ETHIO ≈ SCHOOL
Open in Telegram
ይህ ለተማሪዎች እና ለትምህርት ፈላጊዎች ተብሎ የተዘጋጀ ፈጣን የሆነ መረጃ የሚያገኙበት ቻናል ነው። እንዲሁም በተጨማሪ መረጃወችን በመሰብሰብ በሁሉም የ ት/ት ደረጃ ተማሪን የሚመለከት መረጃ በፍጥነት እናደርሳለን። ለCross ፦ 👇👇👇 👍 @Gashushu 👍 @Gashtiman25 ❤Join❤ 👇👇👇 @merejamnch
Show more5 484
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
5 484
#MoH
ጤና ሚኒስቴር የ2023/24 ትምህርት ዘመን የብሔራዊ የህክምና ስፔሻሊቲ ስልጠና /ERMP/ አመልካቾች የመግቢያ ፈተና ማክሰኞ ታህሳስ 16/2016 ዓ.ም እንደሚሰጥ አሳውቋል፡፡
ስለፈተናው ገለጻ ነገ ታህሳስ 15/2016 ዓ.ም ጠዋት 3:00 ላይ የሚሰጥ ሲሆን፤ ለፈተናው የተመረጡ አመልካቾች በሙሉ ገለጻው ላይ መገኘት አለባቸው ተብሏል፡፡
ጤና ሚኒስቴር ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር በመተባበር በ2016 የትምህርት ዘመን በ21 የህክምና ስፔሻሊቲ ፕሮግራሞች አመልካቾችን በERMP ለማሰልጠን ምዝገባ ሲያደርግ መቆየቱ ይታወቃል፡፡
📌Share&forward📌
📌Join📌
👇👇👇
💯 @merejamnch 💯
💯 @merejamnch 💯
5 484
📌📌📌አንዳንድ ድንቃ ድንቅ አባባሎች እና የ ዓለም ክስተቶችን ወይም ተፈጥሮዎችን መጎብኘት ይፈልጋሉ???
እንግድያውስ...
Join
And
Forward
👇👇👇
https://t.me/+Jj9zCCe-pnoyYmY0
https://t.me/+Jj9zCCe-pnoyYmY0
5 484
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሃዲያ ዞን ለሚገኙ መምህራን ደመወዝ በወቅቱ ባለመከፈሉ 100 ሺህ ገደማ ተማሪዎች ከትምህርት ገበታ ውጪ መሆናቸውን ኢሰመኮ ገለጸ።
ለመምህራኑ “ተገቢው ደመወዝ በወቅቱ ባለመከፈሉ" የመንግሥት ትምህርት ቤቶች መዘጋታቸውንና 100 ሺህ ገደማ ተማሪዎች ከትምህርት ገበታ ውጪ መሆናቸውን የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን አስታውቋል።
ኢሰመኮ አዳዲስ የክልል አደረጃጀቶችን ተከትሎ በተለያዩ አካባቢዎች ተከስተዋል የተባሉ የደመወዝ መዘግየት እና መቋረጥን አስመልክቶ ያካሔደውን የሰብአዊ መብቶች ክትትል ምርመራ ውጤት ይፋ አድርጓል።
በዞኑ የአብዛኞቹ የመንግሥት ተቋማት ሠራተኞች ከነሐሴ 2015 ዓ.ም ጀምሮ ደመወዝ እንዳልተከፈላቸው የገለፀው ኢሰመኮ፤ በተለይ በሾኔ ከተማና በሰባት ወረዳዎች የትምህርት እና ጤና አገልግሎቶች ሙሉ በሙሉ ተቋርጠዋል ብሏል።
በዞኑ ከደመወዝ ጋር በተያያዘ “ቅሬታና ተቃውሞ ባሰሙ” ሰዎች ላይ “ማስፈራራት፣ ዛቻና ድብደባ” እንዲሁም በተለያዩ ጊዜያት “እስራት ጭምር” እንደደረሰባቸው ኮሚሽኑ ገልጿል።
ችግሩ መኖሩን ያመኑ የከተማ እና የወረዳ አስተዳደር ኃላፊዎች፤ ለደመወዝ ይውል የነበረ “የውስጥ ገቢ ማነስ” እና ከፌዴራል የሚመደበው በጀት ለማበዳሪያ ግዢና ለሌሎች ጉዳዮች መዋሉ እንዲሁም “ያልተጠኑ የሰራተኞች ቅጥሮች” በተለያዩ ጊዜያት መፈፀማቸው ለችግሩ መከሰት ምክንያት እንደሆኑ ኃላፊዎቹ መግለፃቸውን ኢሰመኮ በመግለጫው አስፍሯል።
