en
Feedback
Tamene Mengste Wube

Tamene Mengste Wube

Open in Telegram

አገር አገር ስልሽ—ደስ ይበልሽ በጣም ኢትዮጵያዊ ሆነን—የሚያግባባ አናጣም! ዕወቂው ዐለሜ...! ኢትዮጵያዊ መሆን—የውርስ እንቁጣጣ በአጥንት ክስካሽ—በደም ቅብ የመጣ... |ታመነ መንግሥቴ ውቤ—አባ ወራው| ግቡ፦ስለ አገር፣ፍቅር፣ሰላም፣ባሕል እና ጥበብ እናወጋለን! ጀበናዋ ተጥዳለች! ፍንጃሎቹ ሳይሞሉ፣የገባችሁ ሳትቋደሱ ረከቦት አይነሳም! ክሕሎት፣ጥበብ፣ መሻታችሁ በቤቱ ይስተናገዳሉ። ትውልድ❤

Show more
919
Subscribers
+124 hours
-47 days
+1930 days
Posts Archive
#በዕውቀቱ_ሥዩም ወደ ምንም የሚያደርስው መንገድ ቸኳይ የሚመስለው ፈጣን የሚመስለው በውልውል መኪና በፋሺን መጫምያ ወይም በባዶ እግሩ ሸው እልም የሚለው ይሄ ሁሉ ምሁር ይሄ ሁሉ ማይም መንገዱን የሞ
#በዕውቀቱ_ሥዩም ወደ ምንም የሚያደርስው መንገድ ቸኳይ የሚመስለው ፈጣን የሚመስለው በውልውል መኪና በፋሺን መጫምያ ወይም በባዶ እግሩ ሸው እልም የሚለው ይሄ ሁሉ ምሁር ይሄ ሁሉ ማይም መንገዱን የሞላው ከታችም ከላይም ሲመላለስ እንጂ ሲደርስ አይታይም፡፡

ካሳ በዚህ ያለፈ ይመሥለኛል።ሰበዝ ሜዳ ላይ ከተድላ ጓሉ ጋር ለመፈሳፈስ ብቅ ብሎ ነበር የሚል ነገር ሳላነብ አልቀረሁም። ራሥ ዐሊ'ስ ወደ አይሻል ሲዘምቱ በየት ያልፋሉ?—አራጢን ሳይነኩ የሚያልፉ አ
ካሳ በዚህ ያለፈ ይመሥለኛል።ሰበዝ ሜዳ ላይ ከተድላ ጓሉ ጋር ለመፈሳፈስ ብቅ ብሎ ነበር የሚል ነገር ሳላነብ አልቀረሁም። ራሥ ዐሊ'ስ ወደ አይሻል ሲዘምቱ በየት ያልፋሉ?—አራጢን ሳይነኩ የሚያልፉ አይመሥለኝም። ፊታውራሪ ውድነህ ዘ ብሔረ ቢቡኝ «ውዴ በሰራው ገዳይ» ብለው የገዛ መድፋቸውን የተኮሱባት አይሻል የምትባል የጦር ሜዳ ጎጃም ውስጥ ቁይ አካባቢ መሆኗን አአአ ነግሮኛል። አራጢ ወደ ቁይም፣ወደ መሐል እነሴም ለመግባት—በተለይ ተ በጌምድር ለሚመጣ ኃይል ጠቃሚ ቦታ ናት። በዚህ ሰሞን የብሩ ጎሹ ዘውዴን ያህል በፍቅሩ ያነሆለለኝ የኢትዮጵያ ጀግና የለም።ሁላ የአቤ'ን መጣፍ እያነበብኩት ብሩ'ዬ ሥለመሰጠኝ፦ ፈረሱ ዳምጠው ሰውዬው ብሩ ግዛቱ ጎጃም ኢትዮጵያ አገሩ ሚስቱ የውብዳር ዘሯ ወሎዬ የጀግና ጀግና በአገር ያልታዬ አባቱ ጎሹ የዘውዴ ግልገል አጅሬ ብሩ ቱርክን ሊገዛ የሚገለገል ለአንዲት ኢት ሰርክ የሚታገል እሱ ባለበት አብሬው ብኖር አባቴ ይሙት ደስ ይለኝ ነበር! የሚሉ ሥንኞች ጭሬ አለሁ። በሱ ዘመን መኖር፣ብሩን ማግኘት ባይቻለኝ'ንኳን ይሄው ብሩ በገዛው፣ባለፈ—ባገደመበት ቀዬ ዋልኩ። ብሩ ጎሹ መነሐሪያው ሞጣን ይዞ ምሥራቁ የጎጃም ክፍል ነበር።አባቱ ጎሹ ዘውዴ ደምበጫ ላይ ሆነው በአብዛኛው ምዕራቡን የጎጃም ክፍል እየገዙ 'ላሊበላ' እሚያሰኝ የአስተዳደር ጊዜ አሳልፈዋል። ብሩዬ ቅብጥብጥ ነበር። በዚህ በሞጣ ዙሪያ ግን ሴት ልጅ በማድጋ ሙሉ ወርቅ ተሸክማ ብትጓዝ ቀና ብሎ የሚያያት አልበረም። እንዲህ ነው—ሰላም ማስከበር ማለት👏 ኤኒወይስ ተ ድጎ እስተ ሞጣ ዛሬ ስጓዝ ሰላም ነበር። ይልመድባችሁ፤ተ ብሩ ጎሹም ተማሩ🥰

