en
Feedback
AIRDROP ROOM

AIRDROP ROOM

Open in Telegram
2 485
Subscribers
No data24 hours
-157 days
-5230 days
Posts Archive
አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ከመጪው ዓመት ጀምሮ የቅደመ ምረቃ ተማሪዎችን በውድድር ብቻ እንደሚቀበል ገለጸ አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ከመጪው 2016 ዓ.ም. ጀምሮ የቅድመ ምረቃ ተማሪዎችን የሚቀበለው በምደ
አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ከመጪው ዓመት ጀምሮ የቅደመ ምረቃ ተማሪዎችን በውድድር ብቻ እንደሚቀበል ገለጸ አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ከመጪው 2016 ዓ.ም. ጀምሮ የቅድመ ምረቃ ተማሪዎችን የሚቀበለው በምደባ ሳይሆን በውድድር መሆኑን አስታወቀ። ዩኒቨርስቲው ክፍያ የሚፈጽሙ የቅድመ ምረቃ ተማሪዎችን “በልዩ” ሁኔታ ለማስተማር እንዳቀደም ገልጿል። አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ይህንን ያስታወቀው የመጀመሪያው ራስ ገዝ ዩኒቨርስቲ መሆኑን አስመልክቶ ዛሬ ማክሰኞ ነሐሴ 16፤ 2015 በዋናው ቅጥር ግቢ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ነው። መግለጫውን የሰጡት የዩኒቨርስቲው ፕሬዝዳንት ፕሮፌሰር ጣሰው ወልደሃና፤ የከፍተኛ ትምህርት ተቋሙ ራስ ገዝ ለመሆን ላለፉት ሁለት ዓመታት ዝግጅት ሲያደርግ መቆየቱን ተናግረዋል። በትምህርት ሚኒስቴር ስር ያሉ የመንግስት ዩኒቨርስቲዎችን ራስ ገዝ ለማድረግ የተዘጋጀው አዋጅ በተወካዮች ምክር ቤት የጸደቀው ባለፈው ግንቦት ወር ነበር። የዚህን አዋጅ መውጣት ተከትሎም አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የመጀመሪያው ራስ ገዝ ዩኒቨርስቲ እንዲሆን ያስቻለው ደንብ፤ ከሶስት ሳምንት በፊት ሐምሌ 28፤ 2015 በሚኒስትሮች ምክር ቤት ጸድቋል። የዩኒቨርስቲው ፕሬዝዳንት በዛሬው መግለጫቸው፤ የከፍተኛ ትምህርት ተቋሙ ወደ ራስ ገዝነት የሚያደርገውን ሽግግር “ሁለት ዓመት ባልሞላ” ጊዜ ውስጥ ለማጠናቀቅ ማቀዱን አስታውቀዋል። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር) @EthiopiaInsiderNews

በአማራ ክልል በአስር ዞኖች የሚገኙ የመንግስት መስሪያ ቤቶች ገንዘብ እንዳይንቀሳቀስ ታገደ የአማራ ክልል መንግስት በአስር ዞኖች እና አንድ የከተማ አስተዳደር ስር ባሉ አካባቢዎች የሚገኙ የመንግስት
በአማራ ክልል በአስር ዞኖች የሚገኙ የመንግስት መስሪያ ቤቶች ገንዘብ እንዳይንቀሳቀስ ታገደ የአማራ ክልል መንግስት በአስር ዞኖች እና አንድ የከተማ አስተዳደር ስር ባሉ አካባቢዎች የሚገኙ የመንግስት መስሪያ ቤቶች ገንዘብ እንዳይንቀሳቀስ አገደ። የክልሉ መንግስት ይህን ትዕዛዝ ያስተላለፈው፤ በአስሩ ዞኖች እና በደብረ ታቦር ከተማ የሚገኙ የመንግስት መስሪያ ቤቶች የሚጠቀሙባቸው “ደረሰኞች እና ቼኮች በመዘረፋቸው” መሆኑን ገልጿል። የአማራ ክልል ገንዘብ ቢሮ እገዳው ተግባራዊ እንዲደረግ፤ የክልሉ “የመንግስት ሀብት ለሚንቀሳቀስባቸው” ባንኮች ባለፈው ሳምንት ማክሰኞ ዕለት ነሐሴ 9፤ 2015 በጻፈው ደብዳቤ ማሳወቁን የቢሮው የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ደሳለኝ አለምነህ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናግረዋል። እግዱ ከተጣለባቸው አስር ዞኖች መካከል፤ በስራቸው ያሉ ሁሉም መዋቅሮች ላይ እርምጃው ተግባራዊ የሚደረግባቸው አራቱ ናቸው። የገንዘብ እንቅስቃሴ እገዳው ሙሉ ለሙሉ ተግባራዊ የሚደረገው በምዕራብ ጎጃም፣ ምስራቅ ጎጃም፣ ሰሜን ጎጃም እና ደቡብ ጎንደር ዞኖች እንደሆነ በአማራ ክልል ገንዘብ ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ አደራጀው ካሴ ተጽፎ ለባንኮች የተሰራጨው ደብዳቤ ያመለክታል። “ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” በተመለከተችው በዚሁ የደብዳቤ ክፍል ላይ እገዳው ተግባራዊ የሚደረግበት ብቸኛ የከተማ አስተዳደር ደብረታቦር ነው። * ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/11863/ @EthiopianInsider1

