en
Feedback
Ministry of education ethiopia

Ministry of education ethiopia

Open in Telegram

Show more
The country is not specifiedThe category is not specified
1 423
Subscribers
+524 hours
+487 days
+17730 days
Posts Archive
የዩኒቨርስቲ ምደባ ሊደረግ ነው ምደባውን በፍጥነት የሚያሳውቃችሁን ቻናል ልጠቁማችሁ 👇👇👇 ትምህርት ሚኒስቴር 📚 የፈተናዎች ኤጀንሲ ✅

ከመንግስት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚመረቁ ተማሪዎች የመውጫ ፈተና ሊወስዱ መሆኑ ተገለጸ! ከሁሉም የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች የሚመረቁ ተማሪዎች በሰለጠኑባቸውና በተማሩባቸው ሙያዎች ብቁ መሆናቸውን ለማረጋገጥ የመውጫ ፈተና እንዲወስዱ ከዚህ ቀደም ሲደረግ የነበረው ጥረት ወደ ተግባር እንዲገባ ዝግጅት መደረጉን የትምህርት ሚኒስቴር አስታውቋል::የመውጫ ፈተነውን በተመለከተ የመንግስት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ፕሬዝዳንቶች በተገኙበት በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ምክክር እየተደረገ ይገኛል:: የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች የምክክር መድረክ ባዘጋጀው ውይይትም የመውጫ ፈተናው አስፈላጊነት፤ የፈተና አወጣጥና አፈታተን እንዲሁም ተያያዥ ጉዳዮች ዙሪያ ምክክር እየተደረገበት ነው::የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች የምክክር መድረክ ፕሬዚዳንት እና የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ፕሬዚዳንት ፕሮፌሰር ጣሰው ወልደሃና የመውጫ ፈተናው የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ የምሩቃንን ክህሎትና እውቀት ለመፈተሽ የስራ ገበያንም ለማሳደግ የሚያግዝ መሆኑን ገልጸዋል:: በትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት ልማት ሚኒስትር ደዔታ ዶ/ር ሳሙዔል ክፍሌ በበኩላቸው፤ መንግስት በመጪዎቹ አምስት ዓመታት የትምህርት ጥራትን ለማሻሻል ጠንካራ ትግበራና ርምጃዎችን እንደሚወስድ አንስተዋል:: አዲስ የመንግስት ዩኒቨርስቲ እንደማይኖርና የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አቅምና ጥራት ማሻሻል ላይ በትኩረት እንደሚሰራና መውጫ ፈተናው እንዲወሰድ በሁሉም ዩኒቨርሲቲዎች በቂ ዝግጅት መደረጉን አስታውቀዋል::የመውጫ ፈተናው በእያንዳንዱ ዩንቨርስቲ በየሙያውና ትምህርት ዘርፍ ተዘጋጅቶ የሚሰጥ ሲሆን ለዚህም ትግበራ ፖሊሲና ዝርዝር ማስፈፀሚያ መመሪያ መዘጋጀቱን ገልፀዋል::በህግና በህክምና ሙያ የሚሰጠው የመውጫ ፈተናና የብቃት ማረጋገጫ ፍተሻ እንደ ልምድ ይወሰዳልም ነው የተባለው:: [AMN] ♾♾♾♾♾♾♾♾♾ 📚 JOIN : @FDRE_MOE 📚 JOIN : @FDRE_MOE ♾♾♾♾♾♾♾♾♾

በአፋር ክልል በጊዜያዊነት ትምህርት ለማስቀጠል ድንኳኖች ተሰራጩ ----------------------------------- በአፋር ክልል በጦርነት የተፈናቀሉ ተማሪዎችን በጊዜያዊነት ትምህርት ለማስጀመ
+3
በአፋር ክልል በጊዜያዊነት ትምህርት ለማስቀጠል ድንኳኖች ተሰራጩ ----------------------------------- በአፋር ክልል በጦርነት የተፈናቀሉ ተማሪዎችን በጊዜያዊነት ትምህርት ለማስጀመር 38 ድንኳኖች ለወረዳዎች ማከፋፈሉን የክልሉ ትምህርት ቢሮ አስታውቋል፡፡ የክልሉ ትምህርት ቢሮ የትምህርት ቤት መሻሻል ቡድን መሪ አቶ ዑመር መሀመድ እንደገለጹት ድንኳኖቹ የተሰራጩት በጦርነት ተፈናቅለው የመጡ ተማሪዎች ትምህርታቸውን በጊዚያውነት እንዲጀምሩ ለማስቻል መሆኑን ገልፀዋል። ለወረዳዎቹ በተከፋፈሉት ድንኳኖች በጦርነቱ አዲስ ተፈናቅለው የመጡ ተማሪዎችና ትምህርት ቤቶቻቸው በተፈናቃዮች መጠለያነት የተያዙባቸው ተማሪዎች በጊዜያዊነት ትምህርታቸውን እንዲቀጥሉባቸው እንደሚደረግ ቡድን መሪው ተናግረዋል፡፡ በድንኳኖቹም በጊዚያዊነት ከ 3 ሺህ በላይ ተማሪዎችን ለማስተማር ዝግጅት እየተደረገ መሆኑም ተገልጿል። የተሰራጨው ድንኳን ከተፈናቀሉ ተማሪዎች ቁጥር አንጻር በቂ ባለመሆናቸው ተጨማሪ ድንኳኖች እንዲፈለጉ ጥያቄ መቅረቡም ታውቋል፡፡ ክልሉ ላይ በነበረው ጦርነት 65 ትምህርት ቤቶች ሙሉ በሙሉ መውደማቸው ይታወሳል።

