱም በተደረገላቸው ምርመራ በኮቪድ 19 በሽታ መያዛቸው መረጋገጡን ልጃቸው መቅደስ ለ "ኢትዮጵያ ኢንሳይደር" ተናግረዋል። ሆስፒታል ከገቡ ከቀናት በኋላም በእርሳቸው ህመም ለተጨነቁ ወዳጆቻቸው፤ ደህና መሆናቸውን የሚገልጽ መልዕክት በልጃቸው በኩል አስተላለፈው ነበር። “ሆስፒታል ገብቶ ራሱ፤ ‘እኔ አስታማሚ ሆኜ ነው የመጣሁት’ እያለ ይጫወት ነበር። [ባለፈው ሳምንት] ረቡዕ እንደውም አብሮት የነበረው ሰው እየተሻለው ሲመጣ ‘እንደገና መርምሩኝና ከሆስፒታል ልውጣ’ ብሎ ጠይቆ ነበር። ሐሙስ መታመም ጀመረ። ሆስፒታል በገባ በሳምንቱ ቅዳሜ ነው ‘ሲሪየስ’ የሆነ ነገር ያየነው። እንጂ ደህና ነበር” ሲሉ አባታቸው በሆስፒታል የነበሩበትን ሁኔታ ልጃቸው መቅደስ አብራርተዋል። ዝርዝር ዘገባውን ለማንበብ ይህን ሊንክ ይጫኑ፦ https://ethiopiainsider.com/2020/2055/

ፕሮፌሰር መስፍን ወ/ማርያም አረፉ! አንጋፋው ፖለቲከኛና የሰብአዊ መብት ተሟጋቹ ፕሮፌሰር መስፍን ወልደማርያም በተወለዱ በ91 አመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል። @ethiocheck
ፕሮፌሰር መስፍን ወ/ማርያም አረፉ! አንጋፋው ፖለቲከኛና የሰብአዊ መብት ተሟጋቹ ፕሮፌሰር መስፍን ወልደማርያም በተወለዱ በ91 አመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል። @ethiocheck

የፌደራል ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ ዶ/ር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ ጋር ከ"ኢትዮጵያ ኢንሳይደር" ጋር ያደረጉት ልዩ ቃለ ምልልስ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ወደ ስልጣን መምጣታቸውን ተከትሎ በርከት ያሉ ወጣት ባለሙያዎች በተለያዩ የመንግስት ተቋማት ተመድበው ኃላፊነታቸውን ሲወጡ ቆይተዋል። ከእነዚህ መካከል አንዱ የሆኑት ዶ/ር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ፤ በጥቅምት 2011 ዓ.ም. ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የህግ መምህርነታቸው ለቅቀው የፌደራል ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ መስሪያ ቤትን በምክትል ጠቅላይ አቃቤ ህግነት ተቀላቅለዋል። እስካለፈው ነሐሴ ወር በዚሁ የኃላፊነት ቦታቸው የቆዩት ዶ/ር ጌዲዮን፤ ተጨማሪ ሹመት በማግኘት በፍትህ ስርዓቱ ውስጥ ቁልፍ የሚባለውን የፌደራል ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ መስሪያ ቤትን የመምራት ዕድል አግኝተዋል። ወጣቱ ባለሙያ የጠቅላይ ዐቃቤ ህግነት ስልጣኑን የተረከቡት የገዢው ፓርቲ ሁነኛ ሰው ናቸው ከሚባሉት ወ/ሮ አዳነች አበቤ ሲሆን ሹመታቸውም በተወካዮች ምክር ቤት በዚህ ሳምንት ጸድቆላቸዋል። በአንድ ወር የስልጣን ጊዜያቸውም ከድምጻዊ ሃጫሉ ሁንዴሳ ግድያ በኋላ በተቀሰቀሱ ሁከቶች ተጠርጥረው የታሰሩ በሺህዎች የሚቆጠሩ ግለሰቦች ምርመራ ተጠናቅቆ ክስ እንዲመሰረት አድርገዋል። ከተጠርጣሪዎች እስር እና ምርመራ፣ በእነርሱ ላይ ከተከፈቱባቸው ክሶች እንዲሁም ከፍርድ ሂደት ጋር በተያያዘ መስሪያ ቤታቸውን የተመለከቱ ጥያቄያዎችን በመያዝ የ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደሩ” ተስፋለም ወልደየስ ከዶ/ር ጌዲዮን ጋር ረዘም ያለ ቆይታ አድርጓል። የመጀመሪያውን ክፍል ቃለ ምልልስ ለማንበብ ይህን ሊንክ ይጫኑ፦ https://ethiopiainsider.com/2020/2015/

