en
Feedback
በመሠረተ ክርስቶስ ቤ/ክ ቤቴል የዓለም ብርሃን አጥቢያ ዋናው ቻናል

በመሠረተ ክርስቶስ ቤ/ክ ቤቴል የዓለም ብርሃን አጥቢያ ዋናው ቻናል

Open in Telegram
376
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
+630 days
Posts Archive
የተወደዳችሁ የአጥቢያችን ቅዱሳን የጌታ ፀጋና ሰላም ይብዛላችሁ ከዛሬ ሚያዝያ 7 ቀን 2016 ዓ.ም እስከ ሚያዝያ 25 ቀን 2016 ዓ.ም ድረስ በቤተክርስቲያናችን የፆም ፀሎት እንደታወጀ ታውቃላችሁ በመሆኑም ሁላችንም ባለንበት እንድንተጋና በአንድ ሀሳብ እንድንፀልይ የዛሬው ዋናው ርዕሳችን ምስጋና ነው በሁሉ አመስግኑ “ሳታቋርጡ ጸልዩ፤ በሁሉ አመስግኑ፤ ይህ የእግዚአብሔር ፈቃድ በክርስቶስ ኢየሱስ ወደ እናንተ ነውና።” — 1ኛ ተሰሎንቄ 5፥17-18

👉👉👉 ጥናታችን ዛሬ 10:00 ላይ ይጀመራል። 🎼🥁🎹🎤🔉ኑ ለጌታ እንዘምር 🎼🥁🎹🎤🔉 የተወደዳችሁ  የቤተክርስቲያናችን  እናቶች  እና  አባቶች ለትንሳዔ ዋዜማ የአዳር ፕሮግራም እግዚአብሔርን በዝማሬ እንደምናገለግል ከዚህ ቀደም በማስታወቅያ ተገልጿል፤ ስለዚህም ዛሬ እሁድ ሚያዝያ 6፤2016ዓ.ም ጀምሮ ጥናት ስላለን ሁላችሁም እናትና አባቶች በ10:00 ሰዓት ላይ ቤተክርስቲያን እንድትገኙ በፍቅር እንጋብዝዎታለን ። ማሳሰብያ፦ መቅረትም ሆነ ማርፈድ ፈፅሞ የተከለከለ ነዉ ።                        የትንሳዔ  አስተባባሪ ኮሚቴ

የተወደዳችሁ የቤተክርስቲያናችን ባለትዳሮች በዚህ የተወደደ የትምህርት ጊዜ እንዳትቀሩ አደረ እላለሁ ተባረኩ

🎼🥁🎹🎤🔉 ኑ ለጌታ እንዘምር  🎼🥁🎹🎤🔉 የተወደዳችሁ  የቤተክርስቲያናችን  እናቶች  እና  አባቶች ለትንሳዔ ዋዜማ የአዳር ፕሮግራም እግዚአብሔርን በዝማሬ እንደምናገለግል ከዚህ ቀደም በማስታወቅያ ተገልጿል፤ ስለዚህም ከፊታችን ባለዉ እሁድ ሚያዝያ 6፤2016ዓ.ም ጀምሮ ጥናት ስለሚኖረን ሁላችሁም እናትና አባቶች በ10:00 ሰዓት ላይ ቤተክርስቲያን እንድትገኙ በፍቅር እንጋብዝዎታለን ። ማሳሰብያ፦ መቅረትም ሆነ ማርፈድ ፈፅሞ የተከለከለ ነዉ ።                        የትንሳዔ  አስተባባሪ ኮሚቴ