በአፋር ክልል ከአርባ ሺህ በላይ ተማሪዎች ወደ ትምህርት ገበታቸው አልተመለሱም ----------------- በአፋር ክልል ከአርባ ሺህ የሚበልጡ ተማሪዎች እስካሁን ወደ ትምህርት ገበታቸው አለመመለሳቸ
+3
በአፋር ክልል ከአርባ ሺህ በላይ ተማሪዎች ወደ ትምህርት ገበታቸው አልተመለሱም ----------------- በአፋር ክልል ከአርባ ሺህ የሚበልጡ ተማሪዎች እስካሁን ወደ ትምህርት ገበታቸው አለመመለሳቸውን የክልሉ ትምህርት ቢሮ አስታወቀ። የክልሉ ትምህርት ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ደረሳ መሀመድ እንደገለጹት በጦርነቱ ምክንያት ከተፈናቀሉ ተማሪዎች መካከል ወደ ትምህርት ገበታቸው የተመለሱት ግማሽ ያህሉ ብቻ ናቸው። ከጦርነቱ በፊት ከ90 ሺህ በላይ ተማሪዎች በትምህርት ገበታ ላይ እንደነበሩ የጠቀሱት ኃላፊው ከ40 ሺህ በላይ የሚሆኑት እስካሁን እንዳልተመለሰለ ተናግረዋል። ተማሪዎቹ ወደ ትምህርት ገበታቸው ያልተመለሱት ትምህርት ቤቶቻቸው በመፍረሳቸው ፣ የውሃ ፣ የመመገቢያ እና ሌሎችም መሠረተ ልማቶቻቸው በመውደማቸው ነው። በጦርነቱ በነበረው ከፍተኛ የጦር መሣሪያ ድምጽና በትምህርት ቤቶቹ ያዩዋቸው ነገሮች የፈጠሩባቸው አእምሯዊና ስነልቦናዊና ችግሮችም የመማር ፍላጎት እንዲያጡና ወደ ትምህርት ቤት እንዳይመጡ እንዳደረጓቸው ተነግሯል። ቢሮው ተማሪዎቹ ወደ ትምህርት ገበታቸው እንዲመለሱ ለማድረግ በየደረጃው ያሉ የወረዳና የቀበሌ አመራሮችና ከማህበረሰቡ ጋር ውይይት እያደረገ ይገኛል፡፡ በትምህርት ሚኒስቴር የመምህራን ልማት ከፍተኛ ባለሙያ አቶ ተስፋዬ ደገፋ በጦርነት አካባቢ ህጻናት ለከፍተኛ ስነልቦናዊና ማህበራዊ ችግሮች እንደሚጋለጡ ተነግረዋል። ከዚህ ችግር እንዲላቀቁም ስነልቦናዊና ማህበራዊ ምክርና ስልጠና ተደራሽ ማድረግ እንደሚገባ ጠቁመዋል። የትምህርት ሚኒስቴር ከዩኒሴፍ ጋር በመተባበር ስነልቦናዊና ማህበራዊ ችግሮችን ለማቃል በጦርነት ቀጠና ውስጥ ለነበሩ መምህራን የአሰልጣኞች ስልጠና እየሰጠ እንደሚገኝ ይታወቃል።

የምርምር ሥራ ሥነ ምግባሩን በጠበቀ መልኩ መከናወን እንደሚገባ ተገለፀ ---------------------------- ትምህርት ሚኒስቴር ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጤና ሣይንስ ኮሌጅ ጋር በመተባበር
+2
የምርምር ሥራ ሥነ ምግባሩን በጠበቀ መልኩ መከናወን እንደሚገባ ተገለፀ ---------------------------- ትምህርት ሚኒስቴር ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጤና ሣይንስ ኮሌጅ ጋር በመተባበር በምርምር ሥነ ምግባር ላይ ምክክር መድረክ አካሂዷል፡፡ የከፍተኛ ትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ሳሙኤል ክፍሌ (ፒ ኤች ዲ) በሰዎች፣ በእንስሳት፣ በአካባቢና በተቋማት ላይ የሚሰሩ ምርምሮች ሥነ ምግባራቸውን በጠበቀ መልኩ መከናወን እንዳለባቸው አሰገንዝበዋል፡፡ ሚኒስትር ዴኤታው አክለውም በዩኒቨርሲቲዎች የሚሰሩ ምርምሮች ተገቢነት ያላቸው፣ ችግር ፈቺ መፍትሔ ሰጪ ሆነው ማህብሰቡንና ተቋማትን የሚቀይሩ መሆን እንደሚገባቸው ገልፀዋል፡፡ የአንድ አገር እድገት የሚለካው በምርምር ሥራ ቴክኖሎጂዎችን በትክክል በመረዳት ወደ ራሳችን ተጨባጭ ሁኔታ የመቀየር፣ እሴትን በመጨመር መጠቀም፣ አዳዲስ ሃሳቦችን የማመንጨትና የፈጠራ ሥራዎችንም የማበርከት የመፍትሔ ክምችት አቅም ስኖር እንደሆነ አስረድተዋል፡፡ ምርምር የሚመራበት ሥነ ምግባር የራሱ አደረጃጀትና የህግ ማዕቀፍ እንዳለው በመጥቀስ በትምህርት ዘርፍ የሚሰሩ ምርምሮች ሂደታቸው ውጤታቸው ላይ ጉዳት ሳያደርስ ለህብረተሰቡ ዘላቂ መፍትሄ መጠቆም እንደሚገባቸው አሳስበዋል፡፡