በክልሎች ያለውን የደመወዝ ክፍያ ችግር ለመቅረፍ የተለያዩ እርምጃዎች በመወሰድ ላይ” መሆናቸውን በአበረታችነት ያነሳው መግለጫው ፤ ሆኖም ችግሩ በይበልጥ በታየባቸው የክልል እና የዞን አስተዳደሮች “ልዩ ትኩረት” በማድረግ ዘላቂ መፍትሔ ማመቻቸት እንደሚገባ” አሳስቧል። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)
💯 @merejamnch 💯
5 484
ለሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የቀረበ የስልጠና ዕድል
የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስ ሶሳይቲ ከታህሳስ 16 እስከ 18/2016 ዓ.ም ለሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የሕዋ ስልጠና ይሰጣል።
በስልጠናው ለመካፈል በተከታዩ ሊንክ ይመዝገቡ፦
https://forms.gle/MFeQhry3HC5fxwPw9
ቀድመው የተመዘገቡ አመልካቾችን እንደሚቀበል ሶሳይቲው ገልጿል።
📌Share&forward📌
📌Join📌
👇👇👇
💯 @merejamnch 💯
💯 @merejamnch 💯
5 484
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሃዲያ ዞን ለሚገኙ መምህራን ደመወዝ በወቅቱ ባለመከፈሉ 100 ሺህ ገደማ ተማሪዎች ከትምህርት ገበታ ውጪ መሆናቸውን ኢሰመኮ ገለጸ።
ለመምህራኑ “ተገቢው ደመወዝ በወቅቱ ባለመከፈሉ" የመንግሥት ትምህርት ቤቶች መዘጋታቸውንና 100 ሺህ ገደማ ተማሪዎች ከትምህርት ገበታ ውጪ መሆናቸውን የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን አስታውቋል።
ኢሰመኮ አዳዲስ የክልል አደረጃጀቶችን ተከትሎ በተለያዩ አካባቢዎች ተከስተዋል የተባሉ የደመወዝ መዘግየት እና መቋረጥን አስመልክቶ ያካሔደውን የሰብአዊ መብቶች ክትትል ምርመራ ውጤት ይፋ አድርጓል።
በዞኑ የአብዛኞቹ የመንግሥት ተቋማት ሠራተኞች ከነሐሴ 2015 ዓ.ም ጀምሮ ደመወዝ እንዳልተከፈላቸው የገለፀው ኢሰመኮ፤ በተለይ በሾኔ ከተማና በሰባት ወረዳዎች የትምህርት እና ጤና አገልግሎቶች ሙሉ በሙሉ ተቋርጠዋል ብሏል።
በዞኑ ከደመወዝ ጋር በተያያዘ “ቅሬታና ተቃውሞ ባሰሙ” ሰዎች ላይ “ማስፈራራት፣ ዛቻና ድብደባ” እንዲሁም በተለያዩ ጊዜያት “እስራት ጭምር” እንደደረሰባቸው ኮሚሽኑ ገልጿል።
ችግሩ መኖሩን ያመኑ የከተማ እና የወረዳ አስተዳደር ኃላፊዎች፤ ለደመወዝ ይውል የነበረ “የውስጥ ገቢ ማነስ” እና ከፌዴራል የሚመደበው በጀት ለማበዳሪያ ግዢና ለሌሎች ጉዳዮች መዋሉ እንዲሁም “ያልተጠኑ የሰራተኞች ቅጥሮች” በተለያዩ ጊዜያት መፈፀማቸው ለችግሩ መከሰት ምክንያት እንደሆኑ ኃላፊዎቹ መግለፃቸውን ኢሰመኮ በመግለጫው አስፍሯል።
በክልሎች ያለውን የደመወዝ ክፍያ ችግር ለመቅረፍ የተለያዩ እርምጃዎች በመወሰድ ላይ” መሆናቸውን በአበረታችነት ያነሳው መግለጫው ፤ ሆኖም ችግሩ በይበልጥ በታየባቸው የክልል እና የዞን አስተዳደሮች “ልዩ ትኩረት” በማድረግ ዘላቂ መፍትሔ ማመቻቸት እንደሚገባ” አሳስቧል። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)
💯 @merejamnch 💯
5 484
በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በኮንትራት ውል በደብዳቤ የተስተናገዳችሁ የዩኒቨርሲቲው የቀድሞ ተመራቂዎች ወደ ሰርተፊኬት እንዲቀየርላችሁ ያቀረባችሁት ጥያቄ በዩኒቨርሲቲው አስተዳደር ካውንስል ውሳኔ ማግኘቱ ይታወቃል፡፡