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል፤ አቶ ተስፋዬ ይገዙን ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አድርጎ ሾመ አዲሱ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት፤ አቶ ተስፋዬ ይገዙን የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አድርጎ ሾመ። ምክ
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል፤ አቶ ተስፋዬ ይገዙን ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አድርጎ ሾመ አዲሱ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት፤ አቶ ተስፋዬ ይገዙን የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አድርጎ ሾመ። ምክር ቤቱ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የመንግስት ዋና ተጠሪ እንዲሆኑ የተመደቡትን የአቶ አለማየሁ ባውዲ ሹመትንም አጽድቋል። ከትላንት ነሐሴ 12፤ 2015 ጀምሮ በአርባ ምንጭ ከተማ መስራች ጉባኤውን እያካሄደ ያለው የደቡብ ኢትዮጵያ ምክር ቤት፤ በዛሬው ውሎው ከተመለከታቸው ጉዳዮች አንዱ የቀረቡለትን የመንግስት ኃላፊዎችን ሹመት ማጽድቅ ነበር። በዚሁ ጉባኤ የክልሉ ርዕሰ መስተዳደር ሆነው የተሾሙት አቶ ጥላሁን ከበደ፤ የስድስት ኃላፊዎችን ሹመት ለምክር ቤቱ አቅርበዋል። ርዕሰ መስተዳድሩ በቅድሚያ ያቀረቡት፤ ለክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርነት ያጯቸውን አቶ ተስፋዬ ይገዙን ነው። በደቡብ ክልል ተመሳሳይ የስልጣን ደረጃ የነበራቸው አቶ ተስፋዬ፤ የከተማ እና ኮንስትራክሽን ቢሮ ኃላፊነትንም ደርበው ሲሰሩ ቆይተዋል። አቶ ተስፋዬ በደቡብ ክልል ውስጥ በቆዩባቸው ዓመታት፤ የወጣቶች እና ስፖርት፣ የግብይት እና ህብረት ስራ እንዲሁም የውሃ እና ማዕድን ቢሮዎችን በኃላፊነት መርተዋል። * ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/11856/ @EthiopiaInsiderNews

አቶ አንተነህ ፈቃዱ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ሆነው ተሾሙ የቀድሞው የደቡብ ክልል የደን እና አካባቢ ጥበቃ ቢሮ ኃላፊ አቶ አንተነህ ፈቃዱ፤ በአዲስ መልክ የተደራጀው የማዕ
አቶ አንተነህ ፈቃዱ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ሆነው ተሾሙ የቀድሞው የደቡብ ክልል የደን እና አካባቢ ጥበቃ ቢሮ ኃላፊ አቶ አንተነህ ፈቃዱ፤ በአዲስ መልክ የተደራጀው የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ሆነው ተሾሙ። በደቡብ ክልል የትምህርት ቢሮ ኃላፊ ሆነው ሲሰሩ ቆዩት ዶ/ር ዲላሞ ኦቶሬ ደግሞ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የመንግስት ዋና ተጠሪ ሆነዋል። ሁለቱን ሹመቶች የሰጡት፤ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ፕሬዝዳንት ሆነው ዛሬ ረፋድ ላይ ቃለ መሃላ የፈጸሙት አቶ እንደሻው ጣሰው ናቸው። አቶ እንደሻው በወልቂጤ ከተማ አስቸኳይ ጉባኤውን ያካሄዱት የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት አባላት፤ ሰባት የካቢኔ አባላት ሹመትን እንዲያጸድቁላቸው አቅርበዋል። አዲሱ የክልሉ ፕሬዝዳነት የእርሳቸው ምክትል እንዲሆኑ የመረጧቸው፤ ወደ ደቡብ ክልል በቢሮ ኃላፊነት ከመዘዋወራቸው በፊት የከንባታ ጠንባሮ ዞን ዋና አስተዳዳሪ የነበሩትን አቶ አንተነህ ፈቃዱን ነው። አዲሱ ተሿሚ በደቡብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ (ደኢህዴን) የስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባል የነበሩ ናቸው። * ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/11853/ @EthiopiaInsiderNews

አዲሱ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አቶ ጥላሁን ከበደን ርዕሰ መስተዳደር አድርጎ ሾመ በህዝበ ውሳኔ የተመሰረተው አዲሱ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት፤ አቶ ጥላሁን ከበደን የክልሉ የመጀመሪያ ርዕሰ መ
አዲሱ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አቶ ጥላሁን ከበደን ርዕሰ መስተዳደር አድርጎ ሾመ በህዝበ ውሳኔ የተመሰረተው አዲሱ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት፤ አቶ ጥላሁን ከበደን የክልሉ የመጀመሪያ ርዕሰ መስተዳደር አድርጎ ሾመ። የደቡብ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ሆነው ሲሰሩ የቆዩት አቶ ጥላሁን ይህንን ሹመት ያገኙት፤ ዛሬ ቅዳሜ ነሐሴ 13፤ 2015 በአርባ ምንጭ ከተማ እየተደረገ ባለው የክልሉ ምክር ቤት ጉባኤ ላይ ነው። መስራች ጉባኤውን በመካሄድ ላይ የሚገኘው የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት በትላትናው ውሎው፤ ፌዴሬሽኑን በመቀላቀል 12ኛ የሆነውን ክልል ህገ መንግስት አጽድቋል። ምክር ቤቱ በዛሬው የጉባኤው መርሃ ግብር ለተለያዩ የክልሉ መንግስት አመራሮች ሹመት የመስጠት አጀንዳ ይዞ ነበር። በዚህም መሰረት በቅድሚያ ሹመት የተሰጠው ለምክር ቤት አፈ ጉባኤ እና ምክትል አፈ ጉባኤ ኃላፊነቶች ነው። የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አድርጎ የሾመው ወ/ሮ ጸሀይን ወራሳን ሲሆን፤ ወ/ሮ ወላይቴ ቢቶ ደግሞ በምክትል አፈ ጉባኤነት ተመርጠዋል። በዛሬው ጉባኤ ላይ ቀጣይ አጀንዳ ሆኖ የቀረበው የአዲሱን ክልል ርዕሰ መስተዳደር መሰየም ነበር። በቀድሞው የደቡብ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳደር አቶ ተስፋዬ ይገዙ አማካኝነት ለኃላፊነት ቦታው የቀረቡት ብቸኛ ዕጩ አቶ ጥላሁን ከበደ ናቸው። * ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/11837/ @EthiopiaInsiderNews