ተጨማሪ ፦ ጅማ ዩንቨርሲቲ ሲካሄድ በቆየው የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የውይይት መድረክ የተነሱ ኃሳቦችን ከመድረኩ ተሳታፊ አካላት ጠይቀን ተከታዩን መርጃ ሰጥተውናል ፦ - ዩኒቨርስቲዎች ተማሪዎችን የ
ተጨማሪ ፦ ጅማ ዩንቨርሲቲ ሲካሄድ በቆየው የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የውይይት መድረክ የተነሱ ኃሳቦችን ከመድረኩ ተሳታፊ አካላት ጠይቀን ተከታዩን መርጃ ሰጥተውናል ፦ - ዩኒቨርስቲዎች ተማሪዎችን የመቀበል ዝግጁነታቸውን እስከ መስከረም 25/2013 ዓ/ም ድረስ እንዲያሳውቁ በመድረኩ አቅጣጫ የተቀመጠ ሲሆን ዝግጁ የሆኑ ዩኒቨርሲቲዎች ተማሪዎቻቸውን ከመስከረም 25 ጀምሮ መጥራት ይችላሉ፡፡ - በቀድሚያ ተመራቂ ተማሪዎችን ወደ ትምህርት ገበታቸው እንዲመለሱ ይደረጋል፡፡ - ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት የተወጣጣ የዩኒቨርስቲዎችን ዝግጁነት የሚያረጋግጥ ግብረ-ኃይል የተቋቋመ ሲሆን ዩኒቨርስቲዎች ተማሪዎችን ለመቀበል ዝግጁ መሆናቸውን ይመለከታል። - ዩኒቨርሲቲዎች በጥሪ ጊዜ የትራንስፖርት መጨናነቅ እንዳይኖር ዩኒቨርሲቲዎች ተናበው እንዲሰሩ እንዲሁም የትራንስፖርት አገልግሎቶችን ለተማሪዎች እንዲያመቻቹ ኃሳብ ተነስቷል፡፡ - የተማሪዎች ህብረት ተወካዮች ወደ ግቢ እንዲገቡ ጥሪ እየተደረገ ይገኛል፡፡ - በዚህ ዓመት ሌላው ከፍተኛ ትኩረት የተሰጠው የዲሲፒሊን ጉዳይ ሲሆን ባለፈው ዓመት የተፈጠሩ ክስተቶች እንዳይደገሙ ሁሉም ባለድርሻ አካል ልዩ ትኩረት ሰጥቶ ይሰራል። @ethiocheck

#UPDATE የትምህርት ሚኒስቴር የኮሚኒኬሽን ጉዳዮችን ዳይሬክተር ሐረጓ ማሞ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በስልክ እንደገለፁት ፥ የትምህርት ሚኒስቴር አመራሮችና የክልል ትምህርት ቢሮ ሃላፊዎች በቀጣይ የትምህ
#UPDATE የትምህርት ሚኒስቴር የኮሚኒኬሽን ጉዳዮችን ዳይሬክተር ሐረጓ ማሞ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በስልክ እንደገለፁት ፥ የትምህርት ሚኒስቴር አመራሮችና የክልል ትምህርት ቢሮ ሃላፊዎች በቀጣይ የትምህርት ሁኔታ ላይ ውሳኔ ለማሳለፍ እያካሄዱት ያለው ውይይት ዛሬ አልተጠናቀቀም ፤ ነገ ጥዋት መግለጫ ይሰጣል ብለውናል። @ethiocheck