በዚሁ መሠረት የምረቃ ደብዳቤ ወደ ሰርተፊኬት እንዲቀይርላችሁ የምትፈልጉ ተመራቂዎች የቀድሞ ደብዳቤ ኦርጅናል ኮፒ በመመለስ ጊዜያዊ የትምህርት ማስረጃ (Temporary Certificate of Graduation) ከሰኞ ታህሳስ 15/2016 ዓ.ም ጀምሮ ከተቋሙ ሬጅስትራርና አሉምናይ ዳይሬክቶሬት መውሰድ የምትችሉ መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል፡፡
📌Share&forward📌
📌Join📌
👇👇👇
💯 @merejamnch 💯
💯 @merejamnch 💯
5 484
📌📌📌አንዳንድ ድንቃ ድንቅ አባባሎች እና የ ዓለም ክስተቶችን ወይም ተፈጥሮዎችን መጎብኘት ይፈልጋሉ???
እንግድያውስ...
Join
And
Forward
👇👇👇
https://t.me/+Jj9zCCe-pnoyYmY0
https://t.me/+Jj9zCCe-pnoyYmY0
5 484
የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የኢንዶስኮፔ ምርመራ አገልግሎት መስጠት መጀመሩን አሳውቋል።
ነዋሪነታቸው በዩናይትድ ስቴትስ የሆኑ ዶክተር ሳሙኤል ግደይ እና ቤተሰቦቹ የኢንዶስኮፔ መመርመሪያ ማሽን ለዩኒቨርሲቲው ሆስፒታል ድጋፍ ማድረጋቸው ታውቋል።
በዚህም ሆስፒታሉ የኢንዶስኮፒ ማሽኑን በመጠቀም የአንጀት እና የጨጓራ ካንሰር ምርመራን ጨምሮ የተለያዩ የህክምና አገልግሎቶች እንደሚሰጥ ተገልጿል።
📌Share&forward📌
📌Join📌
👇👇👇
💯 @merejamnch 💯
💯 @merejamnch 💯
5 484
#KiburCollege
ክቡር ኮሌጅ በ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና ወስደው የማለፊያ ነጥብ ያላሟሉ ተማሪዎች የአቅም ማሻሻያ መርሐግብር (Remedial Program) ለመስጠት ምዝገባ ጀምሯል!
🔹 በክቡር ኮሌጅ የ2015 የሪሚዲያል ፈተና የወሰዱ ተማሪዎችን 100% አሳልፈናል።
🔹 ትምህርቱ መንግሥት ባስቀመጠው የመግቢያ መስፈርት መሠረት ይሰጣል።
🔹 በተጨማሪ የጥናትና የፈተና አወሳሰድ ክህሎት ስልጠና አካተናል።
🔹የበይነ መረብ የፈተና አሰጣጥ ስልጠና ተካቷል።
🔹ትምህርቱ ብቃት ባላቸው መምህራን ይሰጣል።
📌Share&forward📌
📌Join📌
👇👇👇
💯 @merejamnch 💯
💯 @merejamnch 💯
5 484
ጎንደር ዩኒቨርሲቲ ብሔራዊ የአደጋ ጊዜ የስነ ምግብ ምርምርና ስልጠና ማዕከል አቋቋመ።
ማዕከሉ በተፈጥሮና ሰው ሰራሽ ችግሮች ምክንያት ተጋላጭ የሚሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎችን ለማገዝ የሚያስችል ነው ተብሏል።
ማዕከሉ የአደጋ ስጋቶችን የቅደመ ትንበያ የምርምር መረጃዎችን በማዘጋጀት ለመንግሥት የማቅረብ ተግባራት እንደሚያከናውን ተገልጿል፡፡
በዘርፉ የሰለጠነ የሰው ኃይል ለማፍራት ማዕከሉ አጫጭር ስልጠናዎችን ይሰጣል ተብሏል፡፡
ማዕከሉ የሚያከናውናቸውን ተግባራት የሚያግዙ 10 የሦስተኛ ዲግሪ የትምህርት ክፍሎች መኖራቸውን ተጠቁሟል፡፡
📌Share&forward📌
📌Join📌
👇👇👇
💯 @merejamnch 💯
💯 @merejamnch 💯
5 484
#ጥቆማ
ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት በሀገራዊ ልማት የሚኖራቸው ሚና ላይ ትኩረት ያደረገ ሴሚናር አዘጋጅቷል።