አቶ እንደሻው ጣሰው የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልልን እንዲመሩ ተሾሙ የ“ደቡብ ብሔር ብሔረሰቦች እና ህዝቦች” የሚለውን ስያሜውን ወደ “ማዕከላዊ ኢትዮጵያ” የቀየረው ነባሩ ክልል፤ አቶ እንደሻው ጣሰውን
አቶ እንደሻው ጣሰው የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልልን እንዲመሩ ተሾሙ የ“ደቡብ ብሔር ብሔረሰቦች እና ህዝቦች” የሚለውን ስያሜውን ወደ “ማዕከላዊ ኢትዮጵያ” የቀየረው ነባሩ ክልል፤ አቶ እንደሻው ጣሰውን በምክትል ርዕሰ መስተዳደር ማዕረግ የክልሉ ፕሬዝዳንት አድርጎ ሾመ። ነባሩን ክልልን ሲመሩ በቆዩት አቶ ርስቱ ይርዳው ምትክ የተሾሙት አቶ እንደሻው፤ የብሔራዊ መረጃ እና ደህንነት አገልግሎት ምክትል ዳይሬክተር ሆነው በመስራት ላይ ነበሩ። የ“ማዕከላዊ ኢትዮጵያ” ክልል ምክር ቤት ሹመቱን የሰጠው ዛሬ ቅዳሜ ነሐሴ 13፤ 2015 እያካሄደ ባለው አስቸኳይ ጉባኤው ነው። በትላንትናው ዕለት በተጀመረው በዚሁ የክልሉ ምክር ቤት አስቸኳይ ጉባኤ ላይ፤ ነባሩን ክልል ወደ “ማዕከላዊ ኢትዮጵያ” የሚቀይረው የህገ መንግስት ማሻሻያ ጸድቋል። በደቡብ ብሔር ብሔረሰቦች እና ህዝቦች ክልል ስር የነበሩ መዋቅሮች ከዚህ ቀደም በተለያዩ ጊዜያት በተካሄዱ ህዝበ ውሳኔዎች ራሳቸውን የቻሉ ሶስት ክልሎች መመስረታቸውን ተከትሎ፤ ነባሩ ክልል የስያሜ፣ የአደረጃጃት መዋቅር እና ህገ መንግስት ማሻሻያ አድርጎ እንደሚቀጥል መገለጹ ይታወሳል። ነባሩ ክልሉ ከህገ መንግስቱ ማሻሻያ በተጨማሪ የአስተዳዳሪ ለውጥም አድርጓል። * ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/11833/ @EthiopiaInsiderNews

የሀዋሳ ከተማ ከንቲባ ከኃላፊነታቸው ተነስተው “በህግ እንዲጠየቁ” በሲዳማ ክልል ውሳኔ ተላለፈ ላለፉት ሶስት ዓመታት ገደማ የሀዋሳ ከተማን በከንቲባነት ሲመሩ የቆዩት አቶ ጸጋዬ ቱኬ፤ በ“ብልሹ አሰራ
የሀዋሳ ከተማ ከንቲባ ከኃላፊነታቸው ተነስተው “በህግ እንዲጠየቁ” በሲዳማ ክልል ውሳኔ ተላለፈ ላለፉት ሶስት ዓመታት ገደማ የሀዋሳ ከተማን በከንቲባነት ሲመሩ የቆዩት አቶ ጸጋዬ ቱኬ፤ በ“ብልሹ አሰራር” እና “አፈጻጸም ድክመት” ተገምግመው ከስልጣናቸው መነሳታቸውን የ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” የሲዳማ ክልል ምንጮች ገለጹ። አቶ ጸጋዬ ከኃላፊነት እንዲነሱ ውሳኔ የተላለፈው ትላንት ረቡዕ ነሐሴ 10፤ 2015 ከተደረገ ግምገማ በኋላ መሆኑን ምንጮቹ አስታውቀዋል። በሲዳማ ክልል ደረጃ ያሉ የፓርቲ እና የመንግስት ስራዎች አፈጻጸም እየተገመገሙበት ያለው መድረክ መካሄድ የጀመረው ካለፈው ሳምንት መጨረሻ እሁድ ነሐሴ 7፤ 2015 ነው። በዚህ መድረክ ላይ የተሳተፉ አንድ ምንጭ፤ ከሀዋሳው ከንቲባ በተጨማሪ ሌሎች የክልሉ አመራሮች ላይ ግምገማ መደረጉን አመልክተዋል። ከእሁድ ጀምሮ የነበሩትን ግምገማዎች በአካል ተገኝተው የተሳተፉት አቶ ጸጋዬ፤ እርሳቸውን በሚመልከተው የትላንት ከሰዓቱ ግምገማ ግን አለመገኘታቸውን እኚሁ ምንጭ አክለዋል። በትላንቱ ግምገማ ላይ አቶ ጸጋዬ “ከፍተኛ ሙስና ውስጥ መግባታቸውን” የሚያመለክቱ፣ “በሰነዶች የተረጋገጡ” መረጃዎችን መቅረባቸውን በመድረኩ የተሳተፉ ሁለት የ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ምንጮች ተናግረዋል። በዚሁ ግምገማ “ከፍተኛ ተመራጭ የነበረችው የሀዋሳ ከተማ ወደ ኋላ መሄዷ” መነሳቱን የጠቆሙት ምንጮች፤ የከተማዋ ከንቲባ “የአቅም ውስንነት ጭምር አለባቸው” መባሉን ጠቅሰዋል። * ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/11813/ @EthiopiaInsiderNews

በአዲስ አበባ ከተማ “በትምህርት ቤቶች” እና “በተለያዩ ቦታዎች” የታሰሩ ሰዎች መኖራቸውን የሰላም ሚኒስትሩ አመኑ በአማራ ክልል ከተከሰተው የጸጥታ ችግር ጋር በተያያዘ በአዲስ አበባ ከተማ “በትምህ
በአዲስ አበባ ከተማ “በትምህርት ቤቶች” እና “በተለያዩ ቦታዎች” የታሰሩ ሰዎች መኖራቸውን የሰላም ሚኒስትሩ አመኑ በአማራ ክልል ከተከሰተው የጸጥታ ችግር ጋር በተያያዘ በአዲስ አበባ ከተማ “በትምህርት ቤቶች” እና “በተለያዩ ቦታዎች” የታሰሩ ሰዎች መኖራቸውን የሰላም ሚኒስትሩ አቶ ብናልፍ አንዷለም አመኑ። በፖሊስ ቁጥጥር ስር መዋላቸው በይፋ ከተገለጹ ግለሰቦች ውጭ ያሉ እስሮች የተፈጸሙት፤ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እንጂ በአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መምሪያ ዕዝ (ኮማንድ ፖስት) አለመሆኑንም ገልጸዋል። የሰላም ሚኒስትሩ በአዲስ አበባ የታሰሩ ሰዎችን በተመለከተ ማረጋገጫ የሰጡት፤ ከፖለቲካ ፓርቲዎች ተወካዮች ጋር ከትላንት በስቲያ ሰኞ ነሐሴ 8፤ 2015 ባደረጉት ውይይት ላይ ይህንኑ አስመልክቶ ለተነሱላቸው ጥያቄ በሰጡት መልስ ነው። አቶ ብናልፍ እና የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አለበል የመሩት ይህ ስብሰባ የተካሄደው፤ በአማራ ክልል የተከሰተውን የጸጥታ ችግር አስመልክቶ ለፖለቲካ ፓርቲ ተወካዮቹ ገለጻ ለማድረግ ነበር። ሶስት ሰዓት ከ40 ደቂቃ ገደማ በፈጀው በዚህ ስብሰባ ላይ፤ ሁለቱ ሚኒስትሮች ያቀረቡትን ገለጻ ተከትሎ የፖለቲካ ፓርቲ ተወካዮች ሀሳብ እና ጥያቄዎችን ሰንዝረዋል። አብዛኛዎቹ ተሳታፊዎች በአማራ ክልል ለተከሰተው ግጭት መንግስት ጥፋተኛ ሲያደርጉ ተደምጠዋል። መንግስት በክልሉ ላለው ችግር አስቀድሞ መፍትሄ ከመስጠት ይልቅ “ጉዳዩን በኃይል ለመፍታት ሞክሯል” ሲሉም ወቅሰዋል። * ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/11810/ @EthiopiaInsiderNews