«...ያገሬ ልጅ አንተ ጉብል ሎጋ ወርደህ ከማማው ላይ ቁጭ ብለን እናውጋ!» በወሎ ምድር፣በኒያ በሸጋጎቹ አገር፣ደሞ ማማ ላይ ሆኜ፣ከማማው ሥር ዚነትን የመሰለች ቆንጆ ጓደኛ ኑራኝ አሰብኩት🥰 ዐለም
«...ያገሬ ልጅ አንተ ጉብል ሎጋ ወርደህ ከማማው ላይ ቁጭ ብለን እናውጋ!» በወሎ ምድር፣በኒያ በሸጋጎቹ አገር፣ደሞ ማማ ላይ ሆኜ፣ከማማው ሥር ዚነትን የመሰለች ቆንጆ ጓደኛ ኑራኝ አሰብኩት🥰 ዐለም ማለት ይሄ ነበር። ዚነት ይሄን ዘፈን እየዘፈነች፣ልዥ ሆኜ፣ፍሊፕስ ራዲዮ ታቅፌ ትዝ ይለኛል። ዚነት ማናት?—ብል ገና ጩጬ እያለህ አርፋለች—አለኝ የአማራ ራዲዮ። መልኳን ዕዩት'ማ፣ሥሟን ዕዩት'ማ፣እኔስ ሙሃባ እሚባለው ሥም'ም ይጣፍጠኛል። አፈር ልሁንልሽ😥 ለምን ይሆን ግን እንደ ዚነት፣እንደ ማንአልሞሽ ዲቦ፣እንደ ተስፋዬ ወርቅነህ፣እንደ አክሊሉ ሥዩም፣እንደ ጋሻው አዳል፣እንደ መሥፍን አበበ ያሉ የልቡናችንን ውቅር የሚቀያይሩ ዘፋኞቻችን በሕይወት የሌሉ? የሆነውስ ሆነ'ና ባምላክ ጌትነት ከብዙ መውጣት መውረድ በኋላ ዚነቷን ይዛልን ተከስታለች። የባምሊ ድምጽ ጥሞኛል—ነገር። እስቲ በደንብ አጣጥሜው እመለሳለሁ🥰

አራተኛው ዐፄ ዮሐንስ በጎጃም ሕዝብ ላይ ጭፍCheፋ የፈጸሙ ግዜ የሞጣ ዘመዶች ዐፄውን ትተው ከአምላካቸው እና ከሰማዕታቱ ጋር መሟገት ይዘው ነበር። እንደ ሞጣ... አንዷ ትግሬዎች ዘርፈዋት ባዶ እጇ
አራተኛው ዐፄ ዮሐንስ በጎጃም ሕዝብ ላይ ጭፍCheፋ የፈጸሙ ግዜ የሞጣ ዘመዶች ዐፄውን ትተው ከአምላካቸው እና ከሰማዕታቱ ጋር መሟገት ይዘው ነበር። እንደ ሞጣ... አንዷ ትግሬዎች ዘርፈዋት ባዶ እጇን የቀረች እና አምላኳ መፍትሔ እንዲሰጣት ጠይቃ መልስ ያጣች ጎጃሚት፦ «ከሀበሻ ወዲህ ከሀበሻ ወዲያ ሰውንም ገረመው እኔንም ገረመኝ ዮሐንስ እግዜርን ገድሎታል መሰለኝ!» አለች—አሉ😥 ሞጣ ከዚህ ሌላ ምን ይላል? እነሴ ውስጥ ደሞ አሉ—የዐፄ ዮሐንስ ወታደሮች ቤተ ክርስቲያን ሊዘርፉ ሲሯሯጡ ጎጃሜዎቹ የመርቆርዮስን ሥዕል ለማዳን ሮጡ። በክርስቲያንነታቸው አንገታቸውን ሰጡልን እየተባሉ የሚወደሱት በዝብዝ ካሣ ግን በፈረስ ገስግሰው ባለአገሩን በመቅደም አበረ አረፈዓዬኔ አዳሙ እንንደሚለው «ቤተ ክርስቲያን ደፍረው ገብተው ሥዕሉን በካራ ልጠው...በፈረሳቸው ላይ ተቀምጠውበት ወሰዱት።» የወንድማችን ሞጣ ዘመድ የምትሆን የዚያ ቤተ ክርስቲያን አቃቢም አለች፦ «እንግዲህ አላምንም ሰማዕታትን በፈረስ ቀደመው መርቆርዮስን!» እንዲህ ናቸው፤የጎጃም እናቶች። ይጠይቃሉ።እንደ በዕውቀቱ ሥዩም «ከአሜን ባሻገር» ያያሉ። «ነጋሢዎቹ» በሚለው የ አአአ መጽሐፍ ላይ ያገኘኋቸውን ሌሎች ሥንኞች አቃምሻችሁ ልሰናበት፦ «ዮሐንስ ነው ብለው፣ ሥንሰማ ባዋጅ ዮሐንስ አይደለም ሳጥናኤል ነው'ንጅ! ዮሐንስ አጠፋው አደረገው ዱር ጎጃምን የሚያህል ያን ለምለም ምድር በትግሬ ተዘርፈን እንጀራ ፍለጋ ወንዙን ሳንሻገር ድሮ በአገራችን ቡቃያው በጓሮ በጎታ እህል ነበር ጎጃም ተቃጠለ ዐባይ እስከ ዐባይ ትግሬ ቅጠል ይዞ ሊያጠፋው ነዎይ?» ታሪክ የድሮ ፖለቲካ ነው።በውቄ እንደሚለው ዘንድሮ ውስጥ ድሮ የሚል ቃል አለ።