ሴሚናሩ "የዩኒቨርሲቲዎች ሚና በሀገራዊ ልማት - ትኩረት ለምርምር፣ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ" በሚል ጭብጥ ላይ እንደሚመክር ተገልጿል።
ኢትዮጵያዊው የናሳ ተመራማሪ ኢንጂነር ብርሃኑ ቡልቻ (ዶ/ር) በመድረኩ ንግግር ያደርጋሉ ተብሏል።
ሴሚናሩ እሁድ ታህሳስ 14/2016 ዓ.ም ከሰዓት 8:00 በሐረማያ ዩኒቨርሲቲ አፍራን ካሎ አዳራሽ ይካሔዳል።
ተመራማሪ ብርሃኑ ቡልቻ (ዶ/ር) ጨረቃ ላይ ውሃ ለማግኘት የሚያስችል በመጠን አነስተኛ የሆነ ቁስ የኳንተም ፊዚክስ ቀመርን በመጠቀም መስራታቸው ይታወሳል።
📌Share&forward📌
📌Join📌
👇👇👇
💯 @merejamnch 💯
💯 @merejamnch 💯
5 484
📌📌📌አንዳንድ ድንቃ ድንቅ አባባሎች እና የ ዓለም ክስተቶችን ወይም ተፈጥሮዎችን መጎብኘት ይፈልጋሉ???
እንግድያውስ...
Join
And
Forward
👇👇👇
https://t.me/+Jj9zCCe-pnoyYmY0
https://t.me/+Jj9zCCe-pnoyYmY0
5 484
#ጥቆማ
ሰመራ ዩኒቨርሲቲ ከሌሎች አራት ዩኒቨርሲቲዎች ጋር በመተባበር በቀይ ባህርና የኢትዮጵያ ፍላጎት ላይ ያተኮረ አውደ ጥናት አዘጋጅቷል፡፡
"Unlocking The Red Sea - A Journey through History, Geopolitics and International Law" በሚል ጭብጥ ላይ የሚመክረው አውደ ጥናቱ ፤ ነገ ታህሳስ 13/2016 ዓ.ም በሰመራ ዩኒቨርሲቲ ይካሔዳል፡፡
አውደ ጥናቱን ሰመራ ዩኒቨርሲቲ ከአዲስ አበባ፣ መቐለ፣ ድሬዳዋ እና ጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲዎች ጋር በመተባበር አዘጋጅቶታል፡፡
አምባሳደር ኢብራሒም ኢድሪስ፣ ያቆብ አርሳኖ (ዶ/ር) እና አጥናፉ ገ/መስቀል (ዶ/ር) በመድረኩ የመወያያ ጥናታዊ ፅሑፎች የሚያቀርቡ መሆኑ ተገልጿል፡፡
📌Share&forward📌
📌Join📌
👇👇👇
💯 @merejamnch 💯
💯 @merejamnch 💯
5 484
በአማራ ክልል ከ91 ሺህ በላይ ተማሪዎችን በቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች ለማሰልጠን ዝግጅት መደረጉ ተገለፀ፡፡
ትምህርት ሚኒስቴር ባስቀመጠው የመግቢያ ውጤት መሰረት ከ91 ሺህ በላይ ተማሪዎችን ከደረጃ 1 እስከ 5 በመደበኛ ትምህርት ለማስተማር መታቀዱን የክልሉ ስራና ስልጠና ቢሮ ምክትል ኃላፊ አማረ አለሙ ተናግረዋል፡፡
በ2016 ዓ.ም ትምህርታቸውን በቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች መከታተል የጀመሩ መኖረቸውን የጠቆሙት ኃላፊው ፤ ሌሎችም እንዲመዘገቡና ትምህርታቸውን እንዲከታተሉ ጥሪ አድርገዋል፡፡
በክልሉ 236 የመንግሥት እና የግል የቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች እንደሚገኙ የኢዜአ ዘገባ ያሳያል።
📌Share&forward📌
📌Join📌
👇👇👇
💯 @merejamnch 💯
💯 @merejamnch 💯
5 484
የ70 ዓመቱ አዛውንት የመጀመሪያ ዓመት ተማሪ
ዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ለመጀመሪያ ዓመት ተማሪዎቹ አቀባበል በማድረግ ላይ ይገኛል፡፡ ከአዲስ ገቢ ተማሪዎቹ መካከል የ70 ዓመት ዕድሜ አዛውንት የሆኑት አቶ ዮሐንስ አዲሴ አንዱ ናቸው።
