en
Feedback
FDRE Defense Force -የኢፌዴሪ መከላከያ ሰራዊት

FDRE Defense Force -የኢፌዴሪ መከላከያ ሰራዊት

Open in Telegram

FDRE Defence Force የኢፌዴሪ መከላከያ ሰራዊት # ቁልፍ_እሴቶች 1, ከራስ በፊት ለህዝብና ለሀገር ጥቅም፣ 2, ምንጊዜም የተሟላ ስብዕና፣ 3, ያልተሸራረፈ ዲሞክራሲያዊ አስተሳሰብ፣ 4, በማንኛውም ግዳጅ ወይም ተግባር የላቀ ውጤት። የፌስቡክ ገፃችንን ይከታተሉ https://www.facebook.com/fdredefense.official @FDRE_DEFENCE_FORCE

Show more
4 610
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
ሰኔ 22 ቀን 2014 ዓ.ም አሸባሪው የህወሃት ቡድን የመዋጋት አቅምም ሞራልም የሌላቸውን በማስገደድ ወደ ውጊያ እንደሚያስገባ እጃቸውን ለምዕራብ ዕዝ የሰጡ ወዶ ገቦች ተናገሩ። ወዶ ገቦቹ እንደሚሉት የሽብር ቡድኑ ከ13 ዓመት ጀምሮ ያሉ ህፃናቶችን እና አዛውንቶችን ጭምር በማስገደድ አጭር ስልጠና ሠጥቶ ወደ ጦርነት እንደሚማግድና ወደ ኋላ የሚመለስ ከጀርባው እንደሚመታ ገልፀዋል። ማዕሾ ገ/ሄር የሰባት ልጆች አባትና የ60 ዓመት ሽማግሌ ሲሆኑ በማላውቀውና በደካማ ጉልበቴ ትግራይን ነፃ አውጣ ተብዬ በግዴታ ወደ ጦርነት አስገብተውኝ የእርጅና ዘመኔን ፀጋነት ቀምተው መከራ አድርሰውብኛል ይላሉ። ልጆቼ የት እንዳሉና እንዴት እንደሚኖሩ አላውቅም የሚሉት የ60 ዓመቱ አዛውንት ትግራይ ከተቀሩት ኢትዮጵያዊያን ጋር ለምን ጦርነት ውስጥ ትገባለች ተስማምተን ለምን አንኖርም የሚል ሃሳብ የሚያቀርቡ አባላት በርካታ መከራዎችን ይቀበላሉ ብለዋል። ህወሃቶች አስገድደው ወደ ጦርነት የሚያስገቡትን ሠው በፈጠራ እና በሀሰት ፕሮፖጋንዳ እንደ ህዝብ ሊያጠፉን የሚያስቡ ሃይሎችን ነው የምንዋጋው ይላሉ ያሉት አዛውንቱ እኛ የተለየን ጀግኖች ነን እያሉም በመስበክ ወጣቱን በጦርነት አስጨርሰውታል ብለዋል። ኢትዮጵያን አፍርሰን ታላቋን ትግራይን እንፈጥራለን የሚሉን የህወሃት መሪዎች በጦርነቱ የደረሰባቸውን ሽንፈት ለመደበቅ አዲስ አበባ ሳንገባ የተመለስነው የውጭ መንግስት ተመለሱ ብሎን ነው በማለት ህዝቡን ለሌላ እልቂት ይቀሰቅሡታል ብለዋል። የህወሃት መሪዎች እጃችሁን ለመከላከያ ከሰጣችሁ ቆራርጠው ነው የሚገድሏችሁ። እጃችሁን ከምትሰጡ እራሳችሁን ብታጠፉ ነው የሚሻላችሁ ይሉናል። እኛ ግን እጃችንን ለመከላከያ ስንሰጥ አሸባሪው ቡድን እንዳለው ሳይሆን ደስ በሚልና በተለየ እንክብካቤ ተቀብሎናል ብለዋል። ታገል አልማው ፎቶግራፍ ሽመል እሸቱ @FDER_DEFENCE_FORCE

ሰኔ 22 ቀን 2014 ዓ.ም የመከላከያ መሃንዲስ ዋና መምሪያ ከግልገል በለስ እስከ አባይ ግድብ የሚደርሠውን መንገድ ስራ አጠናቆ አስመረቀ። ዋና መምሪያው 210 ኪ.ሜ ርዝማኔ ያለውን 3ኛ ደረጃ የጠ
+2
ሰኔ 22 ቀን 2014 ዓ.ም የመከላከያ መሃንዲስ ዋና መምሪያ ከግልገል በለስ እስከ አባይ ግድብ የሚደርሠውን መንገድ ስራ አጠናቆ አስመረቀ። ዋና መምሪያው 210 ኪ.ሜ ርዝማኔ ያለውን 3ኛ ደረጃ የጠጠር መንገድ ወደ ከፍተኛ ደረጃ የጠጠር መንገድ በማሳደግ በተቀመጠለት የግዜ ሠሌዳ  አጠናቆ አስመርቋል በምረቃ በስነ-ስረዓቱ ላይ በክብር እንግድነት በመገኘት መንገዱን መርቀው የከፈቱት የመከላከያ መሃንዲስ ዋና መምሪያ ሃላፊ ሌ/ጀኔራል ደስታ አብቼ እና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሃይል ባለስልጣን ዋና ስራ አስፈፃሚ ተወካይ አቶ በላቸው ካሳ ናቸው። ሌ/ጀኔራል ደስታ አብቼ በዕለቱ ባደረጉት ንግግር የመከላከያ መሃንዲስ ዋና መምሪያ የግልገል በለስ-አባይ ግድብ የመንገድ ፕሮጀክትን ስራ ሲረከብ የተሠጠው የመንገድ ፕሮጀክት ስራ ብቻ ሳይሆን ታላቅ ሃገራዊ ሃላፊነትና አደራም ጭምር ነበር ብለዋል። ለታላቁ የህዳሴ ግድብ ግንባታ የሚውሉ ግብዓቶች ሲጓጓዙ በመንገድ ላይ እስከ ሁለት ሳምንት ይቆዩ እንደነበር አስታውሰው የመሃንዲስ ክፍሉ ባከናወነው መንገድ የማሻሻል ጥገና ስራ የግድቡ የግንባታ ግብዓቶች በአንድ ቀን ለመድረስ ይችላሉ ብለዋል። በዚሁ የምረቃ ስነ-ስረዓት ላይ የአካባቢው መስተዳደር አካላት፣ የሠራዊቱ ከፍተኛ አመራሮች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል። ሲሳይ ደመቀ ፎቶግራፍ ክበበው ቶሎሳ @FDRE_DEFENCE_FORCE