ቆንጂዬዋ ሩት ይርጋዐለም ወልደሥላሴ ቀያችንን መጥታ እንድትጎበኝ በአክብሮት እንጋብዛለን። ይህ የጎጃም ቀዬ ጥንት በሙሴ፣ኋላ በፈረሳዊው አርኖ ሚሼል ዳባዲ የተጎበኘ እና የተወደደ ቦታ ነው። ዳባዲ 1
ቆንጂዬዋ ሩት ይርጋዐለም ወልደሥላሴ ቀያችንን መጥታ እንድትጎበኝ በአክብሮት እንጋብዛለን። ይህ የጎጃም ቀዬ ጥንት በሙሴ፣ኋላ በፈረሳዊው አርኖ ሚሼል ዳባዲ የተጎበኘ እና የተወደደ ቦታ ነው። ዳባዲ 10 ዓመት ሙሉ ጎጃም ውስጥ በፍሥሐ መኖሩን ገነት አየለ አንበሴ በተረጎመችለት «በኢትዮጵያ ከፍተኛ ተራሮች ቆይታዬ» የተሰኘ መጽሐፍ ውስጥ አንብበናል። 'እንዲህ ነን እኛ' ሥልሽ ነው😀 ያው ስትመጭ ሸማ እና ነጠላ እናለብስሻለን።እጅግዐየሁ ሺባባውን ታውቂያት የል? «ሸማ ነጠላውን ለብሰው አይሞቃቸው አይበርዳቸው አገሩ ወይና ደጋ ነው» ያለችን እኛን ነው። ሩቴ🥰 ይሄ ሸማ እና ነጠላ ዐድዋ የዘመተ፣ማይጨው የተንከራተተ ነፍጠኛ ይለብሰው የነበረው ነው። ዐድዋ እና ማይጨው ምን እንደነበሩ ደሞ ወዲ ወልደሥላሴን ጠይቂያቸው። ባይዜ የኦሮሞ ባሕላዊ ልብስ በመልበስሽ አንች አላጠፋሽም። ችግሩ ያለው ያልተሠራ አገር ላይ ከሚያኖሩን አባቶቻችን ነው።የኢትዮጵያ—የሚባለው ልብስ ገና አንድ ሆኖ አልተሠራም። እናም ልብ ካለሽ ሙሉ ኢትዮጵያን የሚመሥል ልብስ ፍጠሪ። ይገባኛል—ሥራው ከባድ ነው። ተይኝ በቃ—እዚህ መሥክ ላይ ደቅ ልበልበት😀 ተመጣሽ አፋፍ ላይ ሆነሽ —አያ ታመነ ብለሽ ጥሪኝ🥰

በቅርቡ መኪና እንዲኖረኝ እፈልጋለሁ።የእኔ መኪና ግን ከተማ ለከተማ የሚልከሰከስ ቆርቆሮ እንዲሆን አልሻም። ቢችል መላ አፍሪካን፤ታልሆነለት ሙሉ ኢትዮጵያን መዞር የሚችል «አባ ዳኘው» ይሆን ዘንድ ግ
በቅርቡ መኪና እንዲኖረኝ እፈልጋለሁ።የእኔ መኪና ግን ከተማ ለከተማ የሚልከሰከስ ቆርቆሮ እንዲሆን አልሻም። ቢችል መላ አፍሪካን፤ታልሆነለት ሙሉ ኢትዮጵያን መዞር የሚችል «አባ ዳኘው» ይሆን ዘንድ ግዴታው ነው። ተማሪ ሳለን አአዩ ግቢ ውስጥ የሴት ጓደኞቼን ምራቅ የሚያስውጡ መኪኖች ዕናይ ነበር።እንዷ ጓደኛችን ወዲያው እንደተመረቅን ባለ ራይድ ጠበሰች። ጠባብሶ ተዋት መሰለኝ😀 እኛ ሥንመረቅ ተቀጥሮም ቢሆን ራይድ የሚሠራ ሰው ብርቅ ነበር።አንዳንድ ሴቶቻችን ለመኪና ያላቸው ፍቅር በዚህ ደረጃ አዋራጅ ነው። እኔ የአባ ልጅ ያኔም፣ዛሬም ለመኪና አልሳሳም። ዘናጭ እና አገር አቋራጭ መኪና እንደሚኖረኝ ቀድሞ የታወቀ ነገር ነው። ለምን? የፈረሰኛው የመንግሥቴ ውቤ የልዥ ልዥ ነኛ። አባ ያስተማረኝ'ኮ ቢያንስ እንደሱ፣ቢበዛ ከሱ የተሻልኩ ሰው እንድሆን ነው። እናም እሱ የነጫጭ ፈረሶች ጌታ ሥለነበረ መኪና መሠረታዊ ፍላጎቴ እንደሆነ ይታወቃል። ዋናው ጥያቄ «መቼ እገዛለሁ?» የሚለው ነው። መልሱን ከኬፕ ታውን እስከ ሞሮኮ ጫፍ፣ከኬፕ ቨርዲ እስከ አፍሪካዋ የቀንድ ጫፍ ድረስ ሥነዳ ኮሽ እንደማይልብኝ እርግጠኛ ሥሆን—ብዬ የዘለዓለም ያህል አላርቀውም። ኢትዮጵያ እንደ መለስ ዜና ግዜ ሰላም ሆና ከጫፍ እስከ ጫፍ መኪናዬን ቀን ከሌት ብነዳትም ምንም እንደማልሆን ሳረጋግጥ እገዛለሁ። ከዚያ በፊት አጣዳፊ ሥራ ሥለሌለብኝ ለመኪና ሳንቲም አላወጣም። የምሥል ማብራሪያ፦ መኪናው የሥዩም ተሾመ ነው አሉ።አንድ ጋዜጠኛ ሰሚት 72 ገደማ «ወንድማማቾች» የሚባል ቁርጥ ቤት በር ላይ ቆሞ አገኘሁት ብሎ ያነሳው ነው። አንዳንዴ መንግሥትም V8 ይሰጣል ሥልሽ ነው።በቀላሉ ሰላም አይሰጥም እንጅ😀

አጋራችን ቆምጬ ሚዲያ የሚታዬውን የደጋግ ሰዎች መገኛ ዝርዝር ይፋ አድርጓል። «ደግ ሆነን ተዘለናል» እምትሉ ደጋጎች😀 ወዬ በሉ🤫
አጋራችን ቆምጬ ሚዲያ የሚታዬውን የደጋግ ሰዎች መገኛ ዝርዝር ይፋ አድርጓል። «ደግ ሆነን ተዘለናል» እምትሉ ደጋጎች😀 ወዬ በሉ🤫