በቤተክርስቲያናችን በአራቱም ንዑስ እረኝነት ያላችሁ ባለትዳሮች በሙሉ የፊታችን ቅዳሜ፤ሚያዝያ 5 ቀን 2016 መፅሐፍ ቅዱሳዊ የትዳር ህይወት በሚል ርዕስ ልዩና በጣም ጠቃሚ ትምህርት ከ 8:00 ሰዓት
በቤተክርስቲያናችን በአራቱም ንዑስ እረኝነት ያላችሁ ባለትዳሮች በሙሉ የፊታችን ቅዳሜ፤ሚያዝያ 5 ቀን 2016 መፅሐፍ ቅዱሳዊ የትዳር ህይወት በሚል ርዕስ ልዩና በጣም ጠቃሚ ትምህርት ከ 8:00 ሰዓት ጀምሮ ስለተዘጋጀ በትዳር ለረጅም ጊዜ የቆያችሁ ሆነም አዳዲስ ባለትዳሮች ሁላችሁም በሰዓቱ ተገኝታችሁ የበረከቱ ተካፋዮች እንድትሆኑ በጌታ ፍቅር እናሳስባለን ::

የእሁድ መደበኛ ኘሮግራም መጋቢት 29, 2016 ክፍል 2 Title: ከሰዎች ጋ በጤናማ ህብረት እንደግ መጋቢ አለሙ ከበደ “ነገር ግን በጌታችንና በመድኃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋና እውቀት እደጉ። ለእርሱ አሁንም እስከ ዘላለምም ቀን ድረስ ክብር ይሁን፤ አሜን።” — 2ኛ ጴጥሮስ 3፥18 ከሰዎች ጋ ያለን ግኑኝነት ጤናማ ካልሆነ ከእግዚአብሔር ጋ ያለንም ህብረት ጤናማነትቱ ጥያቄ ውስጥ ነው? 1.ከአማኞች ጋ ያለን ህብረት ሐዋርያት 2 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ⁴⁴ ያመኑትም ሁሉ አብረው ነበሩ፤ ⁴⁵ ያላቸውንም ሁሉ አንድነት አደረጉ። መሬታቸውንና ጥሪታቸውንም እየሸጡ፥ ማንኛውም እንደሚፈልግ ለሁሉ ያካፍሉት ነበር። ⁴⁶ በየቀኑም በአንድ ልብ ሆነው በመቅደስ እየተጉ በቤታቸውም እንጀራ እየቈረሱ፥ በደስታና በጥሩ ልብ ምግባቸውን ይመገቡ ነበር፤ ⁴⁷ እግዚአብሔርንም እያመሰገኑ በሕዝብ ሁሉ ፊት ሞገስ ነበራቸው። ጌታም የሚድኑትን ዕለት ዕለት በእነርሱ ላይ ይጨምር ነበር። 1.1 እርስ በእርስ መዋደድ ፍቅር ማለት :- 1ኛ ዮሐንስ 4 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹⁰ ፍቅርም እንደዚህ ነው፤ እግዚአብሔር እርሱ ራሱ እንደ ወደደን ስለ ኃጢአታችንም ማስተስሪያ ይሆን ዘንድ ልጁን እንደ ላከ እንጂ እኛ እግዚአብሔርን እንደ ወደድነው አይደለም። ¹¹ ወዳጆች ሆይ፥ እግዚአብሔር እንዲህ አድርጎ ከወደደን እኛ ደግሞ እርስ በርሳችን ልንዋደድ ይገባናል። ይህ ፍቅር ስሜት ብቻ አይደለም በተግባር የሚገለጽ ነው። እግዚአብሔር እርሱ ራሱ እንደ ወደደን(አመፀኞች ሳለን) ፍቅር ስንሰጥ ምላሽ በመጠበቅ መሆን የለበትም (“እኔ ግን እላችኋለሁ፥ በሰማያት ላለ አባታችሁ ልጆች ትሆኑ ዘንድ ጠላቶቻችሁን ውደዱ፥ የሚረግሙአችሁንም መርቁ፥ ለሚጠሉአችሁም መልካም አድርጉ፥ ስለሚያሳድዱአችሁም ጸልዩ፤ እርሱ በክፎዎችና በበጎዎች ላይ ፀሐይን ያወጣልና፥ በጻድቃንና በኃጢአተኞችም ላይ ዝናቡን ያዘንባልና።” — ማቴዎስ 5፥44-45) ዩሐንስ ወንጌል 13:34 , 15 :12 “ልጆቼ ሆይ፥ በሥራና በእውነት እንጂ በቃልና በአንደበት አንዋደድ።” — 1ኛ ዮሐንስ 3፥18 ፍቅር የሌለው ክርስቲያን 1ኛ ዮሐንስ 2:9-10 (በጨለማ ይኖራል) 1ኛ ዮሐንስ 4:7-8 (እግዚአብሔርን አያውቅም) 1ኛ ዮሐንስ 3:11-15 (ነፍሰ ገዳይ ነው) እንዴት የእግዚአብሔርን ፍቅር በህይወታችን እንተግብር 1.