የአዲሱ የ“ደቡብ ኢትዮጵያ ክልል” የምስረታ በዓል በመጪው ቅዳሜ በአርባ ምንጭ ከተማ ሊካሄድ ነው 🔴የነባሩ የደቡብ ክልል ምክር ቤትም ለሳምንቱ መጨረሻ አስቸኳይ ጉባኤ ጠርቷል በህዝበ ውሳኔ የተመሰ
የአዲሱ የ“ደቡብ ኢትዮጵያ ክልል” የምስረታ በዓል በመጪው ቅዳሜ በአርባ ምንጭ ከተማ ሊካሄድ ነው 🔴የነባሩ የደቡብ ክልል ምክር ቤትም ለሳምንቱ መጨረሻ አስቸኳይ ጉባኤ ጠርቷል በህዝበ ውሳኔ የተመሰረተው 12ኛው የ“ደቡብ ኢትዮጵያ ክልል” ይፋዊ የምስረታ በዓሉን በሳምንቱ መጨረሻ በአርባ ምንጭ ከተማ ሊያደርግ ነው። የነባሩ የደቡብ ክልል ምክር ቤትም በተመሳሳይ ቀናት አስቸኳይ ጉባኤ መጥራቱን የምክር ቤቱ አፈ ጉባኤ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናግረዋል። በአርባ ምንጭ ከተማ የሚካሄደው የ“ደቡብ ኢትዮጵያ ክልል” ምስረታ ለሁለት ቀናት የሚቆይ መሆኑን የጋሞ ዞን መንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ ኃላፊ ኤደን ንጉሴ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ገልጸዋል። ከነገ በስቲያ አርብ ነሐሴ 12፤ 2015 በሚኖረው መርሃ ግብር፤ የአዲሱ ክልል ምክር ቤት መስራች ጉባኤውን እንደሚያደርግ ኃላፊዋ አስረድተዋል። በዚሁ ጉባኤ ላይ የምክር ቤቱ አባላት የአዲሱን ክልል ህገ መንግስቱን ተወያይተው ያጸድቃሉ ተብሎ እንደሚጠበቅም ተናግረዋል። በማግስቱ ቅዳሜ ደግሞ 12ኛው የፌደሬሽኑ ክልል በይፋ የምስረታ ፕሮግራሙን እንደሚያካሄድ ኤደን ጠቁመዋል። የአዲሱ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እና የካቤኔ አባላትም በዚሁ ቀን ይሾማሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ ምንጮች ገልጸዋል። * ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/11803/ @EthiopiaInsiderNews

ከተበተኑ የአማራ ክልል የልዩ ኃይል አባላት መካከል፤ “አብዛኛዎቹ” ታጣቂ ቡድኖችን መቀላቀላቸውን የሰላም ሚኒስትሩ ገለጹ በአማራ ክልል የልዩ ኃይል አባላትን ወደ ሌሎች የጸጥታ መዋቅሮች የማስገባት
ከተበተኑ የአማራ ክልል የልዩ ኃይል አባላት መካከል፤ “አብዛኛዎቹ” ታጣቂ ቡድኖችን መቀላቀላቸውን የሰላም ሚኒስትሩ ገለጹ በአማራ ክልል የልዩ ኃይል አባላትን ወደ ሌሎች የጸጥታ መዋቅሮች የማስገባት ስራ ከተጀመረ በኋላ 50 በመቶ የሚሆኑ የልዩ ኃይል አባላት “እንደተበተኑ” እና ከእነዚህ ውስጥ “አብዛኛዎቹ” ታጣቂ ቡድኖችን እንደተቀላቀሉ የሰላም ሚኒስትሩ አቶ ብናልፍ አንዷለም ተናገሩ። በአማራ ክልል ከሰሞኑ የተቀሰቀሰው ግጭት የተጀመረው፤ ታጣቂዎች በመከላከያ ሰራዊት ካምፕ ላይ “ዘግናኝ የሚባል ጥቃት መክፈታቸውን” ተከትሎ እንደሆነም ገልጸዋል። የሰላም ሚኒስትሩ አቶ ብናልፍ ይህንን የተናገሩት፤ በአማራ ክልል ከሰሞኑ የተፈጠረውን የጸጥታ ችግር አስመልክቶ ትላንት ሰኞ ነሐሴ 8፤ 2015 ከፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር በአዲስ አበባው ካፒታል ሆቴል በተደረገ ውይይት ላይ ነው። አቶ ብናልፍ እና የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አለበል በመሩት በዚህ ስብሰባ 16 የፖለቲካ ፓርቲ ተወካዮች ተሳትፈውበታል። አቶ ብናልፍ በስብሰባው መጀመሪያ ላይ ባቀረቡት ማብራሪያ፤ መንግስት በአማራ ክልል ያጋጠመው ግጭት “ዝም ብሎ በድንገት የተፈጠረ” ነው የሚል እምነት እንደሌለው እና “በተለያዩ ጊዜ የሚነሱ እና እየተደመሩ የመጡ ችግሮች የፈጠሩት” እንደሆነ አስረድተዋል። የሰላም ሚኒስትሩ በዚሁ ማብራሪያቸው ላይ በአማራ ክልል ለተፈጠረው ችግር ምክንያት የሆኑ ካሏቸው “የህዝብ ጥያቄዎች” ውስጥ፤ የወሰን እና ማንነት ጉዳይ፣ የፍትሃዊ ተጠቃሚነት እና የእኩልነት ጥያቄ እንዲሁም “የፈለጉትን የፖለቲካ ሀሳብ ለማራመድ የሚያስችል ሁኔታ አለመኖር” የሚሉት ይገኙበታል። * ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/11795/ @EthiopiaInsiderNews