'ዕዩዋት ስትናፍቀኝ'🥰 ጎንደር በአንዲት ሥሜታዊት ቃል ትገለጽ ቢባል «ናፍቆት» የምትሰኝ ይመሥለኛል። እዚያው ጎንደር ሆኘ ናፍቃኝ ታውቃለች።በተለዬኋት በወራት ልዩነት ናፍቃኝ ታውቃለች። የደግ እና
'ዕዩዋት ስትናፍቀኝ'🥰 ጎንደር በአንዲት ሥሜታዊት ቃል ትገለጽ ቢባል «ናፍቆት» የምትሰኝ ይመሥለኛል። እዚያው ጎንደር ሆኘ ናፍቃኝ ታውቃለች።በተለዬኋት በወራት ልዩነት ናፍቃኝ ታውቃለች። የደግ እናት ጠባይ ነው—ያላት። የጎንደር አስኳሏም ደጋግ እናቶቿ ናቸው። ባለፈ ጊዜ ከአንድ ጎንደሬ ጋር ሥንጫወት ጎንደር የባሕላዊ ኅብረተሰባዊነት(ሶሻሊዝም) ማዕከል ናት—አለኝ። አሃ...ብዬ ልሞት። ካፒታሊስት ወይም ፊውዳል ከተሞች ለናፍቆት አይጋብዙም።እንደ «ታተይ ሙሽሪት» ያሉት ግን የጨው ውሃ ናቸው። እየጠጣሃቸው ይጠሙሃል። እመጣልሻለሁ—'እናትዋ'🤫

«...የዐለም ታሪክ መነሻ ጎጃም ነው።ይህንን ልካድህ ቢሉት የሚካድ አይደለም።እንደ መቀነት የታጠቀውን ግዮንን ዐይተን መጽሐፍ ቅዱስን አጣቅሰን ተጨባጭ ታሪክ መናገር የምንችልበት አገር ጎጃም ነው፤»
«...የዐለም ታሪክ መነሻ ጎጃም ነው።ይህንን ልካድህ ቢሉት የሚካድ አይደለም።እንደ መቀነት የታጠቀውን ግዮንን ዐይተን መጽሐፍ ቅዱስን አጣቅሰን ተጨባጭ ታሪክ መናገር የምንችልበት አገር ጎጃም ነው፤» ጥንታዊው የጎጃም ታሪክ፣ኹለተኛ መጽሐፍ፣ከአበረአረፈ ዓይኔ አዳሙ፣ገጽ 301 በምሥሉ ላይ የሚታዬው ቀዬ የእኔ የትውልድ ቦታ ነው።ገደብ፣አዳኝ፣ዋብር ሁላ ይታያሉ። እዚህ ያለኝ የዘመድ ብዛት🥰

ይሄ ነው—የእኔ እትብት ያለበት ተራራ። ጮቄ እንለዋለን። አበረ አረፈዓዬኔ አዳሙ «የጎጃም ታሪክ» በተሰኘው መጽሐፉ የኖኅ መርከብ ያረፈችበት አራራት የተባለው ተራራ ይሄ ነው ይላል። ጮቄ የግብጽ እና
ይሄ ነው—የእኔ እትብት ያለበት ተራራ። ጮቄ እንለዋለን። አበረ አረፈዓዬኔ አዳሙ «የጎጃም ታሪክ» በተሰኘው መጽሐፉ የኖኅ መርከብ ያረፈችበት አራራት የተባለው ተራራ ይሄ ነው ይላል። ጮቄ የግብጽ እና ሱዳን ቁርስ፣ምሣ፣እራት ነው። ጎጃሜይቱ፦ «የሚበሉት ውሃ የሚጠጡት ውሃ» ሥትል ሰምታችሁ የል? አዎ። ጮቄ የግብጽ እህል—ውሃ ነው። ጮቄ ለዘመናት ለምን ሥሙ ከሚጎበኙ ቦታዎች ዝርዝር ውስጥ ተፍቆ እንደኖረ በማጥናት ላይ ነኝ። ከአዲስ አበባ፣ከጎንደር፣ከባሕርዳር፣ከካርቱም ወዘተ መሐል ያለ፣ደብረማርቆስ ከምትባለው የጎጃም ከተማ በቅርብ ርቀት የሚገኝ ቀዬ ሆኖ ለምን የጉዞ ወዳጆች መነሐሪያ ሳይሆን ቆዬ? «እንጃ»—እንዳለው ነው—ዘፋኙ። አሁን ጊዜው ይመሥለኛል። ትውልዱ ሩቅ ማማተሩን ትቶ በተወለደበት ቀዬ መኩራት ጀምሯል።በርግጥ የጎጃም ልጅ ለወትሮውም «ድንች እና ወንድ ልጅ ባድማውን አይለቅም» በሚል መርሕ የኖረ ነው። ሆኖም አሁን ውጫዊም፣ውስጣዊም ሁኔታዎች ወጣቱ ጎጃምን እዚያው ተገኝቶ እንዲያለማ እየገፋፉት ነው። እናም ጮቄ መልሚያው፣መጎብኛው ጊዜው አሁን ነው። ሌላዋ ሩቢላ ደብረማርቆስ ላይ ማረፍ መጀመሩ ለጮቄ ጎብኝዎች ታላቅ የምሥራች ይመሥለኛል። ከፈለጉበት ቦታ በሩቢላ ወደ «ተድላው ከተማ» ብቅ ይሉ'ና ረፋዱን ወደ ጮቄ መጓዝ ነው። ጮቄን ለሁለት ሰንጥቆ ወደ ቆላማው የጎጃም ክፍል የሚወርደውን የደብረማርቆስ—ረቡዕገበያ—ዋብር—ድጎጽዮን—ወይን ውሃ—አራጢ አስፋልት መንገድ በቅርቡ እንጨርሰዋለን። ያኔ ሽር ማለት ነው—በገዙት መኪና። በመሐል እኛ አለን። ወተቱን፣ፍትፍቱን፣ማሩን፣ቂቤውን፣ሙዙን፣ብርቱካኑን፣ማንጎውን፣ጤፉን፣ተልባውን ሁሉ እናቀርባለን። ይምጡ፤ይህ ሙሴን በፍቅር ያስተናገደ አገር ነው። ሲጳራም አለች፤እንደ ጠባይዎ እንድርልዎታለን😀