ካለን ማካፈል 1ኛ ዮሐንስ 3:16-20(“እርሱ ስለ እኛ ነፍሱን አሳልፎ ሰጥቶአልና በዚህ ፍቅርን አውቀናል፤ እኛም ስለ ወንድሞቻችን ነፍሳችንን አሳልፈን እንድንሰጥ ይገባናል።” — 1ኛ ዮሐንስ 3፥16) ያዕቆብ 2 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹⁵ ወንድም ወይም እኅት ራቁታቸውን ቢሆኑ የዕለት ምግብንም ቢያጡ፥ ¹⁶ ከእናንተ አንዱም፦ በደኅና ሂዱ፥ እሳት ሙቁ፥ ጥገቡም ቢላቸው ለሰውነት ግን የሚያስፈልጉትን ባትሰጡአቸው ምን ይጠቅማቸዋል? 2. ክፋ ባለማድረግ ሮሜ 13:8-10 (ሮሜ 13 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ⁸ እርስ በርሳችሁ ከመዋደድ በቀር ለማንም ዕዳ አይኑርባችሁ፥ ሌላውን የሚወድ ሕግን ፈጽሞታልና። … ¹⁰ ፍቅር ለባልንጀራው ክፉ አያደርግም፤ ስለዚህ ፍቅር የሕግ ፍጻሜ ነው።) 3. እርስበርስ መከባበር “በወንድማማች መዋደድ እርስ በርሳችሁ ተዋደዱ፤ እርስ በርሳችሁ ተከባበሩ፤” — ሮሜ 12፥10 “ወዳጁን የሚንቅ እርሱ አእምሮ የጐደለው ነው፤ አስተዋይ ግን ዝም ይላል።” — ምሳሌ 11፥12 4. እርስበርስ ይቅር መባባል “እኛም ደግሞ የበደሉንን ይቅር እንደምንል በደላችንን ይቅር በለን፤” — ማቴዎስ 6፥12 ይቅርታ የእግዚአብሔር ተሸጋጋሪ ባህሪ ነው። ማቴዎስ 18 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ²¹ በዚያን ጊዜ ጴጥሮስ ወደ እርሱ ቀርቦ፦ ጌታ ሆይ፥ ወንድሜ ቢበድለኝ ስንት ጊዜ ልተውለት? እስከ ሰባት ጊዜን? አለው። ²² ኢየሱስ እንዲህ አለው፦ እስከ ሰባ ጊዜ ሰባት እንጂ እስከ ሰባት ጊዜ አልልህም። ሮሜ 12 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹⁹ ተወዳጆች ሆይ፥ ራሳችሁ አትበቀሉ፥ ለቍጣው ፈንታ ስጡ እንጂ፤ በቀል የእኔ ነው፥ እኔ ብድራቱን እመልሳለሁ ይላል ጌታ ተብሎ ተጽፎአልና። ²⁰ ጠላትህ ግን ቢራብ አብላው፤ ቢጠማ አጠጣው፤ ይህን በማድረግህ በራሱ ላይ የእሳት ፍም ትከምራለህና። ²¹ ክፉውን በመልካም አሸንፍ እንጂ በክፉ አትሸነፍ። 5. እርስበርስ ተናነፁ 1ኛ ቆሮንቶስ 10 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ²³ ሁሉ ተፈቅዶልኛል፥ ሁሉ ግን የሚጠቅም አይደለም፤ ሁሉ ተፈቅዶልኛል፥ ነገር ግን ሁሉ የሚያንጽ አይደለም። ²⁴ እያንዳንዱ የባልንጀራውን ጥቅም እንጂ አንድ ስንኳ የራሱን ጥቅም አይፈልግ። 6. የደከሙትን እናቅናቸው ገላትያ 6 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹ ወንድሞች ሆይ፥ ሰው በማናቸውም በደል ስንኳ ቢገኝ፥ መንፈሳውያን የሆናችሁ እናንተ እንደዚህ ያለውን ሰው በየውሃት መንፈስ አቅኑት፤ አንተ ደግሞ እንዳትፈተን ራስህን ጠብቅ። … ⁶ ነገር ግን ቃሉን የሚማር ከሚያስተምረው ጋር መልካምን ነገር ሁሉ ይከፋፈል። 2. ውጪ ካሉ ወገኖች ጋ ያለን ህብረት ውጪ ካሉት ጋ በሰላም እንኑር።