በአማራ ክልል “ሁሉንም ኃይሎች” ያካተተ “ጊዜያዊ አስተዳደር” እንዲቋቋም አቶ ገዱ አንዳርጋቸው ጠየቁ የቀድሞው የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ገዱ አንዳርጋቸው በአማራ ክልል “ሁሉንም ኃይሎች”
በአማራ ክልል “ሁሉንም ኃይሎች” ያካተተ “ጊዜያዊ አስተዳደር” እንዲቋቋም አቶ ገዱ አንዳርጋቸው ጠየቁ የቀድሞው የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ገዱ አንዳርጋቸው በአማራ ክልል “ሁሉንም ኃይሎች” ያካተተ “ጊዜያዊ አስተዳደር” እንዲቋቋም ጠየቁ። አቶ ገዱ በአማራ ክልል ያለውን “ችግር በቅንነት ለመፍታት” ፖለቲካዊ ንግግር መደረግ እንዳለበትም አሳስበዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድን ወደ ስልጣን ያመጣውን “ለውጥ” ከመሩ ባለስልጣናት አንዱ መሆናቸው የሚነገርላቸው አቶ ገዱ ይህን ማሳሰቢያ የሰጡት፤ በዋነኛነት በአማራ ክልል ተፈጻሚ የሚሆነው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ በተወካዮች ምክር ቤት ከመጽደቁ በፊት ባስደመጡት አስተያየት ነው። የገዢው ብልጽግና ፓርቲ የፓርላማ ተወካይ የሆኑት አቶ ገዱ፤ ዛሬ በተካሄደው አስቸኳይ ስብሰባ የተገኙት፤ በአማራ ክልል ለተፈጠረው ችግር “በቅንነት” ሃሳባቸውን በማቅረብ “አስተዋጽኦ ለማበርከት” በማሰብ እንደሆነ ገልጸዋል። የአማራ ክልልን ለአምስት ዓመታት የመሩት አቶ ገዱ፤ በክልሉ በአሁኑ ወቅት ያለውን ችግር ለመፍታት መፍትሔው “የፖለቲካ ውይይት፤፡ መሆኑን አጽንኦት ሰጥተው ተናግረዋል። “ይህን ችግር በቅንነት ለመፍታት ከተፈለገ መፍትሔው፤ እስካሁን በአማራ ክልልም ሆነ በሌሎች የኢትዮጵያ ክፍሎች ሲሞከር ከርሞ ሀገርን ወደ ከፋ ጥፋት ያመራው ወታደራዊ ኃይል መጠቀም ሳይሆን፤ የፖለቲካ ውይይት ነው የሚል እምነት አለኝ” ብለዋል አቶ ገዱ። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር) @EthiopiaInsiderNews

የተወካዮች ምክር ቤት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅን በአብላጫ ድምጽ አጸደቀ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ከአንድ ሳምንት በፊት የወጣውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ በአብላጫ ድምጽ አጸደቀ። አዋጁን 16 የፓርላማ
የተወካዮች ምክር ቤት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅን በአብላጫ ድምጽ አጸደቀ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ከአንድ ሳምንት በፊት የወጣውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ በአብላጫ ድምጽ አጸደቀ። አዋጁን 16 የፓርላማ አባላት ሲቃወሙት፤ 12 አባላት ደግሞ ድምጽ ከመስጠት ታቅበዋል። የሚኒስትሮች ምክር ቤት ሐምሌ 28፤ 2015 በሙሉ ድምጽ ባሳለፈው ውሳኔ መሰረት፤ በአማራ ክልል እና “እንዳስፈላጊነቱ በሌሎች የሀገሪቱ ክፍሎች” ተግባራዊ እየተደረገ የሚገኘውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ለማጽደቅ በዛሬው ዕለት የተገኙት የፓርላማ አባላት ብዛት 360 ነበር። በዛሬው አስቸኳይ የፓርላማ ስብሰባ ላይ አስተያየታቸውን ከሰጡ አስራ ስድስት የፓርላማ አባላት መካከል፤ የአዋጁ መጽደቅ የሚቃወም ሀሳብ የሰነዘሩት አራቱ ብቻ ናቸው። የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን የተቃወሙት ሁሉም የፓርላማ አባላት ከአማራ ክልል ተመርጠው የተወካዮች ምክር ቤትን የተቀላቀሉ ናቸው። የገዢው የብልጽግና ፓርቲ ተመራጮች ከሆኑ ሶስት የፓርላማ አባላት በተጨማሪ የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) ተወካዩ አቶ አበባው ደሳለው ተቃውሟቸውን በዛሬው ስብሰባ ላይ አሰምተዋል። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር) [በዚህ ዘገባ ላይ ተጨማሪ መረጃ ይታከልበታል] @EthiopiaInsiderNews

ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ኢትዮጵያ ከጎረቤቶቿ የሚያስፈልጓትን ነገሮች ጉልበት በመጠቀም “አንበርክካ መንጠቅ የምትፈልግ ሀገር አይደለችም” አሉ ኢትዮጵያ ከጎረቤቶቿ እና ከሌሎች አፍሪካ ሀገራት
ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ኢትዮጵያ ከጎረቤቶቿ የሚያስፈልጓትን ነገሮች ጉልበት በመጠቀም “አንበርክካ መንጠቅ የምትፈልግ ሀገር አይደለችም” አሉ ኢትዮጵያ ከጎረቤቶቿ እና ከሌሎች አፍሪካ ሀገራት የሚያስፈልጓትን ነገሮች ለማግኘት “በድርድር፣ በምክክር፣ በሰጥቶ መቀበል መርህ” የምትመራ እንጂ፤ ያላትን ጉልበት በመጠቀም “አንበርክካ መንጠቅ የምትፈልግ ሀገር አይደለችም” ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ተናገሩ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ “ኢትዮጵያ ለሁሉም ጎረቤቶቿ የሰላም ምንጭ እንጂ የጦርነት ምንጭ አትሆንም” ብለዋል። አብይ ይህን ያሉት ቅዳሜ ነሐሴ 6፤ 2015 በብላቴ ኮማንዶ እና የአየር ወለድ ማሰልጠኛ ማዕከል በተካሄደው “የኤሊት ኃይል” የምረቃ ስነ ስርዓት ላይ ባስተላለፉት መልዕክት ነው። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዚሁ መልዕክታቸው ኢትዮጵያ በአፍሪካ ያላት ቦታ ከፍ ያለ እንደሆነ አጽንኦት ሰጥተው ተናግረዋል። “ኢትዮጵያ ትልቅ ኢኮኖሚ እየገነባች ያለች ትልቅ ሀገር ናት” ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ሀገሪቱ የአፍሪካ “powerhouse” መሆኗን “ጠላቶቻችን እየመረራቸው ሊውጡት የሚገባ ጉዳይ ነው” ሲሉ ጠንከር ባለ አነጋገር አስታውቀዋል። ኢትዮጵያ በአፍሪካ ውስጥ “ስመ ገናና፣ ኃያል፣ ተጽዕኖ ፈጣሪ ሀገር ናት” ሲሉ በንግግራቸው ያስገነዘቡት አብይ፤ “የዚህች ታላቅ ሀገር ሰራዊት ሆኖ ማገልገል፣ ቀይ መለዮ ለባሽ መሆን ታላቅ ክብር ነው” ሲሉ ለተመራቂ “ኮማንዶዎች” “የእንኳን ደስ አላችሁ” መልዕክት አስተላልፈዋል። በሺህዎች የሚቆጠሩ እንደሆኑ የተነገረላቸው የዛሬዎቹ ተመራቂዎች፤ “ሙሉ የኮማንዶ እና የአየር ወለድ ስልጠና” የተከታተሉ መሆናቸው ተገልጿል። * ሙሉ ዘገባውን ለማንበብ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/11744/ @EthiopiaInsiderNews

የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ተፈጻሚነት በአማራ ክልል ብቻ እንዲገደብ፤ ጊዜውም ወደ አንድ ወር እንዲያጥር ኢሰመኮ ምክረ ሃሳብ አቀረበ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን የተፈጻሚነት ጊዜ
የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ተፈጻሚነት በአማራ ክልል ብቻ እንዲገደብ፤ ጊዜውም ወደ አንድ ወር እንዲያጥር ኢሰመኮ ምክረ ሃሳብ አቀረበ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን የተፈጻሚነት ጊዜ “ከአንድ ወር ወይም የተወሰኑ ሳምንታት ላልበለጠ ጊዜ ብቻ” እንዲሆን እንዲያደርግ እና የተፈጻሚነት ወሰኑንም በአማራ ክልል ብቻ እንዲገድብ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ጠየቀ። በአዋጁ ለአስቸኳይ ጊዜ ጠቅላይ መምሪያ ዕዝ “የተለያዩ የአስተዳደር እርከኖችን እና መዋቅሮችን መልሶ ለማቋቋም” የተሰጠውን ስልጣን ፓርላማው እንዲሰርዝም ጥያቄ አቅርቧል፡፡ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን እነዚህን ጥያቄዎች ያቀረበው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ በተመለከተ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባቀረበው ባለ 22 ገጽ የምክረ ሃሳብ ሰነድ ላይ ነው። ኢሰመኮ ይህንን ምክረ ሃሳብ ዛሬ ቅዳሜ ነሐሴ 6፤ 2015 ይፋ ያደረገው፤ የተወካዮች ምክር ቤት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅን መርምሮ ውሳኔ ለማሳለፍ ከነገ በስቲያ አስቸኳይ ስብሰባ እንደሚያካሄድ መገለጹን ተከትሎ ነው። ብሔራዊው የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ተቋም፤ የሰብአዊ መብቶች ስጋቶች እና የማሻሻያ ምክረ ሃሳቦች ባካተተበት ሰነድ ላይ በቅድሚያ ያነሳው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ለተወካዮች ምክር ቤት ያለመቅረቡን ጉዳይ ነው። አዋጁ በፓርላማ ሳይጸድቅ ከባለፈው ሳምንት ጀምሮ ተፈጻሚ መሆኑ፤ “የመንግስት የአስቸኳይ ጊዜ ስልጣን ለበርካታ ቀናት ያለ ምክር ቤቱ እይታ እና ቁጥጥር” እንዲቆይ ምክንያት እንደሆነ ኢሰመኮ አመልክቷል። ፓርላማው በሰኞ ስብሰባው አዋጁን የሚያጸድቀው ከሆነ፤ ድንጋጌው ከወጣበት ጊዜ ጀምሮ የነበረውን አፈጻጸም የተመለከተ ሪፖርት መንግስት እንዲያቀርብ እንዲደረግ ኮሚሽኑ ጠይቋል። ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/11740/

አቶ ክርስቲያን ታደለ እና ዶ/ር ካሳ ተሻገር “አካልን ነጻ የማውጣት” አቤቱታ ለፍርድ ቤት አቀረቡ በፖሊስ ቁጥጥር ስር የሚገኙት የፓርላማ አባሉ አቶ ክርስቲያን ታደለ እና የአዲስ አበባ ምክር ቤት
አቶ ክርስቲያን ታደለ እና ዶ/ር ካሳ ተሻገር “አካልን ነጻ የማውጣት” አቤቱታ ለፍርድ ቤት አቀረቡ በፖሊስ ቁጥጥር ስር የሚገኙት የፓርላማ አባሉ አቶ ክርስቲያን ታደለ እና የአዲስ አበባ ምክር ቤት አባሉ ዶ/ር ካሳ ተሻገር በጠበቆቻቸው አማካኝነት “አካልን ነጻ የማውጣት” (habeas corpus) አቤቱታ ለፍርድ ቤት አቀረቡ። አቤቱታው የቀረበለት ፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ተረኛ ችሎት፤ የፌደራል ፖሊስ በጽሁፍ ምላሽ እንዲሰጥ አዝዟል። የአቶ ክርስቲያን እና ዶ/ር ካሳ ጠበቆች አቤቱታቸውን ዛሬ ማክሰኞ ነሐሴ 2፤ 2015 ያቀረቡት፤ የፌደራል ፖሊስ ያለመከሰስ መብት ያላቸው ደንበኞቻቸውን ካለፈው ሳምንት መጨረሻ ጀምሮ “ያለምንም ፍርድ በእስር ላይ ያቆያቸው” መሆኑን በመጥቀስ ነው። በጠበቃ ሄኖክ አክሊሉ እና ሰለሞን ገዛኸኝ አማካኝነት የቀረበው አቤቱታ፤ በምክር ቤት የህዝብ ተወካዮቹ የተያዙበትን መንገድ ለፍርድ ቤቱ አብራርቷል። በአንድ ገጽ የተዘጋጀው ይህ አቤቱታ፤ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል የሆኑት አቶ ክርስቲያን ታደለ ባለፈው ሳምንት አርብ ከመኖሪያ ቤታቸው “እየተደበደቡ ተይዘው” በፌደራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ቢሮ መታሰራቸውን አትቷል። ዶ/ር ካሳ ተሻገርም በዚሁ ቀን ከለሊቱ ስድስት ሰዓት ገደማ በፌደራል ፖሊስ ተይዘው፤ በተመሳሳይ ቦታ ታስረው እንደሚገኙ በአቤቱታው ላይ ሰፍሯል። የፌደራል ፖሊስ ሁለቱንም ግለሰቦች የያዛቸው “ለጥያቄ እፈልጋቸዋለሁ” በሚል መሆኑንም በአቤቱታው ተመላክቷል። * ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/11733/ @EthiopiaInsiderNews

የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በመላው ሀገሪቱ የሚታዩ ግጭቶች “ያላንዳች ቅደመ ሁኔታ ቆመው” “በአስቸኳይ” በምክክር እንዲፈቱ ጥሪ አቀረበ። ኮሚሽኑ ባለድርሻ አካላትን “በማቀራረብ፣ የልዩነት አ
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በመላው ሀገሪቱ የሚታዩ ግጭቶች “ያላንዳች ቅደመ ሁኔታ ቆመው” “በአስቸኳይ” በምክክር እንዲፈቱ ጥሪ አቀረበ። ኮሚሽኑ ባለድርሻ አካላትን “በማቀራረብ፣ የልዩነት አጀንዳዎችን ሰብስቦ ለማወያየት እና ለማመካከር አመቺ ሁኔታዎችን ለመፍጠር ዝግጁ መሆኑን” አስታውቋል። ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽኑ የሚመለከታቸው አካላት ልዩነቶቻቸውን በጠረጴዛ ዙሪያ ተቀምጠው በምክክር እንዲፈቱ የጠየቀው፤ ወቅታዊ ጉዳዮችን አስመልክቶ ዛሬ ማክሰኞ ነሐሴ 2፤ 2015 በጽህፈት ቤቱ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ነው። የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር ፕ/ር መስፍን አርዓያ በንባብ ባሰሙት መግለጫ፤ ለሀገራዊ ምክክሩ የተሳታፊዎች የተሳታፊዎች ልየታ እየተከናወነ ባለበት ሁኔታ በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች አየታዩ ያሉ “ደም አፋሳሽ ግጭቶች” የኮሚሽኑን ስራ “አዳጋች እያደረጉበት ይገኛሉ” ብለዋል። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር) [በዚህ ዘገባ ላይ ተጨማሪ መረጃ ይታከልበታል] @EthiopiaInsiderNews

ጋዜጠኛ በቃሉ አላምረው ለአራተኛ ጊዜ በፖሊስ ቁጥጥር ስር ዋለ “አልፋ ሚዲያ” የተሰኘው የበይነ መረብ መገናኛ ብዙሃን መስራች እና አዘጋጅ የሆነው ጋዜጠኛ በቃሉ አላምረው፤ ትላንት እሁድ ሐምሌ 30፤
ጋዜጠኛ በቃሉ አላምረው ለአራተኛ ጊዜ በፖሊስ ቁጥጥር ስር ዋለ “አልፋ ሚዲያ” የተሰኘው የበይነ መረብ መገናኛ ብዙሃን መስራች እና አዘጋጅ የሆነው ጋዜጠኛ በቃሉ አላምረው፤ ትላንት እሁድ ሐምሌ 30፤ 2015 የሁለተኛ ዲግሪ የምርቃት ስነ ስርዓት ተሳትፎ ወደ መኖሪያ ቤቱ ከተመለሰ በኋላ በጸጥታ ኃይሎች ቁጥጥር ስር መዋሉን ቤተሰቦቹ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናገሩ። በጋዜጠኛ በቃሉ መኖሪያ ቤት ዛሬ ማለዳ ከ12፡30 ጀምሮ ለአንድ ሰዓት ያህል የቆየ ፍተሻ መካሄዱንም ቤተሰቦቹ ገልጸዋል። ሶስት የፌደራል ፖሊስ የደንብ ልብስ እና ሲቪል የለበሱ የጸጥታ አካላት፤ በአዲስ አበባ ከተማ አራት ኪሎ አካባቢ ወደሚገኘው የጋዜጠኛው መኖሪያ ቤት በመጀመሪያ የመጡት ትላንት ከቀኑ ስምንት ሰዓት ገደማ እንደሆነ ቤተሰቦቹ አስረድተዋል። የሁለተኛ ዲግሪ ምርቃቱን ከቤተሰቦቹ ጋር እያከበረ የነበረውን ጋዜጠኛ በቃሉን፤ “ለጥያቄ እፈልግሃለን” ብለው ሜክሲኮ አካባቢ ወደሚገኘው የፌደራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ቢሮ እንደወሰዱትም አክለዋል። ከባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ በአማርኛ ቋንቋ እና ስነ ጽሁፍ መጀመሪያ ዲግሪውን ያገኘው በቃሉ፤ በትላንትናው ዕለት ከ“ኒው ጀነሬሽን” ዩኒቨርሲቲ በ“Global study and international relations” በማስተርስ ዲግሪ ተመርቋል። ጋዜጠኛው ይህን ትምህርት የተከታተለው “ከመሳደድ እና እስር ጎን ለጎን” መሆኑን ከምርቃቱ በኋላ በፌስ ቡክ ገጹ ላይ ጽፎ ነበር። * ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/11707/ @EthiopiaInsiderNews