«አገር አገር አትበል አንተ አገረ ብርቁ እኔስ አገር አለኝ የሚታይ በሩቁ» የምትለዋ ዘፋኛችን በጣም ነው—የምታሳዝነኝ።እንዲህ እያለች ራሡ ኢትዮጵያ መጥታ፣ጎጆ ወጥታ፣እግር ውሃ እየወጣች፣ከማይ መቅጃ
«አገር አገር አትበል አንተ አገረ ብርቁ እኔስ አገር አለኝ የሚታይ በሩቁ» የምትለዋ ዘፋኛችን በጣም ነው—የምታሳዝነኝ።እንዲህ እያለች ራሡ ኢትዮጵያ መጥታ፣ጎጆ ወጥታ፣እግር ውሃ እየወጣች፣ከማይ መቅጃ እየጠጣች መኖር አልቻለችም። እጅግዐየሁ ሺባባውም«ሰለቸኝ ከተማ» እንዳለች «የሰው ከብት» ዕያዬች በዚያ በባሕርማዶ ቀረችብን። እኛ ዕድለኞች ነን። በተወለድንባት ቀዬ እንዲህ በመሥከረም ደጋግመን እየተገኘን ነው። ከአገርም አገር—ጎጃምን በሚያህል አገር እንዲህ በጥቢ መገኘት ሰው የመሆን ዋጋ ይፋ የሚደረግበት ነው። ጎጃም መጽሐፍ ቅዱስ ላይ ግዮን እንዲከባት የታዘዘላት፣ከአንድ አባት የሚወለዱ ልጆቿ መሬት ተከፋፍለው በፍቅር የሚኖሩባት፣ከመነሻዋ እስከ 1920ዎቹ ድረስ በመሐል ማንም ባዕድ ሳይገባ በራሷ ተወላጅ ንጉሥ የተመራች፣እነ መለስ ዜና አመጣነው ካሉት የብሔር ፌዴራሊዝም ቀድማ ራሥን በራሥ ማስተዳደር የተባለውን መርሕ ይዛ የኖረች ቅመም ናት። እነሆ እዚህ ሉባ ሆኘ፣የይሁኔ በላይን «መላ አለው» እየሰማሁ፣የአበረ አረፈዓይኔ አዳሙ'ን «የጎጃም ታሪክ» እያነበብኩ በመደመም ላይ ነኝ። ብቅ በሉ፤ጮቄ'ን ጎብኙ።ሰከላን ዕዩ።ዲማ ዝለቁ፣እስላም እና ክርስቲያን ቃል ኪዳን ይዘው ሞጣ ላይ በፍቅር ሲኖሩ ተመልከቱ። 9 ወር ኖሬባት ፍቅሯን ባጣጣምኩት በጣና እመባት በባሕርዳር ተንሸራሸሩ። መተከል ዝለቁ። እኛ ጎጃሞች አለንላችሁ። ሶስት ዓመት የጦርነት እሳት እየነደደበት ዓመት እስከ ዓመት ጥጋብ የሆነ አገር ዕናሳያችሁ። ሰናይ ቀን🥰

ዝዋይ ነው አሉ።ባቱ'ም ይሏታል።ጓዳችን ቴሣይ በዚያ ሰነበተ።ቀራርጦ ላከልንም። ታቦተጽዮን የሆነ ግዜ ተአክሱም ጽዮን ተወስዳ እዚህ ተደብቃ ነበር መሰለኝ። ዝዋይ የሥምጥ ሸለቆ ከተማ ትመሥለኛለች።እም
ዝዋይ ነው አሉ።ባቱ'ም ይሏታል።ጓዳችን ቴሣይ በዚያ ሰነበተ።ቀራርጦ ላከልንም። ታቦተጽዮን የሆነ ግዜ ተአክሱም ጽዮን ተወስዳ እዚህ ተደብቃ ነበር መሰለኝ። ዝዋይ የሥምጥ ሸለቆ ከተማ ትመሥለኛለች።እምትሞቅ ይመሥለኛል። እሚሞቅ ከተማ ነፍሴ ነው።ሲሞቀኝ ጻፍ ጻፍ ይለኛል።በዚያ ላይ ሐይቅ ኖሮ🥰 በዚያ ላይ ቆንጆ ልጅ ከሐይቁ ዳር አብራኝ ብቶን ዐይን ዐይኗን ዕያዬሁ፦ ዐይንሽን ዐያለሁ ጥርስሽን ዐያለሁ ሰው መሆን አምሮኛል በሕይወት እያለሁ🤫 እምላት ነኝ።

ማነው ደሞ «ደም ምለሳ»ን ኋላ ቀር ባሕል ያደረገው? አባቴ ደምመላሽ ባይኖር ጥጋበኛው ሁሉ እየተነሳ ማንንም ይቀትል ነበር። ደግሞስ የጎጃሙን ጀግና በላይ ዘለቀ ላቀውን «የኢትዮጵያ ደም መላሽ!» የ
ማነው ደሞ «ደም ምለሳ»ን ኋላ ቀር ባሕል ያደረገው? አባቴ ደምመላሽ ባይኖር ጥጋበኛው ሁሉ እየተነሳ ማንንም ይቀትል ነበር። ደግሞስ የጎጃሙን ጀግና በላይ ዘለቀ ላቀውን «የኢትዮጵያ ደም መላሽ!» የምንለው በዚህ የጀግና ግብሩ አደለም እንዴ? ባይዜ ራሡ በላያ እና ወንድሙ እጅጉ ዘለቀ ወደ ጫካ የወጡበት የመጀመሪያ ምክኒያት የአባታቸውን ደም ለመመለስ ነበር። የባሰ ጠላት አገኙ፤ፋነኑ። ምን ለማለት ዩ🥰 ሕግ እና ሥርዓት በተመናመነበት እንደ ኢትዮጵያ ባለ አገር ወንድ ልጅ የወንድሙን ደም የሚመልስ ባይሆን ኖሮ ተከባብረን አንቀጥልም ነበር። በፖለቲካ ፓወር ባለንስ የሚባል እንዲህ ያለው ነገር መሰለኝ። ሂድ መካከለኛው ምሥራቅ... እሥራኤል አንድ ዜጋዋ ሲነካ ተጣድፋ ደሙን ትመልሳለች።ኢራንም እንዲሁ ናት።አሜሪካ ራሧ! ዌል እንግዲክ🤫 ደም የሚያደርቅ አያት ያለኝ ሰው ነኝ።ማስታረቁን እናውቅበታለን።ሆኖም የገዳይ ወገኖች ለመታረቅ ራሡ ደም መላሽ ወንድም እንዳለህ ማወቅ አለባቸው። ምን ለማለት ነው? «ደምመላሽ ተብዬ ሥም ወቶልኝ ነበር» ያለውን ዘፋኝ ሙዚቃውን እንዲያርም ንገሩት። ሥሙንም መሥፍን ከማለት ወደ ደምመላሽነት ይመልሰው። ይሄው ነው🙁