የመጋቢት 29፤2016ዓ.ም፣ የእሁድ መደበኛ አምልኮ ፣ የቃል ጊዜ_በመጋቢ አለሙ

የተወደዳችሁ  የቤተክርስቲያናችን  እናቶች  እና  አባቶች ከዚህ  በፊት  በነበረን  የትንሳኤ አዳር  ላይ በዝማሬ  ያገለገላችሁ  እንዲሁም  በተለያየ  ምክንያት  ያልተገኛችሁ  በአራቱም  እረኝነት  ስር  ያላችሁ  ለመዘመር  ፍቃደኛ  የሆናችሁ  እናቶች እና አባቶች  በሙሉ ጌታ  በሰጠን  ጊዜና  እድል  ለጌታ  እንድንዘምር የ2016  አዳር  ኘሮግራም  ላይ  ጌታን በዝማሬ እንድናገለግል  የጥናት ዝግጅት  እሁድ ሚያዝያ 6፤2016 ፣ ከሰዓት  10  ሠዓት ጥናት  ሰለምንጀምር  ሁላችሁም  እንድትገኙ  ስንል  አደራ  እንላለን። ጌታ ኢየሱስ አብዝቶ ይባርካችሁ!!!                        የትንሳዔ  አስተባባሪ ኮሚቴ

የተወደዳችሁ  የቤተክርስቲያናችን  እናቶች  እና  አባቶች ከዚህ  በፊት  በነበረን  የፋሲካ  አዳር  ላይ በዝማሬ  ያገለገላችሁ  እንዲሁም  በተለያየ  ምክኒያት  ያልተገኛችሁ  በአራቱም  እረኝነት  ስር  ያላችሁ  ለመዘመር  ፍቃደኛ  የሆናችሁ  እናት እና አባቶች ሰዎች  በሙሉ ጌታ  በሰጠን  ጊዜና  እድል  ለጌታ  እንድንዘምር የ2016  አዳር  ኘሮግራም  ላይ  ጌታን በዝማሬ እንድናገለግል  የጥናት ዝግጅት    አሁድ ሚያዝያ 6፤2016 ፣ከሰአት  10  ሠዓት  ሰለምንጀምር  ሁላችሁም  እንድትገኙ  ስንል  አደራ  እንላለን። ጌታ ኢየሱስ አብዝቶ ይባርካችሁ!!!                        የፋሲካ  አስተባባሪ ኮሚቴ