ተጨማሪ መረጃ፦ የፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ በአቶ ጃዋር መሐመድ እና ሌሎች 23 ተከሳሾች ላይ ዛሬ ሰኞ መስከረም 11፤ 2013 በይፋ ክስ መስርቷል። ጉዳዩ የቀረበለት የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የ
ተጨማሪ መረጃ፦ የፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ በአቶ ጃዋር መሐመድ እና ሌሎች 23 ተከሳሾች ላይ ዛሬ ሰኞ መስከረም 11፤ 2013 በይፋ ክስ መስርቷል። ጉዳዩ የቀረበለት የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የጸረ ሽብር እና ህገ መንግስታዊ ጉዳዮች አንደኛ ወንጀል ችሎት፤ በዛሬው ውሎው የክስ ሰነዶቹ ለተከሳሾች እና ጠበቆቻቸው እንዲከፋፈል አድርጓል። ችሎት ፊት የቀረቡ 18 ተከሳሾቹን ማንነትም ከራሳቸው አንደበት አጣርቷል። ችሎቱ ሙሉ ክሱን በንባብ ለማሰማት ለመጪው ሐሙስ መስከረም 14፤ 2013 ቀጠሮ ሰጥቷል። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)

የአሮሚያ ክልል ለዲቦራ ፋውንዴሽን 10 ሚሊዮን ብር ለመለገስ ቃል ገባ የኦሮሚያ ክልል በቀድሞው የተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ እና የክልሉ ፕሬዝዳንት በነበሩት አቶ አባዱላ ገመዳ ለተመሰረተው ዲቦራ ፋውንዴሽን 10 ሚሊዮን ብር ለመለገስ ቃል ገባ። የክልሉ መንግስት ገንዘቡን ለመስጠት ቃል የገባው ፋውንዴሽኑ በለገጣፎ ለሚያሰራው ትምህርት ቤት፣ የጤና አገልግሎት መስጫ እና ማሰልጠኛ ማዕከል ነው። ዲቦራ ፋውንዴሽን በአቶ አባዱላ አራተኛ ልጅ የተሰየመ እና “ዳውንሲንድረም” ተብሎ በሚታወቀው የአእምሮ ዕድገት ውሱንነት የተጠቁ ህጻናትን ለመደገፍ በሐምሌ 2011 ዓ.ም. የተቋቋመ ነው። በቅዳሜ ምሽቱ የፋውንዴሽኑ የማሰልጠኛ ማዕከል የምረቃ ስነ ስርዓት ላይ ከመንግስት እና ከግል ተቋማት ያልተጠበቁ ልገሳዎች በዚያው በመድረኩ ሲሰጡ ታይቷል። ከመንግስት በኩል ከፍተኛውን ድርሻ የወሰደው የኦሮሚያ ክልል ነው። ለማሰልጠኛው ግንባታ የክልሉ መንግስት ለመስጠት ቃል ከገባው 10 ሚሊዮን ብር በተጨማሪ የክልሉ ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን የመዋዕለ ህጻናት ግንባታውን ራሱ ለማከናወን መወሰኑን አስታውቋል። የኦሮሚያ ክልሉ የትምህርት ቢሮ በበኩሉ ሽያጩ ለፋውንዴሽኑ እንዲውል በሚል በአቶ አባዱላ የተጻፉ 10 ሺህ መጽሐፍትን ለመግዛት ቃል ገብቷል። መጽሐፍቱ በክልሉ ባሉ ትምህርት ቤቶች እንደሚከፋፈሉ በስነ ስርዓቱ ላይ ተገልጿል። ከትምህርት ቢሮ በተጨማሪ የተለያዩ የግል ድርጅቶች እና ግለሰቦች ወደ አራት ሺህ ገደማ መጽሐፍት ለመግዛት ቃል ገብተዋል። ዝርዝር ዘገባውን ለማንበብ ይህን ሊንክ ይጫኑ፦ https://ethiopiainsider.com/2020/1981/