ሥለ እንግጫ ነቀላ እና ከስይ አጨዳ ታሪካዊ አመጣጥ፣ሥለ ጎጃም ሴቶች አስደማሚ ጠባይ ለመታደም ይሄን https://youtu.be/CWewJ4SQ0n4?si=6-Z6NbwdIw9Bpacw ሊንክ ይጫኑ። ጎጃም
ሥለ እንግጫ ነቀላ እና ከስይ አጨዳ ታሪካዊ አመጣጥ፣ሥለ ጎጃም ሴቶች አስደማሚ ጠባይ ለመታደም ይሄን https://youtu.be/CWewJ4SQ0n4?si=6-Z6NbwdIw9Bpacw ሊንክ ይጫኑ። ጎጃምን ለሚወዱ ሁሉ ያጋሩ። ሌሎች እንዲህ ያሉ ዝግጅቶች በብዛት እንሠራ ዘንድ ቪዲዮውን ከዩቱዩብ ገጻችን ውጭ ባለመመልከት፣ተቆርጦ ተጭኖ ሲያገኙትም አዘጋጁን ታመነ መንግሥቴ ውቤን ሜንሽን በማድረግ እና ለማኅበራዊ ትሥሥር ገጾች ማመልከቻ በማስገባት አበረታቱን። እንወዳችኋለን🥰

«በውጅግራ ነበር የወንድ ልጅ ሞቱ በአምስት ጎራሽ ነበር የወንድ ልጅ ሞቱ በምኒሽር ነበር የወንድ ልጅ ሞቱ ሥቃ ገደለችኝ ወንዱን ልጅ ሴቲቱ በዐይኗ ገደለችኝ ወንዱን ልጅ ሴቲቱ»👏
«በውጅግራ ነበር የወንድ ልጅ ሞቱ በአምስት ጎራሽ ነበር የወንድ ልጅ ሞቱ በምኒሽር ነበር የወንድ ልጅ ሞቱ ሥቃ ገደለችኝ ወንዱን ልጅ ሴቲቱ በዐይኗ ገደለችኝ ወንዱን ልጅ ሴቲቱ»👏

የእኛ ትውልድ ከብዙ ትግል በኋላ ወደ ማንነቱ ለመመለስ መንገድ ላይ ይገኛል።የትውልድ ቀዬውን፣ወላጆቹን፣ማንነቱን መውደድ ጀምሯል። በታንጎ እና ማሪንጌ ከመደነስ ወደ እስክስታ እና ዋንጫ ልቅለቃ፣ከውቤ
የእኛ ትውልድ ከብዙ ትግል በኋላ ወደ ማንነቱ ለመመለስ መንገድ ላይ ይገኛል።የትውልድ ቀዬውን፣ወላጆቹን፣ማንነቱን መውደድ ጀምሯል። በታንጎ እና ማሪንጌ ከመደነስ ወደ እስክስታ እና ዋንጫ ልቅለቃ፣ከውቤ በረሃ እና ቺቺኒያ ናይት ክለቦች ወደ ሻደይ፣አሸንዳ፣እንግጫ ነቀላ፣ጥምቀት፣ፉከራ፣ቅራርቶ እና የመሳሰሉ አገር በቀል መድረኮች ተመልሷል። ከቤል ሱሪ ወደ ተነፋነፍ፣ቂጥ አጉልቶ ከሚያሳይ የሴት ልብስ ወደ ውብ የአገር ባሕል ቀሚስ ተዛውረናል። ከ90ዎቹ እኛን የማይመሥሉ ፊልሞች ወደ ድለቃ እና የገጠር ድራማዎች አድገናል። ትውልዱ ተገዶም ሆነ ወዶ በጎጃም፣ጎንደር፣ወሎ፣ሸዋ፣ሐረርጌ፣ጋሞጎፋ ገጠሮች ሄዶ ወደመኖር ተሸጋግሯል። ይሄ እጅግ በጣም ደስ የሚል ለውጥ ነው። ሆኖም ዛሬም ቢሆን ነባር እውቀቶች በንባብ፣በቃላዊ የእውቀት ሽግግሮች፣በግጥም እና በማኅበረሰብ ዜማዎች ተቀማጥለው ሲቀርቡ ዓላይም። ውብ ሴቶቻችን ስክሪን ላይ እየመጡ ከዓመታት በፊት በተዜሙ ሙዚቃዎች ከመወዝወዝ ያለፈ ፈጠራ ዕያሳዩን አይደለም። የባሕል ሙዚቃዎቻችን ቪዲዮዋቸው ሲያምር ታሪክ እያበላሹ፣ግጥማቸው ልል እየሆነ፣አዚያዚያማቸው ለልብ አልሞላ እያለ ተቸግረናል። ታነስ አነስ... ፍቅርዓዲስ ነቅዓጥበብ እና ይሁኔ በላይ የተባሉ ውዶቻችን ለመጨረሻ ጊዜ ያወጧቸው አልበሞች የነሱ አልመሥለኝ እስኪሉ ድረስ ሳስተው አግኝቻቸው አለሁ። የማኅበራዊ ትሥሥር ገጾች የኪነጥበብ ሰዎችን ትኩረት መቀማታቸው ለዚህ ዋናው ተጠያቂ ይመሥለኛል። ይህ ግን ለእኛ ገና በ18ኛው የዘመን ክፍል የዓለም ሥልጣኔ ደረጃ ላለን ኋላቀሮች ተገቢ አደለም። ልቦለድ ከጀመርን ገና መቶ ዓመታችን ነው።የተደራጀ ሙዚቃ ከጀመርን 50 ዓመታችን ነው።ፊልማችን ከ30 ዓመት የበለጠ ዕድሜ የለውም።ቴአትራችን ገና ልጅ ነው። ወዘተ ወዘተ እናም ፈጠራ ላይ እንበርታ🥰