ሰኔ 21 ቀን 2014 ዓ.ም የመከላከያ እጅ ኳስ ቡድን ኮልፌ ክ/ከተማን 44 ለ 32 በሆነ ውጤት አሸነፈ። በኢትዮጵያ እጅ ኳስ ፕሪሜየር ሊግ የመጨረሻ ዙር ውድድር በአዲስ አበባ ትንሹ ስታድየም የተ
+2
ሰኔ 21 ቀን 2014 ዓ.ም የመከላከያ እጅ ኳስ ቡድን ኮልፌ ክ/ከተማን 44 ለ 32 በሆነ ውጤት አሸነፈ። በኢትዮጵያ እጅ ኳስ ፕሪሜየር ሊግ የመጨረሻ ዙር ውድድር በአዲስ አበባ ትንሹ ስታድየም የተጀመረ ሲሆን ዛሬ በተካሄደው ጨዋታ የመከላከያ እጅ ኳስ ቡድን ኮልፌ ክፍለ ከተማን በማሸነፍ ለዋንጫ የሚያደርገውን ግስጋሴ አሳምሯል። የእጅ ኳስ ፕሪሜየር ሊጉ ሊጠናቀቅ ሁለት ጨዋታ ብቻ የቀረው ሲሆን የመከላከያ እጅ ኳስ ቡድን እስካሁን ካደረጋቸው 16 ጨዋታዎች 14ቱን አሸንፎ 2 ተሸንፎ ከመሪው ቂርቆስ ክ/ከተማ ጋር ለዋንጫ እየተፎካከረ ይገኛል። ገረመው ጨሬ ፎቶግራፍ ገረመው ጨሬ @FDRE_DEFENCE_FORCE

ሰኔ 21 ቀን 2014 ዓ.ም በምስራቅ ዕዝ የሚገኙ ሴት የሠራዊት አባላትና ሲቪል ሰራተኞች በሀገራችን የሚቃጣ ማንኛውንም ጥቃት ለመመከት ዝግጁ መሆናቸው ተገለፀ። የምስራቅ ዕዝ ሴቶች ጉዳይ ኃላፊ ኮ/
+3
ሰኔ 21 ቀን 2014 ዓ.ም በምስራቅ ዕዝ የሚገኙ ሴት የሠራዊት አባላትና ሲቪል ሰራተኞች በሀገራችን የሚቃጣ ማንኛውንም ጥቃት ለመመከት ዝግጁ መሆናቸው ተገለፀ። የምስራቅ ዕዝ ሴቶች ጉዳይ ኃላፊ ኮ/ል ፅጌ ፈረደ እንደተናገሩት በዕዙ የሚገኙ ሴት የሠራዊት አባላት እና ሲቪል ሰራተኞች የአሸባሪውን ህወሃት ወረራ ለመመከት ያደረጉት ተጋድሎ እና የነበራቸው የደጀንነት ሚና ከፍተኛ ነው። ኃላፊዋ አክለውም በህልውና ዘመቻ ወቅት ሴት ወታደሮች በአውደ ውጊያዎች ላይ በተለያዩ ድጋፍ ሰጪነትና በተዋጊነት በመሳተፍ ጉልህ ድርሻ ማበርከታቸውን ገልፀው ሲቪል ሴት ሠራተኞችም የማይተካ የደጀንነት ሚናቸውን ተወጥተዋል ብለዋል። በምስራቅ ዕዝ የሚገኙ ሴት የሠራዊት አባላት እና ሲቪል ሠራተኞች ካለፉት የህልውና ዘመቻዎች ያገኙትን ልምድና ተሞክሮዎች አዳብረው በቀጣይ ለሚኖሩ ግዳጆች ዝግጁ ናቸውም ብለዋል። ሰመረ እሸቱ ፎቶግራፍ ሰመረ እሸቱ @FDRE_DEFENCE_FORCE