በአፋር ክልል በጦርነቱ ምክንያት በተማሪዎችና በመምህራን ላይ የሚፈጠሩ ስነልቦናዊና ማህበራዊ ጉዳቶችን ለመቅረፍ የሚያስችል የአሰልጣኞች ስልጠና እየተሰጠ ነው። ------------------------
+2
በአፋር ክልል በጦርነቱ ምክንያት በተማሪዎችና በመምህራን ላይ የሚፈጠሩ ስነልቦናዊና ማህበራዊ ጉዳቶችን ለመቅረፍ የሚያስችል የአሰልጣኞች ስልጠና እየተሰጠ ነው። ---------------------------------- ትምህርት ሚኒስቴር በአፋር ክልል በጦርነቱ ምክንያት በተማሪዎችና በመምህራን ላይ የሚፈጠሩ ስነልቦናዊና ማህበራዊ ጉዳቶችን ለመቅረፍ የሚያስችል የአሰልጣኞች ስልጠና እየሰጠ ይገኛል። የስልጠናው ዓላማም በጦርነቱ ምክንያት የተጎዱ ህጻናትና ተማሪዎች አእምሯዊና ማህበራዊ ችግር እንዳይገጥማቸውና ትምህርታቸውን በአግባቡ መከታተል የሚችሉበትን ሁኔታ ለመፍጠር ያለመ መሆኑ ተገልጿል ። በአሁን ሰዓት በክልሉ በጦርነት ከተጎዱ ወረዳዎች የተውጣጡ 50 መምህራን ስልጠናውን እየተሳተፉ ይገኛሉ። በትምህርት ሚኒስቴር የመምህራን ልማት ከፍተኛ ባለሙያ አቶ ተስፋዬ ደገፋው ከተማሪዎች በተጨማሪ መምህራኑም ራሳቸው በጦርነቱ የተጎዱ በመሆናቸው ችግር ሳይገጥማቸው ተማሪዎችን በአግባቡ ማስተማር እንዲችሉ የአሰልጣኞች ስልጠናው እንደሚያግዝ ገልፀዋል። የአፋር ክልል ትምህርት ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ደረሳ መሀመድ በበኩላቸው የአሰልጣኞች ስልጠናው በክልሉ በጦርነቱ ምክንያት የተጎዱ ተማሪዎች መምህራንና ተማሪዎችን ስነ ልቦናዊና ማህበራዊ ድጋፍ እንዲያገኙ እንደሚያስችል ገልጸዋል። ስልጠናውም በአሰልጣኞች ስልጠና ተሳታፊዎች አማካኝነት እስከታች ወርዶ እንደሚሰጥ ተገልጿል።

ሰው በመጋበዝ በቴሌ ብር ተከፋይ ይሁኑ https://t.me/HaHu_Inviting_Bot?start=NWYyM 1) 👆 ሊንኩን ተጭናቹ መክፈት 2) ስልክ ቁጥራቹን ማጋራት(Share) የሚለውን መጫን 3) የ 2ተኛውን ስቴፕ ከጨረሳቹ በኃላ የሚጣውን ሊንክ ተጭናቹ ቻናሉን ጆይን ማረግ 4) ስትጨርሱ ✅ ቼክ ሰብስክሪፕሽን = የሚለውን መጫን

🤖የዩኒቨርሲቲ ምደባ እንዴት ይሰራል⁉️ የዩኒቨርሲቲ ምደባ የሚሰራው እንደድሮው ጊዜ በቀጥታ በሰዎች ሳይሆን ዘመናዊ እና አለምአቀፋዊ ተቀባይነት ባለው ማሽን ነው። ታድያምደባው ሲካሄድ በዋነኝነት የተማሪዎችን ውጤት መሰረት በማድረግ ነው፡፡ ይኸውም:- ምደባው በቅድሚያ ምደባውን ለሚያከናውነው ማሽን እነዚህ የመረጃ ግብዓቶች inpute ይሰጡታል። እነሱም 👉 ከመቁረጫ ነጥብ በላይ ያመጡ ተማሪዎች ስም ዝርዝር 👉 የዩኒቨርሲቲዎች የመቀበል አቅም 👉 የመቁረጫ ነጥብ 👉 የተማሪዎች ውጤት 👉 PHASE (ምድብ) PHASE ማለት ለምሳሌ እነሱ inpute ሲያስገቡ PHASE 1 ከ አንደኛ ምርጫ እስከ አምስተኛ ምርጫ PHASE 2 ከ አምስተኛ ምርጫ እስከ አስረኛ ምርጫ ወ.ዘ.ተ እያለ እንዲሰጥ አድርገው program ያደርጉታል ማለት ነው። ከላይ ያሉት የመረጃ ግብዓቶች ከገቡለት በኋላ ማሽኑ 1⃣ የተማሪውን ውጤት (ነጥብ) 2⃣ የተማሪውን የምደባ ምርጫ አሞላል 3⃣ የዩኒቨርሲቲዎች የመቀበል አቅምን መሰረት በማድረግ ተማሪዎችን ይመድባል፡፡ በዚህ መልኩ ምደባ ሲሰራ እነሱ ብቻ በሚያውቁት scale መሰረት: ➖ በጣም ጥሩ ውጤት ያመጣ ተማሪ PHASE = ONE , CHOICE = ONE ይደርሰዋል ማለት ነው። ማለትም የመጀመሪያ ምድብ የመጀመሪያ ምርጫ ማለት ነው፡፡ ➖ ከዚያ scale ቀጥሎ ያመጣ ተማሪ ደግሞ: PHASE = 1 , CHOICE = 2 ይደርሰዋል ማለት ነው። ማለትም የመጀመሪያ ምድብ ሁለተኛ ምርጫ ማለት ነው። የምደባ ውጤት በቅርብ ሳምንት ውስጥ ይፋ ይደረጋል! ♾♾♾♾♾♾♾♾♾ 📚 JOIN : @FDRE_MOE 📚 JOIN : @FDRE_MOE ♾♾♾♾♾♾♾♾♾