አቶ ዮሐንስ አዲሴ በ2015 ዓ.ም በማኅበራዊ ሳይንስ መስክ ሀገር አቀፍ መልቀቂያ ፈተና ወስደው የማለፊያ ውጤት በማምጣት ዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ተመድበዋል።
የአስር ልጆች አባት የሆኑት አቶ ዮሐንስ ባጋጠማቸው የአካል ጉዳት ምክንያት ለብዙ ዓመታት ከትምህርት ገበታ ርቀው የቆዩ ቢሆንም ለትምህርት ካላቸው ፍላጎት የተነሳ ያቋረጡትን ትምህርት እንደቀጠሉ ይናገራሉ።
በሀዲያ ዞን ዱና ወረዳ ለጠቦ ቀበሌ ነዋሪ የሆኑት አዛውንቱ ፤ የዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸውን በአግባቡ ለመከታተል በቂ ዝግጅት እንዳደረጉ ለዩኒቨርሲቲው የህዝብ ግንኙነትና ዓለም ዓቀፍ ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ተናግረዋል።
📌Share&forward📌
📌Join📌
👇👇👇
💯 @merejamnch 💯
💯 @merejamnch 💯
5 484
📌📌📌አንዳንድ ድንቃ ድንቅ አባባሎች እና የ ዓለም ክስተቶችን ወይም ተፈጥሮዎችን መጎብኘት ይፈልጋሉ???
እንግድያውስ...
Join
And
Forward
👇👇👇
https://t.me/+Jj9zCCe-pnoyYmY0
https://t.me/+Jj9zCCe-pnoyYmY0
5 484
በአማራ ክልል የሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች ለተማሪዎቻቸው በቅርቡ ጥሪ እንዲያደርጉ ከስምምነት ተደርሷል፡፡ - ትምህርት ሚኒስቴርበአማራ ክልል የሚገኙ አስር ዩኒቨርሲቲዎች በክልሉ ባለው የፀጥታ ችግር ምክንያት ለነባር እንዲሁም አዲስ ለተመደቡ ተማሪዎቻቸው ጥሪ ሳያደርጉ ወራት መቆጠሩ ይታወቃል፡፡ ተማሪዎቹ ለስነልቦና እና ለተለያዩ ችግሮች መጋለጣቸውን በተደጋጋሚ ሲያነሱ ይደመጣል፡፡ ዩኒቨርሲቲዎቹ ጥሪ ሳያደርጉ አራት ወራት በማለፉ ተስፋ መቁረጥ ውስጥ መግባታቸውንም ይጠቁማሉ፡፡ "ያለ ትምህርት ቁጭ ብለን ወራት አልፈዋል፣ ፍትህ እንሻለን" የሚሉት ተማሪዎቹ፤ ወደ ሌሎች የትምህርት ተቋማት በጊዚያዊነት መዘዋወርን ጨምሮ አማራጭ መፍትሔዎችንም ያነሳሉ፡፡ በጉዳዩ ዙሪያ ለለሸገር ኤፍኤም አስተያየታቸውን የሰጡት በትምህርት ሚኒስቴር የአካዳሚክ ጉዳዮች መሪ ሥራ አስፈጻሚ ኤባ ሚጀና (ዶ/ር) ፤ "ዩኒቨርሲቲዎቹ ለተማሪዎቻቸው ጥሪ እንዲያደርጉ በትምህርት ሚኒስቴር ተነግሯቸዋል" ብለዋል፡፡ ትምህርት ሚኒስቴር ከአስሩ ዩኒቨርሲቲዎች ጋር ውይይት ማድረጉን የገለፁት ኤባ ሚጀና (ዶ/ር) ፤ ተቋማቱ በቅርቡ ጥሪ ለማድረግ መስማማታቸውን ገልፀዋል፡፡ ለዚህም "መንግሥት አስፈላጊውን እገዛ ያደርጋል" ያሉ ሲሆን ፤ ተማሪዎቹን ወደ ትምህርት ገበታቸው ለመመለስ መንግሥት፣ ትምህርት ሚኒስቴር፣ ክልሉ እና በክልሉ የሚገኘው ኮማንድ ፖስት በጋራ ይሠራሉ ብለዋል፡፡ 📌Share&forward📌 📌Join📌 👇👇👇 💯 @merejamnch 💯 💯 @merejamnch 💯
5 484
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን የካ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የቅዱስ ሚካኤል ትምህርት ቤትና ቅርንጫፎቹን የዕውቅና ፈቃድ መሰረዙን አሳውቋል፡፡