ሰኔ 21 ቀን 2014 ዓ.ም ከመከላከያ ህዝብ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት በወቅታዊ የፀጥታ ጉዳዮች ዙሪያ የተሰጠ ማብራሪያ ሰሞኑን በሱዳን ሰራዊት ቃል አቀባይ የተሰጠውን የተሳሳተ መግለጫ በማስመልከት የመከላከያ ህዝብ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ኮሎኔል ጌትነት አዳነ ማብራሪያ ሰጥተዋል። ከፍተኛ መኮነኑ ድርጊቱን በማስመልከት በመከላከያ ጠቅላይ መምሪያ ለጋዜጠኞች በሰጡት ማብራሪያ ኢትዮጵያ ከሱዳን ህዝብ እና መንግሥት ጋር ያላት መልካም ግንኙነት ረጅም አመታትን ያስቆጠረ ከመሆኑም ባሻገር የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ታሪካዊ በሆነው የሱዳን የአብዬ የሰላም ማስከበር ተልእኮ በሡዳንና በደቡብ ሡዳን ሀገሮች የተመረጠ በመሆኑ በአለም የሰላም ማስከበር ተልዕኮ ላይ ታማኝነቱ ይበልጥ ጎልቶ እንድታይ አድርጎታል። ይሁን እንጅ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የሱዳን መንግሥት ከሽበርተኛው የህወሀት ቡድን ጋር በተናበበ መልኩ የሱዳን ወታደሮች የኢትዮጵያን ድንበር አልፈው እስከ መውረር የዘለቀ የሁለቱን ህዝቦች የእርስ በእርስ ግንኙነት የማይመጥን ተግባር ከመፈፀሙ በላይ ፀብ አጫሪ መግለጫ ሰጥቷል። ዛሬም ድረስ የሱዳን ወታደሮች የኢትዮጵያን ድንበር አልፈው በመግባት ለሰው ህይወት መጥፋት ምክንያት ቢሆኑም በቀጠናው ለደረሰው የሰው ህይወት መጥፋት የተሰማንን ሀዘን እየገለፅን የመከላከያ ሰራዊታችን ግዳጁን በህግና በደንብ የሚወጣ ጀግና መሆኑ እየታወቀ የሠራዊቱን ስም በሀሠት የሚያጠለሹ አካላት ከድርጊታቸው ሊታቀቡ ይገባል። በሠራዊታችን ላይ የሚነዛ የሀሠት ፕሮፖጋንዳን በማስመልከት እውነቱን ለማወቅ አጣራለሁ ለሚል ማንኛውም አካል በትብብር ለመስራት ዝግጁ መሆናችንን እንገልፃለን። በተጨማሪም መንግስታችን ከሱዳን ጋር ያለውን የቀጠና ውጥረት በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት የሚያደርገውን ጥረት እያደነቅን ሰራዊታችን አሁንም ቢሆን ትእዛዝ ከተሰጠው እንደ ሽፍታ ሳይሆን በመደበኛ ውጊያ በአጭር ጊዜ ውስጥ ለማስወጣት በሙሉ ቁመና ላይ ይገኛል ። ፍቅሩ ከበደ ፎቶግራፍ እፀገነት ደቢሳ @FDRE_DEFENCE_FORCE

ሰኔ 20 ቀን 2014 ዓ.ም ከኢ.ፌ.ዴ.ሪ የፀጥታ እና ደህንነት የጋራ ግብረ ኃይል የተሰጠ መግለጫ፡- በቅርቡ የጋምቤላ ነፃነት ግንባር (ጋነግ)፣ የጉሙዝ ሕዝቦች ዴሞክራሲያዊ ንቅንቄ (ጉህዴን) እና የኦነግ-ሸኔ አሸባሪዎች ተደራጅተውና ተቀናጅተው በጋምቤላ ክልል በጋምቤላ ከተማና አካባቢው እንዲሁም በጊምቢና ደምቢ ዶሎ ከተማ ጥቃት ለመፈፀም ሙከራ አድርገው የኢ.ፌ.ዲ.ሪ የፀጥታ እና ደህንነት የጋራ ግብረ ኃይል ከአካባቢው ህብረተሰብ ጋር በመቀናጀት በወሰዱት እርምጃ የሽብር ቡድኖቹ በከፍተኛ ደረጃ እየተደመሰሱና ተፈጥሮ የነበረውም ችግር ተወግዶ አካባቢው ወደ ሰላማዊ እንቅስቃሴ እንዲመለስ ተደርጓል። ይሁን እንጂ የሽብር ቡድኖቹ በምዕራብ ወለጋ ዞን ጊንቢ ከተማ አካባቢ የሚገኝ ቶሌ ቀበሌ ላይ ሰላማዊ በሆኑና ምንም በማያውቁ ንፁሃን ህፃናትና ሲቪሊያን ላይ ጉዳት ማድረሳቸውና በርካቶችንም መግደላቸው ይታወሳል። ወያኔ ሀገር የማፍረስ እኩይ ዓላማውን በጦርነት ማሳካት ስላልቻለ በየቦታው ባደራጃቸውና ባስታጠቃቸው ተላላኪ ቡድኖች አማካኝነት የጅምላ ግድያ በተልዕኮ እየፈፀመና እያስፈፀመ ይገኛል። የዚህ ድርጊት ዋና ዓላማም ህዝብ በመንግስት ላይ ተስፋ ቆርጦ እንዲነሳና ሰላም እንዲደፈርስ ለማድረግ ነው። የሽብር ኃይሎችን በሁሉም አካባቢ የመቆጣጠር እና ህግ ማስከበር ስራ እየተሰራ ባለበት በዚህ ወቅት አንድ መሆንና አሸባሪዎችን በጋራ መፋለም ሲገባን በተለያየ ውዥንብርና ከፋፋይ ሂደት ውስጥ መግባት በፍፁም አይኖርብንም። በተለይ በአሸባሪው ህዋሓት ጁንታ ቡድን ፋይናንስ የተደረጉ ሚዲያዎችን በመጠቀምና እኩይ ዓላማቸውን ለማስፈፀም የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን ሰላማዊ የመማር ማስተማር ሂደት ለማደናቀፍ ተማሪዎችን በብሄርና በሀይማኖት በመከፋፈል ግጭት እንዲፈጠር ለማነሳሳት ሌት ተቀን አሸባሪዎች እየሰሩ መሆናቸውን የጋራ ግብረ ኃይሉ ደርሶበታል። ይህ በእንዲህ እንዳለ የጠላትን ሴራና አካሄድ ጠንቅቀን ካልተረዳንና እነርሱ በከፈቱልን ቦይና ወጥመድ ውስጥ የምንገባ ከሆነ ለውስጥና ለውጭ ጠላቶቻችንን እኩይ ሴራ በራችንን እንደከፈትን ይቆጠራል። እነዚህ በዶላር የተገዙ ሚዲያዎች ከዚህ ቀደም በጎንደር ችግር ከመፈፀሙ አስቀድመው ህዝቡን በሀይማኖት ለመከፋፈል አጀንዳ ቀርፀው ሰላም ለማደፍረስና ግጭት ለማቀጣጠል ሲሰሩ ቆይተዋል፡፡ የተፈጠረውን ግጭት በሁሉም የሀገራችን አካባቢዎች እንዲዳረስና የእምነቱን ተከታዮች ወደ ለየለት ሁከትና ብጥብጥ ለማስገባት ያልፈነቀሉት ድንጋይ አልነበረም። ሆኖም የጥፋት ተልዕኳቸው በህዝባችን የመቻቻል ባህል፣ አርቆ አስተዋይነት፣ ትዕግስት እና በፀጥታ ኃይሎቻችን ከፍተኛ ርብርብ መክሸፉ ይታወቃል። ‘’ጅራፍ ራሱ ገርፎ ራሱ ይጮሃል እንዲሉ’’ እነዚህ ሚዲያዎች ሰሞኑን እንደለመዱት ግጭት ለመቀስቀስ በዩኒቨርሲቲዎች ላይ ያነጣጠረ ግጭት ለማስነሳት «በአማራ ክልል ዩኒቨርስቲዎች የሚማሩ የኦሮሞ እና የሌሎች ብሄር ተማሪዎችን ለማጥቃት የተደራጀ የደህንነት ቡድን ወደ አማራ ክልል ተልኳል» የሚል መልዕክት አስተላልፈዋል። የኢ.ፌ.ዲ.ሪ የፀጥታ እና ደህንነት የጋራ ግብረ ኃይሉ ከራሱ በፊት ለህዝብና ለሀገር ህይወቱን እየሰዋ የህዝብን ሰላምና ደህንነት የሚጠብቅ ኃይል መሆኑ የሚታወቅ ሆኖ ሳለ የተፈጠረውን ክስተት ምክንያት በማድረግ በሽብርተኞች ላይ የተጀመረው ዘመቻ ተጠናክሮ እንዳይቀጥል የተለያዩ እንቅስቃሴዎች እየተደረጉ ይገኛሉ። በመሆኑም የዩኒቨርሲቲዎቹ ተማሪዎችና ማህበረሰብ የተከሰተውን ችግር ምክንያት በማድረግ ሆን ብለው ግጭት ለማነሳሳት እየተንቀሳቀሱ ያሉ የአሸባሪው ህዋሓት ጁንታ ቡድን ተላላኪዎችና ቅጥረኞች መኖራቸውን ተገንዝባችሁ ከነዚህ አሸባሪዎች ራሳችሁን በመጠበቅ አስፈላጊውን ጥንቃቄ እንድታደርጉ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ የፀጥታ እና ደህንነት የጋራ ግብረ ኃይል ያሳስባል። ሆኖም ይሄንን ማሳሰቢያ ተላልፈው ከድርጊታቸው የማይቆጠቡ አካላትን የማይታገስና ጥብቅ ህጋዊ እርምጃም ለመውሰድ የሚገደድ መሆኑን ያስታውቃል። ሰኔ 20 ቀን 2014 ዓ.ም አዲስ አበባ @FDRE_DEFENCE_FORCE