" ከ13,862 ተፈታኞች 3,006 ተማሪዎች ብቻ ናቸው ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም የመግቢያ ዉጤት ያስመዘገቡት " የአዊ ብሔ/አሰ ትምህርት መምሪያ በአማራ ክልል፤ የአዊ ብሔረሰብ አስተዳደር ትምህ
+2
" ከ13,862 ተፈታኞች 3,006 ተማሪዎች ብቻ ናቸው ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም የመግቢያ ዉጤት ያስመዘገቡት " የአዊ ብሔ/አሰ ትምህርት መምሪያ በአማራ ክልል፤ የአዊ ብሔረሰብ አስተዳደር ትምህርት መምሪያ ከ13 ሺ 862 ተፈታኞች 3 ሺህ 6 ተማሪዎች ብቻ ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም የመግቢያ ዉጤት ማስመዝገባቸዉን አሰታወቀ። የመምሪያዉ ኃላፊ አቶ አለሙ ክህነት በ2013ዓ.ም በብሔረሰብ አስተዳደሩ በ29 ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ላይ 13 ሺህ 862 ተማሪዎች ሀገርአቀፋ ፈተና መፈተናቸውን ገልጸዋል። ከነዚህም ዉስጥ በብሄረሰቡ ታሪክ ታይቶ በማይታወቅ ደረጃ 3 ሺህ 6 ተማሪዎች ብቻ ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም የመግቢያ ዉጤት ማምጣታቸውን ነዉ ሀላፊዉ የተናገሩት። አጠቃላይ የማለፋ ምጣኔም 21.7% ብቻ መሆኑ ተገልጿል። ከተፈተኑት የተፈጥሮ ሳይንስ 5 ሺህ 745 ተማሪዋች መካከል 1 ሺህ 943 የመግቢያ ዉጤት አምጥተዋል። በማህበራዊ ሳይንስ ደግሞ ከተፈተኑት 8 ሺህ 117 ተማሪዎች ዉስጥ 1 ሺህ 63 ወደ የመግቢያ ዉጤት ያመጡ መሆናቸዉን ተገልጿል። የእርማት ጥራት ችግር ማሳያ 140 ያመጣ ተማሪ እንደገና ሲፈተሸ 601 ፣ የሲቪክስ ት/ት ፈተና ችግር በሌለበት አካባቢ መሰረዝ እና የፈተና አስተዳደር ስርዓቱ በአግባቡ የተመሩ ባለመሆናቸዉ ለተመዘገበዉ ዝቅተኛ ዉጤት ተጠቃሽ ሞክንያቶች መሆኑን ትምህርት መምሪያው ገልጿል። የፈተና ስርዓቱ ስለመታወኩ በተለያዩ ቴክኖሎጂዎች ቼክ ተደርጎ እንደገና መፈተሽ እንዳለበት ከሚመለከተው ጋር እየሰራ መሆኑን መምሪያው አሳውቋል። እስከአሁንም መምሪያዉ ከክልሉ ትምህርት ቢሮ ጋር የፈተና ሂደቱ እንደገና እንዲታይ ጥረት እያደረገ መሆኑን ገልጾ ተማሪዎች እና የተማሪ ቤተሰቦች በትግስት እንዲጠብቁ አሳስቧል። @FDRE_MOE @FDRE_MOE

የቀጠለ ነገር ግን ከዩኒቨርሲቲዎች ጋር በመነጋገር በ43 የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች 152 ሺ 14 ተማሪዎች እንዲመደቡ መደረጉና ይህም ከአምናው የቅበላ አቅም ጋር ሲነፃፀር ከፍ ያለ መሆኑን አብራርተዋል። ፀጥታ ችግር ያጋጠማቸው አከባቢዎች በተመለከተ የተለየ መቁረጫ ነጥብ ለመወሰን የሚያስገድድ የውጤት ትንተና ስላልተገኘ በበመደበኛው የመቁረጫ ነጥብ ተስተናግደዋል ብለዋል። ባለፈው አመት በ47 ዩኒቨርሲቲዎች 147 ሺ ተማሪዎች ምደባ የተደረገ ሲሆን ዘንድሮ በ43 ዩኒቨርሲቲዎች 152ሺ 014 ተማሪዎች እንዲመደቡ ተደርጓል።