የባለስልጣኑ የካ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የዕውቅና ፈቃዱን የሰረዘበት ትምህርት ቤትና ቅርንጫፎቹ፦
- የካ ወረዳ 5 ቅዱስ ሚካኤል ቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት
- የካ ወረዳ 5 ቅዱስ ሚካኤል አንደኛና መካከለኛ ደረጃ ትምህርት ቤት
- የካ ወረዳ 9 ቅዱስ ሚካኤል ቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት
- የካ ወረዳ 12 ቅዱስ ሚካኤል ቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት
- የካ ወረዳ 12 ቅዱስ ሚካኤል አንደኛና መካከለኛ ደረጃ ትምህርት ቤት
ትምህርት ቤቱ የባለስልጣኑን አዋጅና መመሪያ እንዲሁም ስርዓተ ትምህርት ተከትሎ ያስመስራት ጥሰቶች መፈጸሙን ቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ ገልጿል፡፡
ትምህርት ቤቶቹ ከአሰራር ውጪ የወርሃዊ ክፍያና መመዝገቢያ ጭማሪ ማድረግ እንዲሁም የአፋን ኦሮሞ ትምህርት በትምህርት ቢሮ በወጣለት ስርዓት መሰረት ያለመፈጸም ጥሰቶች መፈጸማቸውም ተመላክቷል፡፡
በዚህም ከህዳር 24/2016 ዓ.ም ጀምሮ የዕውቅና ፈቃድ እገዳ ተጥሎበት የቆየ ሲሆን፤ የማስተካከያ እርምጃዎችን ባለመውሰዱ ከታህሳስ 05/2016 ዓ.ም ጀምሮ የዕውቅና ፈቃዱ መሰረዙን ባለስልጣኑ አረጋግጧል፡፡
በተመሳሳይ አፖሎ ግሎባል አካዳሚ የተባለ የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የዕውቅና ፈቃድ መሰረዙን ባለስልጣኑ አሳውቋል፡፡
ትምህርት ቤቱ የፈጸማቸውን የአሰራር ጥሰቶች ባለማስተካከሉ ከታህሳስ 08/2016 ዓ.ም ጀምሮ የዕውቅና ፈቃዱ መሰረዙን ባለስልጣኑ ጠቁሟል፡፡
📌Share&forward📌
📌Join📌
👇👇👇
💯 @merejamnch 💯
💯 @merejamnch 💯
5 484
የመንግሥት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የድህረ-ምረቃ የነርሲንግ እና የሚድዋይፍሪ ሬዚደንሲ ስልጠና ሙሉ ትግበራ ሊያደርጉ ነው።
የነርሲንግ እና ሚድዋይፍሪ ባለሙያዎች ስልጠናን ወደ ሬዚደንሲ በማሳደግ በተመረጡ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት እየተሰጠ ይገኛል፡፡
ስልጠናውን ለማስፋትና ለማጠናከር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ከጤና ሚኒስቴር፣ ከትምህርት ሚኒስቴር፣ ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት እንዲሁም ከነርሲንግ እና ሚድዋይፍሪ ሙያ ማህበራት የተውጣጡ ኃላፊዎች እና ባለሙያዎች ምክክር አካሒደዋል፡፡
ስልጠናውን አስቀድመው የጀመሩ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መልካም ተሞክሮ እና በትግበራ ሒደት ያጋጠሟቸው ፈተናዎች በመድረኩ ቀርቧል፡፡
በዚህም ሁሉም የመንግሥት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የድህረ-ምረቃ የነርሲንግ እና የሚድዋይፍሪ ሬዚደንሲ ስልጠና ሙሉ ትግበራ እንደሚጀምሩ ተገልጿል።
📌Share&forward📌
📌Join📌
👇👇👇
💯 @merejamnch 💯
💯 @merejamnch 💯