ሰኔ 18 ቀን 2014 ዓ.ም በአዲስ አበባ መቀመጫቸውን ላደረጉ የዓለም አቀፍ ተቋማትና ወታደራዊ አታሼዎች ገለጻ ተደረገ። በከፍተኛ የመንግስት ኃላፊዎችና በሰራዊቱ ከፍተኛ አመራሮች በተደረገው ገለጻ በአሸባሪው የህውሃት ቡድን አማካኝነት በሰሜኑ የሀገራችን ከፍል ያጋጠሙ ግጭቶች መነሻቸውን እና መንግስት የሀገሪቱን ሉአላዊነትን ለማስከበር ስለወሰዳቸው እርምጃዎች ሰፊ ማብራሪያ ተሰጥቷል። በዝግጅቱ ላይ በመገኘት ማብራሪያ የሰጡት የመከላከያ የሜካናይዝድ ስራዎች አስተባባሪና የወታደራዊ ጉዳዮች አማካሪ ሌ/ጀኔራል አለምሸት ደግፌ የሀገራችንን ሰላምና ልማት ለማረጋገጥ ከአለም አቀፉ ማህበረሰብ ጋር በቁርጠኝነት እየተሰራ መሆኑን ገልፀዋል። የመከላከያ ሰራዊቱም የተሰጠውን ሀገርን የመጠበቅ ተልዕኮ ለመፈፀም የሚያስችል አስተማማኝ ቁመና ላይ እንደሚገኝም ጀኔራል መኮንኑ አስረድተዋል። የመከላከያ የውጭ ግንኙነትና ወታደራዊ ትብብር ዋና ዳይሬክትሬት ጀኔራል ዳይሬክተር ሜ/ጀኔራል ተሾመ ገመቹ የህውሃት የሽብር ቡድን በሰሜን ዕዝ ላይ ጥቃት ከፈፀመ በኋላ በተወሰዱ የህግ ማስከበርና የህልውና ዘመቻዎች ላይ የመከላከያ ሰራዊቱ የአለም አቀፉን ድንጋጌዎች በጠበቀ መልኩ ግዳጁን መወጣቱን ጠቁመዋል። የሽብር ቡድኑ የአለም አቀፉን ማህበረሰብና የትግራይን ህዝብን በተከፋይ ሎቢስቶች ፣ ሚዲያዎችና በተለያዩ ድርጅቶች በመጠቀም ሲያሳስት መቆየቱንና እያሳሳተም እንደሚገኝም ጀኔራል ዳይሬክተሩ ገልፀዋል። የኢፌዴሪ የፐብሊክ ዲፕሎማሲ ዳይሬክተር ጀኔራል አቶ ዲና ሙፍቲ መንግስት ለትግራይ ህዝብ ያልተቆጠበ ሰብዓዊ ድጋፍ እንዲደርስ የተለያዩ ስራዎች እየሰራ መቆየቱና ለዚህም የመከላከያ ሰራዊቱ ሚና ከፍተኛ መሆኑ ተጠቁሟል። ያጋጠሙ ችግሮችን ለመፍታት በተደጋጋሚ የሰላም ዕድል ለመስጠት በመንግስት በኩል የተለያዩ እርምጃዎች ቢወሰዱም የሽብር ቡድኑ ወደ አጎራባች ክልሎች በመግባት ከፍተኛ ሰብአዊና ቁሳዊ ጉዳት ማድረሱንም አቶ ዲና ሙፍቲ አስረድተዋል። በዝግጅቱ ላይ መቀመጫቸውን አዲስ አበባ ያደረጉ የተለያዩ ሀገራት ወታደራዊ አታሼዎች፣ የአፍሪካ ህብረት፣ የተባበሩት መንግስታት የልማት ፕሮግራም፣ የአለም አቀፉ ቀይ መስቀልና የምስራቅ አፍሪካ የተጠንቀቅ ኃይል ተወካዮች ተገኝተዋል። ብዙአየሁ ተሾመ ፎቶግራፍ ተሰማ ኡርጌሳ @FDRE_DEFENCE_FORCE