የእሁድ መደበኛ ኘሮግራም መጋቢት 22, 2016 Title: ከእግዚአብሔር ጋ የጤናማ እድገትን መያዝ መጋቢ አለሙ ከበደ 1ኛ ዮሐንስ 1 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ³ እናንተ ደግሞ ከእኛ ጋር ኅብረት እንዲኖራችሁ ያየነውንና የሰማነውን ለእናንተ ደግሞ እናወራላችኋለን። ኅብረታችንም ከአባት ጋር ከልጁም ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር ነው። ⁴ ደስታችሁም እንዲፈጸም ይህን እንጽፍላችኋለን። ክርስትና ስም ብቻ አይደለም። ክርስትና በሁለት ህብረት ውስጥ የተሳሰረ ነው። እሱም ከእግዚአብሔር ጋ እና ከሰዎች። ከአግዚአብሔር ጋ በህብረት መኖር የቤተሰብ አባልነትን ያሳያል። በብሉይ ኪዳን ህብር በሚል ቃል በጋራ በአንድላይ መኖር (ዘፀ 26:6) በአዲስ ኪዳን ኮኖንያ(በሚል የግሪክ ቃል) ህብረትን ፣ አንድነትን 1ኛ ቆሮ 10:16 ዮሐንስ 3:16 “እርሱ ስለ እኛ ነፍሱን አሳልፎ ሰጥቶአልና በዚህ ፍቅርን አውቀናል፤ እኛም ስለ ወንድሞቻችን ነፍሳችንን አሳልፈን እንድንሰጥ ይገባናል።” — 1ኛ ዮሐንስ 3፥16 ከእግዚአብሔር ጋ የሰውልጅ ያለው ህብረት ዘፍ 3:15 በፍጥረት መጀመሪያ ሰው ከእግዚአብሔር ጋ የጠበቀ ነበር በሀጥያት እስከተበላሸበት ቀን ድረስ። ነገር ግን የእግዚአብሔር ፍቅር የህብረት መታደሺያ ተስፋን ሰጠ። ማት 22:34-40 ("ማቴዎስ 22 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ³⁷ ኢየሱስም እንዲህ አለው፦ ጌታ አምላክህን በፍጹም ልብህ በፍጹም ነፍስህም በፍጹም አሳብህም ውደድ። … ³⁹ ሁለተኛይቱም ይህችን ትመስላለች፥ እርስዋም፦ ባልንጀራህን እንደ ነፍስህ ውደድ የምትለው ናት። ⁴⁰ በእነዚህ በሁለቱ ትእዛዛት ሕጉም ሁሉ ነቢያትም ተሰቅለዋል።") ሉቃ 10:25-30 የህብረት መሠረታዊ ማሳያዎች 1. እግዚአብሔርን ማወቅና ባህሪውን መረዳት “ትእዛዜ በእርሱ ዘንድ ያለችው የሚጠብቃትም የሚወደኝ እርሱ ነው፤ የሚወደኝንም አባቴ ይወደዋል እኔም እወደዋለሁ ራሴንም እገልጥለታለሁ።” — ዮሐንስ 14፥21 “እግዚአብሔር መንፈስ ነው፥ የሚሰግዱለትም በመንፈስና በእውነት ሊሰግዱለት ያስፈልጋቸዋል።” — ዮሐንስ 4፥24 “ከእርሱም የሰማናት ለእናንተም የምናወራላችሁ መልእክት፦ እግዚአብሔር ብርሃን ነው ጨለማም በእርሱ ዘንድ ከቶ የለም የምትል ይህች ናት።” — 1ኛ ዮሐንስ 1፥5 1ኛ ዮሐንስ 2 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹⁵-¹⁶ ዓለምን ወይም በዓለም ያሉትን አትውደዱ፤ በዓለም ያለው ሁሉ እርሱም የሥጋ ምኞትና የዓይን