የትምህርት ሚኒስቴር ከ12ኛ ክፍል የመልቀቂያ ውጤት እና ከዩኒቨርሲቲ መግቢያ መቁረጫ ነጥብ ጋር በተያያዘ ተጨማሪ ማብራሪያ ሰጥቷል። ------------------------ የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ
+2
የትምህርት ሚኒስቴር ከ12ኛ ክፍል የመልቀቂያ ውጤት እና ከዩኒቨርሲቲ መግቢያ መቁረጫ ነጥብ ጋር በተያያዘ ተጨማሪ ማብራሪያ ሰጥቷል። ------------------------ የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ሳሙኤል ክፍል (ፒ ኤች ዲ) ከ12ኛ ክፍል የፈተና ውጤት እና የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ነጥብ ጋር ተያይዞ ለጋዜጠኞች ማብራሪያ ሰጥተዋል። ሚኒስትር ዴኤታው የ12ኛ ክፍል ፈተና በሁለት ዙር እንዲሰጥ መደረጉንና በመጀመሪያው ዙር የስነ-ዜጋና ስነ ምግባር ትምህርት ከፈተናው ቀን ቀድሞ በመውጣቱና የውጤት ግሽበት በመምጣቱ እንዲሰረዝ መደረጉን ተናግረዋል። በመጀመሪያ ዙር ፈተና ከወሰዱት ተማሪዎች ውስጥ ከግማሽ በላይ የሚሆኑት 50 ከመቶና በላይ ውጤት ማስመዝገባቸውን የተናገሩት ሚኒስትር ዴኤታው በመጀመሪያው ዙር ፈተና ከወሠዱት 544ሺ 682 ተማሪዎች ውስጥ 44 ከመቶዎቹ 50 ከመቶ እና ከዚያ በላይ ውጤት ማስመዝገባቸውን አብራርተዋል። በሁለተኛው ዙር ከተፈተኑት 53ሺ 997 ተማሪዎች ውስጥ 28 ከመቶዎቹ ወደ መንግስት ዩኒቨርሲቲዎች የሚመደቡ ሲሆን ከመጀመሪያው ዙር 554 ሺ 682 ተፈታኞች ውስጥ ደግሞ 25 ከመቶዎቹ ይመደባሉ ብለዋል። የ 10 ክፍል የማትሪክ ፈተና በመቅረቱ ምክንያት በጣም ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ተማሪዎች በዘንድሮው አመት የ12ኛ ክፍል ፈተናን ወስደዋል ያሉት ሚኒስትር ዴኤታው አራት ዩኒቨርሲቲዎቻችን መቀበል በማይችሉበት ሁኔታ ከአምናው የተሻለ ቁጥር ያለው ተማሪ ወደ መንግስት ዩኒቨርሲቲዎች እንዲመደቡ መደረጉን አብራርተዋል። በትግራይ ያሉ አራት ዩኒቨርሲቲዎች ይማሩ የነበሩ ተማሪዎች ወደ ሌሎች ዩኒቨርሲቲዎች መመደባቸውና ዘንድሮም ይመደቡ የነበሩ ተማሪዎች ወደ ሌሎች ዩኒቨርሲቲዎች እንዲመደቡ መደረጉ 48ሺ ተማሪ የቅበላ አቅም አጥተናል ብለዋል።

ከ20ሺህ በላይ የተማሪዎች ቅሬታዎች ላይ ምላሽ መሰጠቱን የፈተናዎች ኤጀንሲ አስታወቀ፡፡ --------------------------------------------- የፈተናዎች አገልግሎት ምክትል ዋና ዳ
+2
ከ20ሺህ በላይ የተማሪዎች ቅሬታዎች ላይ ምላሽ መሰጠቱን የፈተናዎች ኤጀንሲ አስታወቀ፡፡ --------------------------------------------- የፈተናዎች አገልግሎት ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ተፈራ ፈይሳ ከፈተና እርማት እና ቅሬታዎች ጋር በተያያዘ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡ ም/ዋ/ዳይሬክተሩ በመግለጫቸው የፈተናው እርማት ከሰው ንክኪ ነፃ በሆነ መልኩ በጥንቃቄ የተከናወነ ቢሆንም በሁለተኛው ዙር ፈተና እርማት ላይ የቴክኒክ ችግር ማጋጠሙን እና እርማት መደረጉን ገልፀዋል፡፡ የእርማት ችግሩ የተፈጠረው በ 559 ባልበለጡ ተማሪዎች ላይ እንደሆነ እና ዳግም ምልከታ ተደርጎ መሰተካከል እንደተደረገም ጨምረው ገልፀዋል፡፡ የፈተና እርማት ችግር ማጋጠሙ የተገኘውም የፈተናዎች አገልግሎት ባደረገው ምርመራ እንደሆነም ተናግረዋል፡፡ ቅሬታዎችን በተመለከተም ተማሪዎች ሳይጉላሉ ባሉበት ቦታ ሆነው ቅሬታቸውን ለመፍታት የ ሚያስችል ስርዕት ተዘርግቶ መሰራቱን ገልፀዋል፡፡ በስርዓቱም ከ 20ሺህ በላይ ተማሪዎች ቅሬታቸውን አቅርበው ምላሽ መሰጠቱንም ነው የተናገሩት፡፡ በተደጋጋሚ የሚነሱ የፆታ እና የስም ስህተቶች በትምህርት ቤቶች አካባቢ የተፈጠረ ክፍተት እንጂ የፈተናዎች አገልግሎት ክፍተት አለመሆኑን ም/ዋ/ዳይሬክተሩ ገልፀዋል፡፡ በዘንድሮው አመት የተፈታኝ ተማሪዎች መብዛት እና በአገራችን ውስጥ ካሉት 47 ከፍተኛ ት/ት ተቋማት ውስጥ አሁን 43 ቱ ከፍተኛ የት/ት ተቋማት ብቻ የሚቀበሉ ስለሆነ ይህም የዩኒቨርስቲ ቅበላ አቅም አነስተኛ እንዲሆን በማድረጉ መግቢያ ነጥቡን ከፍ እንዳደረገውም ተገልጿል፡፡ በዚህም ምክኒያት በዘንድሮው አመት ፈተናውን ከወሰዱት ውስጥ 25 ፐርሰንት ተማሪዎች ወደ ዩኒቨርስቲ እንደሚገቡ ተነግሯል፡፡ 👇 @FDRE_MOE @FDRE_MOE