ሰኔ 18 ቀን 2014 ዓ.ም "ሰራዊት እና ሀገር ግንባታ" የተሰኘው የ ዶ/ር ስራው ደማስ መፅሀፍ ተመረቀ። ሰራዊት እና ሀገር ግንባታ የተሰኘው መፅሀፍ በመከላከያ አዛዥነት እና ስታፍ ኮሌጅ የጥናት
+2
ሰኔ 18 ቀን 2014 ዓ.ም "ሰራዊት እና ሀገር ግንባታ" የተሰኘው የ ዶ/ር ስራው ደማስ መፅሀፍ ተመረቀ። ሰራዊት እና ሀገር ግንባታ የተሰኘው መፅሀፍ በመከላከያ አዛዥነት እና ስታፍ ኮሌጅ የጥናት እና ምርምር ትምህርት ክፍል ኃላፊ በሆኑት በ ዶ/ር ስራው ደማስ ተዘገጅቶ ዛሬ ተመርቋል። መፅሀፉ በኢትዮጵያ የዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታ የሀገር መከላከያ ሰራዊት ያለውን ሚና የሚያብራራ ነው። ዶ/ር ስራው ደማስ እንደተናገሩት ለመከላከያ ሰራዊቱ ግንባታ የተፃፈ ቢሆንም ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብ የመከላከያ ሰራዊት በሀገር ግንባታ ሂደት ያስቀመጠውን መልካም አሻራ ለማስተዋወቅ እና ለትውልዱ ታሪክ ለማስተላለፍ ታስቦ ነው። የባህር ኃይል ዋና አዛዥ ሪል አድሚራል ክንዱ ገዙ በፕሮግራሙ ላይ ተገኝተው በሰጡት አስተያየት የህውሃት ባለ ስልጣናት መከላከያን እንደምሽግና እንደ ማስፈራሪያ በመጠቀም የህዝቡንና የሰራዊቱን ግንኙነትን በማሻከር ህዝባዊ አደራቸውን በአግባቡ ሳይወጡ መቅረታቸውን እና ህዝቡ ለውትድርና ያለው አመለካከት እንዲዋዥቅ አድርጎት እንደነበር በመፅሀፉ በግልፅ መጠቀሱን አድንቀዋል። የኢትዮጲያ መከላከያ ሰራዊት ያልተነገሩ የጀግንነት እና መልካም ተግባር ለመጭው ተውልድ ተሰንዶ እንዲቆይ መፅሐፉ ትልቅ ድርሻ እንደሚያበረክትም ተገልጿል። በረከት አዳነ ፎቶግራፍ አቢዮት ዋሚ @FDRE_DEFENCE_FORCE