ኦሮሞ ከአዶናይ ብርሃነ በጣም የላቀ የባሕል አምባሳደር አለው። አርፏል። ሥሙ ተስፋዬ ገብረአብ ይባላል። ለኦሮሞ ሕዝብ ያለውን ፍቅር ያልገለጸባቸው መጽሐፍቱ ጥቂት ናቸው። ተስፋዬ በአደኣ ገጠሮች፣በጋ
ኦሮሞ ከአዶናይ ብርሃነ በጣም የላቀ የባሕል አምባሳደር አለው። አርፏል። ሥሙ ተስፋዬ ገብረአብ ይባላል። ለኦሮሞ ሕዝብ ያለውን ፍቅር ያልገለጸባቸው መጽሐፍቱ ጥቂት ናቸው። ተስፋዬ በአደኣ ገጠሮች፣በጋራበሩ ኮረብታዎች፣በቢሾፍቱ ሐይቅ ዳርቻ አብሯቸው እንደኖረ ሥለሚናገርላቸው ኦሮሞዎች ሲጽፍ በፍቅር ያነሆልላል። የኦሮሞ ልሂቃንም ይሄንን ውለታው አስልተው «ገዳ(?)» ብለውታል። ከባድ ማዕረግ ነው። ኦሮሞ ከተስፋዬም በላይ ሌላ የላቀ አምባሳደር አሉት።ፕሮፌሠር አሥመሮም ለገሰ ናቸው። ወደ ጥንት የኦሮሞ መሠረት—ቦረና ወርደው ከአርብቶ አደሩ ጋር ኖረው ነው—ባሕሉን እና የገዳ ሥርዓቱን አጥንተው ለዓለም ያሳወቁት። እኔ ራሴ በእሳቸው ጥናት ላይ የተመሠረተውን የኦሮሞ ታሪክ ሳይሆን ይቀራል የተማርኩት? በዚያም ምክኒያት የኦሮሞ ሕዝብ ይደላኛል። አዶኒ ግን በእነ ጸገመ፣በእነ በዓሉ ግርማ፣በእነ ሰለሞን ዴሬሳ ደረጃ ሊወከል የማገባውን ኦሮሞ ወክሎ አምባሳደር መሆን የሚችል አይመሥለኝም። ሚሊዮን ማስከተል ሌላ፤ምልዑ አርኣያ መሆን ሌላ። ከሁሉ በፊት ያንብብ፣ይወቅ፣ይጻፍ—ይዘት—የሚባለውን ነገር የሚያሟላ ሥራ ይከውን። በመርሕ ደረጃ የአዶናይ ደጋፊ ነኝ።ግን እውቀቱ፣ጥልቀቱ እና ችሎታው ላይ ባለፈው ሕዳር ያነሳሁትን ጥያቄ አልመለሰልኝም። በውነቱ tt ላይ ይዘቱ ሲመጣልኝ ለመመልከት አመነታለሁ🙁

«...ከሀገራችን ሕዝቦች መካከል በጣም የታወቁት እና በነገሥታቱ ዘንድ ጭምር 'ዘንድሮ ምን አሉ?' ተብለው የሚጠበቁት ሰላሌዎች እና ጎጃሜዎች ነበሩ። እነዚህ የአንድ ወንዝ ልጆች የተዋጣላቸው ተጫዋቾ
«...ከሀገራችን ሕዝቦች መካከል በጣም የታወቁት እና በነገሥታቱ ዘንድ ጭምር 'ዘንድሮ ምን አሉ?' ተብለው የሚጠበቁት ሰላሌዎች እና ጎጃሜዎች ነበሩ። እነዚህ የአንድ ወንዝ ልጆች የተዋጣላቸው ተጫዋቾች፣ገጣሚዎች እና ደፋሮችም እንደመሆናቸው ተፈጥሮ ባጎናጸፈቻቸው ጸጋዎች በመጠቀም በአገር ላይ፣በሕዝብ ላይ የሚደርሱ በደሎችን፣የሚፈጸሙ ግፎችን ለማጋለጥ ግንባር ቀደሞች ነበሩ።» የሻሞላው ትውልድ፣ፋሲካ ሲደልል፣ገጽ 73 ይሄ ድልድይ ደግሞ የጎሃጽዮን እና የደጀን፣የደብረማርቆስ እና የፊቼ፣የአዲስ አበባ እና የጎንደር፣የኢትዮጵያ እና የሱዳን መገናኛ ሥለሆነ ባዬነው ቁጥር ያስደስተናል። ከተጓዛችሁበት ሥንት ዓመት ሆናችሁ🙁?