የ2013ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ፈተና የውጤት አያያዝ እና የማለፍያ ነጥብን በተመለከተ የ2013ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና በሁለት ዙር መሰጠቱ የሚታወስ ሲሆን የውጤት አያያዝ እና የማለፊያ ነጥ
+1
የ2013ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ፈተና የውጤት አያያዝ እና የማለፍያ ነጥብን በተመለከተ የ2013ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና በሁለት ዙር መሰጠቱ የሚታወስ ሲሆን የውጤት አያያዝ እና የማለፊያ ነጥብም እንደየዙሩ የተለያየ ነው። በመጀመሪያው ዙር ተፈታኞች የሲቪክስ ትምህርት ፈተና ውጤት ያልተያዘ ሲሆን ለከፍተኛ ትምህርት መግቢያ ውጤት 50% እና ከዚያ በላይ ነው።በዚህም መሰረት ለመጀመሪያ ዙር ተፈታኞች ▪️ለተፈጥሮ ሳይንስ ከ 600 ▪️ለማህበራዊ ሳይንስ ከ 500 ▪️ለአይነ ስውራን ተፈታኞች ከ 400 የተያዘ ሲሆን ለሁለተኛ ዙር ተፈታኞች ▪️ለተፈጥሮ ሳይንስ ከ 700 ▪️ለማህበራዊ ሳይንስ ከ 600 ▪️ለአይነ ስውራን ተፈታኞች ከ 500 ባስመዘገቡት ውጤት መሰረት ተይዟል በአጠቃላይ በሁለት ዙር በተሰጠው ፈተና በተፈጥሮ ሳይንስ እና ማህበራዊ ሳይንስ የውጤት አያያዝ እና የማለፍያ ነጥብን ከተያያዘው ምስል ላይ ይመልከቱ። 👉ሌሎች መረጃዎችን ለማየት ይህንን ሊንክ ይጫኑት 👇 @FDRE_MOE @FDRE_MOE

የ2013ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ፈተና ማለፊያ ነጥብ ይፋ ሆነ። የትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስቴር ዴኤታ ሳሙኤል (ዶ/ር) ለጋዜጠኞች የ12ኛ ክፍል መለቀቂያ ፈተና መቁረጫ ነጥብ ዙሪያ መግለጫ ሰጥተዋል። በሁለት ዙር ለተሰጠው የመልቀቂያ ፈተና የተሰጠው የማለፊያ ነጥብ የተለያየ መሆኑ የተገለፀ ሲሆን በዚህም መሰረት በመጀመሪያ ዙር ፈተናቸውን የወሰዱ የተፈጥሮ ሳይንስ እና የማህበራዊ ሳይንስ መደበኛ ተፈታኞች ውጤት የሚከተለውን ይመስላል በመንግስት ዩኒቨርስቲዎች ለመማር ለተፈጥሮ ሳይንስ መደበኛ ተፈታኞት ማለፊያ ነጥብ ለወንድ 363 ለሴት 351 ሲሆን በተፈጥሮ ሳይንስ በታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢዎች ላሉ መደበኛ ተፈታኞች ለወንድ 351 ለሴት 339 ማለፊያ ነጥብ መሆኑ ተገልጿል።ለተፈጥሮ ሳይንስ መስማት ለተሳናቸው ሁለቱም ፆታ የማለፊያ ነጥብ 300 ሆኗል።በተፈጥሮ ሳይንስ ድጋሜ ተፈታኞች ማለፊያ ነጥብም 380 ሆኖ መቆረጡ ተገልጿል። በመጀመሪያው ዙር የተፈተኑ እና በግል የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ትምህርታቸውን ለመከታተል የተፈጥሮ ሳይንስ መቁረጫ ነጥብ 300 ሆኗል። ለማህበራዊ ሳይንስ መደበኛ ተፈታኞች የማለፊያ ነጥብ ለወንድ 264፣ ለሴት 254 ሲሆን በማህበራዊ ሳይንስ በታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢዎች ላሉ መደበኛ ተፈታኞች ለወንድ 254፣ ለሴት 250 ማለፊያ ነጥብ ሆኖ ተቆርጧል። ለማህበራዊ ሳይንስ መስማት ለተሳናቸው ሁለቱም ፆታዎች ማለፊያ ነጥብ 250 መሆኑን እና በማህበራዊ ሳይንስ ድጋሜ ተፈታኞች ለሁለቱም ፆታ የማለፊያ ነጥብ 280 እንደሆነ ተገልጿል። በግል የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ትምህርታቸውን ለመከታተል የማህበራዊ ሳይንስ መቁረጫ ነጥብ 250 ሆኗል። በሁለተኛ ዙር ፈተናቸውን የወሰዱ የተፈጥሮ ሳይንስ እና የማህበራዊ ሳይንስ መደበኛ ተፈታኞች ውጤትም ይፋ የሆነ ሲሆን በዚህም መሰረት በመንግስት ዩኒቨርስቲዎች ለመማር ለተፈጥሮ ሳይንስ መደበኛ ተፈታኞት ማለፊያ ነጥብ ለወንድ 423 ለሴት 409 ሲሆን በተፈጥሮ ሳይንስ በታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢዎች ላሉ መደበኛ ተፈታኞች ለወንድ 410 ለሴት 396 ማለፊያ ነጥብ መሆኑ ተገልጿል።ለተፈጥሮ ሳይንስ መስማት ለተሳናቸው ሁለቱም ፆታ የማለፊያ ነጥብ 350 ሆኗል።በተፈጥሮ ሳይንስ ድጋሜ ተፈታኞች ማለፊያ ነጥብም 443 ሆኖ መቆረጡ ተገልጿል። በሁለተኛ ዙር የተፈተኑ እና በግል የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ትምህርታቸውን ለመከታተል የተፈጥሮ ሳይንስ መቁረጫ ነጥብ ከ350 በላይ መሆኑ ተነግሯል። ለማህበራዊ ሳይንስ መደበኛ ተፈታኞች የማለፊያ ነጥብ ለወንድ 317 ፣ ለሴት 305 ሲሆን በማህበራዊ ሳይንስ በታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢዎች ላሉ መደበኛ ተፈታኞች ለወንድ 305፣ ለሴት 300 ማለፊያ ነጥብ ሆኖ ተቆርጧል። ለማህበራዊ ሳይንስ መስማት ለተሳናቸው ሁለቱም ፆታዎች ማለፊያ ነጥብ 300 መሆኑን እና በማህበራዊ ሳይንስ ድጋሜ ተፈታኞች ለሁለቱም ፆታ የማለፊያ ነጥብ 335 እንደሆነ ተገልጿል። በግል የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ትምህርታቸውን ለመከታተል የማህበራዊ ሳይንስ መቁረጫ ነጥብ ከ 300 በላይ መሆኑም ተገለጿል። ውጤቱ ለመጀመርያ ዙር ተፈታኞች ለተፈጥሮ ሳይንስ ከ600 እዲሁም ለማህበራዊ ሳይንስ ከ500 የተያዘ መሆኑን እና በሁለተኛ ዙር ተፈታኞች ለተፈጥሮ ሳይንስ ከ700 እዲሁም ለማህበራዊ ሳይንስ ከ600 የተያዘ መሆኑ ተገልጿል። 👉ሌሎች መረጃዎችን ለማየት ይህንን ሊንክ ይጫኑት 👇 @FDRE_MOE @FDRE_MOE