ሰኔ 18 ቀን 2014 ዓ.ም "በመስዋዕትነቱ ሀገርን እያስከበረ የሚገኘው ጀግናው የመከላከያ ሰራዊታችን ጋር ስገኝ እጅግ ከፍተኛ ኩራትና ክብር ይሰማኛል።" የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ክብር ሳህለወርቅ ዘውዴ የኢፌዴሪ የአየር ኃይል "ነብሮች-2014" በሚል መሪ ቃል ባስመረቃቸው የአብራሪዎች ምርቃት ላይ በክብር እንግድነት የተገኙት የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ክብርት ሳህለወርቅ ዘውዴ ለተመራቂዎች የእንኳን ደስ ያላችሁ መልዕክት አስተላልፈው የሀገር ኩራት በሆነው ጀግናው የመከላከያ ሰራዊት ጋር መገኘቴ ከፍተኛ ክብርና ኩራት ይሰማኛል ብለዋል። የሰራዊታችን አንዱ አካል የሆነው አየር ኃይላችን የብዙ ጀግኖች መፍለቂያ መሆኑን ያወሱት ክቡር ፕሬዝዳንቷ ከለውጡ በኋላ በተሰራው የሪፎርም ስራ አየር ኃይሉ በከፍተኛ ለውጥ ላይ መሆኑን ገልፀዋል። ዘመኑ የሚጠይቀውን ቴክኖሎጂ በመታጠቅና ብቁና ጀግና ባለሙያዎችን ለመፍጠር የበለጠ በመትጋት የሀገራችንን ሰማይ እንዲጠብቁም መንግስትና ህዝብ ያልተቋረጠ ድጋፍ እንደሚያደጉ አረጋግጠዋል። የኢፌዴሪ የጦር ሀይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ብርሀኑ ጁላ ለውጥ ሳይታይበት ለረጅም አመታት ተቀብሮ የነበረው አየር ኃይላችን አቧራው ተነስቶለት በከፍተኛ ለውጥ ላይ እንደሚገኝ ገልፀዋል። የአየር ኃይሉ ሀገራችን የምትመካበትና ከአፍሪካ ጠንካራ ተቋም እንዲሆን በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ጠቁመው ሀገራችን ገናናነቷ እና ክብሯ ተጠብቆ እንዲቆይ ተመራቂ አብራሪዎች የራሳቸውን ሚና እንዲወጡ ኤታማዦር ሹሙ አሳስበዋል። የኢፌዴሪ አየር ኃይል ዋና አዛዥ ሌ/ጀኔራል ይልማ መርዳሳ በበኩላቸው ሀገራችን የተደገሰላትን የመፍረስ አደጋ ከሌሎች የፀጥታ ሀይሎች ጋር በመሆን ለመከላከል የአየር ኃይሉ ሚና ከፍተኛ እንደነበር ገልፀው ተመራቂ አብራሪዎችም የጀግኖችን አደራ በመቀበል ህዝባቸውንና ሀገራቸውን እንዲያገለግሉ አሳስበዋል። የኢፌዴሪ አየር ሀይል ባለሙያዎችን በቀጣይነት ከማፍራቱ በተጨማሪ አዳዲስ ትጥቆችን በመታጠቅና የሚሻሻሉትንም በማሻሻል ላይ ትኩረት ሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን ገልፀዋል። በምረቃ ዝግጅቱ ላይ የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ክብርት ሳህለወርቅ ዘውዴ፣ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈጉባኤ አቶ አገኘሁ ተሻገር፣ የመከላከያ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላን ጨምሮ የክልል መስተዳደሮች፣ የተለያዩ ሀገራት ወታደራዊ አታሼዎች፣ ከፍተኛ የሰራዊቱ አመራሮች፣ የመንግስት የስራ ሀላፊዎች፣ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶችና የቢሾፍቱ ከተማ ነዋሪዎች ተገኝተዋል። ብዙአየሁ ተሾመ ፎቶግራፍ ብዙአየሁ ተሾመ @FDRE_DEFENCE_FORCE

ሰኔ 18 ቀን 2014 ዓ.ም የኢፌዲሪ ባህር ኃይል አመራሮችና አባላት ከቀድሞ የባህር ሃይል አባላት ጋር የልምድና ተሞክሮ ልውውጥ አካሄዱ፡፡ ባህርተኞቹ በቢሾፍቱ የመከላከያ ዩኒቨርሲቲ ባካሄዱት የልምድና ተሞክሮ ልውውጥ መድረክ ላይ የኢፌዲሪ ባህር ሃይል ዋና አዛዥ ሬር አድሚራል ክንዱ ገዙ በክብር እንግድነት ተገኝተዋል። ዋና አዛዡ እንደገለፁት ከ31 ዓመታት በኋላ ሀገራችን ኢትዮጵያ እንደ ቀድሞው ጊዜ ሁሉ መልካም ስምና ዝና ያለው፣ ከምስራቅ አፍሪካ አልፎ በመላው ዓለም የሚፈራና የሚከበር ተወዳዳሪ የሆነ ዘመናዊ የባህር ኃይል እንዲኖራት በማሰብ በአዲስ መልኩ መቋቋሙን ገልፀዋል፡፡ ሬር አድሚራል ክንዱ ገዙ አክለውም በምናደርገው የተቋም ግንባታ የበፊቱን ጥለን የአሁኑን ብቻ በመያዝ የምናሳካው ነገር ስለማይኖር በዓለም ላይ ተዘዋውረን ከምንቀስመው ዕውቀት በላይ ከእናንተ አንጋፋ የሙያ ባልደረቦቻችን የምንወርሰው ዕውቀት፣ ባህል እና ወግ እንደ ሀገርና እንደ ተቋም እውን ማድረግ ለምንፈልገው ዘመናዊ የባህር ኃይል ትልቅ መሰረት ነው ብለዋል። የቀድሞ ባህርተኞች በተቋም ግንባታው ላይ ባላቸው የሙያ ዘርፍ ሁሉ አብሮ ለመስራት ላሳዩት ከፍተኛ መነሳሳት እኔ መልካም ፍቃደኝነት በተቋሙ ስም ያላቸውን ከፍተኛ ምስጋናና አድናቆት ገልፀው በቀጣይም በሁሉም የሙያ መስኮች በጋራ ልንሰራ ይገባናል ብለዋል፡፡ የቀድሞው የባህር ሃይል አባልና የመምሪያ ኃላፊ የነበሩት ካፒቴን መዝገበ ወርቄ በበኩላቸው በቅድሚያ ለበርካታ ዓመታት ፈርሶና ተረስቶ የነበረው ተቋም በአዲስ መልክ ተቋቁሞ ማየታቸው ከፍተኛ ደስታ እንደተሠማቸው ገልፀዋል፡፡ የባህር ኃይል አባል መሆን ማለት በከፍተኛ የሀገር ፍቅርና ሙያዊ ዲሲፕሊን የሚታነፁበት ከፍተኛ የሆነ የዓላማ ፅናትን የሚጠይቅ የተከበረና የሚያስከብር ሙያ ነው ብለዋል፡፡ አዲሱ ትውልድ የዚህ ተቋምና ሙያ ባለቤት መሆን በራሱ ትልቅ ኩራት መሆኑን በሚገባ በመረዳት በዘርፉ ከባህር ማዶ ከሚቀስመው ዕውቀት በበለጠ ከአንጋፋ የሙያ አባቶቹና ወንድሞቹ ሀገራዊ የሆነውን እውቀት ባህልና ልማድ በመውሰድ ከዘመኑ እውቀት ጋር በማጣመር የበለፀገች ኢትዮጲያን ማስረከብ ይጠበቅበታል ብለዋል። በዕለቱ በተከናወነው መርሃ ግብር ላይ በሁለቱ የባህር ሃይል አባላት መካከል የቀድሞውንና የአሁኑን ዘመን ባህር ሃይልን የሚገልፁ የማስታወሻ ስጦታዎች ልውውጥ የተደረገ ሲሆን በመጨረሻም ለቀድሞው የባህር ሃይል አባላት የአዲሱን የባህር ሃይል አርማ በዋና አዛዡ ሬር አድሚራል ክንዱ ገዙ አማካኝነት በማበርከት የዕለቱ ፕሮግራም ተጠናቋል፡፡ ኤልያስ ከለለኝ ፎቶግራፍ ኤልያስ ከለለኝ @FDRE_DEFENCE_FORCE