የኢትዮጵያ አየር መንገድ በረራዎችን ጨምሮ ወደ ሶማሊያ የሚደረጉ ሌሎች በረራዎች በጊዜያዊነት ተቋርጠዋል የኢትዮጵያ አየር መንገድ በረራዎችን ጨምሮ ወደ ሶማሊያ የሚደረጉ ሌሎች በረራዎች ከሞቃዲሾ ወደ
የኢትዮጵያ አየር መንገድ በረራዎችን ጨምሮ ወደ ሶማሊያ የሚደረጉ ሌሎች በረራዎች በጊዜያዊነት ተቋርጠዋል የኢትዮጵያ አየር መንገድ በረራዎችን ጨምሮ ወደ ሶማሊያ የሚደረጉ ሌሎች በረራዎች ከሞቃዲሾ ወደ ሌሎች አየር ማረፊያዎች እንዲዛወሩ እየተደረገ ነው፡፡ በረራዎቹ የሚዛወሩት ሞቃዲሾ የሚገኘው የአደን አዴ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ በጊዜያዊነት በመዘጋቱ ነው ተብሏል፡፡ በዚህም የኢትዮጵያን ጨምሮ ሌሎች አየር መንገዶች ወደ ኢትዮጵያ አለበለዚያም ወደ ጅቡቲ ለመብረር መገደዳቸው ነው ሶማሊ ጋርዲያን የአየር ማረፊያውን ባለስልጣናት ዋቢ አድርጎ የዘገበው፡፡ ንብረትነቱ የኬንያ ሲልቨርስቶን ኤር የሆነ እቃ ጫኝ አውሮፕላን ዛሬ በአደን አዴ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ተከስክሷል፡፡ በዚህም ምክንያት አየር ማረፊያው ይሰጥ የነበረውን አገልግሎት ያቋረጠ ሲሆን በጊዜያዊነት መዘጋቱንም ነው ሶማሊ ጋርዲያን የዘገበው፡፡ ከኪስማዮ፣ጋሮዌ፣ሃርጌሳ እና ባይዶዋ ወደ ሞቃዲሾ ሊደረጉ የነበሩ በረራዎች መቋረጣቸውም ተዘግቧል፡፡ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ሁኔታውን በተመለከተ ይህ ዘገባ እስከተጠናቀረበት ጊዜ ድረስ በማህበራዊ ድረገጾቹም ሆነ በይፋዊ የድረገጽ አድራሻው የሰጠው ነገር የለም፡፡ @ethiocheck

አቶ ጃዋር መሐመድ እና አቶ በቀለ ገርባን ጨምሮ 24 ሰዎች ላይ "አስር ተደራራቢ ክሶች" መመሥረቱን ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ አስታወቀ። ድምጻዊ ሐጫሉ ሁንዴሳ በተገደለ ማግሥት የታሰሩት አቶ ጃዋር መሐመድ፣ አቶ በቀለ ገርባ እንዲሁም አቶ ሐምዛ አድናን ክስ ከተመሠረተባቸው መካከል እንደሚገኙበት ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ በዛሬው ዕለት ያወጣው መግለጫ ይጠቁማል። የኦሮሚያ ሚዲያ ኔትወርክ እና የቴሌቭዥን ጣቢያው ጋዜጠኛ አቶ ደጀኔ ጉተማ፤ በአሜሪካ የኢትዮጵያ ዲፕሎማት የነበሩት ዶ/ር ብርሃነ መስቀል አበበ፣ መቀመጫቸውን በአውስትራሊያ ያደረጉት አቶ ጸጋዬ ረጋሳ በሌሉበት ክስ ተመስርቶባቸዋል። ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ "በአጠቃላይ በ24 ሰዎች ላይ እንደየተሳትፏቸው በ1996 የወጣውን የወንጀል ሕግ አንቀፅ 240 በመተላለፍ ብሔርን እና ሐይማኖትን መሰረት ያደረገ የእርስ በርስ ግጭት በመቀስቀስ አንዱ ወገን በሌላው ወገን ላይ እንዲነሳሳ በማድረግ" ክስ እንደተመሠረተባቸው አስታውቋል። በመግለጫው መሠረት እነ አቶ ጃዋር "የሽብር ወንጀልን ለመከላከል እና ለመቆጣጠር የወጣውን አዋጅ፤ የቴሌኮም ማጭበርበር ወንጀል አዋጅ ፤ የጦር መሳሪያ አስተዳደርና ቁጥጥር አዋጅ" የመተላለፍ ክሶች ጭምር ተመስርቶባቸዋል።https://p.dw.com/p/3iib1?maca=amh-RED-Telegram-dwcom