በአማራ ክልል የተቋቋሙት አራት ኮማንድ ፖስቶች በስራቸው እነማንን ያካልላሉ? ለስድስት ወር ጸንቶ የሚቆየው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ በዋነኛነት ተፈጻሚ የሚሆንበት የአማራ ክልል በአራት “ኮማንድ ፖስት” መከፈሉን አቶ ተመስገን ጥሩነህ በዛሬው ማብራሪያቸው አስረድተዋል። ኮማንድ ፖስቶቹን የሚመሩት አባላት ከመከላከያ ሰራዊት፣ ከብሔራዊ መረጃ እና ደህንነት አገልግሎት፣ ከፌደራል ፖሊስ፣ ከክልሉ መንግስት፣ ከገዢው ብልጽግና ፓርቲ እና ከኮሙኒኬሽን የተውጣጡ መሆናቸውን ገልጸዋል። 1. “የምዕራብ አማራ ኮማንድ ፖስት” 🔴 ባህር ዳር ከተማ 🔴 ደብረ ማርቆስ ከተማ 🔴 ምስራቅ ጎጃም ዞን 🔴 ምዕራብ ጎጃም ዞን 🔴 የአዊ ብሔረሰብ አስተዳደር 2. “የሰሜን ምዕራብ አማራ ኮማንድ ፖስት” 🔴 ጎንደር ከተማ 🔴 ደብረ ታቦር ከተማ 🔴 የቀድሞው ሰሜን ጎንደር ዞን የአሁኑ ሰሜን ምዕራብ ጎንደር ዞን 🔴 ማዕከላዊ ጎንደር ዞን 🔴 ደቡብ ጎንደር ዞን 3. “ማዕከላዊ ሸዋ ኮማንድ ፖስት” 🔴 ደብር ብርሃን ከተማ 🔴 ሰሜን ሸዋ ዞን 🔴 ኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን 4. “ምስራቅ አማራ ኮማንድ ፖስት” 🔴 ደሴ ከተማ 🔴 ኮምቦልቻ ከተማ 🔴 ወልዲያ ከተማ 🔴 ሰሜን ወሎ ዞን 🔴 ደቡብ ወሎ ዞን 🔴 የዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር * * ዝርዝር ዘገባውን ለማንበብ ይህን ሊንክ ይጫኑ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/11682/

በአማራ ክልል የሚንቀሳቀሱ ኃይሎች “አንዳንድ የዞን እና የወረዳ ከተሞችን መቆጣጠራቸውን” እንዲሁም በተወሰኑ ቦታዎች “ወንጀለኞችን ከማረሚያ ቤት ማስለቀቃቸውን” የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ጠቅላይ መመሪያ
በአማራ ክልል የሚንቀሳቀሱ ኃይሎች “አንዳንድ የዞን እና የወረዳ ከተሞችን መቆጣጠራቸውን” እንዲሁም በተወሰኑ ቦታዎች “ወንጀለኞችን ከማረሚያ ቤት ማስለቀቃቸውን” የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ጠቅላይ መመሪያ ዕዝ ዋና ሰብሳቢ አቶ ተመስገን ጥሩነህ አስታወቁ። አቶ ተመስገን “ዘራፊ” ሲሉ የጠሯቸው እነዚሁ ኃይሎች፤ “የክልሉን መንግስት በማፍረስ ወደ ፌደራል ስርዓት የመሄድ” ፍላጎት እና ግብ ያላቸው መሆናቸውን ተናግረዋል። አቶ ተመስገን ጥሩነህ ይህን የተናገሩት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ጠቅላይ መመሪያ ዕዝ ቀጣይ ስራዎችን በተመለከተ ዛሬ ሐምሌ 30፤ 2015 ከተደረገ ስብሰባ በኋላ በሰጡት ማብራሪያ ነው። የዕዙ ሰብሳቢ በዚሁ ማብራሪያቸው በ“ጎጃም ቀጠና” ላይ በታዩ “የጸጥታ መደፍረስ እንቅስቃሴዎች”፤ “የመንቀሳቀስ መብት የሚገድቡ ሁኔታዎች ተስተውለዋል” ብለዋል። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር) [በዚህ ዘገባ ላይ ተጨማሪ መረጃ ይታከልበታል]

በክልሎች መካከል የሚኖረው የንብረት ክፍፍል የተፈጻሚነት ወሰን፤ በደቡብ ክልል ምክር ቤት ጉባኤ ላይ ጥያቄ አስነሳ በነባሩ የደቡብ ክልል እና በአዲሱ የ“ደቡብ ኢትዮጵያ” ክልል መካከል የሚኖረውን የ
በክልሎች መካከል የሚኖረው የንብረት ክፍፍል የተፈጻሚነት ወሰን፤ በደቡብ ክልል ምክር ቤት ጉባኤ ላይ ጥያቄ አስነሳ በነባሩ የደቡብ ክልል እና በአዲሱ የ“ደቡብ ኢትዮጵያ” ክልል መካከል የሚኖረውን የንብረት ክፍፍል በተመለከተ የቀረበ የውሳኔ ሃሳብ (ሞሽን) በደቡብ ክልል ምክር ቤት አባላት ጥያቄ አስነሳ። የክልሉ ምክር ቤት አባላት ጥያቄውን ያነሱት፤ የንብረት ክፍፍሉ በሲዳማ እና በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልሎች ላይ ጭምር “ተፈጻሚ ይሆናል” በመባሉ ነው። ለጥያቄዎች መነሻ የሆነውን የውሳኔ ሃሳብ ዛሬ ቅዳሜ ሐምሌ 29፤ 2015 በተካሄደው የደቡብ ክልል ምክር ቤት መደበኛ ጉባኤ ላይ ያቀረቡት፤ አዲሱን ክልል የሚያደራጀው ፕሮጀክት ጽህፈት ቤት ምክትል ስራ አስኪያጅ አቶ ኑርዬ ሱሌ ናቸው። የውሳኔ ሃሳቡ፤ በነባሩ የደቡብ ክልል እና ዛሬ በይፋ ስልጣን በተረከበው የ“ደቡብ ኢትዮጵያ” ክልል መካከል የሚኖረውን አስተዳደራዊ እና ህጋዊ ጉዳዮች የሚመሩበትን ስርዓት የያዘ ነው። በስድስት ክፍሎች በተዘጋጀው የውሳኔ ሃሳብ ከተነሱ ጉዳዮች መካከል፤ የተፈጻሚነት ወሰንን የሚያትተው ይገኝበታል። በነባሩ እና በ12ኛነት ፌዴሬሽኑን በተቀላቀለው ክልል መካከል የሚነሳው የሃብት እና ዕዳ ክፍፍል፤ በሲዳማ እና በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልሎች ላይ ተፈጻሚ እንደሚሆንም በውሳኔ ሃሳቡ ላይ ሰፍሯል። * ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/11667/ @EthiopiaInsiderNews