ሰኔ 18 ቀን 2014 ዓ.ም "ነብሮች 2014" በሚል መሪ ቃል የኢፌዴሪ አየር ኃይል ያሰለጠናቸውን አብራሪዎች እያስመረቀ ይገኛል። በምረቃ ዝግጅቱ ላይ የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ክብርት ሳህለወርቅ ዘውዴ፣
+3
ሰኔ 18 ቀን 2014 ዓ.ም "ነብሮች 2014" በሚል መሪ ቃል የኢፌዴሪ አየር ኃይል ያሰለጠናቸውን አብራሪዎች እያስመረቀ ይገኛል። በምረቃ ዝግጅቱ ላይ የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ክብርት ሳህለወርቅ ዘውዴ፣ የመከላከያ ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላን ጨምሮ የክልል መስተዳደሮች፤ የተለያዩ ሀገራት ወታደራዊ አታሼዎች፣ ከፍተኛ የሰራዊቱ አመራሮች፣ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች፣ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶችና የቢሾፍቱ ከተማ ነዋሪዎች ተገኝተዋል። ብዙአየሁ ተሾመ ፎቶግራፍ ብዙአየሁ ተሾመ ለተጨማሪ መረጃዎች  ከታች ያሉትን ሊንኮች ይጠቀሙ።                ቴሌግራም  👇 https://t.me/FDRE_DEFENCE_FORCE                    ፌስቡክ 👇 https://www.facebook.com/fdredefense.official

ታህሳስ 2 ቀን 2014 በክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የተመራው ዘመቻ ለኅብረ ብሔራዊ አንድነት፣ ዋናውን የወልድያ መቀሌ ጎዳና ቆርጦታል፡፡ በክቡር ጠቅላይ ሚኒስትሩ የሚመሩት የጸጥታ ኃይሎች ጥምረት፣ በአሸባሪው ወራሪ ላይ በሰነዘሩት ክንደ ብርቱ ማጥቃት፣ በምሥራቅ ግንባር ስትራቴጂያዊ የሆኑትንና ወራሪው በፍጻሜ ዋዜማ ላይ መሆኑን የሚያሳዩትን የዞብል ሠንሠለታማ ተራሮችን ጨምሮ ከፍተኛ ወታደራዊ ጠቀሜታ ያላቸውን የአርጆ፣ ፎኪሳ እና ቦረን ከተሞችን ተቆጣጥሯል፡፡ በተመሳሳይ ሁኔታ የጉራ ወርቄ አካባቢዎችን በመቆጣጠር የወልድያ መቀሌ ዋናውን አውራ ጎዳና በመቁረጥ ጠላት መውጫ አጥቶ ነፍስ ውጪ ነፍስ ግቢ ውስጥ እንዲገባ አድርጎታል፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ በዚሁ ግንባር የድሬ ሮቃና የሶዶማ ከፍተኛ ወታደራዊ ጠቀሜታ ያላቸውን ከተሞችና ተራሮች በመቆጣጠር ጥምር ጦሩ ወደ ሐራ ከተማ እየገሠገሠ ይገኛል፡፡ በውጫሌ ግንባር ደግሞ የአምባሰል ከፍተኛ ሠንሠለታማ ተራሮችን ጨምሮ የሮቢትና የጎልቦን፣ በወረባቦ ወረዳ የሚሌ ኮትቻን፣ በሐብሩ ወረዳ የኮልቦን፣ የመርካታና የፋጂን አካባቢዎችን በመቆጣጣር ወደ መርሳ ከተማ እየገሠገሠ ነው፡፡ በእነዚህ ግንባሮች በተደረገው ኦፐሬሽን በአሸባሪው የጠላት ኃይል ላይ በተሠነዘረበት ማጥቃት ጠላት ሙት፣ ቁስለኛና ምርኮኛ ሆኗል፡፡ የወገን የመካናይዝድ ኃይልና ንሥሮቹ የአየር ኃይሉ በጥምረት ባካሄዱት ኦፐሬሽን የጠላት ኃይል ምንም ዓይነት ተሸከርካሪ እና ከባድ መሣሪያዎችን ይዞ እንዳይንቀሳቀስ ስላደረጉት፣ ጠላት በየአቅጣጫው ጥሎ ለመፈርጥጥ ተገድዷል፡፡ ለበርካታ ቀናት ያከማቻቸውን ቁስለኞችንም ጥሎ ፈርጥጧል፡፡ የዘረፈውን ንብረትም በየቦታው እያዝረከረከ እግሬ አውጪኝ በማለት ላይ ይገኛል፡፡ ጠላት ዋናው የቆቦ ወልድያ መንገድ ስለተዘጋበት በድንብርብር በጋሸና ላሊበላ በኩል ለማምለጥ ከፍተኛ ትንቅንቅ ቢያደርግም በወገን ጥምር ጦር እንደ ቅጠል ከመርገፍ አልተረፈም፡፡ በወረራ ውስጥ የቆየው ኅብረተሰብ በከፍተኛ ወኔና ጀግንነት በመነሣሣት ከወገን ጦር ጋር ተባብሮ በመሰለፍ አኩሪ ተጋድሎ ፈጽሟል፡፡ አሁንም ክንደ ብርቱውን የወገን ጥምር ጦር መቋቋም አቅቶት በየጢሻው የተበተነውን የአሸባሪውን ጀሌ፣ የየአካባቢው ሕዝብ በመማረክ፣ እምቢ ያለውንም በመደምሰስ የጀግንነት ተግባሩን እንዲፈጽም መንግሥት ጥሪ ያቀርባል፡፡ ነጻነታችንን የምናረጋግጠው በተባበረ ክንዳችን ነው! የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት

ኅዳር 30 ቀን 2014 የመከላከያ የሰራዊት ግንባታ ስራዎች ዋና አስተባባሪ ሌ/ጄ ባጫ ደበሌ ፣ የልዩ ዘመቻዎች ሀይል ፣ የሪፐብሊክ ጥበቃ ሀይል እና የአየር ወለድ አባላት በጭንቅ ላይ ያለች አገርን
ኅዳር 30 ቀን 2014 የመከላከያ የሰራዊት ግንባታ ስራዎች ዋና አስተባባሪ ሌ/ጄ ባጫ ደበሌ ፣ የልዩ ዘመቻዎች ሀይል ፣ የሪፐብሊክ ጥበቃ ሀይል እና የአየር ወለድ አባላት በጭንቅ ላይ ያለች አገርን ችግር የፈቱ የጭንቅ ቀን ደራሾች መሆናቸውን አስታወቁ። ሌ/ጄ ባጫ ደበሌ ይህንን የተናገሩት ፣ የመጀመሪያውን ምዕራፍ የሽብር ቡድኑን የመደምሰስ ግዳጅ በድል መገባደድ እና ለቀጣይ ወሳኝ ተልዕኮ መነቃቃትን ለመፍጠር በሚያስችል መልኩ በግንባር በተካሄደ መድረክ ላይ ተገኝተው ነው ። ቀይ መለዮ ለባሾቹ በወሳኝ ወቅት አስቸጋሪና ፈታኝ ግዳጆችን በድል በመወጣት በደማቅ ቀለም የተፃፈ ታሪክ መስራታቸውን ተናግረዋል። ጀግኖቹ ከሰሞኑ በጣርማበርና ዙሪያገባዎቹ የፈፀሙት አንፀባራቂ ድል የጠላትን ቅስም የሰበረ ነው ያሉት ሌ/ጄ ባጫ ደበሌ ፣ አሁንም የደም የመስዋዕትነት እና የድል አድራጊነት ምልክት የሆነውን ቀይ መለዮአቸውን አጥልቀው ለዳግም ድል መትጋት እንዳለባቸው አሳስበዋል። የልዩ ዘመቻዎች ፣ የሪፐብሊኩ ሀይልና አየር ወለዶች የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጆች እና የምድር ላይ ድሮን መሆናቸውን እንዳስመሰከሩ ሁሉ ፣ የህልውናችን ጠንቅ ሆኖ በምዕራባውያን የሚጋለበውን የህወሀት ሽብር ቡድን እስከ መጨረሻው በመቅበር ታላቁን የድል ዜና መቀሌ ላይ ሆነን እናበስራለን ብለዋል። መላክ በቃሉ (ከግዳጅ ቀጣና) ፎቶግራፍ እፀገነት ዴቢሳ

ኅዳር 30 ቀን 2014 የሃገርን ደህንነት ለማስጠበቅ የሚያስችልና ከውስጥና ከውጭ የሚመጡ ችግሮችን የሚመክት ዘመናዊ የሆነ ባህር ሃይል መገንባት ማደራጀትና ማሰልጠን አስፈላጊ መሆኑን የመከላከያ ባህ
+4
ኅዳር 30 ቀን 2014 የሃገርን ደህንነት ለማስጠበቅ የሚያስችልና ከውስጥና ከውጭ የሚመጡ ችግሮችን የሚመክት ዘመናዊ የሆነ ባህር ሃይል መገንባት ማደራጀትና ማሰልጠን አስፈላጊ መሆኑን የመከላከያ ባህር ሃይል የሰው ሃብት ልማት ዳይሬክተር ካፒቴን ተዘራ በቀለ ተናገሩ ፡፡ ካፒቴን ተዘራ ፣ ቢሾፍቱ ባቦጋያ የሚገኙትን የባህር ሃይል መሠረታዊ ባህርተኞች ፣ በውሃ ዋና የሚሰጡ ግዳጆችን ለመወጣት የሚያስችል ስልጠና ላይ ተገኝተው እንደተናገሩት ፣ የውጭ ሀገራት የእጩ መኮንን ስልጠናዎችና ባህር ዳር ማሪታይም አካዳሚ በኤሌክትርካልና መካኒካል የኢኒጂነሪግ መስክ ሥልጠናዎችን ማከናወን መቻሉን አስረድተዋል ፡፡ አሁን እየሰለጠናችሁ ያላችሁት በመርከብ ላይ ሊደረጉ የሚገቡ የጥንቃቄና የአደጋ መከላከል ደንቦች ጠቀሜታው የጎላ በመሆኑ ያገኘነውን የስልጠና አቅም የኢትዮጵያን ባህር ሃይል በፍጥነት ለግዳጅ ዝግጁ ከማድረግ አንፃር ጠቀሜታው ስትራተጂካዊ ነው ብለዋል፡፡ ካሣሁን ኪዳኔ ፎቶግራፍ ካሣሁን ኪዳኔ ‼️ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት፦ የፌስቡክ ገፃችንን ይከታተሉ https://www.facebook.com/fdredefense.official የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ https://t.me/FDRE_DEFENCE_FORCE በቲዉተር ለመከታተል https://twitter.com/Fdre_defence