የአሥራት ጋዜጠኞች ከእስር መፈታታቸው ታውቋል! ጋዜጠኛ በላይ ማናዬ፣ ሙሉጌታ አንበርብርና ምስጋናው ከፈለኝ ዛሬ መስከረም 9 ከእስር ተፈትተዋል። ጳጉሜ 2 በዋስ እንዲፈቱ ከተወሰነ በኋላ፣ ፖሊስ እን
የአሥራት ጋዜጠኞች ከእስር መፈታታቸው ታውቋል! ጋዜጠኛ በላይ ማናዬ፣ ሙሉጌታ አንበርብርና ምስጋናው ከፈለኝ ዛሬ መስከረም 9 ከእስር ተፈትተዋል። ጳጉሜ 2 በዋስ እንዲፈቱ ከተወሰነ በኋላ፣ ፖሊስ እንደገና አስሮ ጳጉሜ 3 ሌላ መዝገብ ከፍቶባቸው የነበር ቢሆንም ፍርድ ቤቱ በትናንትናው ዕለት ሁለተኛውን መዝገብ ውድቅ አድርጎ እንዲፈቱ መወሰኑ ይታወሳል። @ethiocheck

ዝርዝር ዘገባ፦ አቃቤ ህግ በታገደው የእነ ጃዋር መሐመድ ንብረት ላይ የሰጠው ምላሽ አቶ ጃዋር መሐመድ “ለግል ፍጆታዬ ቤት ያስቀመጥኩት ጥሬ ገንዘብ እና ውድ ዋጋ ያላቸው ዕቃዎች ከቤቴ ተወስደውብኛል” በማለት በጠበቆቻቸው በኩል ላቀረቡት አቤቱታ አቃቤ ህግ በሰጠው ምላሽ፤“የፌደራል ፖሊስ ለወንጀል ምርመራው ይጠቅመኛል በማለት በብርበራ ከቤቱ ውስጥ በኢግዚቢትነት የተወሰደ ሲሆን በዚህ ጉዳይ ላይ የፌደራል አቃቤ ህግ ምላሽ ሊሰጥ አይገባም” ብሏል። ሁለተኛው የአቃቤ ህግ ምላሽ የተመለከተው በአቶ በቀለ ገርባ፣ ሀምዛ አዳነ፣ ቦና ትቢሌ በተባሉ ሶስት ተጠርጣሪዎች እንዲሁም በኦሮሚያ ሚዲያ ኔትወርክ (OMN) ስም የተመዘገቡ ስድስት መኪኖች ላይ የቀረበ አቤቱታን ነው። አምስቱ መኪኖች የወንጀል ድርጊት የተገኙ እና ለወንጀል መፈጸሚያ የዋሉ በመሆናቸው የተያዘው ንብረት ይመለስልኝ በሚል የቀረበው አቤቱታ “ውድቅ ሊሆን ይገባል” ሲል አቃቤ ህግ ምላሽ ሰጥቷል። ዝርዝሩን ለማንበብ ይህን ሊንክ ይጫኑ፦ https://ethiopiainsider.com/2020/1975/

የኢትዮጵያውያን ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ (ኢዴፓ) የብሔራዊ ምክር ቤት አባል የሆኑት አቶ ልደቱ አያሌው በቢሾፍቱ ከተማ ፍርድ ቤት የወከሏቸውን ጠበቆች አሰናበቱ። አቶ ልደቱ እርምጃውን የወሰዱት ከዚህ በኋላ በከተማው ፍርድ ቤት የህግ ክርክር ማድረግ ባለመፈለጋቸው እንደሆነ ዛሬ ረቡዕ በጻፉት ደብዳቤ አስታውቀዋል። ከዚህ በኋላ የሚካሄደውን ክርክር “ትርጉም የሌለው” ሲሉ የጠሩት አቶ ልደቱ፤ “ህግ የፖለቲካ መሳሪያ በሆነበት ሁኔታ በህግ ክርክር መብትን ማስከበር ስለማይቻል ከአሁን በኋላ ግዴታዬን ለመወጣት ቀጠሮ ሲሰጠኝ በችሎት ፊት ከመገኘት ባለፈ የህግ ክርክር የማድረግ ፍላጎት የለኝም” ሲሉ በፓርቲያቸው በኩል ባሰራጩት ደብዳቤያቸው አስፍረዋል። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)

photo content