አምሮት ስለ ገንዘብም መመካት ከዓለም ስለ ሆነ እንጂ ከአባት ስላልሆነ፥ ማንም ዓለምን ቢወድ የአባት ፍቅር በእርሱ ውስጥ የለም። ¹⁷ ዓለሙም ምኞቱም ያልፋሉ፤ የእግዚአብሔርን ፈቃድ የሚያደርግ ግን ለዘላለም ይኖራል። ት. ኢሳ 6:1-4 ("እግዚአብሔር ቅዱስ ነው") ኤፌሶን 3: 14-19 “ዳሩ ግን፦ እኔ ቅዱስ ነኝና ቅዱሳን ሁኑ ተብሎ ስለ ተጻፈ የጠራችሁ ቅዱስ እንደ ሆነ እናንተ ደግሞ በኑሮአችሁ ሁሉ ቅዱሳን ሁኑ።” — 1ኛ ጴጥሮስ 1፥15-16 1.1 የእግዚአብሔርን ፈቃድ ማወቅ በተገለጠው በእግዚአብሔር ፈቃድ መኖር አለብን:: 1ኛ ዩሐንስ 2:12-28(አለምንንና በአለም ያለውን አለመውደድ) የሚፈልገውንና የማይፈልገውን ደስ የሚለውንና ደስ የማይለውን የሚወደውንንና የማይወደውን “መፋታትን እጠላለሁ፥ ይላል የእስራኤል አምላክ እግዚአብሔር፥ ልብሱንም በግፍ ሥራ የሚከድነውን ሰው እጠላለሁ፥ ይላል የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር፤ ስለዚህ እንዳታታልሉ መንፈሳችሁን ጠብቁ።” — ሚልክያስ 2፥16 ከእግዚአብሔር ጋ ያለንን የህብረታችንን ጤናማነት በአንደበት ብቻ መሆን የለበትም የምንገልፀው። ከሀጥያት መራቅና በደሙ መታጠብ አለብን ፤ ምህረት ማረግና መቀበል መቻል አለብን ፤ ጌታን መውደድ በተግባር ብቻ ነው የሚገለፀው። 1ኛ ዮሐንስ 2 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹ ልጆቼ ሆይ፥ ኃጢአትን እንዳታደርጉ ይህን እጽፍላችኋለሁ። ማንም ኃጢአትን ቢያደርግ ከአብ ዘንድ ጠበቃ አለን እርሱም ጻድቅ የሆነ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። ² እርሱም የኃጢአታችን ማስተስሪያ ነው፥ ለኃጢአታችንም ብቻ አይደለም፥ ነገር ግን ለዓለሙ ሁሉ ኃጢአት እንጂ። 1.2 መታዘዝ 1ኛ ዮሐንስ 2 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ³ ትእዛዛቱንም ብንጠብቅ በዚህ እንዳወቅነው እናውቃለን። ⁴ አውቄዋለሁ የሚል ትእዛዛቱንም የማይጠብቅ ውሸተኛ ነው እውነትም በእርሱ ውስጥ የለም። ⁵ ቃሉን ግን የሚጠብቅ ሁሉ በእርሱ የእግዚአብሔር ፍቅር በእውነት ተፈጽሞአል። በእርሱ እንዳለን በዚህ እናውቃለን፤ ⁶ በእርሱ እኖራለሁ የሚል እርሱ እንደ ተመላለሰ ራሱ ደግሞ ሊመላለስ ይገባዋል። 