«ቀይ ባሕር ሲቀላ» ሥለ ሰሜን ካነበብኳቸው የቅርብ ጊዜ መጽሐፍት መካከል ምናልባትም ሁለተኛው ጣፋጭ መጽሐፍ ነው።«አውሮራ»ን ስለደገምኩት እሱ ቀዳሚ ሆኖ ማለት ዩ። «ቀይ ባሕር ሲቀላ» ውስጥ ሥለ
«ቀይ ባሕር ሲቀላ» ሥለ ሰሜን ካነበብኳቸው የቅርብ ጊዜ መጽሐፍት መካከል ምናልባትም ሁለተኛው ጣፋጭ መጽሐፍ ነው።«አውሮራ»ን ስለደገምኩት እሱ ቀዳሚ ሆኖ ማለት ዩ። «ቀይ ባሕር ሲቀላ» ውስጥ ሥለ ምጽዋ የተጻፈው ሁሉ በአግራሞት ሲያተራምሰኝ ነበር። ምጽዋ የባሕር ዳርቻ ከተማ ናት።ሞቃታማ ከተማም ናት። እናም ሰዎች በዚያ ነፃ ናቸው። እንዲህ ያለ ከተማ ነው—እኔን የሚደላኝ። ጄጅ—የሚያረገኝ ሰው የሚበዛበት ቦታ መገኘት አልወድም።የራሴ የአመጋገብ፣አለባበስ፣አነጋገር፣አጻጻፍ፣አኗኗር ዘዴ አለኝ። በቃ አለኝ። ግን የመሐል አገሩ እና የእኔ ዐይነቱ ሰው ፕሮቶኮል ያበዛል።ሥለሆነም ያስጨንቀኛል። በዚህ ምክኒያት ነው—ድግስ የማይመቸኝ። ሥለ ድግስ መጻፍ ወይም ማውራት እንጅ መሳተፍ አልወድም።ወደ ዘመድ ቤት መሔድም ምቾት አይሰጠኝም። «ብላ» ይሉኝ'ና አበላሌን ይገመግማሉ። ኤጭ😥 እናም እንደ ምጽዋ፣ሎግያ፣ሰመራ፣ወንጂ፣አዳማ ወዘተ ያሉ ሰው ለቀቅ ብሎ ሳይገማገም የሚኖርባቸው ከተሞች የነፍሴ ፍሥሐ የሚቀዳባቸው ይመሥሉኛል። «ቀይ ባሕር ሲቀላ» ውስጥ ያዬኋት ባጽዕ(?) እንዲያ ናት። ፍርድአወቀ ማሞ ሲነግሩንኮ «ምጽዋ ባል እና ሚስት በረንዳ እና የእግረኛ መንገድ ላይ አልጋቸውን አውጥተው፣ተቃቅፈው የሚተኙባት ከተማ ናት፤» ደሞ ምጽዋ—ፊያሜታ ጊላይ እና ዳግም ጸጋዬ ኃይለማርያም የተገናኙባት ከተማ ናት። ፊያሜታ ያን'ለት ቀዩን ባሕር ከአድማስ ባሻገር ድረስ ዕያዬች ከራሷ ጋር ስትጫወት ነው—ጸጋዬ ያገኛት።ውብ ነጠላ ለብሳ «ነጭ እርግብ ትመሥል ነበር» ብሎናል—ደራሲው። ያች ምጽዋ ትናፍቀኛለች። «የማያውቁት አገር አይናፍቅም፤» ያለ ማነው? ጭዌው የኢማጂኔሽን ልዩነት ነው—ብሮ። ጎንደርን ሳላያት ትናፍቀኝ ነበር። ሜይ ቢ አለማወቅ—አለማንበብ፣ሙዚቃ ላይ አለመሥማት ምናምን ተሆነ እሺ...

ሕዳር መጨረሻ 2014 ዓመተ ምኅረት በሕይወቴ ለመጀመሪያ ጊዜ ደሴ ገባሁ። የዚያን'ለት ደሴ ግራ የተጋባች ከተማ ነበረች።ለ40 ቀናት በሕወሓት ተዋጊዎች ቁጥጥር ሥር ሰንብታ ገና እኛ የገባን'ለት ወደ
ሕዳር መጨረሻ 2014 ዓመተ ምኅረት በሕይወቴ ለመጀመሪያ ጊዜ ደሴ ገባሁ። የዚያን'ለት ደሴ ግራ የተጋባች ከተማ ነበረች።ለ40 ቀናት በሕወሓት ተዋጊዎች ቁጥጥር ሥር ሰንብታ ገና እኛ የገባን'ለት ወደ መደበኛ ሕይወት መመለሷ ነው። ላይኛው አንቀጽ ፖለቲካ ነው። እነሆ ውበትን ፍለጋ በጥምዙ እና ጠባቡ የደሴ መንገድ ወደ ቧንቧ ውሃ ሰፈር እንጓዝ። በዚህ ሁሉ ጉዞ ሂደት ያ—የጸሐፊ ብዕር ያስጨረሰ፣የባለቅኔ ምናብ ያሟጠጠ፣የዘፋኝ ጉሮሮ የቧጠጠ፣የተመልካች ቀልብ የበጠበጠ የወሎ ሴት ልጆች ውበት የለም። አንዲትም ቆንጅዬ—ወሎዬ ዕያዬሁ አይደለም። ቧንቧ ውሃ ደረስን።በቀኝ በኩል «Time» የሚባል ሆቴል ደብሮት ቆሟል። እዚህ ሥር ግን ትክክለኛዋ የወሎ ቆንጆ ከትንሽ እህቷ ጋር ቁጭ ብላ ለወራት የሆነውን፣ዛሬ እየሆነ ያለውን እና ነገ የሚሆነውን ታሰላስላለች። ተያዬን። ብርቅ ሆነችብኝ።ብቻዋን የወሎን ልጆች ቁንጅና ልታስመሰክር በዚያ የከተማ ምድረ በዳ የተከሰተች የውበት እርግብ መሰለችኝ። እየፈራሁ—እየተባሁ ወግ አስጀመርኳት። ከ40 ቀን በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ከግቢ መውጣቷን ነገረችኝ።እኛ ብርቅ እንደሆንባትም አጫወተችኝ። በጠይም ፊቷ ውስጥ የተከማቸው ደም የውበት ቅመም ይመሥለኝ ጀመር።እዚያው ሥለቁንጅናዋ እያሰብኩ ስሟሟ ትዝ ይለኛል። ምን ይሆናል🙁? እነ መንጌ በጦርነት መሐል እንዲህ እንድመሰጥ አይፈቅዱልኝም።ወዲያው አጣድፈው ከወሎዋ አበባ ለዩኝ።እሷም ከርቀት ዕያየችን እጆቿን አውለበለበች። ከዚያች ቀን በኋላ ደሴ ውስጥ ለአምስት ወራት ኖሬዐለሁ።ከጦርነቱ በኋላም ሁለት ጊዜ ተመላልሸ አለሁ። ግን ያችን ለመጀመሪያ ጊዜ የወሎ ልጆችን ውበት በአካል ያዬሁባትን እንቁ ደግሜ ለማግኘት አልታደልኩም። እዚህ የሚታዩት የወሎ ልጆች በይሁኔ በላይ ሰሞነኛ «ዞማዬ» ቪዲዮ ውስጥ ያሉ ናቸው።