Repost from N/a
በመላው ኢትዮጵያ በየቀኑ የሚለቀቁ የስራ ማስታወቂያዎች እና የስኮላር ሺፕ መረጃዎች በቴሌግራም ለማግኘት 👇👇 ይጫኑ https://t.me/+YpyTQI-cZ5EwMjlk https://t.me/+YpyTQI-cZ5EwMjlk

በ2013 ዓ.ም.ለትምህርት ሚኒስቴር ያመለከቱና እውቅና የተሰጣቸው የሃገር ውሰጥ የምርምር ጆርናሎች 👉ሌሎች መረጃዎችን ለማየት ይህንን ሊንክ ይጫኑት 👇 @FDRE_MOE @FDRE_MOE
በ2013 ዓ.ም.ለትምህርት ሚኒስቴር ያመለከቱና እውቅና የተሰጣቸው የሃገር ውሰጥ የምርምር ጆርናሎች 👉ሌሎች መረጃዎችን ለማየት ይህንን ሊንክ ይጫኑት 👇 @FDRE_MOE @FDRE_MOE

የቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሌኒየም ሕክምና ኮሌጅ በ2014 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የሕክምና ትምህርት መማር ለሚፈልጉ የመግቢያ መስፈርቶቹን አሳውቋል። ለማመልከት የሚያስፈልጉ መስፈርቶች፦ • በ2014
የቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሌኒየም ሕክምና ኮሌጅ በ2014 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የሕክምና ትምህርት መማር ለሚፈልጉ የመግቢያ መስፈርቶቹን አሳውቋል። ለማመልከት የሚያስፈልጉ መስፈርቶች፦ • በ2014 ዓ.ም በመደበኛ ትምህርት ፕሮግራም 12ኛ ክፍል ትምህርት ያጠናቀቀ/ያጠናቀቀች፣ • በኢትዮጵያ የከፍተኛ ትምህርት መግቢያ ፈተና ሲቪክስ ውጤት ለተያዘላቸዉ ከ700 ያገኙትን ወደ 600 ከቀየሩ በኋላ እንዲሁም ሲቪክስ ውጤት ያልተያዘላቸው የሲቪክስ ውጤቱን ቀንሰው በሚያገኙትን ውጤት መሠረት ከስር ከተዘረዘሩት ክልሎች እና ዞኖች ውጪ ያሉ ሁሉም ክልሎች፦ ➢ ለወንድ 475 እና ከዚያ በላይ ውጤት ያለው፣ ➢ ለሴት 460 እና ከዚያ በላይ ውጤት ያላት፣ • ለአፋር ክልል፣ ለቦረና ዞን (ኦሮሚያ ክልል)፣ ለቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል፣ ለጋምቤላ ክልል፣ ለሱማሌ ክልል፣ ለደቡብ ኦሞ ዞን(ደቡብ ክልል)፣ ለዋግ እምራ ዞን ( አማራ ክልል) እና ለምዕራብ ኦሞ ዞን (ደቡብ ክልል) ፦ ➢ ለወንድ 450 እና ከዚያ በላይ ውጤት ያለው ➢ ለሴት 440 እና ከዚያ በላይ ውጤት ያላት • ከ9ኛ-12ኛ ክፍል አማካይ የትራንስክሪፕት ውጤት 80 ከመቶ እና ከዚያ በላይ የሆነ ማመልከት የሚቻለው ከመጋቢት 05 እስከ 11/2014 ዓ.ም ድረስ በኦንላይን ብቻ መሆኑ ተገልጿል። ለተጨማሪ ዝርዝር መረጃ የኮሌጁን ድረ-ገጽ á‹­áŒ á‰€áˆ™ www.sphmmc.edu.et/ á‹ˆá‹­áˆ ለኮሌጁ ሬጅስራር ቢሮ ይደውሉ +251 118 96 5125 👉ሌሎች መረጃዎችን ለማየት ይህንን ሊንክ ይጫኑት 👇 @FDRE_MOE @FDRE_MOE

የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በኢትዮጵያ ከፊላንድ አምባሳደር ሆሎፔነን ኦቲ ጋር ተወያዩ። --------------------------------------------- ሚኒስትሩ የፊንላንድ መ
+2
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በኢትዮጵያ ከፊላንድ አምባሳደር ሆሎፔነን ኦቲ ጋር ተወያዩ። --------------------------------------------- ሚኒስትሩ የፊንላንድ መንግስት በትምህርት ጥራት ማረጋገጫ ፕሮግራም እና በልዩ ፍላጎት አካታች ትምህርት ላይ እያደረገ ላለው ድጋፍ ምስጋና እውን አቅርበዋል። የኢትዮጵያ የትምህርት ጥራት በሚፈለገው ደረጃ ላይ ባለመድረሱ ጠንካራ ስራ መስራት እንደሚጠይቅ የጠቀሱት ሚኒስትሩ በጦርነት የወደሙ ትምህርት ቤቶችን በተሻለ እና ደረጃውን በጠበቀ ዲዛይን ለመገንባት እንደታቀደና በዲዛይኑ ፅንሰ ሃሳብ ዙሪያም ገለፃ አድርገዋል። በኢትዮጵያ የፊንላድ አምባሳደር ሆሎፔነን ኦቲ በበኩላቸው አገራቸው የትምህርት ቤት ምገባ ፕሮግራም በመዘርጋቷ የትምህርት ጥራት እንዲኖርና የትምህርት ስርዓቱ ውጤታማ እንዲሆን ትልቅ እገዛ እንዳደረገ ገልፀዋል። በሁለቱ ሀገራት መካከል በሚደረጉ የሁለትዮሽ ትብብር ስራዎች በዋናነት የትምህርት ፍትሃዊነት እና አካታችነት ትኩረት የሚሰጥባቸው ተግባራት ሲሆኑ የመምህራን ስልጠናን እንደሚያካትትም አብራርተዋል። የትምህርት ቤቶች ምገባን ለማጠናከርና ለአደጋ ጊዜ ትምህርት ፕሮግራም የሚውል 3 ሚሊዮን ዩሮ እርዳታ መሰጠቱን ገልጸዋል። በቀጣይ በቅርብ በሚዘጋጀው የሁለትዮሽ ትብብር ስምምነት ሰነድ ላይ የትምህርት ዘርፉ የጥራት ሪፎርም ስራዎች ትኩረት ይሰጣቸዋል ተብሏል። ___ ለተጨማሪ መረጃዎች ይቀላቀሉን 👇 @FDRE_MOE @FDRE_MOE

" የ2014 ዓ.ም የከፍተኛ ትምህርት መግቢያ ፈተና መስጫ ቀን አልተቆረጠም " - የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት በተያዘዉ የ2014 ዓ.ም 12ኛ ክፍል ለሚማሩ ተማሪዎች “የከፍተኛ ትምህርት
" የ2014 ዓ.ም የከፍተኛ ትምህርት መግቢያ ፈተና መስጫ ቀን አልተቆረጠም " - የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት በተያዘዉ የ2014 ዓ.ም 12ኛ ክፍል ለሚማሩ ተማሪዎች “የከፍተኛ ትምህርት መግቢያ ፈተና ከግንቦት 22 - 25/ 2014 ዓ.ም ይሰጣል” የሚል መረጃ በማህበራዊ ትስስር ገጾች እየተጋራ የገኛል። የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ባለሙያ የሆኑት አቶ ቤከማ ስለሺ " የ2014 /ፈተና/ መቼ እንደሚሰጥ አልታወቀም። ቀኑ አልተቆረጠም፤ ስለ ፈተናዉ ቀንም የተባለ ነገር የለም” ብለዋል። በማህበራዊ ትስስር ገጾች እየተዘዋወረ ያለዉ (ፈተናዉ ከግንቦት 22 - 25/ 2014 ዓ.ም ይሰጣል) የሚለዉ መረጃም በተቋሙ እዉቅና እንደሌለዉ ተናግረዋል። “ፈተና የሚሰጥበት ቀን ሲቆረጥና ሲታወቅ በሚዲያዎች መግለጫ ይሰጣል” ብዋል አቶ ቤከማ ስለሺ። ___ ለተጨማሪ መረጃዎች ይቀላቀሉን 👇 @FDRE_MOE @FDRE_MOE

+4
ከላይ ያሉት ፋይሎች ናቸው ድንገት ኔትወርክ ካስቸገራችሁ ከእነዚህ ተጠቀሙ😊 ___ ለተጨማሪ መረጃዎች ይቀላቀሉን 👇 @FDRE_MOE @FDRE_MOE