1.3 ማገልገል ነው የሰውልጅ የተፈጠረው የፈጠረውን ያገለግልና ያመልከው ዘንድ ነው። “እግዚአብሔርም ሙሴን ተናገረው፦ ወደ ፈርዖን ግባ እንዲህም በለው፦ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ ያገለግለኝ ዘንድ ሕዝቤን ልቀቅ።” — ዘጸአት 8፥1 “የሚያገለግለኝ ቢኖር ይከተለኝ፥ እኔም ባለሁበት አገልጋዬ ደግሞ በዚያ ይሆናል፤ የሚያገለግለኝም ቢኖር አብ ያከብረዋል።” — ዮሐንስ 12፥26 “ለእያንዳንዱ እንደ ዓቅሙ፥ ለአንዱ አምስት መክሊት ለአንዱ ሁለት ለአንዱም አንድ ሰጠና ወደ ሌላ አገር ወዲያው ሄደ።” — ማቴዎስ 25፥15 1ኛ ጴጥሮስ 2 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹ እንግዲህ ክፋትን ሁሉ ተንኰልንም ሁሉ ግብዝነትንም ቅንዓትንም ሐሜትንም ሁሉ አስወግዳችሁ፥ ²-³ ጌታ ቸር መሆኑን ቀምሳችሁ እንደ ሆነ፥ ለመዳን በእርሱ እንድታድጉ አሁን እንደ ተወለዱ ሕፃናት ተንኰል የሌለበትን የቃልን ወተት ተመኙ። ዮሐንስ 15 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹ እውነተኛ የወይን ግንድ እኔ ነኝ፤ ገበሬውም አባቴ ነው። … ⁴ በእኔ ኑሩ እኔም በእናንተ። ቅርንጫፍ በወይኑ ግንድ ባይኖር ከራሱ ፍሬ ሊያፈራ እንዳይቻለው፥ እንዲሁ እናንተ ደግሞ በእኔ ባትኖሩ አትችሉም። … ⁸ ብዙ ፍሬ ብታፈሩና ደቀ መዛሙርቴ ብትሆኑ በዚህ አባቴ ይከበራል። “ነገር ግን እውነትን በፍቅር እየያዝን በነገር ሁሉ ወደ እርሱ ራስ ወደሚሆን ወደ ክርስቶስ እንደግ፤” — ኤፌሶን 4፥15 ሳናቋርጥ በየእለቱ ከጌታ ጋ ህብረት የምናደርግበት መንገድ በፀሎትና በቃሉ ነው። ሁለቱም የአንድ ሳንቲም ሁለት ገፅታዎች ናቸው። የፈረሰውን የፀሎትና የቃሉን መሰዊያ እናድስ። መሳፍንት 6 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ²⁵ እግዚአብሔርም በዚያ ሌሊት፦ የአባትህን በሬ፥ ሰባት ዓመት የሆነውን ሁለተኛውን በሬ፥ ውሰድ፥ የአባትህ የሆነውንም የበኣል መሠዊያ አፍርስ፥ በእርሱም ዙሪያ ያለውን የማምለኪያ ዐፀድ ቍረጥ፤ ²⁶ በዚያም ኮረብታ አናት ላይ ለአምላክህ ለእግዚአብሔር መሠዊያ አሳምረህ ሥራ፤ ሁለተኛውንም በሬ ውሰድ፥ በዚያም በቈረጥኸው በማምለኪያ ዐፀዱ እንጨት ላይ የሚቃጠለውን መሥዋዕት አቅርብ አለው። ²⁷ ጌዴዎንም ከባሪያዎቹ አሥር ሰዎችን ወስዶ እግዚአብሔር እንዳለው አደረገ የአባቱን ቤተ ሰቦች የከተማውንም ሰዎች ስለ ፈራ ይህን በቀን ለማድረግ አልቻለም፥ ነገር ግን በሌሊት አደረገው።

የመጋቢት 22፤2016ዓ.ም፣ የእሁድ መደበኛ አምልኮ ፣ የቃል ጊዜ_በመጋቢ አለሙ

የመጋቢት 22፤2016ዓ.ም፣ የእሁድ መደበኛ አምልኮ ፣ የቃል ጊዜ_በመጋቢ አለሙ

የመጋቢት 22፤2016ዓ.ም፣ የእሁድ መደበኛ አምልኮ ፣ ልጆችን ለጌታ አሳልፎ የመስጠት ስነ- ስርዓት

የመጋቢት 22፤2016ዓ.ም፣ የእሁድ መደበኛ አምልኮ ፣ የዝማሬ ጊዜ_በሻሎም መዘምራን -3