፭ ኪሎ ግቢ ጉባኤ
በኢ/ኦ/ተ/ቤ/የሰ/ት/ቤ/ማ/መ/ማኅበረ ቅዱሳን አ.አ ማዕከል መርሐ ግብራት ፥ #የቅዱሳን_ታሪክ #መጽሐፍ_ትረካ #መጽሐፍ_ጥቆማ #ብሒላተ_አበው https://t.me/amstkilogbigubae በዩትዩብ ቤተሰብ እንሁን ☟☟☟https://www.youtube.com/@5kilogbigubae
Show more1 949
Subscribers
+124 hours
+357 days
+8730 days
- Subscribers
- Post coverage
- ER - engagement ratio
Data loading in progress...
Subscriber growth rate
Data loading in progress...
Photo unavailableShow in Telegram
ኑ ለእግዚአብሔር እናበድረው !!
"ለድሀ ቸርነትን የሚያደርግ ለእግዚአብሔር ያበድራል፥ በጎነቱንም መልሶ ይከፍለዋል።" እንዲል ምሳሌ 19 ÷ 17ኑ ብል እና ዝገት በሌለበት ሀብትን እናከማች !! ኑ በበረከት ለማጨድ በበረከት እንዝራ !! ኑ ምስጋና እና ክብር ሊቸረው የሚገባን የአራጣ ብድር እንስጥ !!
የፊታችን እሁድ ከላይ ያሉት ሁሉ ለማድረግ በግቢ ጉባዔያችን ተዘጋጅተናል ። ከቤት ንብረታቸው ተፈናቅለው እና በተለያየ ምክኛት ጎዳና የወጡ ወገኖቻችን ለመደገፍ በ፭ ኪሎ ግቢ ጉባዔ በሞያ እና በጎ አድራጎት ክፍል የተዘጋጀ መርሀግብር ።ኑ ቸርነት እናድርግ !!
❤ 13
Photo unavailableShow in Telegram
#ጉባዔ_ቂሳርያ
“ኑ፥ በእግዚአብሔር ደስ ይበለን፤ ..... ።”
መዝሙር 95፥1
ኅሙስ ግንቦታ 15 , ማህበረ ቅዱሳን 3ተኛ ፎቅ እንገናኝ
ሰዓት ---> 11:20
❤ 8👍 2
Photo unavailableShow in Telegram
🌹🌹🌹እንኳን ለቅዱስ ያሬድ ዓመታዊ ክብረ በዓል በሰላም አደረሳችሁ🌹🌹🌹
ኢትዮጵያ ከመላእክት ጋር የሚዘምር ማሕሌታዊ ከካህናተ ሰማይ ጋር የሚያጥን ካህን የምታፈራ ሀገር ናት። ለሰማይ አገልጋዮችን ገና ሳይሞቱ የምትልክ፣ ከተዋጊዎች መካከል ወደ ድል ነሺዎች መልእክተኛ የምትልክ ቤተ ክርስቲያን እንዴት ያለች ናት?
ቅዱስ ያሬድ በትሕትናው ከትል ተማረ። ትሑታንን ከፍ የሚያደርግ ፈጣሪም ከፍ አደረገውና ከመላእክት ጋር ዘመረ። ትልዋን ከዛፍ አውርዶ ቢጨፈልቃት ኖሮ ለአንድ ሺህ አምስት መቶ ዓመታት ያልነጠፈው የምስጋና ጅረት በሀገራችን ባልፈሰሰ ነበር። ኃይል አለኝ ብለህ የምትጨፈልቃቸው ትሎች ሰማይ የሚያደርሱህ መምህራኖችህ እንዳይሆኑ ተጠንቀቅ ይላል የታሪኩ ተግሣፅ።
ቅዱስ ያሬድ እግሩን በጦር እየተወጋ እንኩዋን ዝማሬው ሰማያት ወስዶት አልተሰማውም ነበር። የእኛው ሲላስ የእኛው ጳውሎስ ቅዱስ ያሬድ ሆይ በዘመርክባት ሀገርህ ዛሬ ብዙ ጦር ተሰክቶባታል። ከአንተ ዜማ በቀር ዛሬም መጽናኛ የለንምና በምልጃህ አስበን።
ጥዑመ ልሳን ያሬድ: ሊቀ ጠበብት ያሬድ: ሊቀ ሊቃውንት ያሬድ የቤተ ክርስቲያን ጌጥ!!
ምንጭ : ዲ/ን ሄኖክ ኃይሌ
❤ 10👍 8🤗 1